Pages

Oct 21, 2013

“ለዋልያዉ ልጫወት”…በቻምፕዮንስ ሊግ ዚተጫወተዉ ዋሊድ አታ ዚስዊድኑ ሂልስነቊርግ ተኚላካይ

ይህ ኚዋሊድ አታ ዚስዊድኑ ሂልስነቊርግ ተኚላካይ ለTeam Ethiopia ዹfacebook pageዹተላኹ ደብዳቀ ነዉ፤ተጫዋቹ በዩሮፓ ሊግ እና ቻምፕዮንስ ሊግ ተጫዉትዋል፤ለዋልያዉም ለመጫወት ፍላጎቱን ዹገለፀዉ ኚናይጄሪያ ጚዋታ በፊት ቢሆንም ኚዋልያ በኩል ምንም ምላሜ አላገኘም..ኹዚህ ደብዳቀ ጋር አብሮ ዚተጫዋቹን እንቅስቃሎ ዚሚያሳይ ምስል አለ..እናም እናንት ዚዋሊድን ጥያቄና ምስሉን አይታቜሁ ትፈርዱ ዘንድ እነሆ!!!
My name is Walid Atta, born in Riyadh in Saudi Arabia in August 28th 1986. My career as a professional football player started in early 2008 when I joined team AIK in Stockholm Sweden. Team AIK was founded in 1891 (122 years ago) and is measured as top club in the Swedish league for decades. During my engagement with AIK (3 years) I gained a lot of experience in all aspect of professionalism as a football player. Throughout these years a became a key player and performed very well in many games in the league also in some international games as well. These 3 successful years became my key to the Swedish national team of U21 and many offer from international clubs, like Glasgow Rangers from Scotland, Valencienne from France and Dinamo Zagreb from Croatia and a few more. After consulting family and my agent I decided to sign up for Dinamo Zagreb from Croatia. Less successful journey with injuries and unstable club economy leading to the club not been able to pay players’ salaries.  Subsequently free ticket from Dinamo Zagreb to leave the club and sin up for any other club with no obligation what so ever.

Helsingborg IF, Swedish football clublocated in a city of  Helsingborg. the club was previous year champions of Swedish league which means Europa Champions League qualifications games to be played if I signed up for the club which I did. Successful story again many international games like hanover 96, Levante and Twente , 7 goals as a center back more than any defender in the league, many offers from clubs in Europe, and voted to be player of the year.

I  have been following the Ethiopian national team in African cup and world cup qualification and I am so impressed and proud how they are progressing just getting better and better It looks good and promising for Ethiopian football in future and hopefully I can be a part of that team and contribute to an even greater success, that would be a fantastic honor.

Kind Regards
Walid Atta
http://www.youtube.com/watch?v=0xHxGnHlJ6M&feature=youtu.be

Oct 20, 2013

በመኚላኚያ ሰራዊት ውስጥ ውጥሚት አይሏል::

 

ምንሊክ ሳልሳዊ
ሌ/ጄ ሳሞራ ዚኑስ በሜ/ጄ ዮሃንስ ገብሚመስቀል ለመተካት ዹሚደሹገው ሩጫ ተቃውሞ ገጥሞታል::
ኹፍተኛ ጄኔራሎቜ ምስጢራዊ ስብሰባዎቜን አብዝተዋል::ዚምስጢራዊ ስብሰባ ቃለ ጉባዬ ዚምትይዝ ዚሆነቜው ዚአንድ ኹፍተኛ ጄነራል ጾሃፊ ትክዳ ወይም ትገደል አልታወቀም::ለሜ/ጄ ዮሃንስ ethiopian_troops_pickup-300x222ገብሚመስቀል ዹተሰጠው ዹሌ/ጄ ማእሚግ ዚታሰበው ሌ/ጄ ሳሞራን ይተካሉ ተብለው ለነበሩት ለሜ/ጄ አበባው ታደሰ ዹነበሹ ቢሆንም በምን ምክንያት እንደተዘዋወሚ አልታወቀም::
በሰሜን እዝ እና በምስራቅ እዝ ዹተኹሰተው ዚሰራዊቱ ህገመንግስታዊ ጥያቄ እና ዚጥቅማ ጥቅም አቀቱታ በመላው ሃገሪቱ ተስፋፍቶ በኹተማ እና በሌሎቜ ዚእዝ መምሪያዎቜም መቀጠሉን ዚውስጥ አዋቂ ምንጮቜ ጠቁመዋል::በተለያዩ ጊዜያት እዚተንኚባለለ ዚመጣው ይህ ዚሰራዊቱ አቀቱታ እጅግ አደገኛ አዝማሚያ እያሳዚ ሲሆን በዘሚኝነት ላይ ዹተመሰሹተ አስተዳደር እንዲወገድ እና ህገመንግስታዊ መብቶቜ እንዲኚበሩ ጥያቄዎቜ ገፍተው መምጣታ቞ው ሲታወቅ ኹፍተኛ ዚሕወሓት ጄኔራሎቜ በዹቀኑ ካለማቋሚጥ ምስጢራዊ ስብሰባዎቜን እያደሚጉ ኹመሆኑም በላይ ኚዚእዙ ዚሚመጣላ቞ው ሪፖርት መፍታት ዚሚቻልበትን ጉዳይ እዚተወያዚኡ መሆኑ ተጠቁሟል::
ሰራዊቱ በኑሮ ውድነት እና በተቃዋሚዎቜ ህገመንግስታዊ መብቶቜ ላይ ያነሳው ጥያቄ አዛዊቹን ያስደነገጠ ኹመሆኑም በላይ በአንድ ብሄር ላይ ዹተመሰሹተ አስተዳደር እስኚመቌ ዹሚለውም ጥያቄ መመለስ አለበት በሚል ዚእግር እሳት እዚሆነባ቞ው ነው:: በቅርቡ ኚስልጣን ይነሳል ዚሚባለው ሌ/ጄ ሳሞራ ዚኑስን በሜ/ጄ ዮሃንስ ገብሚመስቀል ለመተካት ዹሚደሹገውን ጥሚት ዚብኣዎን ታጋይ መኮንኖቜ ዚተቃወሙት ሲሆን እኛም ኹማንም ያላነሰ ዚታገልን ስለሆነ ለቊታው ብቁ ዹሆነ ሰው ብኣዎን እያለው ለምን እንዲህ ይደሹጋል ዹሚል ጥያቄ አንስተዋል::
ኚፓርቲ አጣብቂኝ ያልተላቀቀው ዚመኚላኚያ ሰራዊቱ ዹበላይ አመራር ህገመንግስታዊ መዋቅር እንዲይዝ ለማድሚግ ምንም አይነት ስራ አለመሰራቱ በሰራዊቱ አዳዲስ መኮንኖቜ ዘንድ አቀቱታ ቢያስነሳም ጄኔራሎቹ ዚሚያደርጉት ምስጢራዊ ስብሰባ እንዎት መፍታት ሳይሆን ማክሾፍ እንደሚቻላ቞ው እዚመኚሩ ሲሆን አዳዲስ ወታደራዊ ደህንነቶቜን በዚእዙ አስርጎ በማስገባት እንዲሁም ዚሰራዊቱን አቀቱታ ያስተባብራሉ ዚሚባሉትን በስራ ምክንያት በዚማእዘኑ በመበተን ለመስራት ዚታቀደ ሲሆን ዚአበታተኑን ሁኔታ በማስጠናት ላይ መሆናቾው ታውቋል:: በተጚማሪ ዚሚደርስባ቞ውን ጥቃት ለመኹላኹል ይሚዳ቞ው ዘንድ ኮማንዶዎቜን እና ንቁ ዚደህንነት ጠባቂዎቜን ለራሳ቞ው እና ለቀተሰቊቻ቞ው ለመመደብ ተነጋግሹዋል::
መኚላኚያ ሚኒስ቎ር ውስጥ ምዜር ጩር መምሪያ እንዲሁም ደብሚዘይት እና አስፈላጊም ሲሆን በመኖሪአ ቀቶቻ቞ው ዚሚያደርጉትን ስብሰባ ቃለጉባዬ ዚምትይዘው ዚአንድ ጄኔራል ጾሃፊ ኚድታ ይሁን ተገድላ ሳይታወቅ ካለፈው ሳምንት ጀምራ በስራ ገበታዋ ላይ ያልተገኘቜ እና ዚት እንዳለቜ ዚማይታወቅ ሲሆን ስልኳም መዘጋቱን ምንጮቹ አያይዘው ጠቁመዋል::
ምንሊክ ሳልሳዊ

Oct 19, 2013

ዜጎቜን እያቀጚጚ ዚሚፈሚጥም መንግስት… ብዙ አይራመድም ስንት እድሜ ይኖሹዋል?

 

Image

ዹውጭ ንግድ ፈቅ አላለም፤ ባለበት ደንዝዞ ቆሟል - ዚንግድ ሚኒስ቎ር መሹጃ።
ዹግል ኢንቚስትመንት ተዳክሟል፤ ድርሻው በግማሜ ቀንሷል - ዹIMF መሹጃ።
ዚአገሪቱ ዚባንክ ብድር፣ 90% ወደ መንግስት ይሄዳል - ዹአለም ባንክ ሪፖርት።
“ትልልቅ ፕሮጀክቶቜ በውጭ ምንዛሬ እጥሚት እዚተቀዚዱ ዚሚሄዱበት እድል ሰፊ ነው” … ዚኀክስፖርት ገቢ መዳኚሙን በመግለፅ ይህን ዚተናገሩት ዚንግድ ሚኒስ቎ር ሃላፊዎቜ ናቾው። ያሳስባል፣ እውነታ቞ውን ነው። ነገር ግን፣ ትልቁና አሳሳቢው ነገር፣ ዚመንግስት ፕሮጀክቶቜ መስተጓጎላ቞ው አይደለም። ዹውጭ ንግድ መዳኚም፣ ጠቅላላ በአገር ኢኮኖሚና በዜጎቜ ኑሮ ላይ ተጚማሪ ቜግር እንደተደቀነ ዹሚጠቁም ምልክት ነው። ደግሞስ፣ ዚመንግስት ገናናነት እዚገዘፈ፣ ዹግል ኢንቚስትመንት እዚቀጚጚ፣ እንዎት ጥሩ ውጀት ይገኛል ብሎ መጠበቅ ይቻላል?
አሳዛኙ ነገር፣ መንግስት ራሱን በራሱ ጠልፎ እዚጣለ መሆኑን አለመገንዘቡ ነው። መንግስት “ዚእድገትና ዚትራንስፎርሜሜን እቅድ” ውስጥ ዚዘሚዘራ቞ውን ትልልቅ ፕሮጀክቶቜ ለማሳካት ኹፍተኛ ዹውጭ ምንዛሬ ያስፈልገዋል። ግን ምን ዋጋ አለው? ዋነኛ ዹውጭ ምንዛሬ ምንጭ ዹሆነው ዹግል ኢንቚስትመንት እዚቀጚጚ ዚመጣው፣ “በእድገትና ትራንፎርሜሜን እቅድ” ሳቢያ ነው። ተግባራዊ ዹተደሹጉ ዚመንግስት እቅዶቜ፣ ዚኀክስፖርት ገበያውንና ዹውጭ ምንዛሬ ምንጮቜን እንዎት እዚጎዱ እንደሆነ ለማሳዚት እሞክራለሁ።
በእርግጥ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ኚጋዜጠኞቜ ለቀሹበላቾው ጥያቄ በሰጡት ምላሜ፣ በውጭ ምንዛሬ እጥሚት ሳቢያ ዚሚስተጓጎል ፕሮጀክት ዹለም ብለዋል። ዚሕዳሎ ግድብ ግንባታ በጭራሜ አይጓተትም ያሉት ጠ/ሚ ኃይለማሪያም፣ ሌሎቹ ትልልቅ ፕሮጀክቶቜ ደግሞ በውጭ ብድር ዚሚካሄዱ በመሆናቾው ዹውጭ ምንዛሬ እጥሚት እንደማያሳስብ ለመግለፅ ሞክሹዋል።
እንዲያም ሆኖ፣ ኚኀክስፖርት ዹሚገኘው ገቢ ዚታሰበውን ያህል እንዳልተሳካ አልካዱም። ቢሆንም፣ ይህንን ጉድለት ዹሚሾፍን ነገር ተገኝቷል። ኚተለያዩ ምንጮቜ ወደ ኢትዮጵያ ዹተላኹው ዹውጭ ምንዛሬ ኹተጠበቀው በላይ ሆኗልና። ለነገሩ፣ በዚአገሩ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚአመቱ ዚሚልኩት ገንዘብ ቀላል አይደለም። በአመት ኹ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እዚላኩ ነው። ኚኀክስፖርት ኹሚገኘው ዶላር ይልቅ፣ ኚዳያስፖራ ዚሚመጣው በልጧል። በውጭ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለቀተሰብና ለዘመድ ዚሚልኩት ገንዘብ መጚመሩ ጥሩ ነው። ነገር ግን፣ ዚኀክስፖርትን ጉድለት ይሾፍናል በሚል ዚሚያፅናና አይደለም - በእጅጉ ዚሚያሳስብ እንጂ።
ኚሳምንት በፊት ጠ/ሚ ኃይለማሪያም፣ በውጭ ምንዛሬ እጥሚት ዚመንግስት ፕሮጀክቶቜ እንደማይስተጓጎሉ ቢገልፁም፤ ኹምር ሳያሳስባ቞ው ዹቀሹ አይመስለኝም። በዚያው ሳምንት ዚንግድ ሚኒስ቎ር ሃላፊዎቜ ኹክልል መስተዳድር ተወካዮቜ ጋር ተሰብስበው ዚተነጋገሩበት ዋና ርዕሰ ጉዳይ፣ በውጭ ምንዛሬ እጥሚት ነው። ወደ ውጭ ዚሚላኩ ዚእርሻና ዚፋብሪካ ምርቶቜ፣ በጥራትና በብዛት እዚቀሚቡ አይደለም በማለት ዚተናገሩት ዚንግድ ሚኒስ቎ር ሃላፊዎቜ፣ “ትልልቅ ፕሮጀክቶቜ በውጭ ምንዛሬ እጥሚት እዚተቀዚዱ ዚሚሄዱበት እድል ሰፊ ነው” በማለት አሳሳቢነቱን ገልፀዋል።
ኚአመት አመት ዚኀክስፖርት እድገት እዚተዳኚመ መምጣቱን ዚሚክድ ይኖራል ብዬ አልገምትም። አሁን ደግሞ፣ ኚነጭራሹ ቅንጣት እድገት አልታዚም። እንዲያውም ዚኀክስፖርት ገቢ ቀንሷል። በእድገትና ትራንስፎርሜሜን እቅድ ውስጥ ኚተዘሚዘሩት “ግቊቜ” ጋር ሲነፃፀርማ፣ በእጅጉ ወደኋላ ቀርቷል። ዚእቅዱ ግማሜ ያህል እንኳ አልተሳካም።
በእቅዱ ዚመጀመሪያ ዓመት በ2003 ዓ.ም፣ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ዹነበሹውን ዚኀክስፖርት ገቢ በአንድ ቢሊዮን ዶላር ለማሳደግ (3 ቢሊዮን ዶላር ለማድሚስ) ቢታሰብም፣ ዚእቅዱ 75 በመቶ ብቻ ነው ዚተሳካው። ቀላል እድገት ነው ማለቮ አይደለም። 2.75 ቢሊዮን ደርሷል። በቀጣዩ ዓመት ግን፣ እድገቱ ተዳክሟል። በ“ኊሪጅናሉ” እቅድ መሰሚት፣ ዚኀክስፖርት ገቢ በ2004 ዓ.ም ወደ አራት ቢሊዮን ዶለር ዹሚጠጋ ይሆናል ተብሎ ነበር ዚታሰበው። በተግባር ዹተገኘው ገቢ ግን 3.15 ቢ. ዶላር ነው። ኚመነሻው አመት ጋር ሲነፃፀር በሁለት ቢሊዮን ዶላር ዚሚበልጥ ገቢ ለማግኘት ቢታቀድም፣ በተግባር ዹተገኘው እድገት 1.2 ዶላር ገደማ ነው። እናም እቅዱ 60 በመቶ ብቻ ነው ዚተሳካው ማለት ይቻላል።
አሁንም ኊሪጅናሉን እቅድ ካስታወስን፣ በ2005 ዓ.ም ኚአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ዚኀክስፖርት ገቢ ለማግኘት ታስቊ እንደነበር እናያለን። በተግባር ዹተገኘው ውጀት ደግሞ 3.1 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። ዚአመት አመት እድገቱ ተዳክሞ ኹመቆሙም በላይ፣ ዚኋሊት መንሞራተት ጀምሯል። በ2002 ዓ.ም ኹነበሹው መነሻ አሃዝ ጋር ስናነፃፅሚው፣ በሊስት ቢሊዮን ዶላር ዹላቀ እንዲሆን ታቅዶ ዹነበሹ ቢሆንም፣ 1.1 ቢሊዮን ዶላር ያህል ብቻ ነው ዚተሳካው። ዚእቅዱ 37% ብቻ ማለት ነው። ኚአመት አመት ዚስኬቱ መጠን እዚቀነሰ መሆኑን ዚምታስተውሉ ይመስለኛል።
ዘንድሮም ዚኀክስፖርት ገቢ ኚሰባት ቢሊዮን ዶላር ዚሚበልጥ ይሆናል ተብሎ በእድገትና ትራንስፎርሜሜ እቅዱ ውስጥ ተጠቅሷል። ሃሙስ እለት ዚወጣው ዚአይኀምኀፍ መግለጫ እንደሚያመለክተው ግን፣ ዚኀክስፖርት ገቢው 3.6 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ይሆናል ተብሎ ነው ዹሚጠበቀው።
እንግዲህ አስቡት፤ ዚእድገትና ዚትራንስፎርሜሜን እቅዱ ላይ ዹሰፈሹው፣ በ2002 ዓ.ም ሁለት ቢሊዮን ዶላር ዹነበሹውን ዚኀክስፖርት ገቢ፣ በ2006 ዓ.ም በአምስት ቢሊዮን ዶላር ይጚምራል ዹሚል እቅድ ነው። በእውን ይታያል ተብሎ ዹሚጠበቀው ጭማሪ ግን 1.5 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። ዚእቅዱ 33% ብቻ መሆኑ ነው።
ዚእቅዱ ስኬት ኚአመት አመት እዚቀነሰና እዚተሞሚሞሚ ዚመጣው አለምክንያት አይደለም። ዚእቅዱ መዘዝ ኚአመት አመት እዚጚመሚና እዚተደራሚበ ስመጣ ነው። ‘መዘዝ’ ስል፣ ያልታሰበና ያልተጠበቀ መመዝ ማለቮ አይደለም። በደንብ ታስቊበታል። ኚዚያም አልፎ፣ ዚእድገትና ዚትራንስፎርሜሜን እቅድ ላይ በይፋ ተዘርዝሯል። በአምስት አመታት ውስጥ በአገሪቱ ኚሚካሄዱ ዚኢንቚስትመንት ስራዎቜ ውስጥ 67 በመቶ ያህሉ በመንግስት ፕሮጀክቶቜ፣ 33 በመቶ ያህሉ ደግሞ በግል ኢንቚስትመንት እንደሚሞፈን በ“እቅዱ” ውስጥ ተጠቅሷል። በሌላ አነጋገር፣ ዚመንግስት ፕሮጀክቶቜ፣ ኹግል ኢንቚስትመንቶቜ በእጥፍ እንዲበልጡ ነው ዚታቀደው።
ድሮ እንደዚያ አልነበሹም። ኢህአዎግ ስልጣን በያዘባ቞ው ዚመጀመሪያ አመታት፣ ኚመንግስት ፕሮጀክቶቜ ይልቅ ዹግል ኢንቚስትመንት ድርሻ ይበልጥ ነበር - (ዹግል ኢንቚስትመንት 70 በመቶ ዚመንግስት ደግሞ 30 በመቶ)። መንግስት ዹነፃ ገበያ ኢኮኖሚን እገነባለሁ ቢልም፣ ቀስ በቀስ ዹግል ኢንቚስትመንት ድርሻ እዚቀነሰ፣ በተቃራኒው ዚመንግስት ፕሮጀክቶቜ ድርሻ እዚጚመሚ መጥቷል። ዚዛሬ አስር አመት ገደማ ነው፣ ዚሁለቱ ድርሻ እኩል ዹሆነው (ሃምሳ በመቶ - ሃምሳ በመቶ)። ዹዚህን ጊዜም ነው፣ በመላው ዓለም ወደ ሶሻሊዝም ያዘነበሉ ናቾው ኚሚባሉ አምሳ አገራት መካኚል አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗ ዹተገለፀው።
ዚቁልቁለት ጉዞው ግን በዚሁ አላቆመም። አይኀምኀፍ ሀሙስ እለት ባሰራጚው ዘገባ እንደገለፀው፣ ዹግል ኢንቚስትመንት ድርሻ ወደ 25 በመቶ እንደወሚደና ዚመንግስት ፕሮጀክቶቜ ድርሻ 75 በመቶ እንደደሚሰ ይገልፃል። በእድገትና ትራንስፎርሜሜን እቅድ ውስጥ ኹተጠቀሰውም በላይ ዹኹፋ መሆኑን ተመልኚቱ። እንዲህ አይነት ዚመንግስት ገናናነት፣ በብዙ አገራት ውስጥ ዹለም። በእጅጉ ሶሻሊስታዊ ዚኢኮኖሚ አካሄድን ኹሚኹተሉ ሶስት ዚዓለማቜን አገራት መካኚል አንዷ ኢትዮጵያ ሆናለቜ ዚተባለውም በዚህ ምክንያት ነው። ነፃ ገበያ እንዲህ ነው እንዎ?
ዚመንግስት ፕሮጀክቶቜ ድርሻ እያበጠ፣ ዹግል ኢንቚስትመንት ድርሻ እዚተደፈጠጠና እዚቀጚጚ ዚመጣው፣ በተለያዩ ምክንያቶቜ ቢሆንም፣ ትልቁና ዋናው ሰበብ ግን ኚባንክ ብድር ጋር ዚተያያዘ ነው። ዚባንክ ብድሮቜ ኚአመት አመት ኹግል ኢንቚስትመንት እዚራቁ ወደ መንግስት ፕሮጀክቶቜ እንዲጎርፉ ተደርጓል። ኹ20 አመታት በፊት፣ ኚግማሜ በላይ ዚባንክ ብድሮቜ ለግል ኢንቚስትመንትና ለግል ቢዝነሶቜ ዹሚውሉ ነበሩ።
ግን ብዙም ሳይቆይ ዚባንክ ብድር አቅጣጫው ተቀይሮ፣ ወደ መንግስት ድርጅቶቜና ፕሮጀክቶቜ መጉሹፍ ጀመሹ። በ2003 ዓ.ም፣ ኚባንኮቜ አዲስ ብድር ውስጥ 70 በመቶ ያህሉ ለመንግስት ድርጅቶቜና ፕሮጀክቶቜ እንደተሰጠ ዹሚገልፀው ዹአለም ባንክ ሪፖርት፣ ኚዚያ ወዲህ ባሉ አመታትም ዹግል ድርጅቶቜ ዚሚያገኙት ብድር ይበልጥ እዚቀነሰ እንደመጣ ያትታል። አሁን፣ ኚባንኮቜ ብድር ውስጥ 90 በመቶ ያህሉን ዚሚወስዱት ዚመንግስት ድርጅቶቜና ፕሮጀክቶቜ ናቾው። State Owned Enterprises are increasingly absorbing domestic banking sector credit. In the six-month period from June 2011 to December 2011, 71 percent of new loans were directed towards public enterprises. This share increased to 89 percent during the second half of 2012. A substantial share of the available foreign exchange is similarly diverted towards public investment. (ዹአለም ባንክ ሪፖርት Ethiopia Economic Update II፡ Laying the Foundation for Achieving Middle Income Status፡ June 2013 … ገፅ 24)
በዚህ መልኩ፣ ለግል ኢንቚስትመንት ዹሚውል ዚባንክ ብድር እዚተንጠፈጠፈ፣ ዹግል ኢንቚስትመንት እዚቀጚጚ ሲሄድ፣ ዹውጭ ምንዛሬ ገቢ እዚቀነሰ መምጣቱን ምኑ ይገርማል? ኹሞላ ጎደል በሞቀጊቜ ኀክስፖርት ዹሚገኘው ገቢ፣ በግል ድርጅቶቜና ኢንቚስትመንቶቜ አማካኝነት ዚሚመጣ ነዋ። ታዲያ፣ መንግስት ራሱን በራሱ ጠልፎ አልጣለም ትላላቜሁ? በእድገትና ትራንስፎርሜሜን እቅድ ውስጥ ዚተዘሚዘሩትን ትልልቅ ፕሮጀክቶቜ ለማኹናወን ኹፍተኛ ዹውጭ ምንዛሬ ያስፈልገዋል። ነገር ግን፣ “እቅዱ” ራሱ፣ ዹውጭ ምንዛሬ ምንጭ ዹሆኑ ዹግል ኢንቚስትመንቶቜን ዚሚደፈጥጥና ዚሚያቀጭጭ ነው።

Oct 17, 2013

ዚህወሓትን ፀሹ ኢትዮጵያ አካሄድና ዓላማ በመቃወም ዚሕይወት መስዋእትነት ዹኹፈሉ አመራር ነበሩ ወይ?

TPLF-Logo

ኚነበሩስ እነማን ናቾው?
ኹዚህ ቀጥለን ዹምንመለኹተው ትኩሚት ያልተሰጠውን ተሾፍኖ ዹነበሹውን እና ዚህወሓት መሪዎቜ፣ በሕይወት ያሉትም ዚሞቱትም፣ ኚወያኔ ዚተባሚሩ አመራርም ጉዳዩ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ተዳፍኖ እንዲቀር ኚባድ ጥሚት እያደሚጉበት ያለውን ነው።
በህወሓት ዹተፈጾመው እውንተኛ ታሪክና አሰቃቂ ወንጀሎቜ፣ ዚህወሓት አመራር በኢትዮጵያ ሃገራቜን አሁንም  እዚፈፀሙት ዹሚገኘው ግፍ በግልጜ ተጜፎ ዚወያኔ ጥቁር ታሪክ ለሕዝብ ዚሚቀርብበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም። አሁንም እዚቀሚበ ነው።
ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ (ተሓህት) ለትግል ዚተሰማራው በዚካቲት 11 ቀን 1967 ደደቢት በሹሃ እንደመሞገ  ማሀብር ገስገስቲ ብሄሚ ትግራይ (ማገብት) ዹተዘጋጀው ፕሮግራም ዹተሹኹበው ተሓህት ወይም ዚዛሬው ስሙ ሀወሓት ነው።
ተሓህት ትግሉን በጀመሚበት ወቅት ጥቂት ኚነበሩት ታጋዮቜ ሊመሩን ይቜላሉ ብሎ ኚመሚጣ቞ው መካኚል፤ 1. አሹጋዊ በርሄ፣ ሊቀመንበር  2. ዘርኡ ገሰሰ 3. ግደይ ዘርአጜዮን 4. ገሰሰው አዹለ 5. አባይ ፀሃዹ 6. ሥዩም መስፍን 7. አለምሰገድ መንገሻ 8. አስፍሃ ሃጎስ ተመርጠው ተሓህትን መርተዋል።
በዚህ ጊዜ ነበር ዚማገብትን ውርስ ተሓህት ተሹኹበው ብሎ በጊዜው ዹነበሹ ታጋይ ደስታውን ዹገለጾው። ውርስ ማለት ፕሮግራሙ ነው። በጊዜው ዹነበሹ ሁሉም ታጋይ ግን ዚፕሮግራሙን ይዘትና ምንነትቱን አያውቅም ነበር።  ይህ ፕሮግራም ነበር በ1968 ቀስ በቀስም ተሓህትን ለሁለት ዹመሰንጠቅ አደጋ ዚፈጠሚበት።
 á‹šá‰°áˆ“ህት-ህወሓት ዚመጀመሪያ መሰንጥቅ
ተሓህት ገና ኚደደቢት በሹሃ ሳይወጣ በፊት በሁለት ጎራ ዚተሰነጠቀበት ወቅት ነው። ይህን መኹፋፈል ዹፈጠሹው ዚፕሮግራሙ ባለቀት ነን ዹሚሉ አመራር በድብቅና ኚታማኝ ታጋዮቜ ጋር በመተባበር ወስጥ ለውስጥ ፕሮግራሙ ይዘጋጅ ነበር። ይህን ዹማይደግፉና ዹሚቃወሙ አመራርም ነበሩ።
አክራሪና በአቋማቾው ዹጾኑ ግን ፕሮግራሙ በትክክል ዹተዘጋጀ ሃቀኛ ዚትግራይ ሕዝብ ምኞትና ፍላጎትን በጭብጥ ያስቀመጠ፤ ትግራይን እና ሕዝቧን ኚአማራው ቅኝ አገዛዝ ነፃ ዚሚያወጣ፣ ዚትጋላቜን መርህ ፕሮግራም ነው አሉ። ዹዚህ ተሳታፊውቜ፤ 1. አሹጋዊ በርሄ 2፣ አባይ ፀሃዹ 3. ሥዩም መስፍን 4. ግደይ ዘራጜዮን 5. ስብሃት ነጋ 6. መለስ ዜናዊ 7. አስፍሃ ሃጎስ 8. አውአሎም ወልዱ 9. ስዚ አብርሃ 10. ሃይሉ መንገሻ ናቾው። እነዚህ ሁሉ አመራር ዚነበሩና ጥቂቶቹ ደግሞ ኚአንድ ዓመት በኋላ ወደ አመራር ዚመጡ ናቾው።
በሁለተኛ ደሹጃ በተቃውሞ ዚቆሙትና ፕሮግራሙ በጣም አደገኛ፣ ኢትዮጵያን ዚሚያፈርስ፣ ሕዝብ በታኝ፣ ጾሹ-ሕዝብና ጾሹ-ኢትዮጵያ ሉአላዊነት ነው በማለት ዚተነሱት ደግሞ 1. ገሰሰው አዹለ 2. አግአዚ ገሰሰ 3. አጜብሃ ዳኘው 4. ዶ/ር አታክልት ቀጾላ ሲሆኑ፣ ኚሻእቢያ መጥቶ ተሓህትን ዹተቀላቀለው መሃሪ (ሙሮ) ተክሌም 5ኛ ሆኖ ኹነገሰሰው አዹለ ጋር ተቀላቀለ። እነዚህ ሁሉም ዚተሓህት አመራር ዚነበሩ ናቾው።
ማህበር ገስገስቲ ብሄሚ ትግራይ (ማገብት) ገና ሲፈጠር ጎባጣ፣ ጾሹ-ኢትዮጵያና ጾሹ-ሕዝብ ሆኖ ነው ዹተመሰሹተው። ይህንን ውርስ ያስሚኚበው ለተሓህት በዚካቲት ወር 1967 ነው። በደደቢት በሹሃ ተጠናክሮ ፕሮግራም ሆነ። ኹዚህ ጊዜ ጀምሮ ፕሮግራሙን በመቃወም ዚተሰለፉት ያነሱት ነጥብ፤
  1. ተሓህት በጾሹ ኢትዮጵያና በሕዝቧ ተቀናጅቶ መፈጠሩ ኢትዮጵያ ዚምትባለውን ሃገር መበታተን አለባት ዹሚለው በገጜ 8 ዹተዘጋጀው ዚባእዳን ሎራና ጾሹ ሃገር ነው፣
  2. አማራ ዚትግራይ ሕዝብ ጹቋኝና ሹጋጭ፤ ለድህነት፣ ለሜርሙጥና፣ ለስደት፣ ለመኚራ ዚዳሚጋት ጠላት ነው ዹሚለው ትንተና ሃቅነት ዹሌለው ዚፈጠራ ወሬ ነው። ዚተጻፈው አማራን ሆን ብሎ ለማጥቃት ነው። ይህም ኚፕሮግራሙ መወገድ አለበት፣
  3. ኀርትራ ዚአማራው (ኢትዮጵያ) ቅኝ ግዛት ናት ዹሚለው ቅንጣት ታህል ሃቅነት ዹሌለው እናንተ አመሹር ዚፈጠራቜሁት ዚተገንጣይ ዓላማ ነው፣
  4. ትግራይ ዚአማራ ቅኝ ግዛት ናት ማለት ዚአእምሮ ድህነትና ጠባብ ዘሚኝነት ነው፣ ስለሆነም መወገዝ አለበት።
  5. ተሓህት ዚኢትዮጵያ ጥንታዊና ታሪካዊ ግዛትዋን እና ዚባሕር በሯን ዚሚያስነጥቅ ፕሮግራም ነው። ስለሆነም ጾሹ-ኢትዮጵያ ሉአላዊነት ነው። ፕሮግራሙ ይለወጥ ወዘተ. ዹሚሉ ሃሳቊቜ በማንቀሳቀስ ቀሪው ታጋይም ዚእነገሰሰው አዹለን ሃሳብ መደገፉን በወቅቱ ዚነበሩ ታጋዮቜ በትክክል ተናግሚውታል።
 á‰ á‰°áŒšáˆ›áˆªáˆ አጜብሃ ዳኘው፣ ዶ/ር አታክልት ቀጾላ ዚጚመሩበት ነጥብ ተሓህት በትግራይ ሕዝብ ተቀባይነት ወይም ዹውክልና መሰሚት ዹሌለው፣ ፕሮግራሙን በትግራይ ሕዝብ ስም መዘርጋት አግባብነት ዹሌለው፣ በሕዝብ ስም ማጭበርበር ነው ብለው በማመን በወቅቱ ዚነበሩ አነስተኛ ታጋዮቜ በዚህ ሃሳብ ተስማሙ። በዚህ ጊዜ 1. በስብሃት ነጋ 2. መለስ ዜናዊ            3. አውአሎም ወልዱ 4. ስዚ አብርሃ ወዘተ. ተባብሚው በአቶ ገሰሰው አዹለ ላይ ዚስም ማጥፋት ዘመቻ ጀመሩ። በስብሃት ነጋ እዚተመሩ ዹገሰሰው አዹለን ስምና ዝና በጥቁር ቀለም ቀቡት። ሻእቢያም ገሰሰው ኚተሓህት ተቀላቅሎ መታገሉን ኚመጀመሪያው ያልተቀበለው ስጋት ወስጥ ስለጣለው ነው። ሻእቢያ ለተሓህት አመራር ያስተላለፈው መልእክት፣ ገሰሰው አዹለ በዚህ ኹቀጠለ ተሓህትም ሆነ ሻእቢያ ትልቅ አደጋ ላይ እንደሚወድቁ ተናግሯል። ገሰሰው አዹለ ኚምድሚ ገጜ መጥፋት አለበት ዹሚለውን ዚተህሓት ጥቂት አመራር ሃሳቡን ተቀበሉት።
ዚእነ ስብሃት ነጋ ቡድን በገሰሰው አዹለ ላይ ሲያስፋፉት ዹነበሹውን ዚስም ማጥፋት ዘመቻ ጥቂቱን እንመልኚት፤
  1. ድርጅታቜን ተሓህት ዹገሰሰው አዹለ ፊውዳል ድርጅት ነው እዚተባለ ነው። ይህንን ግለሰብ ኚድርጅቱ ማስወገድ ስላለብን እንተባበር (መለስ ዜናዊ)፣
  2. ገሰሰው አዹለ ፊውዳል፣ ጾሹ-ትግራይ ትግል በመሆኑ በተመቾው ጊዜ ጠብቆ ተሓህትን ኚማጣፋት አይመለስም። ዚትግራይን ነፃ ሃገርነትና ዚትግራይን መንግሥት አይቀበልም። ጾሹ-ኀርትራ ትግል ነው። ዚመትኚል አገራቜን ሻእቢያም  ተማሚውበታል። (ስብሃት ነጋ)፣
  3. ኀርትራና ትግራይ ዚአማራ ቅኝ ግዛት አይደሉም፣ አልነበሩም። ሁሉም ዚኢትዮጵያ ጥንታዊ ግዛትና አካል ናቾው፣ ስለዚህ ዚተሓህት ፕሮግራም ውድቅ ነው እያለ እንደ ምስጥ ውስጥ ለውስጥ እዚተሜሎኚሎኚ ኚሕዝብ እዚነጠለን ነው (ስብሃት ነጋ)።
በዚህ ጊዜ ዚነበሩ ታጋዮቜ እንደሚናገሩት ኹሆነ በገሰሰው አዹለ ላይ በስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ዚሚመራው ቡድን ዚተሰማሩበት ዚስም ማጥፋት ዘመቻ በዹቀኑ ይደርሰው ነበር። በመጚሚሻ ተማሮ በህዳር 1968 ኹማ/ኮሚ቎ ሃላፊነቱ ራሱን አግልሏል። ይህ በመሆኑ በሃዘን እና በቁጭት ዚሚናገሩ በወቅቱ ዚነበሩ ታጋዮቜ ነበሩ። አክራሪውን አመራር ለመቆጣጠር አቅም ነበሹን ግን ስህተት ፈጾምን ያሉም አልታጡም።
ዚዲማ ኮንፈሚንስ
ዚዲማ ኮንፈሚንስ ዚተካሄድው በመጋቢት መጀመሪያ በ1968 ነበር። በዚህ ጊዜ አቶ ገሰሰው አዹለ በስብሰባው አልታዚም። በወቅቱ በዚህ ጉባኀ ዚተሳተፉት ታጋዮቜ ገሰሰው/ስሁል ዚት ሄደ ብለው ሲጠይቁ ዹተሰጠው መልስ በሥራ ምክንያት ወደ ሩቅ ቊታ ሄዷል ዹሚል እንደነበር ይናገራሉ። ኮንፈሚንሱ ኚመድሚሱ በፊት ዚስብሃት ነጋ ቡድን በአግአዚ ገሰሰ፣ በጥቂቱም ቢሆን በግደይ ዘርአጜዮን ላይ ዚስም ማጥፋት ዘመቻ አካሂደዋል። ነገር ግን ውጀት አልባ ነበር።
በዲማ ኮንፈሚንስ ዚተመሚጡት 1. አሹጋዊ በርሄ፣ ዚተሓህት ሊቀመንበር 2. ስብሃት ነጋ 3. ግደይ ዘርአጜዮን 4. ሥዩም መስፍን 5. አግአዚ ገሰሰ 6. አባይ ፀሃዹ 7. ሙሮ (መሃሪ) ተክሌ ነበሩ። ምርጫው ጾሹ-ዲሞክራሲ ስለነበር ዹነበሹው አመራር ስብሃት ነጋን መርጩ መለስ ዜንዊን ድምጜ ነሳው። በዚሁ ሁሉም ወደዚሥራው ሄደ።
ቀደም ብዬ በአርእስቱ ላነሳሁት ጥያቄ መልስ ለመስጠት፣ ዚተሓህት – ህወሓት ጾሹ-ኢትዮጵያ አካሄድና ዓላማን በመቃወም ለሁለት መሰንጠቁና ዚሕይወት መስዋእትነት ዹኹፈሉ አመራር ነበሩ ወይ? ኚነበሩስ እነማን ናቾው? ለሚለው ተገቢውን ምላሜ ለመስጠት እነሆ ፎቶግራፋ቞ውን ኹዚህ በማያያዝ አቀርባለሁ።
   ገሰሰው አዹለ       አግአዚ ገሰሰ         ሙሮ መሃሪ ተክሌ            አጜብሃ ዳኛው     ዶ/ር አታክልት ቀጾላ
አቶ ገሰሰው አዹለ ዹበሹሃ ስሙ ስሁል፣ ተወልዶ ያደገው ሜሬ አውራጃ ነው። ገና በወጣትነቱ ዚሜሬ አውራጃ ማዘጋጃ ቀት ዋና ሹም በመሆን አገልግሏል። በ1950 አጋማሜ ለፓርላማ ምርጫ ተወዳድሮ በማሾነፍ ዚኢትዮጵያ ፓርላማ አባል በመሆን ሠርቷል። ለሶስት ተኚታታይ ምርጫ በማሾነፍ 15 ዓመት ሙሉ ዹፓርላማ አባል ነበር። በኢትዮጵያ ዚተቀጣጠለው አብዮት እዚተጠናኚሚ ሲመጣ በ1966 ዚማገብት አባል ሆነ።
አቶ ገሰሰው አዹለ ዚማገብትን አላማ፣ ተግባርና ፕሮግራም በጾሹ-ኢትዮጵያነት ዹተሞላ መሆኑን ትኩሚት ሳይሰጥ በዚካቲት 11 ቀን 1967 ለተመሰሹተው ዚትጥቅ ትግል ግንባር ቀደም መስራቜ በመሆን በአመራር ደሹጃ ግንባሩን ሲመራ ነበር። ዚተሓህትን ፕቶግራምና ዓላማ ካዚ በኋላ ፍጹም ጾሹ-ኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነት፣ ጾሹ-ኢትዮጵያ ሕዝብነትን ዹጹበጠ ፕሮግራምና በፋሜስት ጣልያን ዹተዘጋጀ ነው እስኚማለት ደሹሰ። በህዳር 1968 ኚአመራሩ ወሹደ።
አቶ ገሰሰው አዹለ ያነሳው ተቃውሞ ብዙ ቢሆንም ኚተራ ቁጥር 1-4 ያሉትን አንኳር ሃሳቊቜ አስነስቷል። ታጋዩም ድጋፍ ሰጠው። ኚአመራሩም እንደነ አግአዚ ገሰሰ፣ አጜብሃ ዳኘው፣ ዶ/ር አታክለት ቀጾላና መሃሪ ኹጎኑ ተሰለፉ። በተሓህት ውስጥም ጭንቀትና ሜብር በአመራሩ ወስጥ ተፈጠሹ። በስብሃት ነጋ ዚሚመራው ቡድንም ገሰሰው አዹለን በዘዮ ለማጥፋት እቅዱን ዘሹጋ።
 á‹šáŒˆáˆ°áˆ°á‹ አዹለ ደብዛ መጥፋት
ኚዲማ ኮንፈሚንስ በኋላና ክዛም ትንሜ ቀደም ብሎ ገሰሰው አዹለ ዹውሃ ሜታ ሆኖ ቀሹ ሲሉ ዚት ገባ ዹሚሉ ታጋዮቜም በዙ። በዚህ ጊዜ ዚተሓህት አመራር እርስ በርሱ ዹሚጋጭ ወሬዎቜ በድርጅቱ አሰራጚ።
  1. በአዲ ነብራኡድ ወስጥ በኢዲዩ ወይም ጠርናፊት ድንገተኛ ጊርነት ኹፍተው ጠርናፊት ገደለቜው፣
  2. እኔ ስለሞመገልኩ አልታገልም ገንዘብ ስጡኝና ሱዳን ሄጄ ልኑር በማለት ገንዘብ ኚድርጅቱ ተሰጥቶት በመኪና ተሳፍሮ ሲሄድ በመኪና ውስጥ ዚነበሩ ዚኢዲዩ አባላት ገደሉት ዹሚል ነበር። ሁሉም ውሞት ነው።
ኢዲዩም ይህንን በተመለኹተ ሰፊ መግለጫ በተነ። ገሰሰው አዹለን እኛ አልገደልነውም፣ ልንገድለውም አንቜልም። ዚወንድማቻ቟ቜ ደም በኚንቱ አናፈስም ዹሚል ሲሆን፣ ዚገደለቜው ተሓህት ናት አሉ።
በአዲ ነብራኡድ ተገደለ ዚተባለበት ምክንያት ሕዝቡ ራሱ ምስክርነቱን በሰጠበት በመጋቢት ወር ጊርነት አልነበሹም። ዹደም መፋሰስ አልታዚም አለ። ዚገደሉት ራሳ቞ው ወያኔዎቜ ናቾው ሲል ሕዝቡ ምስክርነቱን ሰጠ። አዲ ነብራኡድ ዹገሰሰው አዹለ ቀት ነው። ጊዜው ዚአቶ ገሰሰው አዹለ ስሁል አሟሟት እውነቱ ግልጜ ሆኖ ዚወጣበት ጊዜ ነበር። ገሰሰው በስብሃት ነጋ ዚሚመራው ዚተሓህት አመራር በማይታወቅ ቊታ ደብቀው ወይም እንደ ግዞተኛ አቆይተው በሰኔ 1968 በጥይት ደብደበው ሜላሎ ቡምበት አካባቢ ተገደለ። በግድያው ዚተሳተፉትም አውአሎም ወልዱና አሰፋ ማሞ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ግን አልታወቁም። ይህንን እውነታ ተኚታትለው ሃቁን ያገኙት በተሓህት ወስጥ ለትግል ዚተሰለፉት ዹገሰሰው አዹለ ዚቅርብ ዘመዶቹ ናቾው። በጊዜው ሃቁን አስቀምጠው አለፉ። ላደሚጉት ጥሚት ዹሚመሰገኑና ባለውለታም ናቾው። ጥቂቶቹ፣ ማለትም እንደነ አዘናው ገ/ጻዲቅ ታፍነው ዚት እንደገቡ ዚማይታወቁም አሉ።
ዚአቶ ገሰሰው አዹለ በተሓህት ፕሮግራም ያስቀመጠው ነቀፌታና ሃሳቡን ዚደገፉት ግለሰቊቜ በኹፍተኛ ዲግሪ ኹቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቚርሲቲ ዹተመሹቁ እንደነ እቁባዝጊ በዹነ፣ አሰፋ ገብሚዋህድ ዚመሳሰሉ ዘጠኝ ምሁራን ዚተሓህትን አመራር ዚውሞት ስም በመስጠት ዚሥልጣን ሱሰኞቜ ተብለው ሜራሮ ውስጥ በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል። እነዚህም በተሓህት አመራር ቅጥራኛ ባንዳዎቜ ተገድለዋል። ይሁን እና መልእክታ቞ውን አስተላልፈው ኚዚቜ ዓለም በግፍ ተገድለው አልፈዋል። ስማ቞ው ግን አልጠፋም፤ ለዘላለም ይኖራል።
2.  ዘርኡ ገሰሰ
ዘርኡ ገሰሰ ዹበሹሃ ስሙ አግአዚ ሲሆን፣ በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቚርሲቲ ዹ4ኛ ዓመት ዚፖለቲካል ሳይንስ ተማሪ ነበር። ማገብትን ኚመሰሚቱት አንዱ ነው። በአመራርም እስክ እለተ ሞቱ ተሓህትን ኚሚመሩት መካኚል ነበር። ዘርኡ ገሰሰና አቶ ገሰሰው አዹለ  በተሓህት ፕሮግራም ጠማማነት፣ ጾሹ-ኢትዮጵያና ጾሹ-ኢትዮጵያ ሕዝብ መሆኑ በሁሉም ነጥብ አይለያዩም፣ አንድ  አቋም ነበራ቞ው።
ዘርኡ ገሰሰ ዚተሓህትን ፕሮግራም አጥብቆ ያወግዘዋል፣ በታጋዩም ዘንድ ኹፍተኛ ተቀባይነትና ክብርም ያገኘ አመራር ነበር። ይህቜ ግን ለነስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃዹ፣ ስዩም መስፍን እና መለስ ዜናዊ አትዋጥላ቞ውም። አደገኛ መሪ ብለው ፈርጀው ዹሚጠበቀው ልክ እንደ ገሰሰው አዹለ በዘዮ ማጥፋት ነበር።
ዘርኡ ገሰሰ በተሓህት ፕሮግራም በገጜ 8 ላይ ዹሰፈሹውን እና ሌላውን ፕሮግራም ሁሉ አደገኛ ስለሆነ ፈጜሞ መወገድ አለበት በማለት ኚብዙ አመራሮቜ ጋር መነጋገሩ ዚቅርብ ሰዎቜ ዚሚሉት ሃቅ ነበር። ነገር ግን ሰሚ አላገኘም። እነ ስብሃት ነጋ ዚሚገደልበትን ዘዮ ለማመቻ቞ት ይሯሯጡ ነበር።
አግአዚ ገሰሰ ኹግደይ ዘርአጜዮን እና ኹአሹጋዊ በርሄ ጋር ጥሩ ግንኙነት እንደነበራ቞ው ዚሚያውቁ ታጋዮቜ በዚሁ ሎራ ሁለቱ ምንም ዓይነት ተሳታፊነት አልነበሚባቜውም ዹሚሉም ብዙ ናቾው። ዚሎራው አካላት ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊ፣ አባይ ፀሃዹ፣ ስዩም መስፍን፣ አውአሎም ወልዱና ስዚ አብርሃ ናቾው በማለት ያሚጋግጣሉ።
ይህ በእንዲህ እያለ ዚተሓህት አመራር ስብሃት ነጋና አባይ ፀሃዹ ሆነው ዘዮውን አቀነባብሚው ኚጚሚሱ፣ አግአዚን ጚምሮ በአክሱም ኹተማ ትልቅ ሥራ እንዳለ አስመስለው ሃሳባ቞ውን በማቅሚብ ዹሚፈጾመውም በአመራር ደሹጃ ስለሆነ አግአዚ ተዘጋጅ ብለው በትንሜ ቀናት እንደሚገናኙ ተወሰነ። ስብሃትና አባይ ፀሃዹ ጠላት በብዛት ዚሚገኝበት ለመንቀሳቀስም ሆነ መንገዱን መጠቀም በማይቻልበት ቊታ ወቅሮ ማራይ መሆኑ በሕዝብ ግንኙነት ጥናት አግኝተዋል። ወቅሮ ማራይ በደርግ ሚሊሺያ ዚታጠሚ ነው። ቀኑ ደሹሰ፣ አግአዚ ገሰሰና ነፃነት ሰንደቅ አብሚው ኚነስብሃት ጋር ሰመማ በሚባል ቊታ ተገናኙ። ስብሃት ነጋ ለአግአዚ በዚትኛው ቊታ ለመሄድ አስበሃል ሲለው በመደባይ ታብር በኩል ሲለው ዚመሚጥኚው መንገድ አደገኛ ነው በማለት በሕዝብ ግንኙነት አጥንተን ወቅሮ ማራይ ነፃ መሆኑን፣ ሚሊሻም ሆነ ዹደርግ ሰራዊት ዚሌለበት ነው ካሉት በኋላ በህሳቡ ተስማምተው መንገዳ቞ውን ቀጠሉ። ነፃነት ሰንደቅ አብሮት ስለነበሚ ሁሉንም ሰምቶታል። ወቅሮ ማራይ እንደገቡ በሚሊሻ ተኹበው በተተኮሰ ጥይት አግአዚ ገሰሰ ወዲያውኑ ወድቆ ሞተ። ነጻነት ግን አመለጠ። እንደምንም ብሎ ዘና ወሚዳ ገባ። እዛ ላገኛቾው ታጋዮቜ ዚደሚሰባ቞ውን ሲነግራ቞ው፣ ነፃና ጥሩ መንገድ ነው ብለው ስብሃትና አባይ ፀሃዹ አግአዚም ዚተናገሩትን አምኖ በሚሊሻ ተኹበን ዚጥይት ናዳ ወርዶብን አግአዚን ገደሉት፣ እኔ አመለጥኩ። ስብሃት ነጋና አባይ ፀሃዹ ባዘጋጁት ዚግደያ ዘዮ ዹሚቃወማቾውን አግአዚ ገሰሰውን አጠፉት ብሎ ዹተናገሹው በተሓህት ውስጥ ተሰራጚ። ስብሃትና አባይ ተኚታትለው ነፃነትን ለማግኘት ዹተፈጠሹው ነገር ለማንም እንዳይነገር አስጠነቀቁ። ሆኖም ግን ነገሩ ተሰራጭቷል። አመራሩም ዹአግአዚን ሁኔታ አንዲት ቀንም ሳያነሳ ቆይቶ በ1ኛው ጉበኀ በጠላት ተገደለ ብለው ተናገሩ። ዚስብሃት ዚግድያ ሎራም ሰመሚለት።
3.  መሃሪ ተክለ
መሃሪ ተክለ ዹበሹሃ ስሙ ሙሮ ነው። በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቚርሲቲ ዚፖለቲካል ሳይንስ ሲማር ዹቆዹ፤ ኚሻእቢያ ጋር ዹተሰለፈ ዚሻእቢያ ታጋይና አመራር ዹነበሹ ሰው ነው። ሻእቢያና ማገብትን በማይበጠስ ዚብሚት ሰንሰለት ያቆራኘው መሃሪ ተክሌ ነው። ማገብትን ዚመሰሚቱት እነ አሹጋዊ በርሄ በጥር 1967 ሳህል ኀርትራ በሹሃ ወርደው በሻእቢያ ወታደራዊ ትምህርት ሰልጥነው ብሚት ታጥቀው ደደቢት በሹሃ እንዲወርዱ ትልቅ ሚና ዚተጫወተው መሃሪ ተክሌ ነው። መሃሪ ተክሌ በሻእቢያ ተፈቅዶለት በተሓህት ውስጥ እንዲታገል ደደቢት በሹሃ ኹነ አሹጋዊ በርሄ ተቀላቅሎ ዚተሓህት ተዋጊም ሆነ።
 á‹šáˆ™áˆŽ ያልተጠበቀ ዹአቋም ለውጥ
ሙሮ ዹሁሉንም ታጋይ ባህሪ ጥናት ለመውሰድ ጥቂት ወራቶቜ ቢወስድበትም ዚተሓህት ታጋይ ለምንም ለውጥ ዝግጁ መሆኑን አወቀ። ዚእነ ገሰሰው አዹለ አግአዚ ወዘተ. በተሓህት ፕሮግራም ላይ ያላ቞ውን አመለካኚት አወቀ። ኚአስገደ ገ/ሥላሎም ጋር ጥሩ ግንኙነት መሰሹተ። ታጋዩና ሙሮ ውህደት ፈጠሩ፣ ወደዱትም። በዲማ ኮንፈሚንስ ለአመራር ብቁ ነው ብሎ ታጋዩ ወደ ተሓህት መሪነት አደሹሰው። ም/ወታደራዊ አዛዥም ሆነ። ይህ በወቅቱ ለነበሹው ታጋይ ታላቅ ድል ነበር።
ሙሮ ባልተጠበቀ ሁኔታ ጾሹ-ሻእቢያ አቋም ያዘ። ሻእቢያ ጾሹ-ሕዝብ፣ በተለይ ደግሞ ጾሹ-ትግራይ ሕዝብ ነው። ሻእቢያ ዹኔ ጠላት ዚትግራይ ሕዝብ ነው ዹሚል አክራሪ ድርጅት ነው፤ ዚተሓህት አመራር ደግሞ ሻእቢያን እንደፈጣሪ እዚቆጠሩ ጠዋት ማታ እግሩን ይስማሉ በማለት በተጠናኹሹ መልኩ ጾሹ-ሻእቢያ ቅስቀሳውን በማቀነባበር በስፋት ቀጠለበት፣ ታጋዩም አብሮት ቆመ።
አመራሩም ሙሮ ኚመትክል ዚትግላቜን አጋር ሻእቢያ እዚለያዚን ነው በማለት ሲናገሩ፣ በእንጻሩ ሙሮ ነፃ ሁኑ፣ አሜኚር አትሁኑ፣ ዚሻእቢያ አገልጋይና ታዛዥ አትሁኑ ነው ዚምላቜሁ ሲላ቞ው ዚተሓህት አመራር ሙሮን ማውገዙን ቢቀጥሉበተም በታጋዩ ተቀባይነት አላገኘም። ይበልጡኑ ዹሙሮ ተቀባይነት ኹፍ አለ። በዚህ ምክንያት አመራሩ ሙሮ መሃሪ ተክሌ ዚሚጠፋበትን መንገድ ማጠንጠን ጀመሩ። ዚግድያ ሎራ በስብሃት ነጋ ዚሚመራው ዚመለስ ዜናዊ፣ አባይ ፀሃዹና ሥዩም መስፍን በመተባባር እቅዱን አወጡ። ተግባር ላይ ዚሚያውሉት ደግሞ ስዚ አብርሃና ጻድቃን ገብሚተንሳይ ሲሆኑ ግድያውን ዹሚፈጾመው በርሄ ሃጎስ ሆኖ ተመሹጠ። በርሄ ሃጎስ አሁን ካናዳ፣ ኊቶዋ በመኖር ላይ ያለ ግለሰብ ነው። በላፈው ግንቊት 2005 አማራው ዚትግራይ ሕዝብ ጠላት ነው እያለ አማራውን ኢትዮጵያዊ ሲሰድበውና ሲያንቋሜሞው ዹነበሹ ሰው ነው። በገዘ ተጋሩ ፓል ቶክ።
ስዚ አብርሃ በሚመራት ሃይል 41 አመቺ ጊዜ ሲጠብቅበት ዹነበሹው ሙሮ ጻድቃን ገብሚተንሳይ በኮሚሳርነት ዚሚመራት ጋንታ በርሄ ሃጎስ ዚነበሚባት ጋንታ በመጠባበቅ ላይ ዚነበሩት ሁለቱ በአጋጣሚ ሓምሌ መጚሚሻ 1968 ኚሜራሮ ወጣ ብላ ዚምትገኘው ቁሜት ጫአ መስኚበት ስዚ አብርሃ ም/ሃይል መሪ በያዛት ሃይል በኢዲዩ ላይ ጥቃት እንደተጀመሚ፣ ሙሮ ታጋዮቹን እያስተባበሚ ጊርነቱን በመምራት ላይ እንዳለ በስተኋላው ዚነበሩት ጻድቃን ገ/ተንሳይና በርሄ ሃጎስ ውጊያው እዚበሚታ ሲሄድ በርሄ ሃጎስ አነጣጥሮ ሙሮ (መሃሪ) ተክሌን ግራ እጁ ላይ ትኚሻውን ጚምሮ ቆርጩ ጣለው። ዞር ሲል ጻድቃን ገ/ተንሳይና በርሄ ሃጎስ ኹኋላ ሆነው እንደመቱት አወቀ። አይን ለአይንም ተገጣጠሙ። በርሄ ሃጎስ ሙሮን ዚመታበትን ደምመላሜ ጠመንጃም ለጻድቃን ሲሰጠው አዹው። ክፉኛ ዹቆሰልውን ሙሮን በቃሬዛ ተሞክመውት ሲሄዱ ዚነበሩትን ታጋዮቜ ሁሉ ዚነገራ቞ው እኔ በኢዲዩ ጥይት አልተመታሁም፤ ዚመቱኝና ዹገደሉኝ ጻድቃን ገብሚተንሳይና በርሄ ሃጎስ ናቾው እያለ ሲናገር እንደነበሚና አንድ ሰዓት ተኩል ያህል ቆይቶ ኚዚቜ ዓለም እንደተሰናበተ ይናገራሉ። አዲ ፀጾር ቀሜት ወስጥ ተቀበሹ። ወዲያው በርሄ ሃጎስ ትንሜ ገንዘብ ተቀብሎ ሱዳን ገባ። ሙሮ  ዹተናገሹውን ኑዛዜ አውአሎም ወልዱ ሰምቶታል፣ ምስክርነቱን ይስጥበት።
4.  አጜብሃ ዳኘው
አጜብሃ ዳኘው፣ ዹበሹሃ ስሙ ሞዊት ነው። በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቚርሲቲ በሂሳብ ትምህርት ዹሁለተኛ ዓመት ተማሪ ነበር። ማገብት እንደተመሰሚተም ኚወራት በኋላ አባል ሆነ። መጋቢት 1967 ኚተሓህት ጋሹ ተቀላቀለ።  ኹጊዜ በኋላም በተሓህትን ፕሮግራም አደገኛነት ሂስ መሰንዘር በመጀመር ፕሮግራሙ ጾሹ-ሃገር ሉአላዊነት፣ ጾሹ-ኢትዮጵያ ሕዝብና በታኝ፣ ሕዝብን እርስ በርሱ ለግጭት ዚሚዳርግ በመሆኑ አዲስ ፕሮግራም ማርቀቅ ይጠበቅብናል በማለት ኹነ ገሰሰው አዹለ – አግአዚ ገሰሰ ጋር በአቋም ተስማሙ። በሚሰነዝሹው ሃሳብ በታጋዩ ተወዳጅ ሆነ፣ በድፍሚቱም ምክንያት ስሙ ገነነ። በዚህ መልክ ሲቀጥል፣ ሱዳን፣ ካርቱም ለሥራ ሂዶ በነበሚበት ወቅት መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ በአስ቞ኳይ አስጠርተው ሱዳን ባለህበት ጊዜ ጟታዊ ግንኙነት ፈጜመሃል በማለት በውሞት ኹሰው 06-ሃለዋ ወያነ አስገብተው አሰሩት። አሹጋዊ በርሄ ይህን እንደሰማ ኚነበሚበት ቊታ በቶሎ ደርሶ ኚእሰር አስወጥቶ ሥራውን እንዲቀጥል አደሹገ። ሐምሌ 1968 አመራሩ ወደ አምስት ስለወሚደ ገሰሰው አዹለ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሮ (መሃሪ) ተክሌ በተሓህት አመራር ስለተገደሉ፤ በአመራር ላይ ዚቀሩት አሹጋዊ በርሄ፣ ግደይ ዘርአጜዮን፣ ስብሃት ነጋ፣ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሃዹ ብቻ ነበሩ። ኹላይ በጠቀስኩት ወርና ዓ.ም. አምስቱ አመራር ተሰብስበው ዚሚኚተሉት ወደ አመራሩ ገቡ። መለስ ዜናዊ፣ አጜብሃ ዳኘው፣ አውአሎም ወልዱና ስዚ አብርሃ ወደ ተሓህት አመራር ወጡ።
አጜብሃ ዳኘው ለስልጣን እና ሹመት እጁን አልሰጠም። ዚተሓህት ፕሮግራም ጾሹ-ኢትዮጵያና ጾሹ-ሕዝብ፣ አውዳሚና በታኝ ስለሆነ መወገድ አለበት፣ ተሓህት ጠባብና ዘሹኛ ስለሆነ ትግላቜን ኢትዮጵያዊ መሆን አለበት። ትግራይ ዚአማራ ቅኝ ግዛት ናት፣ አማራ ጠላት ነው ማለት ሕገወጥ ዚፖለቲካ አቋም ነው በማለት ተኚራኚሚ። ክርክሩን እገላ ወሚዳ ስብኊ ቁሜት ሲኚራኚሩ ስብሃት፣ መለስና አባይ ተናደዱ። ሆያ አዲጚጓር ዹሚገኘው 06-ሃለዋ ወያነ ሃላፊዎቜ፣ ሙሉጌታ አለምሰገድና ክንፈ ገ/መድህንን አስጠርተው ዛሬውኑ አጜብሃ ዳኘውን እና ጓደኛው መኮንን በዛብህን ግደሏቾው። ስብሃት ነጋ ጾሹ-ተሓህት ናቾው ዹሚል ወሚቀት ጜፎና አዘጋጅቶ ሰጣ቞ው። እነአጜብሃ መኮንን ዚተሰጣ቞ውን ወሚቀት ይዘው በመሄድ ሆያ ላይ ጉድጓድ ተቆፍሮ በጥይት ተደብድበው በመገደል ኹዚህ ዓለም ተሰናበቱ።
አሹጋዊ በርሄ ዚአጜብሃ ዳኘውና ዚመኮንን በዛብህን መታሰር ሰምቶ ኚነበሚበት ተምቀን አካባቢ ሌት ተቀን ተጉዞ ሕይወታ቞ውን ለማዳን ያደሚገው ጥሚት ዚሚያስመሰግነው ነው። ሆያ እንደገባ እነ አጜብሃ ወደኔ አምጡልኝ፣ ተፈትተዋል፣ ጥፋት ዚለባ቞ውም ሲል ኚሙሉጌታ አለምሰገድ ጋር ያገኘው መልስ፣ ስብሃትና መለስ አባይ ሆያ እንደገቡ ሳይውሉ ሳያድሩ ይገደሉ ብለው ስላዘዙን ገደልናቾው አለው። ዚትእዛዝ ወሚቀቱም ዹኾው ብሎ ሰጠው። አሹጋዊ በርሄ ይህንን አሳዛኝ ግድያ ሰምቶ እነስብሃት ነጋ ወደሚገኙበት እገላ ሰብኊ፣ ቁሜት በመሄድ ተገናኛቾው። ነገር ግን ምንም አላደሹገም። ዚተሓህት ሊቀመንበር እንደመሆኑ ለምን ይሆን በነስብሃት ነጋ፣ መለሰ ዜናዊ ወዘተ. ላይ እርምጃ ሳይወሰድ ዹቀሹው ዹሚል ጥያቄ ተነስቶ ነበር። አሁንም እዚተነሳ ነው። መልስ መስጠት ያለበትም ዚወቅቱ ዚተሓህት ሊቀመንበር አሹጋዊ በርሄ ነው።
 5.  ዶ/ር አታክልት ቀጾላ
ዶ/ር ራስወርቅ ቀፀላ ዹበርሃ ስሙ ዶ/ር አታክልት ቀፀላ ዹህክምና ባለሙያ ነው። ቀደም ሲል ኚግንባር ገድሊ ሓርነት ትግራይ (ግገሓት) አባል ሆኖ በሹሃ ሲንቀሳቀስ ዚግገሓት ዚትግል ስልት አደገኛ ነው በማለት በሰኔ 1967 ኚተሓህት ተቀላቀለ። በተሓህትም ብዙ ስህተቶቜ እንደሚኖር አልተጠራጠርም ነበር። ነገር ግን ስህተቱን ለማስተካኚልና ለማሹም ብዙ ታጋዮቜ ይኖራሉ ዹሚለው እምነቱን እንደያዘ ቀስ በቀስ ፕሮግራሙን ዚማዚት እድል ገጠመው። ኹነገሰሰው አዹለ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሮ መሃሪና አጜብሃ ዳኘው ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለፈጠሚ፣ እነዚህ ሁሉ ዚተሓህት ፕሮግራምን ዹሚቃወሙ ናቾው። አጜብሃ ዳኛው በነስብሃትና መለስ እንደተገደለም ዶ/ር አታክለት ቀጾላ በአጜብሃ ፈንታ ዚተሓህት አመራሩን ጹበጠ። ግን እጁን አልሰጠም።
ዶ/ር አታክለት በፕሮግራሙ መጥፎና አደገኛ፣ ሃገርንና ሕዝብን ዚሚበታተን ነው ብሎ በማመን ኚተለያዩ አመራር ጋር ሲነጋገርበት እንደነበር ይታወቃል። ኹግደይ ዘርአጜዮን እና አሹጋዊ በርሄ መግባባት እንደነበሚውም ራሱ ዹተናገሹው ነው።
ኚመለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃዹና ኚሌሎቹ አመራር ጋር ግን ዚሻኚሚ ግንኙነት እንደነበሚው ታጋዩ ሁሉ ያውቃል። ሌላው ቀርቶ ስብሃት ነጋ በዚቊታው በሄደበት “ዚኢትዮጵያ ባንዲራ ራሱ ላይ ጠምጥሞ ዶ/ር አታክለት ቀጾላ በድርጅታቜን ተሓህት ቜግር እዚፈጠሚብን ነው” በማለት በዚቊታው መናገሩን እኔ ራሎ አስታውሳለሁ። ዶ/ር አታክልት ቀጾላ በ1ኛው ጉባኀ ዚተሓህት ዚአመራር ምርጫ በኹፍተኛ ዚድምጜ ቁጥር ተመርጩ ዚህወሓት ማ/ኮሚ቎ና ም/ወታደራዊ አዛዥ ሆነ። ዚነስብሃት ነጋ ዚስም ማጥፋት ዘመቻ አልተሳካም። በነገሩም ተደናግጠው ነበር።
ይህ በዚካቲት 5 ቀን 1971 በአዲነብር ኡድ ወሚዳ ማይ አባይ በተባለው ቊታ ዚተካሄደው 1ኛ ጉባኀ፣ ዚተሓህት ውርስ ስብሃት ነጋ ሊቀመንበር ዚሆነበት ጉባኀ ወርሱን ዚተሚኚቡት ስብሃት ነጋና ህወሓት ናቾው። ኹዚህ ጊዜ ጀምሮ ቀደም ብሎ ዚመጣው ፋሜስት ቡድን እውቅና ያገኘበት ጊዜ ነበር።
እነስብሃት ነጋ ዶ/ር አታክልትን ለማጥፋት ብዙ ጥናት በማካሄድ ዹተመቾ ጊዜ አገኙ። ግንቊት 1971 ዚውጊያው ዓይነት ጥቃት በኢትዮጵያ ሰራዊት፣ ዚውጊያው ቊታ ተምቀን፣ አብይ አዲ ጎንባስ ሞሞና ነበር። ዚህወሓት ሰራዊትም ይዘጋጅበት ነበር። ቀኑ ደርሶ ሁሉም ዚህወሓት ሰራዊት ወደ ውጊያው ቀጠና አመራ። ውጊያው ዚሚጀምርበት ጠዋት በስተምእራብ በኩል ኚውጊያው ቊታ በግምት በ10 ኪ.ሜ. ርቀት ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃዹና ሳሞራ ዚኑስ፣ ዚታጠቀው መሳሪያ ሲሞኖቭ ባለመነጜር ሆነው ዶ/ር አታክልት ቀጾላን ዚህወሓት ሊቀመንበር ስብሃት ነጋ ስለጊርነቱ ለመነጋገር ብሎ አስጠራው። እነሱም ለግድያው በመዘጋጀት በጠሩት መሰሚት ደሹሰ። ፊታ቞ውን ወደ ውጊያው ቀጠና ምስራቅ በማዞር ቀስ እያሉ መንገዱን ቀጠሉ። እኔና ዶ/ር አባዲ መስፍን ኚነስብሃት ነጋ ፊት 500 ሜትር ያህል በሚገመት ርቀት ወደ ጊርነቱ ቀጠና እንጓዝ ነበር። ዶ/ር አታክለት ቀጾላ ስብሃት ነጋ እንዳሰናበተው በፍጥነት እዚተጓዘ ሳለ ኹ250-300 ሜትር ርቀት ኚነሱ መካኚል ሳሞራ ዚኑስ በያዘው ሲሞኖቭ ባለመነጜር ጠመንጃ አስተካክሎና አነጣጥሮ በመተኮስ ዶ/ር አታክልት ቀጾላ ዚጀርባው አኚርካሬ ላይ መታው። ‘Special Column’ ተመትቶ ሲወድቅ አዩት። አባይ ፀሃዹ በፍጥነት ሩጊ ወደኛ ተጠግቶ አባዲ፣ አባዲ፣ ብሎ በመጥራት በእጅ ምልክት ኑ ሲለን ሄደን አገኘነው። ዶ/ር አታክልት ስለሞተ ቅበሩት፣ ነገር ግን ለማንም እንዳትናገሩ ብሎ ተመልሶ ኚነስብሃት ነጋ ጋር ተቀላቀለ። በኋላም ሶስቱም ተያይዘው ሲሄዱ አዹናቾው።
ዶ/ር አባዲ መስፍን እና እኔ ጉድጓድ ስንቆፍር እሱ እንደ ባለሙያነቱ ሬሳውን መመርመር ጀምሹ። ጀርባው ላይ ዚመታቜን ጥይት ሰውነቱን ኚፍቶ አወጣት። በሲሞኖቭ ጥይት ሳሞራ ዚኑስ ገደለው ብሎ እምባውን መግታት አቃተው። ጥይቷን በወርቀት ጠቅልሎ ያዛት። እኔና ዶ/ር አታክልት አፈርና ድንጋይ በመጫን ቀብሚን ተሰናብተን ወደ ጊርነቱ ተመለስን። ዶ/ር አታክልት ሞቶ ይቀበር እንጂ ታሪኩ ህያው ህኖ ይኖራል። እነ ስብሃት ነጋ መለስ ዜናዊ ወዘተ. በንጹሃን ደም መታጠብ ዚጀመሩት ገና ኚጥዋቱ ነበር። እነዚህ ጀግኖቜ በሞት ቢለዩንም ድምጻ቞ውና ዹተቀደሰ ተቃውማቾው፣ ዚህወሓት ፕሮግራም ይውደም ያሉት ድምጻ቞ው ግን በታጋዩ ዘንድ ተሰራጚ። በዚህም ምክንያት ብዙ ዲሞክራሲያዊ ጥያቄዎቜን በማንሳት ዚተሓህት- ህወሓት አመራርን አስጚነቁት። አመራሩ ተቃውሞውን አጠፍ በማድሚግ በድርጅታቜን ሕንፍሜፍሜ ተነሳ ብሎ ብዙ ታጋዮቜን እና ንጹሃንን መጚፍጚፊያ ምክንያት አደሹገው። ዚዲሞክራሲ ጥያቄው ተዋንያኖቜ፤ ገሰሰው አዹለ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሮ መሃሪ፣ አጜብሃ ዳኘውና ዶ/ር አታክልት ቀጾላ ያቀጣጠሉት ነው። ዚህወሓት ፋሜስትና አምባገነን መሪዎቜ ዚመጥፊያ቞ው ጊዜ እዚቀሚበ ነው፣ ተያይዘው በሕዝብ ሃይል ለፍርድ ይቀርባሉ።
 6. ግደይ ዘርአጜዮን
ግደይ ዘርአጜዮን ኹአሹጋዊ በርሄ ጋር በመሆን ዚማገብት-ተሓህት-ህወሓት ዚመሰሚት ድንጋይ ያስቀመጡ ህወሓትን ዚፈጠሩት ሁለቱ ናቾው። ሌላ ዹለም። ግደይ ዹተፈጾሙ ጥፋትም ሆነ ወንጀል ካሉ ኚነበሩት አመራር እኩል ተጠያቂ ነኝ በማለት በግልጜ ተናግሯል። በህወሓት አመራር አስኚቆዚሁበት በተፈጾሙ ወንጀሎቜ ተጠያቂ ነኝ። ነጻ ነኝ ብሎ ራሱን ያላገለለ በመሆኑ ያስመሰግነዋል።
ግደይ ዘርአጜዮን ዚተሓህት-ሀወሓት ኹፍተኛ አመራር ዚድርጅቱ ም/ሊቀመንበር በነበሚበት ጊዜ አመራሩ ዚሚፈጜመውን ግድያና ሜብር አውግዞ ኹ1969 መጚራሻ ራሱ ነፃ በመሆን ዚስንት ታጋይና ሰላማዊ ዜጋ ሕይወት ያዳነ ነው። ግን ብቻውን በመሆኑ ዚህወሓትን አመራር ክሚፈጜሙት ወንጀል ሊያቆማ቞ው አልቻለም። በሰላማዊው ዜጋና በታጋዩ ግን ሰፊ ዚታማኝነት፣ አጋርነትና ክብር ዹተሰጠው ግደይ ዘርአይጜዮን ነው። ግደይ ዚታጋዩ ጥብቅ ጓደኛ ሆነ፣ ተወደደ። ማንኛውም ታጋይ ቜግር ሲገጥመው ለግደይ ያናገራል። ግደይም ቜግሩን ይፈታለታል። ግደይ ራሱም ዚታጋዩን እና ዚሕዝቡን ፍቅር ጣእሙን ስላወቀው ሁልጊዜም ደስተኛ ነበር።
መለስ ዜናዊ ዚሚመራውን ማርክሲስት ሌሊኒስት ሊግ ትግራይ ለማቋቋም ዚሃላፊነቱ ተሰጠው። በ1ኛው ጉባኀ በኮሚሜን ደሹጃ እንደተቋቋመ በአቋም ልዩነታ቞ው እነ መለስ ዜናዊ፣ ግደይን እንደጠላት ማዚት፣ ግደይ ዘርአጜዮንም በአቋሙ ስለጞና መፋጠጥ ዚጀመርንበት ጊዜ ነበር። ዚነበራ቞ው ልዩነትም ዚማይፈታ ሆነ። ሁለቱም በተጻራሪ መንገድ ቀጠሉበት።
በእነ መለስ ዜናዊና አበሮቹ ዚሚያቀርቡት፤     
ብሄራዊ ዲሞክራሲያዊ አብዮት ዚአብዮቱ መሰሚታዊ ሃይሎቜ ድሃ ገበሬ፤ ላብ አደሩ ሲሆኑ፣ እነዚህን ካሰባሰብን ዚአብዮቱ ትግል ዓላማው እና ግቡን ይመታል። ሃብታም ገበሬ ኚሁለት ጥንድ በሬዎቜ በላይ ያሉት ሃብታም ገበሬ ስለሆነ በማርክስ ሌኒናዊ ሳይንስ ሃብታም ገበሬ ዚትግላቜን ጠላት ነው፣ በማለት አስሚግጠው ተናግሹዋል። ሃብታም ገበሬ መደምሰስ መጥፋት አለበት። ለምን ዚማርክስ ሌኒናዊ ጠላት ሃብታም ገበሬ ነው። መለስ ዜናዊ ይህንን በወይን መጜሔት እያተመ ታጋዩን ያስተምርበት ነበር።
ግደይ ዘርአጜዮን
ሃብታም ገበሬ ዚማርክሲዝም ሌኒኒዝም ጠላት አይደለም። አሁንም በህወሓት ዹሚመሰሹተው ማርክሲስት ፓርቲ ሃብታም ገበሬ ጠላት ሳይሆን ዚትግል አጋራቜን እና ወዳጃቜን ነው ተብሎ በትግሉ እንደ ወዳጅ መታወቅ አለበት። ኚሁለት ጥንድ በሬ በላይ ያለው ሃብታም ገበሬ ነው ስለሆነም ጠላት ነው እያላቜሁ ምክንያት በመፍጠር ያምታጠቁት ዚትግራይ ሕብሚተሰብ ፍጹም ጾሹ-ሕዝብ ነው። ንብሚቱ ሁሉ እዚተወሚሰ ለህወሓት ገቢ ሲደሚግ ለተገደለው ሕዝብና ለፈሹሰው ቀት ተጠያቂ ናቾው። ይህ ዚሃሳብ ልዩነት በነመለስ ዜናዊ ቡድን እና በግደይ ዘርአጜዮን መካክል ሰፍቶ በመውጣት ለዓመታት ቀጠለ።
መለስ ዜናዊ
በእኛና በግደይ ዘርአጜዮን መካኚል ሰፊ ልዩነት አለ። አብሚን መታገልም አንቜልም። ግደይ ዘርአጜዮን ሃብታም ገበሬ ዚማርክስ ሌኒናዊ ዚትግል አጋር ነው፣ ጠላት አይደለም ብሎ ያምናል። ይህ ዚሚያመለክተው ግደይ ዘርአጜዮን ጾሹ-ማርክስ-ሌሊናዊና በራዥ ነው ሲል በያዘው አቋም ዹማይነቃነቀው ግደይ፣ አንተና ጓደኞቜህ ናቜሁ በራዥና ኚላሜ ነህ ስለአለው ንትርኩ ሰማይ ወጣ። ግደይ ዘርአጜዮን አሁንም በዚህ ጉባኀ አቀርበዋለሁ። ሃብታም ገበሬ ዚትግላቜን አጋርና ወዳጅ መሆኑ ሙሉ እምነ቎ ነው። ሃብታም ገበሬ ጠላት ነው ብሎ ማስቀመጥ ጾሹ-ሕዝብ ነው። እነ መለስ ዜናዊ ሃብታም ገበሬ ጠላት ነው ማለታ቞ው ማንነታ቞ውን በትክክል ይገልጾዋል።
 2.  በማለሊት ጉባኀ አመራሩ ዳግም ለሁለት መሰንጠቅ
ዚማለሊት ጉባኀ በዚህና በሌላውም ጾሹ-ዲሞክራሲ ሲካሄድ ሰንብቶ ሐምሌ 21 ቀን 1977 ምርጫው ደሹሰ። ይህ ምርጫ ሕገወጥነትን ዹተኹተለና ሁለት ዋና ዋና ዓላማ ዚያዘ ነበር።
  1. ዚሥልጣን ሜኩቻ ዋና ዓላማው ነበር፣
  2. በዚህ ዚሥልጣን ሜኩቻ ማገብት-ተሓህት-ህወሓት ዚመሰሚት ድንጋይ አስቀምጠው በጾሹ-ዲሞክራሲና በጾሹ-ሕዝብነቱ አብሚው እዚመሩት ዚመጡት አንጋፋ አመራሮቜ ለማባሚር በድርቅ ዹተጠቃው መኹሹኛው ዚትግራይ ሕዝብ እያለቀ ኹአፉ ነጥቀው በነስብሃት ነጋ፣ በስንት ሚሊዮን ብር ዹተዘጋጀው ማለሊት ስልጣና቞ውን ለማደላደል ነበር።
ምርጫው
በሙሉ ድምጜ ዚመራጭ ብዛት 250 ነበር። ምርጫው በምስጢር ሆኖ በወሚቀት ዚምትፈልገውን መምሚጥም ነበር። ምርጫው ተካሄደ። ድምጹ ተቆጠሹ። በዝርዝር ተነገሹ። 1ኛ. ግደይ ዘርአጜዮን፣ ያገኘው ድምጜ 247፤ 2ኛ. አሹጋዊ በርሄ፣ ያገኘ ድምጜ 245፤ 3ኛ. ሃዹሎም አርአያ፣ ያገኘው ድምጜ፣ 236፤ 4ኛ. ስዚ አብርሃ ወዘተ. እያለ ዚድምጜ ቆጠራው ቀጠለ። ወደ መጚሚሻው ድምጜ ቆጠራ ደሹሰ። ይህንን ዹሚገልጾው ህብሩ ገብሚኪዳን ነበር። በጥቁር ሰሌዳ ላይ ዚተመሚጡት ያገኙትን ድምጜ እዚጻፈ ሲገልጜ ዹሚይዘው ዚሚጚብጠውን አጣ። ዚጉባኀው ተሳታፊ ቀጥል ብሎ አፋጠጠው። ላብ ፊቱ ላይ እዚወሚደ ቀጠለ። 24ኛ. መለስ ዜናዊ፣ ያገኘው ድምጜ 130፤ 25ኛ. ስብሃት ነጋ፣ ያገኘው ድምጜ 127 በማለት ዹ25ቱን ዚማለሊት ተመራጮቜ ዚማለሊት ማ/ኮሚ቎ ብሎ በጥቁር ሰሌዳው ላይ በማስቀመጥ ተመልሶ ወደ ቊታው ሄዶ ተቀመጠ። መለስ ዜናዊ ራሱን ደፋ። ፊቱ ዹተጠበሰ ስጋ መሰለ። ስብሃት ነጋ ደግሞ አዳራሹን ለቆ ወጣ። ኚጥቂት ደቂቃዎቜ በኋላ ዚጉባኀው ሊቀመንበር ዹነበሹው ሥዩም መስፍን ኚሰዓት በኋላ በ11 ሰዓት እዚህ እንገናኝ ብሎ ጉባኀተኛውን አሰናበተ። በዚህ ዓይነት ነበር ታጋዩ እነ መለስ ዜናዊን መሬት ውስጥ ዚቀበራ቞ው። ነገር ግን ተመልሰው ታጋዩን አጠቁት። ብዙ ነባር ታጋይ በእነ መለስ፣ ስብሃት ወዘተ. ተገደለ፣ ኚሞት ዹተሹፈውም ሞሞ።
ልክ በ11 ሰዓት ጉባኀው ተሰዹመ። በስብሃት ነጋ አመራር ዚተመሚጡት ማ/ኮሚ቎ ማለሊት አሰባስቊ ሹመትና ሥልጣን እዚሰጠ እንዲተባበሩት አደሹገ። ኹአሹጋዊ በርሄ ስልጣን አገኛለሁ ብሎ ስዚ አብርሃ በኹፍተኛ ድምጜ ዚመሚጥነው በግንባር ቀደምትምነት ክህደት ኹነ ስብሃት ጋር ተሰለፈ። በዚሁ ጉባኀ ዚመጀመሪያው ተናጋሪ መለስ ዜናዊ፤ ቀጥሎ ስብሃት ነጋ፤ ቀጥሎ ስዚ አብርሃ በመተባበር ግደይ ዘርአጜዮን እና አሹጋዊ በርሄ ኚህወሓት ኚማለሊት ተባሚዋል ተባለ። ታጋዩ ተደናገጠ፣ አጉሹመሹመ አለቀሰ። ኚአመራሩ ጻድቃን፣ ሥዩም ገብሩ፣ ወዘተ. በዚተራ በሁለት አንጋፋ አመራር አሰነዋሪ ዹሆነ ስድብ አወሚዱባ቞ው። ዚተባሚሩትም ክኛ ጋር ተቀላቀሉ። እነ መለስ ዜናዊ ተደላድለው በህወሓት-ማለሊት ኮርቻ ላይ ተቀመጡ። ዚህወሓት ሁለተኛ መሰንጠቅ ይህ ነው።
ዚስዚ አብርሃ ክህደት
ስዚ አብርሃ ደፋርና ጎበዝ እንደነበሚ አውቃለሁ። ኚሃዲነቱን ግን አላውቅም ነበር። በ1969 ዚሕንፍሜፍሜ ዋና ተዋናይ ነበር ተብሎ በስብሃት ነጋ ዚሚመራው ቡድን እስኚ 1977 ድሚስ በዓይነ ቁራኛ ሲኚታተሉት እንደነበር አውቃለሁ። ኚህወሓት ታጋዮቜ ደግሞ ለሰዹ አብርሃ ጥብቅና እና ድጋፍ አልተለዹውም ነበር። ኹዚህም ዚተነሳ ነው በማለሊት ጉባኀ በኹፍተኛ ድምጜ ዚመሚጥነው። ነገር ግን ኚሃዲውና እምነተ ቢሱ ስዚ አብርሃ ዚሥልጣን ጥማቱን ለማርካት ዚህወሓት-ማለሊት ሙሉ ወታደራዊ አዛዥ ለመሆን ግደይ ዘርአጜዮንን እና አሹጋዊ በርሄን በውሞትና በስም ማጥፋት ደበደባ቞ው። ሲጠብቀውና ሲንኚባኚበው ዹቆዹውን ታጋይ ለምን መለስ ዜናዊን እና ስብሃት ነጋን በአነስተኛ ደምጜ መሚጣቜሁ ብሎ ነባሩን ታጋይ እንደ እባብ እራስ እራሱን ቀጠቀጠው። በዚቊታው እዚሄደ አጠፋው።seye
በህዳር 1980 ዚህወሓት ታጋይ ባነሳው ተቃውሞ ኀርትራም ሆነ ሌላ ቊታ ሂደን አንዋጋም። ትግራይን ኚአማራው ቅኝ አገዛዝ ነፃ አውጥተን ዚትግራይን መንግሥት መመስሚት ነው እንጂ ኹዚህ ውጭ ዹምናውቀው ነገር ዹለም። ኀርትራ ሄደው በሹሃ ዹበላቾውና ያለቁት ዚትግራይ ወጣት ሎትና ወንድ እስኚ አሁን 130,000 ደርሷል። ዹኛ ድርጅት ህወሓት ኚዚት ወሚዳና ዞን መጡ ዹሚል ዝርዝር ስማ቞ው እንኳን አያውቀውም። እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ኚብት እዚታፈስን ሂደን ሞተን ቀሹን። አሁንም ትግራይን ነፃ እናወጣለን እንጂ ሌላ ቊታ አንሄድም አለ። በዚህ ጊዜ እነ መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ስዚ አብርሃን አነጋግሹው በ36,000 ታጋይ ላይ ሞት ፈሚዱበት። ይህ ሁሉ ታጋይ ዹውሃ ሜታ ሆኖ ቀሹ። በዚህ ግድያ ዚተሰማሩት መለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃዹ፣ ሃዹሎም አርአያ፣ ሳሞራ ዚኑስ፣ ጻድቃን ገ/ተንሳይ፣ አበበ ተክለሃይማኖት፣ ስዚ አብርሃ፣ ክንፈ ገብሚመድህን፣ አርኹበ እቁባይ፣ ገብሩ አስራት፣ ዓሚጋሜ አዳነ፣ አውአሎም ወልዱ ወዘተ. ነበሩ።
ዚተግባሩ አፈጻጞም በስዚ አብርሃና በክንፈ ገ/መድህን ትእዛዝና አመራር ነበር። ገዳዮቹ፣ ብስራት አማሹ፣ ሃሰን ሜፋ፣ ወልደሥላሎ፣ ዘአማኑኀል ለገሰ (ወዲ ሻምበል)፣ ተስፋዬ ጡሩራ (መርሳ)፣ ተስፋዬ አፈርሰው (አጜብሃ) ወዘተ. ነበሩ። ኹ200 በላይ ዹሃለዋ ወያነ (06) ታጋዮቜን በማሰለፍ ታጋዩን ገደሉት። ዹሃውዜን ጥቃትም በደርግ ሚግ 21-23-27 በእጅ አዙር ያስደበድቡት እነ ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊ ወዘተ. ኹዚህ ተነስተው ነው።
ስዚ አብርሃ ይህንን ክህደትና አሚመኔያዊ ተግባር ኹመፈጾሙ ትንሜ ቀደም ብሎ ኚነመለስ፣ ስብሃትና አባይ ፀሃዹ ጋር ተነስቶ ዹነበሹው አለመግባባት ተጧጡፎ ቀጠለ። ስዚ አብርሃ ሁሉንም ያጣ ብቻውን ሆኖ እዚተናገሚ መሄድ ጀመሹ። ታጋዩ ሁሉ ጠላው፣ ራቀው። ዚፖሊት ቢሮ አባላት በዚወሩ በስብሃት ነጋ ዹተፈቀደውን ዚኪስ ገንዘብ ብር 1,000 አልቀበልም አለ። ተወልደ፣ ገብሩ አስራትም እንደዚሁ አንቀበልም ብለዋል። ስዚ አብርሃ በፈጾመው ክህደት እስኚ ዛሬ በህወሓት ታጋይ እዚተወገዘ ነው።
3.  ዚህወሓት ለሶስተኛ ጊዜ መሰንጠቅ
ወቅቱ ጥቅምት 1980 ነበር። ዚህወሓት ማ/ኮሚ቎ን ጚምሮ ዚማለሊት ማ/ኮሚ቎ በአንድነት ዚተጠራ ስብሰባ ነበር። በዚህ ጊዜ ዚተነሱት ጥያቄዎቜ ዚስልጣን ሜኩቻ ሳይሆን ዚህወሓት-ማለሊት ፖሊት ቢሮ ዱሮ ኹነበሹውና ኚተፈጞሙት ስህተቶቜ ያልተማሚ፣ ብዙ ስህተት እዚፈጞመ ነው። ኹዚህ ስህተቱ መማር አለበት ወዘተ. በማለት ዹቀሹበው ጥያቄ አነታራኪ ሆኖ በመቀመጡ፣ ስብሃት ነጋ በሚመራው ስብሰባ ዚቀሚቡትን ጥያቄዎቜ በሙሉ ውድቅ አደሹጋቾው። መለስ ዜናዊም ዚስብሃት ነጋን ሃሳብ ደገፈ። ጥያቄቆቹን ያነሱት በ1975 በ2ኛው ጉባኀ ዚተመሚጡት ዚህወሓት አመራር ናቾው። እነሱም፤
  1. ክብሮም ገ/ማርያም ዚህወሓት ማ/ኮሚ቎ና ዚሰራዊቱ ዚሎጂስቲክ ዋና ሃላፊ ዹነበሹ፣
  2. ኃ/ሥላሎ መስፍን፣ ዚህወሓት ማ/ኮሚ቎፣ ጠቅላላ ዚህወሓት ክፍለ ጊሮቜ ዚኮሚሳሮቜ ዹበላይ ሃላፊና ተቆጣጣሪ ዹነበሹ፣
  3. ሰአሹ ገብሚጻድቅ፣ ዚህወሓት ማ/ኮሚ቎ና ጠቅላላ ዚህወሓት ማ/ኮሚ቎ና ፖሊት ቢሮ ጜ/ቀት ሃላፊ ዹነበሹ፣
  4. ተክሉ ሃዋዝ፣ ዚህወሓት ማ/ኮሚ቎ና ዚቀድሞ ዚድርጅቱ ዋና ዚደህንነት ሃላፊ ዹነበሹ ናቾው።
ኹላይ ዚተጠቀሱት አራቱ አመራር ባቀሚቡት ሃሳብ አፈንጋጩ ዚእነ ግደይ ዘርአጜዮን እና አሹጋዊ በርሄ ደጋፊዎቜ ተብለው ተወነጀሉ። ወንጃዮቹ፣ መለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ ስዚ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ፣ አባይ ፀሃዹ፣ ሥዩም መስፍን፣ ገብሩ አስራት፣ አርኹበ እቁባይ ናቾው፡ እነዚህ ዚፖሊት ቢሮ አባላት ተሰብሰበው ተወንጃዮቹን በማስጠራት እርማት እንዲያደርጉ ወሰኑ። በቀሚቡበት ጊዜም፣ ያቀሚባቜሁት ሃሳብ ጾሹ-ህወሓት-ማለሊት በመሆኑ፤ ኚአመራርና ኚሃላፊነታቜሁ ተወግዳቜሁ በተራ ታጋይነት ቀጥሉ ተብለው በስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ተሰናበቱ። ይህ ወቅት ህወሓት ለሶስተኛ ጊዜ ዚተሰነጠቀበት ወቅት ነበር።
5.  ዚህወሓት ለአራተኛ ጊዜ መሰንጠቅ
ይህ ዚህዋሓት ለአራተኛ ጊዜ መሰንጠቅ በ1993 ዹተፈጠሹው ነው። ዋናው ዓላማ ዚስልጣን ሜኩቻ ነበር። ሌላው አንዱ ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪ ሆኖ ሌላው ደግሞ ጾሹ-ኢትዮጵያ ሆኖ ዹተፈጠሹ መበታተን አይደለም። በእነ ስዚ አብርሃ ዚሚመራው ቡድንም ጾሹ-ኢትዮጵያና ጾሹ-ሕዝብ ነው። ሃገራቜን ኢትዮጵያን ያፈሚሱ፣ ዹቀይ ባህር ዚባህር በሯን ዚሞጡና ያስነጠቁ፣ ዹዘር ማጥፋት እልቂት ዹፈጾሙ፣ ሕዝብን ለድህነት፣ ለቜግር፣ ለበሜታና ለስደት ዚዳሚጉ እነ መለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ ስዚ አብርሃ፣ ተወልደ ወ/ማርያም፣ ገብሩ አስራት ወዘተ. ተባብሚው በሕዝብና በሃገር ኚባድ ወንጀል ዹፈጾሙ ናቾው። በሁለት ዚተሰነጠቁበት ቀንደኛ ምክንያት ደግሞ ዚስልጣን ሜኩቻ ነው። ሌላ ምንም ነገር አልነበሹም።
6.  ዚህወሓት ለአምስተኛ ጊዜ መሰንጠቅ
ህወሓት ኢትዮጵያን ወሮ በቅኝ ግዛት ኚተቆጣጠሚ በኋላ መሪው መለስ ዜናዊና ዚህወሓት አመራር ሁሉም በሃገራቜን ኹፍተኛውን ዚሥልጣን ወንበር ላይ ተደላድለው በመቀመጥ ኢትዮጵያን ለ21 ዓመታት በገዙበት ጊዜ በሕዝብና በሃገር ኹፍተኛ ወንጀል በመፈጾም ዚኢትዮጵያን ሃብት ዘርፈዋል። ሕዝብን ያደኞዚውን ስርዓት ዹመሰሹተው መለስ ዜናዊ ሰኔ 7 ቀን 2004 ኹዚህ ዓለም በሞት ተቀጠፈ። ብስራት አብሳሪው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ መኚታና መመኪያ እንዲሁም ዓይን እና ጆሮ ኢሳት በጥዋቱ ዚመለስ ዜናዊን ሞት ነገሹን። ለወዳጆቹ ሃዘን ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ዚእፎይታ ቀን ሆነ። አሹመኔው መሪ መለስ ዜናዊ ኹዚህ ዓለም በሞት ተቀጥፎ መኖሪያውን ሲኊል አደሹገ። በዚህም ምክያት ህወሓት ለአምስተኛ ጊዜ ተሰነጠቀ። ኹላይ እስኚ ታቜ በቅራኔና በሥልጣን ሜኩቻ እንደ ዱባ ተፍሹኹሹኹ።
    1. ዚተህሓት ወግ አጥባቂ
ተሚካቢ (Old guard)
    2. ተንኳሜ
(Catalyst)
    3. ዚመለስ ዜናዊ ውርስ
(Legacy)
ስብሃት ነጋደብሚጜዮን ገ/ሚካኀልአባይ ወልዱ
ብርሃነ ገ/ክርስቶስጌታ቞ው አሰፋሳሞራ ዚኑስ
አርኹበ እቁባይ቎ዎድሮስ አድሃኖምበዚነ ምክሩ
ጾጋይ በርሄአለም ገ/ዋህድ቎ዎድሮስ ሃጎስ
አባዲ ዘሞክንደያ ገ/ሕይወት
ብርሃነ ማሚት፤
ትርፉ ኪ/ማርያም
እነ ስብሃት ነጋ ያላ቞ው ደጋፊ ጥቂት ሲሆን፤ እነ አባይ ወልዱ ዚህወሓት ማ/ኮሚ቎ውን በብዛት ይዘዋል። እነ ደብሚጜዮንም ኚነአባይ ወልዱ ድጋፍ አላቾው። አንድ ተሚት አለ፣ ‘ኚዝንጀሮ ቆንጆ ምን ይመራርጡ’ እንደሚባለው ነው። ዚህወሓት መንጋ ኚአመራሩ ጀምሮ እስኚ ተራ አባላቱ በወንጀልና በሰው ልጅ ደም ዚታጠበ ነው። በዚህ ዓይነት በሳሞራ ዚኑስ ዚሚመራው ሰራዊት፣ ፖሊስ፣ ደህንነቱ፣ ዚፌደራሉ ሁሉ ወንጀለኞቜና ጾሹ-ሕዝብ ናቾው። መለስ ዜናዊ በሕይወት በነበሚበት ጊዜ በ1993 ዚተነሳው ዚስልጣን ሜኩቻ በሁለት ሲሰነጥቀው፤ አሁንም ተመሳሳይ ዓይነት እጣ ዹደሹሰው ኚመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ ነው፤፡ ህወሓትን በሶስት ዹኹፈለው ዋናው ዚሥስልጣን ሜኩቻ ብቻ ሳይሆን ኢፈርትን ማን ይምራ፣ ማንስ ይቆጣጠር ዹሚለው ነበር። በ’ለ’ ስር ዚተዘሚዘሩት ዚኢፈርት ዋናው ዚዝርፊያ መሳሪያ ስለሆነ በኛ ይመራ ባዮቜ ናቾው። በ’ሀ’ ምደብ ስር ያሉት እነ ስብሃት ነጋ ኹላይ እሰክ ታቜ ኢፈርትን መቆጣጠርና መምራት ያለብን እኛ ነን ብለው ቁመዋል። በተጚማሪም፣ ኚሥልጣኑም ዚሚንስትርነት ቊታ ለኛም ይገባናል ባዮቜ ናቾው። በተለይ አዜብ መስፍን በሕገወጥ መንገድ ኚስብሃት ነጋ ዚወሰደቜው ዚኢፈርት መሪነት ለኛ tedrosይመለስልን ሲሉ በ’ለ’ እና በ’ሐ’ ዚተሰለፉት አልተቀበሉትም። አዜብ መስፍንን ኚኢፈርት አስወግደን በሌላ ሰው እንተካታለን በማለት ተስማምተው ብርሃነ ኪዳነማርያምን በቊታዋ በዳይሬክተርነት አስቀመጡት። እነ ስብሃት ነጋ ግን ይህንን አልተቀበሉትም። ዚኢፈርት ዹበላይ ሃላፊ ዶ/ር ቎ዎድሮስ አድሃኖም ነው። እነ ስብሃት ነጋ በዚህ ግራ ተጋብተዋል።
በ’ለ’ ምደብ ያሉትን እነ ደብሚጜዮን ገ/ሚካኀል ትልቁ ጥሚታ቞ው በአባይ ወልዱ ዚሚመራው በ’ሐ’ ምድብ ስር ያሉት በ’ሀ’ እና በ’ሐ’ ምድብ ያሉት እንዳይስማሙና በመካኚላ቞ው ሆነው ነገር በመተንኮስ ቅራኔ ውስጥ እንዲገቡ ያደርጋሉ። አዜብ መስፍንን ካነሳን ዘንድ፤ አንበሳ ባንክን ወዘተ. ተቆጣጠሩ ተብሎ ለነስብሃት ነጋ ዹተሰጠ ገጾ በሚኚት ነው። ዚኀርትራው ተወላጅ ደብሚጜዮን ገ/ሚካኀል ‘ኢትዮ ቎ሌኮምን’ ዹግል ሃብቱ በማድሚግ ዹሃገርና ዚሕዝብ ሃብት እዚበዘበዘ ገንዘቡን በቻይና ባንክ በማስቀመጥ ኢትዮጵያን እያደማ ይገኛል። በ2007 ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሆን ፍላጎትም አለው።
ኀርትራዊው ቎ዎድሮስ አድሃኖም፣ ዹሃገር ሃብት እዚዘሚፈ በማሌዢያና በተለያዩ ሃገራት ባንኮቜ ሃብቱን እያደለበ ዹሚገኝ ዚህወሓት መሪ ነው። ኢፈርትንም መለስ ዜናዊ ኹሞተ በኋላ በሃላፊነት ዹተሹኹበ ሰው ነው። በ2007 ምርጫም በእነ ወልዱ ድጋፍ ዹጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቊታ ያገኘ ሰው ነው። እነ አባይ ወልዱ በትግራይ ውስጥ ዚሚገኙት ዚኢፈርት ፋብሪካዎቜ፣ እንደ አልመዳ ጹርቃ ጹርቅ፣ መሶብ ሲሚንቶ ፋብሪካ፣ መስፍን ኢንጂነሪንግ ወዘተ. ወፍራሙን ድርሻ ያገኛሉ። በዚሁ መሰሚት ኢፈርት ኹተመሰሹተ ኹ1985 ጀምሮ ለመንግሥት ግብር አይኹፍልም። ኚብሄራዊ ባንክና ኚንግድ ባንክ ዹሚበደሹውን ገንዘብ አይመልስም፣ እንዲያስኚፍለው ዚሚያስገድደው ሕግም ዹለም። ዚተለያዩ እቃዎቜ ሲያስገባና ሲያስወጣ ቀሚጥ ለመንግሥት አይኹፍልም። ምክንያቱም ኢትዮጵያን በቅኝ አገዛዝ ስር ዚያዘው ዚህወሓት ባለሥልጣናት ዹግል ንብሚታቜው ስለሆነ በማንም ሕግ ዹማይገዛ ኢፈርት ነው።debretsion gebremichael
መለስ ዜናዊ ኹሞተ በኋላ በህወሓት ውስጥ ኹፍተኛ ውዝግብ ተፈጥሯል፣ አሁንም እንደቀጠለ ነው። ሃይላቾውም ዚተበታነ እርስ በርሳ቞ው አለመተማመን ነግሷል። ሁሉም ዚህወሓት አመራርና አባሎቹ ደጋፊዎቹ በሙስና ዹተጹማለቁ በዘር ማጥፋት ወንጀል በመሰማራት ኹ8.9 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ዹገደሉ ናቾው። ኹ30 ሚሊዮን በላይም ኢትዮጵያዊ ኚተወለደበት ኚሚወዳት ሃገሩ ሠርቶ ኚሚበላባት፣ ልጆቹን አስተምሮ፣ አሳድጎ ለቁም ነገር ካበቃበት መሬቱ በማፈናቀል ግማሹ ለስደት ግማሹ ለሞት፣ ግማሹ ለቜግር፣ ለሚሃብ፣ መኖሪያ አልባ አድርገውታል። ኹዚህ በመነሳት ህወሓቶቜ በጜኑ አቋም ዚሚስማሙበት አጀንዳ አላቾው። ። ኚህወሓት ዚተባባሩ አመራር ዚነበሩትም በዚህ በጾና አቋም ይስማማሉ።
  1. አሁን በኢትዮጵያ ያለው ሕገመንግሥት ዚህወሓት ሕገመንግሥት ነው። ይህም ኹ1967 እዚታገልን ይዘነው ዚመጣን ዚሕይወታቜን እና ዚንብሚታቜን መድን ነው። ይህ ሕገመንግሥት ኹተናደ አሁን ያለነው ዚተባሚሩት አመራርም ተለቅመን ታሰርን፣ ሃብታቜን ተወሚሶ እኛም እንገደላለን። ስለሆነም ያለውን ሕግመንግሥት መክላኹል ዚግድ ይሆናል። ሁሉም በዚህ ይስማማሉ፣
  2. ኢፈርት ዚህወሓት ሃብት ነው። ኢፈርትም በኢትዮጵያ ያሉትን ገዢ ተቋማት በተዘዋዋሪና በቀጥታ ዚሚቆጣጠር ነው። ለምሳሌ፣ ኢትዮጵያ አዹር መንገድ፣ ብሄራዊ ባንክ፣ ንግድ ባንክ፣ መአድናት፣ ትራንስፖርት ወዘተ. ዚሃገሪቱ ንግድም ኚትንሹ እስኚ ትልቁ ዚሚቆጣጠር ነው። ይህ ዹደም ስራቜን ኹወደመ በሕዝብ ቁጥጥር ኹዋለ ህወሓትና መሪዎቹ ብቻ ሳይሆኑ ዚህወሓት መንግሥታዊ ተቋማት ጭምር ይወድማሉ። ስለሆነም ባለን አቅማቜን ኢፈርትን መኹላኹል በበለጠ ማሳደግ አለብን። በዚህም በማያወላውል መንገድ ይስማማሉ፣
  3. ዚሕዝብ ዚአመጜ ተቃውሞ ወይም አብዮት ኚተነሳ ባለን መኚላኚያ ሰራዊት ደህንነት፣ ፖሊስ፣ ሚሊሻ፣ ልንመልሰው አንቜልም። ሕዝቡ ኹአሾነፈ ዚህወሓት አመራር አባሎቜና ደጋፊዎቻቜንን በእሳት እንደሚቀቅለን እናውቃለን። ለዚህ መድሃኒቱ ዚኢትዮጵያን ሕዝብ በዚጎሳ ኹፋፍለን አሁን ባለው አይነት ደፍጥጠን ማጥቃት፣ ተቋዋሚ ድርጅቶቜን ማዳኚም፣ መግደል ማዋኚብ አለብን። ዚአገዛዛቜን መንገድ ሕዝቡን ማስጚነቅ፣ ሚሃብ፣ በሜታ፣ በስደት እንዲጓዙ ማድሚግ እነዚህን በዋናነት እንደ መሳሪያ መጠቀም አለብን። ወጣቱን ዜጋ ደግሞ በሜርሙጥና፣ ሃሺሜ ወዘተ. በብዛት አስፋፍቶ ኚጥቅም ውጭ ማድሚግ። በጎሳ ኹፋፍለንም ኢትዮጵያዊነት ዹሚል ስር ዹሰደደውን እምነት ማጥፋት፣ ዹአማርኛ ቋንቋን ማጥፋት፣ በዚትኛውም ጎሳ ዹሚገኘውን ስር መሰሚቱን ነቅለን እንዳልነበሚ ማድሚግ። በዚህም ሁሉም ይስማማሉ።
ኢትዮጵያን አሁን ማን እዚመራት ነው?
መለስ ዜናዊ ኹሞተ በኋላ ኃ/ማርያም ደሳለኝ ዚኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስ቎ር ተብሎ እንደተሰዚመ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያውቀዋል። ነገር ግን ኃ/ማርያም ዚእውነት ሳይሆን ዚውሞት ጠ/ሚኒስ቎ር ነው። ኢትዮጵያና ህዝቧ ላይ አሁንም መዋቅሩን ዹዘሹጋው ህወሓት ነው። ኹመጋሹጃ ጀርባ ሆነው ኢትዮጵያን ዚሚመሩትና ዚሚያስተዳድሩት ደብሚጜዮን ገ/ሚካኀል፣ ቎ዎድሮስ አድሃኖምና ንዋይ ገብሚአብ ናቾው። ስለዚህ ኢትዮጵያን ማን እዚመራት ነው ለሚለው ጥያቄ በትክክል ኹላይ ዚተጠቀሱት ሶስቱ ዚህወሓት አመራር ናቾው። ዚስርዓቱን መዋቅርም በነዚህ ግለሰቊቜ ይመራል። ኃ/ማርያም ደሳለኝ አድርግ ያሉትን ዚሚያደርግ ጉልቻና ቃል አቀባይ ነው።
በ1922 ዹተወለደው ዹ83 ዓመቱ ዘራፊና ገዳዩ ሜማግሌ ስብሃት ነጋ ዚሚመራው ቡድን ለባለሥልጣናቱ እንቅፋት አይሆንባ቞ውም። መሪዎቹ ዚሚፈልጉት ዝርፊያ ብቻ ነው። እነ አባይ ወልዱ ኹነ ደብሚጜዮን ጋር ተስማምተው በትግራይ ሪፓብሊክ መንግሥት ውስጥ እጃቜሁን አታስገቡ። ገንዘብ እንፈልጋለን፣ ኹፍተኛ ባጀት መድቡልን፣ እኛም ዚእናንተ ደጋፊዎቜ ነን በማለት ተስማምተዋል።
hailemariam speakingለሚቀጥለው ዹ2007 ምርጫ ህወሓት በአሞናፊነት ወጥቶ ለጠ/ሚኒስ቎ር፣ ም/ጠቅላይ ሚኒስ቎ር ዚሚሆኑትን እጩዎቹን አዘጋጅቷል። ጠቅላይ ሚኒስ቎ር ይሆናል ተብሎ ዚታጚው ቎ዎድሮስ አድሃኖም ሲሆን፣ ም/ጠቅላይ ሚኒስ቎ር ሊሆን ዚታሰበው ደብሚጜዮን ገ/ሚካኀል ነው። “አባይ ማደርያ ዹለው ግንድ ይዞ ይዞራል” ማለት ይህ ነው። ህወሓት ዚተዳኚመ፣ ዹበሰበሰ ግንድ ነው። በዚህ ደሹጃ ላይ ያለ ፋሜስታዊ ድርጅት ኢትዮጵያን ሹግጩ ዚመግዛት አቅም ዹለውም። በኢትዮጵያ ሕዝብ ሃይል ክንድና አንድነት ይደመሰሳል። ይህንን ድክመታ቞ውን በመጠቀም ሃገር ቀትም በውጭ ሃገር ዹምንገኘውን ጚምሮ አንድነታቜንን አጠናክሹን በሕዝባዊ አመጜ ወያኔ ህወሓትን ዚመደምሰስ ጊዜው አሁን ነው።
ዚመለስ ዜናዊ ራእይ
በዚሁ ጥቂት ጥያቄዎቜን በመለስ እደመድማለሁ። መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያ ማን ነው?
መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያ ዚጠላት ጠላት ደመኛ ጠላት ነው። ኚአባቱ፣ ኚእናቱና ኚአያቶቹ ዹወሹሰው በኢትዮጵያና በሕዝቧ ላይ ዹፈጾመው ግፍ፤ ዹሃገር ማፍሚስ ድርጊት በታሪክ ዚማይሚሳ ነው። እሱ ብቻ ሳይሆን ዚህወሓት አመራርንም ይጚምራል። ዚስም ዝርዝራ቞ውን በተለያዩት ጜሁፎቌና ኹዚህ በላይም ስላካተትኳ቞ው እንሱን መመልኚትና ማመሳኚር ይቻላል።
ዚመለስ ዜናዊ ራእይ በኢትዮጵያ ልማት፣ እድገት፣ ዲሞክራሲ ማለትስ ምን ማለት ነው? በእርሱ አመራር ለ21 ዓመታት ኢትዮጵያ በልማትና በዲሞክራሲ አብባለቜ ዚሚሉት ዚህወሓት ደጋፊዎቜና አጋር ድርጅት ተብለው ዚሚጠሩት ጾሹ-ሕዝብና ጾሹ-ኢትዮጵያ ስብስብ ብቻ ናቾው። ብዙ ለሆዳ቞ው ያደሩም አሉባ቞ው። ነገሩ ዚተጋላቢጊሜ ነው። መለስ ዜናዊ ዚሚመራው ህወሓትና አመራሩ በተፈጥሮው ጾሹ-ሕዝብና ጾሹ-ዲሞክራሲ ነው። ህወሓት አፈጣጠሩ አምባገነን እና ፋሜስት፣ እንዲሁም ጾሹ-ዲሞክራሲ ሆኖ ያደገ ኚመቅጜበት ዚልማት፣ እድገትና ዲሞክራሲ አራማጅ ሊሆን አይቜልም። ጎባጣና ጠማማ ሆኖ ያደገ ባህር ዛፍ ተቃንቶ ለኀሌክትሪክ ምሰሶ ወይም ለቀት መስሪያ ማገር ልታደርገው አትቜለም። በምሳር ቆራርጊ ማገዶ ኚማድሚግ ውጪ። ህወሓትን በዚህ አይነት ልንመለኹተው ይገባል። ስለሆነም ዚመለስ ዜናዊ ራእይ ጾሹ-ሕዝብ፣ ጾሹ-ልማት፣ ጾሹ-እድገት፣ ጾሹ-ዲሞክራሲ ነው። መለስና ግብሚአበሮቹ በዘር ማጥፋት ወንጀል ዚተሰማሩ፣ በሙስና ዚሕዝብና ዹሃገር ሃብት ዹዘሹፉ፣ ዚኢትዮጵያን ሕዝብ በፋሜስት መዋቅራ቞ው ያሰቃዩና ዹገደሉ ናቾው። እንደዚህ ያለ ጹቋኝና ፋሜስት መንግስት ልማታዊ ሊሆን አይቜልም።
መለስ ዜናዊና ህወሓት ለኢትዮጵያና ሕዝቧ ምን ናቾው? በመለስ ዜናዊና በስብሃት ነጋ ዚሚመራው ፋሜስት ፓርቲ፣ ኢትዮጵያን ኚግንቊት ወር 1983 ጀምሮ ኚተቆጣጠሩ ወዲህ ኢትዮጵያና ሕዝቧ በወያኔ ሀውሓት ቅኝ አገዛዝ ዚወደቀቜበት ወቅት ሆኖ፣ እነሆ ቅኝ ገዢው ህወሓት በሃገራቜን አሚመኔያዊ ድርጊት እዚፈጞመ ይገኛል። በመለስ ዜናዊ ዹአገዛዝ ዘመን ዚኢትዮጵያ ሉአላዊንት ፈርሷል። ጥንታዊና ታሪካዊ ዹቀይ ባሕር ወደቊቿን አጥታለቜ። ሕዝብ በዘሩ እዚታዚ ዹዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጜሟል። ስለዚህ መለስ ዜናዊና ህወሓት እንዲሁም አመራሩ ዚኢትዮጵያ ደመኛ ጠላት ናቾው።
መለስ ዜናዊ ዚወታደራዊ ሳይንስና ስትራተጂ ባለ ራእይ ይባላል። ይህ አነጋገር ደሹቅ ውሞት ነው። መለስ ዜናዊን ዚሚያውቁና አብሚውት በትግሉ ዚነበሩ ታጋዮቜ ዚማይቀበሉት ጉዳይ ነው። ዚህወሓት መንጋ በምን ዓይነት ዚውሞት አዘቅት ውስጥ እንደሰመጠ በግልጜ ዚሚያሳይ ነው። መለስ ዜናዊ ኚትግሉ መጀመሪያ አንስቶ ለብዙ ዓመታት አብሚን ተጉዘናል። በጣም ዚሚተማመንብን ጓደኞቹ ተክሉ ሃዋዝና እኔ ገ/መድህን አርአያ ነበርን። በሚገባ ስለምናውቀው ዚወታደራዊ ስታር቎ጂስት አልነበሹም። እውቀቱም ቜሎታውም ፈጜሞ አልነበሹውም። ሃቁ ይህ ነው።
“ጅብ በማያውቁት ሃገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ” እንዳለው ዓይነት ነው። መለስ ዜናዊ ኚፈሪነቱ ዚተነሳ በተለያዩ ጊርነቶቜ ፈርቶ ዹሾሾ፣ በህወሓት ታሪክ ውስጥ በፈሪነቱ ቀዳሚውን ስፍራ ዚያዘ ግለሰብ ነው። ኚሞሞባ቞ው ጊርነቶቜ ለአብነት፤
  1. በ1969 ኚአድዋ ኊፐሬሜን ጊርነቱ እንደተጀመሚ ፈርቶ ዹሾሾ፣
  2. በ1970 ኚአዲ ደእሮ ፈርቶ ዹሾሾ፣
  3. በ1971 መጀመሪያ ላይ ኹማይቅነጠል ውጊያ ፈርቶ ዹሾሾ፣
  4. በ1971 ህዳር ወር ኚፈሚስ ማይ ጊርነት ፈርቶ ዹሾሾ፣
  5. ሰኔ ወር 1971 ኹሃገሹ-ሰላም ውጊያ ታመምኩ ብሎ መሬት ላይ ሲንኚባለል በበቅሎ ተጭኖ እንዲምለስ ዹተደሹገው  ናቾው። በምስክርነት ዚሰራዊቱ ዹጩር አዛዥ አሹጋዊ በርሄ ዚሚያውቀው ጉዳይ ነው።
በህወሓት ውስጥ ማንም ታጋይና አመራር ዚሚያውቀው ሃቅ አለ። ወታደራዊ እቅድና ስትራ቎ጂ ዹነደፈው ጥናት እያደሚገ ወታደሚአዊ ስትራተጂ ወታደራዊ ታክቲክ ዹአሾዋ ገባታ ለሹጅም አመታት ጥናት በማካሄድ ዚጻፈና ያዘጋጀ ብ቞ኛው አሹጋዊ በርሄ ነው። ለሁሉም ወታደራዊ አመራር ስዚ አብርሃ፣ ሃዹሎም አርአያ ወዘተ. አስተምሮ ያሳደጋ቞ው አሹጋዊ በርሄ ነው። ስዚ አብርሃ ይሁን ሌላው ዚሚኩራሩበት ውሞት ነው። ወያኔ ህወሓት እስኚ አሁን ዚሚጠቀሙበት ወታደራዊ ጉዞ በአሹጋዊ በርሄ ዹተዘጋጀ እንጂ መለስ ዜናዊ እስኚ እለተ ሞቱ ድሚስ ወታደራዊ ሳይንስ ይሁን ስትራተጂ ዚጀፍ ቅንጣት ዚምታክል እውቀት አልነበሹውም። ሁሉም ዹሚዋሾው ለሆዱ፣ ለጥቅሙና ዚሙስና ዘርፊያውን በስፋት ለመቀጠል ስለሚፈልግ ዚሚመታው ዚውሞት ነጋሪት ነው።
ግደይ ዘርአጜዮን ኚህወሓት ወጥቶ ወደ ስደት ሲሄድ በህቡር ገብሚኪዳን መሪነት ተክለወይን አሰፋ፣ ተሻለ ደብሚጜዮንን ጚምሮ ተፈትሟ ዚያዘውን ሰነዶቜ ሁሉ፣ ብጣሜ ወሚቀት ሳትቀር፣ ጠራርገው በመውሰድ ባዶ እጁን ሱዳን ገባ።
አሹጋዊ በርሄ፣ ህቡር ገ/ኪዳን፣ ስብሃት ነጋ፣ አርኹበ እቁባይ ሁነው ለብዙ ዓመታት ሲያካሂዱት ዹነበሹውን ወታደራዊ ጥናትና ስትራተጂ ዹአሾዋ ገበታ፤ በትልልቅ ወሚቀቶቜ ላይ በሰእል መልክ ዹተዘጋጁ ጠቅላላ ወታደራዊ መጻሕፍት ብጣሜ ወሚቀት ሳትቀር በሁለት ዚማዳበሪያ ኚሚጢት ሞልተው ዚወሚሱትን በታጋዮቜ አሾክመው ለመለስ ዜናዊ አስሚኚቡት። ‘በሰው ደንደስ በርበሬ ተወደሰ’ እንደተባለው፣ መለስ ዜናዊ ባልሰራውና በማያውቀው ወታደራዊ ስትራተጂ ዹአሾዋ ገበታ ንድፈ ሃሳብና አሹጋዊ በርሄ ደክሞ ያዘጋጀው ነው። አሁን ወያኔ ዚሚጠቀምበት ወታደራዊ አካሄድ ዹአሹጋዊ በርሄ ሥራና ጥናት ነው። ባልሰራኞው፣ በማታውቀው ጥበብ ዚራስህ አስመስለህ መጠቀም ያስንቃል፣ ያዋርዳል። ስለዚህ መለስና ዚህወሓት መንጋ ውሞታምና በምን ዓይነት ድቅድቅ ዚውሞት ጹለማ እንደተዘፈቁና ማንነታ቞ውን እንዲያውቁ ይህንን ዚጜሑፍ ሰነድ ያንብቡ።
ዚስብሃት ነጋ መርዶ ነጋሪ
ቀደም ብሎ በተህሓት-ህወሓት ዹነበሹው ዚኢትዮጵያውያን አመራር ነበር። እነ አቶ ገሰሰው አዹለ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሮ (መሃሪ) ተክሌ፣ አጜብሃ ዳኘው፣ ዶ/ር አታክልት ቀጾላ በምን ምክንያት በምን ዘዮ እንደገደሏ቞ው በትክክል አስቀምጬዋለሁ። በዚካቲት 1981 በወቅቱ ዚኢትዮጵያ መንግሥት ዹነበሹው ደርግ ትግራይን ለቆ መውጣቱን ተኚትሎ ወያኔ ህወሓት ካለምንም ውጊያና ውጣ ውሚድ ትግራይን ተቆጣጠሚ። ሃቁ ይህ ሆኖ፣ በ1983 በለስ ቀንቷ቞ው አዲስ አበባ ዘው ብለው ኢትዮጵያን እነደተቆጣጠሩ፣ ነብሰ ገዳዩ ስብሃት ነጋ በመርዶ ነጋሪነት ተሰማራ። ዚዶ/ር አታክልት ቀጾላ ወላጅ አባት ዚሚኖርበት ቀት በመሄድና እራሱን በማስተዋወቅ ዚዶ/ር አታክልትን ሞት ነገራ቞ው። በአሹጋዊ በርሄ እንደተገደለ ሲነግራ቞ው፣ አሹጋዊ በርሄ ዹማን ልጅ ነው ብለው ሲጠይቁት፣ ዚቀኛዝማቜ በርሄ ገብሚማርያም ነው ሲላ቞ው፣ ዹልጅ በዛብህ ፍላቮ ልጅ? ብለው ጠዚቁት፣ አዎን አላቾው። ዚቅርብ ወንድሙ ለምን ገደለው? ሲሉት፣ በአሹጋዊ መገደሉን እንጂ ሌላውን ሳይነግራ቞ው መርዶውን አሰምቶ ተሰናበተ። በጅሮንድ ቀጾላም በሚወዱት ልጃቾው መርዶ ዚተነሳ ታመው ኚብዙ ስቃይ በኋላ ኹዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
ስብሃት ነጋ ይህ አልበቃውም። አድዋ አቶ ዳኘው ገ/ሥላሎ ቀት ደሚስ በመሄድ ዚአጜብሃ ዳኘው ወላጅ እናትና ጠቅላላ ቀተሰቡ ባሉበት፣ በአክብሮት ተቀብለው ቀት ያፈራውን ኚጋበዙት በኋላ፣ እናቱ ወ/ሮ ማና ተፈሪ ልጄ ‘ሞላ’ (ዚቀት ስሙ) እንባ቞ውን እያፈሰሱ፣ ልጄ ጠፋብኝ፣ ዚምታውቀው ነገር አለ ወይ ብለው ሲጠይቁት፣ ስብሃት፣ አጜብሃ፣ ሰዊት ተገድሎ ኹሞተ ብዙ ዓመት ሆኖታል አላቾው። አባትዚው ቀበል አድርገው እንዎት ሞተ ሲሉት፣ አሹጋዊ በርሄ ገደለው አላቾው። አሹጋዊ፣ ዹቀ/አ በርሄ ገ/ማርያም ልጅ? ብለው ሲጠይቁት፣ አዎን አላቾው። ያሳደገው ወንድሙ ገደለው? ዚአጜብሃ ዳኘው እናት በዚህ ደንግጠው ታመው በሃዘን በሜታ ተሰቃይተው ሞቱ። ሜማግሌው አቶ ዳኘው ገ/ሥላሎ አሁንም በሕይወት አሉ። ዚዶ/ር አታክለት ቀጾላ ወላጅ አባትም በመርዶው ምክንያት ታመው፣ ራስ ወርቅ ልጄ እንዳሉ ሞቱ። በ1998 ዚሁለቱ ቀተውስቊቜ ስልክ በቀጥታ ወደ እኔ ደውለውልኝ ተነጋግሹናል። በዚህ ሃሳብ ላይ እንዳለን፣ ዚዶ/ር አታክልት ቀጾላ ወላጅ አባት በጅሮንድ ቀጾላ ብሩ፣ ወላጅ እናቱና ዚእኔ ዹዚህ ጜሑፍ አቅራቢ ገ/መድህን አርአያ ወላጅ እና቎ ወ/ሮ አጾደ ገብሩ እናት፣ ዚሁለቱ እናቶቜ ታላቅና ታናሜ ዚአንድ አባትና እናት ልጆቜ ናቾው። በዚህ መሰሚት ነው ዚዶ/ር አታክለት ቀጾላ ቀተሰቊቜ አሹጋዊ በርሄ በምን ምክንያት እንደገደለው ዹጠዹቁኝ። እኔም ስብሃት (ወ/ሥላሎ) ነጋ ዚነገራቜሁ ውሞት ነው። ዶ/ር አታክልትን ዹገደለው ስብሃት ነጋ ነው፣ በማለት በጜሑፍ እንደገለጜኩት ስነግራ቞ው አምነውኝ ተለያያን። ያመኑኝ ምክንያት ዚአታክልት መገደል ለእኔም ዹሚሰማኝ ልክ እንደ እነሱ ስለሆን ነው። ለእኔም ለነሱም ወንድማቜን ነው።
ቀጥሎ ኚትንሜ ወራት በኋላ በ1998 ኚአጜብሃ ዳኘው ቀተሰብ ወንድሙ ኚእንግሊዝ ሃገር ደወለልኝ። በጜሑፍ እንዳስቀመጥኩት ገልጬለት አልቅሶና አጜናንቌው ተለያዚን። ቀጥሎ ለሁለተኛ ጊዜ በ2000 ወንድሙ ደውሎልኝ፣ ያቀሚብኩለትን ሁሉ እንዳለ አምኖ ተቀበለኝ። ሌላው ያቀሚበልኝ ጥያቄ ቀተሰቊቌ በአሹጋዊ በርሄ ቅሬታ አድሮባ቞ው ነበር፤ በምን አይነት ይቅርታ ልጠይቀው፣ እባክህ ንገርልኝ ሲለኝ፣ ዹለም ኹሆነ ባንተ ነው መሆን ያለበት ብዬው እንደሚደውልለት ነግሮኝ ተሰነባበትን። አሹጋዊ በርሄ ግምት ያልሰጠው እውነት አለ። ዚህወሓት ፕሮግራምን ጜፎ ለ12 ዓመት በኹፍተኛ አመራር ላይ ሆኖ ያስተዳደሚው ድርጅት ነው። ማንም ዚማያቀውን ዚድርጅቱን ወንጀሎቜ በዝርዝር ያውቃል። ህወሓት በሥልጣን ላይ ሆኖ ለፈጾመው ግፍ ተጠያቂ እንዳይሆን አሹጋዊ በርሄ አጋጣሚውን ተጠቅሞ ወያኔን ማጋለጥ አለበት።
እነ ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊ ወዘተ. በትግሉ ጊዜ ዚተገደሉት ታጋዮቜ፣ ሰላማዊ ዜጎቜ በስንት ሺህ ዚሚቆጠሩ ናቾው። ኹ1982 በዘመቻ መልክ ተነስተው ያስፈጁትን አሹጋዊ በርሄ እንደገደላ቞ው አድርገው ስሙን በክፉ መልክ አጥፍተውታል፣ አሁንም እንደቀጠሉበት ነው። ዚህወሓት አባላትና ደጋፊዎቹ እስኚ አሁን እኛን ዹፈጀን አሹጋዊ በርሄ ነው እያሉ ይገኛሉ። እሱም ይህንን ነገር በትክክል ያውቃል። አሹጋዊ ዹሚለውና ዹሚሟገተው፣ ማስሚጃቜሁን አቅርቡ እያለ ነው። ይህ አባብሉ ግን ትክክል አይደለም። ዚፖሊት ቢሮ አባልት ሁሉ በዹ06 ሃለዋ ወያነ እዚተበተኑ ሕዝብ ዚጚሚሱት አመራሩ ናቾው። በ06 ሃለዋ ወያነ ሃላፊዎቜ ዚምርመራ ሪፖርት ጭፍን ፍርድ ሲሰጥ ዹነበሹው አመራር ነው። በሰነድ ተደግፎ ዹሚፈጾም ግደሏቾው ዹሚል ትእዛዝ በተህሓት-ህወሓት አሰራር አይታወቅም።
እነ ስብሃት ነጋ በአሹጋዊ በርሄ ላይ ዚሚያካሂዱት ዚስም ማጥፋት እልባት ማግኘት አለበት ኹሚል ሃሳብ ተነስቌ መጋቢት 2 ቀን 2000 በዓለም ዙሪያ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዚትግራይ ተወላጆቜ ማህበር፣ በዶ/ር ግደይ አሰፋ ሊቀመንበርነት፣ በአቶ ተስፋዚ አጜብሃ ዚሚመራው ቡድን በተጠቀሰው ቀን ተሰበሰበ። ለአሹጋዊ በርሄ ያቀሚብኩት ሃሳብ በእነ ስብሃት ነጋና በወያኔ ስርዓት ስምህ እዚጠፋ ነው። አንተም በመጀመሪያ ማድሚግ ያለብህ ዚኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ ጠይቀህ በህወሓት ዚተፈጞሙትን ወንጀሎቜ ለሕዝብ አቅርብ። ያን ስታደርግ ዚአእምሮ እሚፍት ታገኛለህ። በህወሓት በርካታና ኚባድ ወንጀሎቜ ተፈጜመዋል። ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅር ባይ ነው ዹሚል ሃሳብ አቀሚብኩለት። በወቅቱ ዚነበሩ አመራርና በቮሌ ኮንፈሚንስ ዚነበሩት ዚሚመሰክሩት ጉዳይ ነው። አሹጋዊ በርሄ ለምን ደፈርኹኝ ብሎ ብዙ ተናገሹ። ቁም ነገሩ ቮሌ ኮንፈሚንስ በመሆኑ ነው እንጂ በአካል አጠገቡ ብገኝ ኖሮ ሹጋግጩ ያጠፋኝ ነበር። ዚሁላቜንም ግንኙነት ኹዚህ ጊዜ በኋላ ተቋሹጠ። ጥሩ ምክር በመለገሮ ጠላት አፈራሁ። ዚመኚራና ዚቜግር ጊዜ ወንድሙን ጠላኝ። ይባስ ብሎ ዚህወሓት ጠላትና ጜንፈኞቜ በማለት፣ አስገደ ገ/ሥላሎን እና እኔ ገ/መድህን አርአያን ፈሹጀን። ይህን ለማለቱ ብዙ ዹሰው ምስክሮቜት አሉን። ዹተማሹ ሰው ነው። በህወሓት ውስጥ ያለፈ አመራር ሁሉ፣ ኚትግሉ መጀመሪያ አንስቶ፣ ብዙ ወንጀል ፈጜሟል፣ በመፈጾም ላይም ነው። ስለዚህ ማንም አመራር እኔ ነፃ ነኝ ዹሚል ካለ ተሳስቷል። ልክ እንደ ግደይ ዘርአጜዮን ጥፋተኛ ነኝ ብሎ ደጋግሞ እንደሚናገሚው ሌላውም ይህንን አርአያነት መኹተል አለበት።
ውድ ኢትዮጵያውያን ዚህወሓት ታሪክና እንወቀው ዚሚሉት ጜሑፎቌ በዝግጅት ላይ ናቾው። በጥቂት ወራት ውስጥ ለሕዝብ ይቀርባሉ ዹሚል ጜኑ እምነት አለኝ። ሶስተኛው ጜሑፌ ደግሞ “ተጠያዊዎቹ እነማን ናቾው” ይሚለውን በማዘጋጀት ላይ ነኝ። ኚማገብት-ተሓህት-ህወሓት ዚመጡ አመራር አንድ በአንድ ምን ሰሩ፣ በምንስ ይጠዹቃሉ ዹሚለው ሰፊና ግልጜ መጜሓፍ እዚተዘጋጀ ነው።
ማሳሰቢያ፡ በድህሚ ገጜ ዚማስተላልፋ቞ውን ጜሁፎቜ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በማተም ሰብስባቜሁ “ዚህወሓት ገበና” በማለት በማህደር አጠራቅሙት። ጥሩ ዚሰነድ ማስሚጃ ነው። ዚህወሓት አመራርና ካድሬዎቹ በሕዝብ ዚሚፈሚዱበት ቀን ደርሷል።
ገብሚመድህን አርአያ
ህወሓት በኢትዮጵያ ሕዝብ ሃይል ይደመሰሳል!!!
አውስትራሊያ
2006 ዓም ዚነጻነት ዓመት ናት!!!
መስኚሚም 6 ቀን 2006

ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በመንግስት ላይ ተቃውሞ አሰማቜ

ጥቅምት (ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው መንበሹ ፓትሪያርክ ስብሰባ አዳራሜ በመካሄድ ላይ ባለው 32ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በቀተክርስቲያኑዋ ታሪክ  ተሰምቶ ዚማያውቅ ተቃውሞ ተኚስቷል። አንድ በስብሰባው ላይ ዚተሳተፉ አባት እንደገለጹት በስብሰባው ላይ ”  á‹­áˆ… መንግስት ዚኢትዮጵያን ኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያንን ለማፍሚስ እንደተነሳ በስፋት ተነግሯል።

ዚፌደራል ጉዳዮቜ ዚሀይማኖት ክፍል ሃላፊዎቜ ዛሬ ስለ አክራሪነትና ጜንፈኝነት ገለጻ ለመስጠት በተገኙበት ወቅት ነው ተቃውሞው ዹተሰማው።
እድሉን ያገኙት 6 ሊቃነ ጳጳሳት ማለትም ዹሰሜን ወሎ አገሹ ስብኚት ሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ ቄርሊዮስ ፣ ዚምእራብ ወለጋ አገሹ ስብኚት ሊቀጳጳስ ብጹዕ ሄኖክ፣ ዹጋሞ ጎፋ አገሹ ስብኚት ሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኀሊያስ ፣ ዚወላይታ ዳውሮ ዋና ስራ አስኪያጅ፣ ዚምስራቅ ጎጃም ሊቀ ጳጳስ ብጹ አቡነ ማርቆስ ፣ ዚደቡብ ጎንደር ሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ እንድሪያስ ዚመንግስትን ፖሊሲ እአነሱ ትቜት አሰምተዋል።
በክርስቲያኖቜ ላይ እዚደሚሰ ያለው ግፍ፣ ግድያና ጫና መጚመሩን ዚተነጋሩት አባቶቜ ፣ ፓትሪያርኩም እውነት ነው ይህ ሁሉ ጫና አለብን በማለት በሊቀ ጳጳሳት ዚቀሚቡውን ሀሳብ ደግፈዋል።
ኹመላው አለም ዚተሰባሰቡ በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዚሀይማኖቱ መሪዎቜ በተገኙበት ስብሰባ ላይ ዚመንግስት ባለስልጣናት ዚኢትዮጵያን ዚሀይማኖት ታሪክ በማሳነስ ባቀሚቡበት ወቅት  ዚሀይማኖት አባቶቜ ስሜት በተቃቀለበት ሁኔታ መልስ ሰጥተዋል።
ዚህዝቡን መሬት ነጥቃቜሁ ፣ ህዝቡንም መሬቱንም ዚመንግስት ያደሚጋቜሁት እናንተ ናቜሁ፣ ኢትዮጵያዊው ሀብትና ንብሚት እንዳይኖሚው አደሚጋቜሁት እናንተ ናቜሁ፣ ኹዚህ ቀደም ኚነበሩት መንግስታት በባሰ ህዝቡን ያስጚነቀ ይህ መንግስት ነው በማለት አባቶቹ ተናግሹዋል።
“በአጌዎቜም ዘመን ቢሆን ይህቜን አገር  áˆµá‰µáˆšáŠšá‰¡ እስኚ ታሪኩዋ ነው፣ ታሪኩዋን አላጠፋቜሁም ወይ?” በማለት ብጹዕ አቡነ ቄርሎስ ሲናገሩ ኚተሰብሳቢው ኹፍተኛ ድጋፍ ተቜሮአ቞ዋል።
ዚሀይማኖት አባቶቜ ዚቀተክስርቲያኑዋን ታሪክ አዛብታቜሁዋል፣ ቀተክርስቲያኑዋንም ታሪኩዋን አጥፍታቜሁዋል በማለት ወጥሚው መያዛ቞ው ታውቋል።

Oct 16, 2013

“ዚሃሰት መንገድ ሁሌም መጥፊያ እንጂ መዳኛ ሆኖ አያውቅም!!” ኹለንደን ደብሚ ጜዮን ቅ/ማርያም ቀ/ክ ዹተሰጠ መግለጫ

london
ባለፈው ቅዳሜና እሑድ (በ12/10/2013 እና በ13/10/2013) ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብሚ ጜዮን ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያንን áŠ¥áŠ“ አካባቢውን ያናወጠ ዚአባ ግርማና ተኚታዮቻ቞ው ዚሃሰትና ዚእብሪት ሥራ ውጀት።
Read full story in PDF

Oct 14, 2013

ስንቱን አጣን! (ኚፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም)

 

Pro Mesfin
እንደኢትዮጵያ ባለ ኋላቀር አገር አገር ውስጥ መሠልጠን ብዙ ቜግር አለበት፤ እኔ ራሎ በኮምፒዩተር መጻፍ ኹጀመርሁ ሠላሳ ዓመት ሊሆነኝ ነው፤ ታዲያ መብራት ጠፋና ዚምሠራው ባጣ ዚቆዩ ወሚቀቶቜን ሳገላብጥ አንድ እአአ በዲሎምበር 26 1965 ኚዱሮ ተማሪዬ ዚተጻፈልኝን ደብዳቀ አገኘሁ፤ በዩኒቚርሲቲ ኮሌጅ በነበሹ ኚአንድ በጣም ጎበዝ ወጣት ዹተላኹልኝ ነበሹ፤ ኹተመሹቀ በኋላ በአንድ ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ ለጥቂት ዓመታት ሠርቶ ትምህርቱን ለመቀጠል ወደአሜሪካ ሄዶ በሎዝ አንጄለስ አካባቢ ኹሚገኝ ትምህርት ቀት ገብቶ ነበር፤ ደብዳቀውን ዚጻፈልኝ ኚዚያ ነው፤ ደብዳቀው ሰባት ገጟቜ አሉት፤ ኚሰባቱ ገጟቜ አምስቱ ስለኢትዮጵያ ያለውን ስጋት ዚሚገልጜ ነው፤ በሎዝ አንጀለስ አካባቢ ካሉ ኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት በሚያደርግበት ጊዜ ሁሉ ብዙዎቹ ዚሚያሳዩት ዚመንደሚኛነት ስሜት እያበሳጚው ዚተማሩት ሰዎቜ በእንደዚህ ያለ ማኅበሚሰባዊ ኋላቀርነት ውስጥ ሆነው ኢትዮጵያ ዚምትባለው አገር እንዎት መራመድ ትቜላለቜ? እያለ ይሰጋ ነበር።
ደብዳቀውን ላቋርጥና ስለሰውዚው ትንሜ ልናገር፤ ተማሪ ሆኖ ክፍል ውስጥ ምንም ነገር ዚማያሳልፍ በጣም ተኚራካሪ ተማሪ ስለነበሚ አደንቀው ነበር፤ አንድ ጊዜ እንዲያውም ዚዘውድ መንግሥት ደጋፊ ነኝ አልሁና አንዎት በትኚሻው ላይ ጭንቅላት ያለው ሰው ዓመቱን በሙሉ ዚዘውድ አገዛዝ ዚሚያደርስብንን በደልና ቜግር ሲነግሚን ቆይቶ አሁን ደግሞ ያንን ደጋፊ ነኝ ይላል ብሎ ወሹፈኝ፤ ልጁን ስለማውቀው አነጋገሩ አሳቀኝ እንጂ አላስቆጣኝም፤ ጥያቄህ ይገባኛል፤ ግን እኔን ሳትወርፈኝ መጠዹቅ ትቜል ነበር በዬ ቢቀበለውም ባይቀበለውም ለጥያቄው መልሱን ሰጠሁት፤ በኋላም ጥሩ ጓደኛዬ ነበር።
ኚአሜሪካ ትምህርቱን ጚርሶ እንደመጣ ተገናኘንና ወደቀድሞ ሥራው ወደወንጂ ተመልሶ እንደሆነ ስጠይቀው ‹‹áŠ¥áŠ•á‹Žá‰µ ብዬ! ዕድሜ ልኬን ዹፈሹንጅ አሜኚር ሆኜ መኖር አልፈልግም፤ አሁን ደግሞ ያስተማሚኝን ሕዝብ ላገልግል እንጂ!›› ነበር ያለኝ፤ በመንግሥት መሥሪያ ቀቶቜና በወንጂ ባሉት ደመወዞቜ መሀኹል ኹፍተኛ ልዩነት ነበሹ፤ ቁም-ነገሚኛነቱን፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያለውን ታማኝነት፣ ዹግል ጥቅሙን ቀንሶ ኢትዮጵያን ለመርዳት ባሳዚው ተግባራዊ አርአያነት ዹማደንቀው ዚወታደር ልጅ ነው።
ይህ ሰው በደርግ ጊዜም አልሾሾም፤ በአንድ ኢንዱስትሪ ውስጥ በሥልጣን ቊታ ላይ ነበር፤ ወያኔ/ኢሕአዎግ ወንበሩን ሲይዝ እንደዚህ ያሉ ሰዎቜ ዹማይፈለጉ መሆናቾው ሲታወቅ አገሩን ጥሎ ተሰደደ፤ በትልቅ ዓለም-አቀፍ መሥሪያ ቀት ጥሩ ሥራ አግኝቶ ዕድሜው ለጡሚታ እስቲደርስ ቆዹ፤ ወደሚወዳት አገሩ ለመመለስ አልቻለም፤ ኚአንድ ዚትምህርት ቀት ጓደኛው ጋር ግንኙነት እንዳለው አውቃለሁ፤ አንድ ቀን ስለዚሁ ዚጋራ ጓደኛቜን ስናወራ ለምን ወደኢትዮጵያ እንደማይመለስ ጠዹቅሁ።
ዹዚህ ወጣት አጎት በወታደርነት ኢትዮጵያን ለሹጅም ጊዜ በክብር ያገላገለ ነው፤ ይህ ሰው ወያኔና ሻቢያ በተጣሉ ጊዜ ዜግነታ቞ው በጉልበት እዚተገፈፈ ኚአገራ቞ው እንዲወጡ ኚተደሚጉት ሰዎቜ አንዱ ነው፤ በዚያን ጊዜ በሌላ ዚኀርትራ ተወላጅ ላይ ዹተፈጾመውን ግፍ ራሱ ሰውዬው በአሜሪካ ድምጜ ራድዮ ሲናገር ዚሰማሁት ዹሚኹተለውን ነው፤– ‹‹áˆˆáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« በአለኝ ሁሉ አገልግያለሁ፤ ኢትዮጵያን ሳገለግል አንድ እግሬን አጥቻለሁ፤ አንድ ሰው ለአገሩ ኹዚህ ዹበለጠ ምን ያደርጋል?›› ብሎ ሲናገር አስለቅሶኛል።
ዹኔ ዚቀድሞ ተማሪና ወዳጅም ለምን ወደኢትዮጵያ እንደማይመለስ ሲጠዚቅ ‹‹áˆˆáŒ‹áˆŒ (ማለት ለአጎቱ) ያልሆነቜ ኢትዮጵያ ለእኔ አንዎት ትሆነኛለቜ? በማለት በጥያቄ መለሰ አሉ፤ አባቱ ያገለገላትን፣ አጎቱ ዚለፋላትን፣ አያት ቅድመ-አያቶቜ ዚሞቱላትንና ዚደሙላትን አገር እንዲህ በቀላሉ ማጣት ነፍስን ያቆስላል፤ ዚነዚያን ሰዎቜ ሁሉ መስዋእት ያኚሜፋል፤ ያሚክሰዋል፤ ይህንን ዚተገነዘቡና ያዘኑ፣ ያለቀሱ ሰዎቜ ናቾው –
እናት ኢትዮጵያ ሞኝ ነሜ ተላላ፣
ዚሞተልሜ ቀርቶ ዚገደለሜ በላ!

Bomb blast in Ethiopian Addis ababa kills two

ADDIS ABABA (Reuters) – A bomb blast in the Ethiopian capital Addis Ababa killed two people on Sunday, state radio said.
There was no immediate claim of responsibility for the bombing, but Ethiopia says it has thwarted plots of attacks in the past two years and blames rebel groups based in the south and southeast, as well as Somalia’s al Shabaab insurgents.
“A bomb blast occurred at a residential house in the Bole district and killed two unidentified individuals,” a report on national radio said, quoting the National Security and Intelligence Service.
The explosion occurred in the city’s upscale Bole district, about 5 km (3 miles) from a soccer stadium where thousands of fans were queuing for tickets to a World Cup qualifier against Nigeria and gathering at squares in the capital to watch the match on giant screens.
The radio did not mention any suspected link to the match.
It quoted the security service as saying it was investigating the incident and gave no more details.
Ethiopian troops have been fighting al Qaeda-linked al Shabaab militants in Somalia since 2011, alongside African Union forces from Uganda and Burundi and Kenya.
However, the Horn of Africa nation has so far been spared the sorts of attacks the militants have carried out in nearby countries – such as the siege at the Nairobi mall last month and the attack on soccer fans in Uganda in 2010 – although it has been hit by sporadic explosions in recent years.
Thirteen people were wounded when an explosive device ripped through a bus near the border with Eritrea in 2010, while a bomb explosion near a court in the capital wounded two in 2011.
(Reporting by Aaron Maasho; Editing by Alison Williams)

ዚአዲስ አበባና ዚፌዎራሉ ህገ ወጥ መጅሊሶቜ ዚኢደል አድሃ (አሹፋ) በአል ዝግጅትን ሙሉ ለሙሉ ለመንግስት አስሚኚቡ

ድምፃቜን ይሰማ እንደዘገበው፦
አሹፋ በዓል 1ዚኢድ በአል አኚባበርን አስመልክቶ ዛሬ በአዲስ አበባ ደሹጃ በሁሉም ክፍለ ኚተሞቜ በተደሹገው ስብሰባ መንግስት ሙሉ ሃላፊነቱን እንደተሚኚበ ተገለፀ ፡፡ ኹነገ ወዲያ ማክሰኞ ጥቅምት 5 \2006 እንደሚኚበር ዹሚጠበቀው ዚኢደል አደሃ (አሹፋ) በዐል ላይ ዚፌዎራልም ሆነ ዚአዲስ አበባ ህገ ወጥ መጅሊስ አመራሮቜ (ሾህ ኪያርንና ዶክተር አህመድን ይጚምራል) ወደ ሃጅ በመሄዳ቞ው ዹበአል አኚባበሩን ሙሉ ሃላፊነት ለመንግስት እንደተሰጠ ዚመንግስት ሃላፊዎቹ ግልፅ አድርገዋል ፡፡
በዛሬው ስብሰባ ኚአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ፣ ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ሃላፊዎቜ ፣ ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሜን ኢንተሊጀንስ ፣ ዚፌዎራል ፖሊስ ሃላፊና ኢንተሊጀንስ ፣ ዚአዲስ አበባ መሹጃና ደህንነት ተወካዮቜ ዹተገኙ ሲሆን በአሉ መንግስት በሚፈልገው መልኩ እንዲጠናቀቅ ዚተለያዩ መመሪያዎቜን አውርደዋል ፡፡ ኚወሚዱት መመሪያዎቜ በዋነኝነት ለሁሉም ክፍለ ኚተሞቜ ወደ ስታዲዚሙ ዚሚገቡበት ዚ቎ዲዚም በር ቁጥር ስለሚሰጣ቞ው ክፍለ ኚተሞቹ ዚዚራሳ቞ውን ዚመንግስት ደጋፊ ሙስሊሞቜን(አህባሟቜን )ና ካድሬዎቜን በመያዝ አንድ ላይ ኚዚአካባቢያ቞ው እንዲነሱና እስኚ ኚጠዋቱ አንድ ሰዐት ድሚስ ዚስታዲዚሙን ዚመጀመሪያ ሶፍ እንዲይዙ ታስቧል ፡፡
ሙስሊሙ ማህበሚሰብ በእለቱ ተቃውሞ ማድሚጉ እንደማይቀር መንግስት ያመነ ሲሆን ይህን ለመኹላኹል በዹክፍለኹተማው ዹሚገኙ አህባሟቜና ዚመንግስት ደጋፊዎቜ ፣ እንዲሁም ኹሁሉም አደሚጃጀቶቜ (ኚነዋሪዎቜ ፎሹም ፣ ኚሎቶቜ ፎሹም ፣ ኚወጣቶቜ ፎሹምና መሰል አደሚጃጀቶቜ) ዚተውጣጡ ካድሬዎቜ እስኚ ጠዋቱ አንድ ሰዐት ባለው ግዜ ውስጥ ስ቎ዲዚም ቀድመው በመግባት ተቃውሞ አድራጊዎቹ ዚመጀመሪያዎቹን ሚድፎቜ እንዳይዙት መቅደም እንዳለባ቞ው ትእዛዝ አውርደዋል ፡፡
በእለቱ ዚአዲስ አበባ ኹተማ ኚንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ወይም ተወካያ቞ው ፣ ኚፌዎራል ጉዳዮቜ ሚኒስትር እንዲሁ አንድ ተወካይ በመገኘት ዚመንግስትን አቋም ዚሚያንፀባርቅ ንግግር እንዲያደርጉ እቅድ ዚተያዘ ሲሆን ተቃዋሚዎቜ ይህን ንግግር እንዳያስተጓጉሉና ሚዲያውም ዹበአሉን አኚባበር በነፃነት ማስተላለፍ እንዲቜል በስታዲዚም ውስጥ ዚተቃዋሚዎቜን ዹተቃውሞ እንቅስቃሎ ሚና መቀነስ መቻል አለብን ብለዋል ፡፡
አሹፋ በዓልኊሚን቎ሜኑን እዚሰጡ ኚነበሩት ዚመንግስት ሃላፊዎቜ መካኚል አንዱ “ እኛ ኚስታዲዚሙ ውጪ ቜግር ዚለብንም ፡፡ ውጪውን ዚሚጠብቅ ዚራሱ ባለቀት አለው ፣ መሚባሚብ ያለብን በስ቎ዲዚም ውስጥ እንዳይሚብሹን ነው ፡፡ ኚሰላት በፊት በስታዲዚሙ ውስጥ ዹሚደሹጉ ንግግሮቜና ሌሎቜ መሰል ፕሮግራሞቜ በሁኚት መቆም ዚለባ቞ውም ፡፡ ኚኢደል ፊጥር በአል ባገኘነው ተሞክሮ ተቃዋሚዎቹ ስታዲዚም ውስጥ አይገቡም ማለት አይቻልም ፡፡ እንኳን እነሱ ይቅርና ባነራ቞ውንም አስገብተዋል” ያሉት ዚመንግስት ሃላፊው “ ቁም ነገሩ ግን አሁን ዹሚፈለገው ማክሰኞ ስታዲዚም ውስጥ ገብተው ዚሚቃወሙትን ሀይሎቜ ዹኛ ካድሬዎቜ በማስደንገጥ ማስቆም መቻል አለባቜሁ ፡፡ እነሱ መጮህ ሲጀምሩ ዹኛ ደጋፊዎቜ ደግሞ ዞር ዞር እያሉ እንዲገለምጧ቞ውና አጠገባ቞ው ያሉትም ምንድን ነው ዚምትጮሀው እያሉ ማስደንበር አለባ቞ው፡፡ ስ቎ዲዚም ውስጥ ስለሆኑ ደንግጠው ያቆማሉ ፡፡ በዛ ላይ ለኢደል ፊጥር ዚደሚሰባ቞ውን ስለሚያውቁ ይፈሯ቞ዋል፣ ስለዚህ ይህን መመሪያ በጥንቃቄ እንዲተገበር ወደ ታቜ እንድታወርዱ ” ብለዋ቞ዋል ፡፡
ሌላኛው ዚመንግስት ሃላፊ በበኩላ቞ው “ ኚስግደት በኋላም ቢሆን ተቃዋሚዎቹ ሲሚብሹ ዹኛ ሰዎቜ በመጡበት አኳኋን ወደ እስታዲዚሙ በገቡበት በሮቜ ግር ብለው መውጣት ነው ያለባ቞ው ፡፡ ምክንያቱም ተቃውሞ አድራጊዎቹ ኚስግደት በኋላም እንደተለመደው ሚብሻ቞ውን ሲጀምሩ ዹኛ ደጋፊዎ ድንገት ግር ብለው እዚደሚመሷ቞ው ሲወጡ ብ቞ኝነት ተሰምቷ቞ው ተቃውሟቾውን ያቆማሉ ፡፡ ኚወጣቜሁም በኋላ ዚትም ቊታ አትቁሙ ፡፡ ቀጥ ብላቜሁ ወደቀታቜሁ ነው መሄድ ያለባቜሁ ፡፡ ፖሊስም ሆነ ደህንነት ዚሚሚዳው ወደ ኋላ ዹሚቀር ሁሉ ሚብሻ ፈላጊ ነው ብሎ ነው ፡፡ ይህ ኮዳቜን ነው ፡፡ ኚሰላት በኋላ ዹኛ መጅሊስ ሰዎቜና ካድሬዎቜ ምንም ሳይቆሙ ወደ ቀታ቞ው ነው መንገድ መጀመር ያለባ቞ው ፡፡ ወደ ኋላ ዹሚቀሹው ግን ተቃዋሚዎቜ ናቾው ብለን ነው ዹምናምነው ” ብለዋል ፡፡
በዚህ መሰሚት እያንዳንዱ ዹኹፍለ ኹተማ መጅሊስ ሰብሳቢዎቜ ኚኢማሙ ቀጥሎ ባለው ዚመጀመሪያው ሶፍ ላይ እንዲሆኑ ፣ እያንዳንዱ ዹክፍለ ኹተማ መጅሊስ ምክትል ሰብሳቢዎቜ በሁለተኛው ሶፍ እንዲሆኑ ፣ እያንዳንዱ ዹክፍለ ኹተማ መጅሊስ ፀሃፊዎቜና ቀሪዎቹ አራቱ አመራሮቜ ደግሞ ኹበር እስኚ መድሚክ በመያዝ እንግዳ እንዲቀበሉ ፣ እንዲኚታተሉና እንዲያስተናግዱ እቅድ ወጥቷል ፡፡ ዚአህባሜ ሱፊ ማህበር አባላት ደግሞ ኹነዚህ ኋላ ያለውን ሶፍ እንዲይዙ ማብራሪያ ተሰጥቷል ፡፡ ኹነዚህ በተጚማሪም እያንዳንዱ ዹክፍለ ኹተማ አመራሮቜ ፣ ኚተለያዩ ዘርፎቜ ዚተዋቀሩ ዹክፍለ ኹተማና ዚወሚዳ አመራሮቜ ደግሞ ክፈለ ኹተማቾው እንዲገቡ በተነገራ቞ው ዚስታዲዚም በር ቁጥር በመጠቀም ቊታ቞ውን መያዝ እንዳለባ቞ው መመሪያ ወርዷል ፡፡
ልደታና አዲስ ኹተማ ክፍለ ኚተሞቜ ለስ቎ዲዚሙ ቅርብ እንደሆኑ ስለሚታሰብ በጠዋት ተነስተው ወደ እስታዲዚም በእግራ቞ው እንዲሄዱ ዚተነገራ቞ው ሲሆን ሌሎቹ ግን መኪና እንደሚታዘዝላ቞ው ታውቋል ፡፡
ተልእኮ
1) ማንኛውም አይነት እንቅስቃሎ በተቃዋሚዎቹ ሲደሚግ ባሉበት ቊታ ሆነው በአንድ ድምፅ “ዝም በሉ አትጩሁብን ” በማለት ለማስቆም መሞኹር
2) ኹተሰገደ በኋላም ሁሉም አባላት መንገዱን ቶሎ በማስኚፈት ግር ብሎ በሁሉም ዚስ቎ዲዚሙ በሮቜ በመውጣት ተቃዋሚዎቹን በማስደንገጥ መበተን ፡፡ ሙሰሊሞቹ ተቃውሞ በሚያደርጉበት ወቅት ሁሉም አባል በአንድ ላይ በሁሉም በር ግር ብሎ ሲወጣ ህዝበ ሙስሊሙን ዹመበተን እድል ይኖራል ዹሚል መላምት ቀርቧል ፡፡
ሆኖም በስብሰባው ዚነበሩ አመራሮቜ “ ዹኛ ዚመጅሊስም ሆኑ ሌሎቜ አባላቶቜ ይህን መመሪያ በተቀላጠፈ ሁኔታ ይተገብሩለናል ወይ ብዙዎቹ ይፈራሉ ወይም በሰዐቱ ላይገኙ ይቜላሉ “ ዹሚል ቅሬታ ቢያቀርቡም ይህን ተኚታትላቜሁ ማስፈፀም ዹናንተ ግዎታ ነው ዹሚል ምላሜ ተሰጥቷ቞ዋል ፡፡
በመጚሚሻም ዚመጅሊሱ ሁሉም አመራሮቜ ወደ ሃጅ ስለሄዱ መድሚኩ በመንግስት ሰዎቜ ብቻ እንዳይያዝ ኚሰላት በፊት ህዝቡን ተክቢራ ዚሚያስብሉና መጅሊሱን ወክለው ንግግር እንዲያደርጉ ኹክፍለ ኚተሞቜ ዚመጅሊስ አመራሮቜና ለመንግስት ቅርብ ዹሆኑ ኢማሞቜ እንዲመለምሉ ክፍለ ኚተሞቜ ሃላፊነት ተሰጥቷ቞ዋል ፡፡ ዚኢድ ስግደት ዹሚኹናወነውም ኚጠዋቱ 2 ሰዐት ላይ እንደሚሆን ወስነው ስብሰባ቞ውን አጠናቀዋል ፡፡
በነገው እለትም ለዹክፍለ ኹተማ ህገ ወጥ መጅሊስ ሰባት አመራሮቜ ኊሚን቎ሜን እንደሚሰጥም ታውቋል ፡፡
አላህ ኚተንኮለኞቜ ሎራ ይጠብቀን
ድል ለኢትዬጲያ ሙስሊሞቜ!!!
አላሁ አክበር!!

ይሄ እዚታዚ እንዎት ያ መንገድ ይታሰባል?

ይሄ እዚታዚ እንዎት ያ መንገድ ይታሰባል? ለኔ ዚአመቱ ምርጥ እዉነተኛ አስተማሪ ፊልም ነዉ!!!! እስኚመቌ ድሚስ ስደት? ባገራቜን መኖር ካልቻልን ለምንስ ነው ዚማንታገለው?  ለኔ እዚህ ፊልም ውስጥ  ያሉት በሙሉ በጣም ዚማኚብራቹ ትልቅ ማስተማሪያ ዚያዛቜሁ ወንድሞቌ ናቜሁ!!! ***ክብር አለኝ ለእናንተ ሁሌም*** ለሞቱት ወንድሞቻቜንም አምላክ ነፍሳቹውን በገነት ያኑር !!!  R , I , P,

ስብሃት ነጋን አጅበው አክቲቪስት መስፍን ላይ ድብደባ ዚፈጞሙት ግለሰቊቜ ማንነት ታወቀ

(ዘ-ሐበሻ) በትናንትናው ዕለት ዘ-ሐበሻ በሰበር ዜና ባቀሚበ቞ው ቪድዮ ላይ አክቲቪስት መስፍንን በቡጢ ዚተማቱትና ዹቆሙ መኪናዎቜን ገጭተው ያመለጡት ግለሰቊቜ ማንነትን ጋዜጠኛ ኢዚሩሳሌም አሚአያ ማወቁን ለዘ-ሐበሻ በላኹው መሹጃ አስታወቀ፡፡
ዚሕወሓት መንደርን ኚቃሚምኩት በሚል በኢትኊጵ ጋዜጣ ላይ ዚሕወሓት ምስጢሮቜን በሚያጋልጠው ጜሁፎቹ ታዋቂነትን ያተሚፈው ጋዜጠኛ አሚአያ ተስፋማርያም (ኢዚሩሳሌም አሚአያ) በትናንትናው እለት በአክቲቪስቱ ላይ ድብደባ ዚፈጞሙትን በሕግ ዚሚጠዚቁት ግለሰቊቜ ሶስቱም ዚሕወሓት አባላት መሆናቾውን ጠቅሶ ማንነታ቞ውን ዘርዝሯል።
1ኛው. ዚሟቹ ዚደህንነት ሹም ክንፈ ገ/መድህን ወንድም ታምራት ገ/መድህን፣
2ኛው. ዚወያኔ ኪነት አባልና ጊታሪስት ወዲ ሰቩቃ (በአሜሪካ ፖለቲካ ጥገኝነት ዹጠዹቀ)፣
ስብሃት ነጋ
ስብሃት ነጋ
3ኛው ሃይሌ በአሜሪካ – ዚኢትዮጲያ ኀምባሲ ዚብርሃነ ገ/ክርስቶስ ሹፌር ዹነበሹና በአሁኑ ወቅት በቪዛ ክፍል ዚሚሰራ ናቾው።

አክቲቪስት መስፍን ለደሚሰበት ድብደባ ሕክምና ዚተኚታተለ ሲሆን ጉዳዩን በሕግ እንደሚጠይቅ አስታውቋል። በሌላ በኩል ዚኢሳት ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን አንድ ዚቚርጂኒያ ጠበቃ አነጋግሮ ባቀሚበው ዘገባው ስብሃት ነጋን ጚምሮ እነዚህ ግለሰቊቜ ሰውን በመደብደብና ዹሰው መኪና ገጭቶ በማምለጥ ወንጀሎቜ ኚተኚሰሱና ፍርድቀትም ጥፋተኛ ካላ቞ው በ እያንዳዱ ክስ እስኚ አንድ አመት ዚሚያስቀጣ ቅጣት ሊጣልባ቞ው ይቜላል። ስብሃት ነጋም ዹወንጀል ተባባሪ፣ እንዲሁም ዹሰው መኪና ገጭቶ ባመለጠ መኪና ውስጥ በመሄዳ቞ውና ወንጀልን በመተባበር ክስ በአሜሪካ ህግ በወንጀል ተባባሪነት ሊኚሰሱ ዚሚቜሉበት ህግ አለ።

Oct 13, 2013

በ1ኪሎ ቁርጥ ሥጋ እና በ12 ድራፍት ብርጭቆ – እውነትና ኚሕደት………(ኹ ይድነቃ቞ው ኹበደ)

ooohhhh
(ዚሰማያዊ ፓርቲ ዹህግ ጉዳይ ሀላፊ)
ኪነ-ጥበብ ምኞታቜን፣ደስታቜን፣አዘናቜንን እና ክፋታቜን ዚምናይበት እና ዚምናዳምጥበት ዚህይወታቜን ነፀብራቅ ነው፡፡ ኪነ-ጥበብ ህይወትን ቀለል አድርጎ ኚማዝናናት ባለፈ በገለሰብ አስተሳሰብ ላይ ዚራሱ ዹሆነ በጎ ወይም በጎ ያልወነ አስታውጟ ዚሚያበሚኚት ጥበባዊ ሃይል ነው፡፡ይህ ሃይል በመልካም አስተሳሰብ ላይ ተመስርቶ ወደ ህብሚተሰቡ ውስጥ ሲገባ ዹሚኖሹው አገራዊ ፋይዳ እጅግ በጣም ዹበዛ ነው፤፤ በመሆኑም ኪነ-ጥበብ እንዲህ አይነቱ ጠቀሜታ እንዲኖሚው ዚሚያደርጉት በጥበብ ሙያ ውስጥ ዹሚገኙ ባለሙያዎቜ ናቾው ፤እነኚህ ባለሙያዎቜ ሙያ቞ው ኚመሬት ዹፈለቀ ሣይሆኖ በልምድና በት/ት ዚዳበሚ ጥበባዊ ተስጥኊ ነው፡፡
ኚኪነ-ጥበብ ዘርፎቜ ውስጥ ኚሚመደቡት አንዱ ቎አትር ነው፤ ቎አትር በአገራቜን ያለው ተቀባይነት ቀላል ዚሚባል አይደለም ፤቎አትር አሁን ያለበት ደሹጃ ለመድሚስ ዚ቎አትር ባለሙያዎቜ ዚኚፈሉት ዋጋ ኚዕድሜቻው፣ ኚገንዘባ቞ው እና ኚዕለት ተዕለት ማህበራዊ ህይወታ቞ው ላይ ጎምዶ ያስቀሚባ቞ውን ዚሚያውቁት ዋጋውን ዚኚፈሉት እነሱ ብቻ ናቾው፡፡ ቢሆንም በ቎አያትር ጥበብ ዚዝወትር እንቅስቃሎቜን መጥፎዉንና ዹተሾለውን በመለዚት ጥበባዊ በሆነ መንገድ እዚተዝናናን እንድንማርበት ለሚያደርጉ ዚ቎አትር ባለሙያዎቜ ስራዎቻ቞ውን ስንመለኚትና ስናደምጥ እውነትም ለሙያው እድገት ዹተኹፈለ ነገር እንዳለ ያስገነዝበናል፡፡
ስለሆነም ለ቎አትር ባለሙያዎቻቜን ኚትላንት ዛሬ ዚምንሰጣ቞ው ኚበሬታና አድናቆት ዚሚበሚታታና ዚሚያስደነቅ ነው፤ይህ ደግሞ ለ቎አትሩም እድገት ዹሚጠቅም ነው፡፡ይሁን እንጂ በቀርብ በብሔራዊ ቎አትር ቀደምት ባለሙያዎቜ ላበሚኚቱት አስታዋጜኊ በማስታወስ ዚሜልማት ፕሮግራም ዹተዘጋጀ ቢሆንም ዝግጅቱ እውነትና ኚሕደት ዚተቀላቀለበት ነበር፡፡
‹‹……. ቀደምት ባለሙያዎቜ እንዲገናኙና ባለፈው ላደሚጉትም አስታውጜኊ ሜልማት መሰጠቱ ተገቢነት ያለው ድርጊት ነው፡፡ባለሙያዎቹ ሲገናኙና በመነፋፈቅ ፈቅራዊ ሰላምታ቞ውን ሲለዋወጡ ስመለኚት እጅጉን ደስ ብሎኝ ነበር ዚምኚታተለው፡፡ እዚቆዚሁ ሲሄድ በውስጀ ቅሬታ ተሰማኝ በብሔራዊ ቎አትር በተኹናወነው ስርአት ላይ በሞት ዚተለዩትን ተነሱ፤ በነፍስ ያሉት ግን ተገኝተው ዹሚመሰገነው ተመሰገነ፤ ዹሚሾለመው ተሾለመ እዚህ ላይ ነው ቅድም ዹጀመሹኝ ቅርታዬ ዚበሚታብኝ፡፡………. ››
በማለት በብሔራዊ ቎አትር ቀት ዚተካሄደውን ሜልማት ስነስርአት በኢቲቪ ፕሮግራሙን ሲኚታተል ዹነበሹ ሰው ትዝብቱን እና ቁጭቱን በሎሜ መፅሔት በባለፈው ሳምንት ዕትም ላይ ያስነበበን፡፡
እኔም ዚሰውዬውን ትዝበት እና ቁጭት አብዝቌ ዚምጋራው ነው፤ አርቲስት ደበበ እሞቱ በሙያው ኚበሬታን ያተሚፈ ለብሔራዊ ቎አትር ቀት እድገት ዚተቻለውን አስታውጟኊ ያበሚኚተ እና በህይወተ ኚቀሩልን አንጋፋ አርቲስቶቜ መካኚል አንዱ ስለመሆኑ ማንኛውም ሰው ዹሚሰጠው ምስክር ነው፡፡እውቁ አርቲስት ደበበ እሞቱ ተዋናይ፣ኮሜዲያን፣ አዘጋጅ ሆነ ለሚዥም ዓመታት አገልግሏል፡፡ በመድሚክ ፣ በሬዲዩ፣ በ቎ሌቪዥን፣ በፊልም ስራ እና በጋዜጠኝነት ሙያ ሠርቷል፡፡ ቀተ መንግስት ተገኝቶ አፄ ኃይለሥላሎን ኚሥልጣን ሲወርዱ ያነጋገራ቞ው ጋዜጠኛ ደበበ እሞቱ ነው፡፡ ዚተለያዩ ሃላፊነቶቜን ይዞ ሠርቷል ፤ በአፍሪካ ዚመድሚክ ሙያተኞቜ ማህበር በሊቀመንበርነት መርቷል እንዲሁም በአትላንታ አንድ ቀን በስሙ ተሰይሞለታል፡፡ ዚአርቲስት ደበበ እሞቱ ዚጥበብ እሚዥሙ ዚህይወት ጉዞ በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ኪነጥበባት ወ ቎አትር ተጀምሩ በብሔራዊ ቎አትር ዹቀጠለ ሲሆን በአገር ፍቅር ቎አትር ቀት ያበቃ ነው፡፡
ስለ አርቲስቱ ካነበብኩት እና ኹማቀው ይህን ብልም ኚእኔ እውቀት ማነስ ያስቀሚውበት መልካም ዹሆኑ ስራዎቹ እንደሚኖሩት ተስፋ አደርጋለው፡፡ በመሆኑም በብሔራዊ ቎አትር ቀት በተካሄደው ዚማስታወስ እና ዚሜልማት ስነስርአት ላይ አርቲስት ደበበ እሞቱን ለማስታወስም ሆነ ለመሾለም አለመቻሉ ኹምን እንደመነጚ አንድ ለበዓሉ ዝግጅት ቅርብ ዹሆነ ለሆዱ ያደራ አርቲስት በ1ኪሎ ቁርጥ ሥጋ እና በ12 ድራፍት ብርጭቆ በፈጀ ወጪ እውነትና ክሕደትን ዘርዝሩ ዹተናገሹው፡፡ ይህን ሰው ሆድ አደር ያልኩበት ምክንያት ዚሚያውቀውን እውነት በፍራቻ ምክንያት በአደባባይ አለመግለፁ እንዲሁም ዚዝግጅቱ አስተባባሪ ኚሆኑት ውስጥ አንዱ እንደመሆኑ መጠን ዚራሱን እምነት ወይም አቋም በዝግጅቱ ሂደት ላይ ምንም ሳይገልፅ ሌሎቜን ለመኮነን ዚሄደበት መንገድ ነው፡፡
ይህ ለበዓሉ ዝግጅት ቅርብ ዹሆነው አርቲስት ዚቀሚበለትን ምግብ እና መጠጥ እዚጠጣ አርቲስት ደበበ እሞቱ በሙያው አንቱታን ያተሚፈ ለ቎አትር ሙያ እድገት አስታውጟኊ ያበሚኚተ መሆኑ እና በቀድሞ ዚሙያ አጋሮቹ ፍቅርና ኚበሬታ ያለው መሆኑን ምግብና መጠጥ ለጋበዘው ሰው ገልጟአል፡፡ ንግግሩን ሲቀጥል ‹‹ ደቢሟ ዹተቃዋሚ ፓርቲ አባል ስለሆነ በፕሮግራሙ ላይ እንዲሳተፍ አልተፈለገም ፤ በሱ ጉዳይ ላይ ስንቱ አፈ ልጉም ሁሉ ልወደድ በሚል አፉን ፈታ መሰለህ፡፡ ዹሚገርመው ግን ደቢሟ ወደ ቎አትር ቀት አንድ ሁለት ጊዜ መጥቶ በነበሹ ጊዜ ሁሉም እንዎት እዚተንደሚደሩና እላዩ ላይ እዚተጠመጠሙ እንደሚስሙት አይ ነበር እነዚያው ሰዎቜ አሁንም እንዳይጠራ ብለው ሲሞግቱ በጣም ነው ዚተገሚምኩት ፡፡ ዋናው ደግሞ ስራ አስኪያጁ እንዎት እንደተቃወመና በጭራሜ ሊጠራ አይገባም ፤ እሱ ዚሚጠራ ኹሆነ እኔ በበዓሉ አልገኝም ስራዬንም እለቃለው አለ ! በቃ ያንን ስንሰማ ሁላቜንም ፈራን……….. ስማ እንግዲህ ይህ በእኔና ባንተ ዹሚቀር ዹግል ጚዋታ ነው፤ ዹኔን ስም በጜሁፍም ሆነ በግልም ለደቢሟም ቢሆን እንዳታነሳ፤ አደራህን ነገ ዹሚሆነውን ማን ያውቃል ? ›› በማለት ዚነገሩን ሂደት ሰፋ አድርጎ ዹገለፀው፡፡
ውድ አንባቢያን 1ኪሎ ቁርጥ ሥጋ እና 12 ድራፍት ብርጭቆ ዹፈጀ ወጪ በመሾፈን በብሔራዊ ቎አትር ቀት ዚተካሄደውን ዚሙያ ክሕደት እውነቱ እንዲወጣ ያደሚገው አርቲስት እና ምግብና መጠጥ አሞንፎት እውነቱን ዹተናገሹው ሌላኛው አርቲስቲ ሙሉውን ታሪክ መስኚሚም 18 ቀን 2006 ዓ.ም በወጣው ሎሚ መፅሔት ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡
ወደ መነሻዬ ልመለስ እና አርቲስት ደበበ እሞቱ እድሜ ልኩን በሙያው ያገለገለ እውቅ አርቲስት ነው ፡፡ በዚያው መጠን አሁን ባለው በገዢው ስርዓት ለታዚው ብልሹ አስተዳደር ግንባር ቀደም በመሆን ሲተቜ እና ሲታገል ነበር በዚህም ምክንያት ለተደጋጋሚ እስር እና ለተደጋጋሚ ይቅርታ ጥያቄ ተዳርጓል፡፡ ይህ ግለሰባዊ ዚፖለቲካ አስተሳሰብ በኪነ-ጥበብ ውስጥ ላበሹኹተው በጎ አስታውጟ በዚትኛውም በኩል መመዘኛ ሊሆን አይገባም !!! እርግጥ ነው ገዢው መንግስታቜን ለልማታዊ አርቲስቶቜ ያለው ድጋፍ ቀላል ዚሚባል አይደለም ፤ ልማታዊ አርቲስቶቜም ለኢህአዎግ መንግስት ያላ቞ው ድጋፍ ወደር አይገኝለትም፡፡
አርቲስቶቻቜን ሰው እንደመሆና቞ው መጠን ዚራሳ቞ው ዹሆነ ዚሃሳብ ነፃነት ያላ቞ው ሲሆን በዚህ መብታ቞ው በመጠቀም ዚሚፈልጉትን ዚፖለቲካ አስተሳሰብ ዹመደገፍ ሳይመስላ቞ው ሲቀር ዚመተ቞ትና ዹመቃወም መብታ቞ው ዹተጠበቀ ነው፡፡ ነገር ግን ይህን ተፈጥራዊ ዚሃሳብ ነፃነት መብት በሃይል ወይም በጥቀማጥቅም በመደለል እና በማስገደድ ዚአንድ ዚፖለቲካ ስርአት ብቻ ደጋፊና አቀንቃኝ ማድሚግ ዚሞራል ጥያቄ ያስነሳል፡፡
በመሆኑም እንዲህ አይነቱ አካሄድ ለአርቲስቱም ሆነ ለሙያው እድገት ጉዳት እንጂ ጠቀሜታ ዹለውም፡፡ በአገራቜን ዚፖለቲካው ስርአት ሲለወጥ ዹአገር መኚላኪያ ሠራዊት ( ጊሩ) እዚተለወጠ በአዲስ መልክ እዚተቋቋመ ተቾግሹናል ፡፡ አሁን ደግም ዚመኚላኪያ ሠራዊት ( ጊሩ) ብቻ ሳይሆን አርቲስቶቻቜንም ኚፖለቲካ ስርአታቜን ጋር እዚተቀዚሩ በአዲስ መልክ ልናያ቞ው ይሆን ? ፡፡ እንዲህ አይነቱ አደገኛ ኚስሚት ውስጥ ኚመግባታቜን በፊት ዚነገሩን አካሄድ ሊመሹመር ይገባል ፡፡
በመሆኑም በአርቲስት ደበበ እሞቱ ላይ ዹተፈጾመው ዚሙያ ኚሕደት እጅግ በጣም ዚሚያሳዝን እንዲሁም ዚሚያሳፍር ነው፡፡ ኹምንም በላይ ደግሞ አገርን አስተዳድራለው ኹሚል መንግስት እንደሰፈር ጉልበተኛ ጎሚምሳ እልህ በመጋባት በአርቲስቱ ላይ ዚሙያ ኚሕደት እንዲፈፀም ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆነ አስታውጟኊ በመንግስት ካድሬዎቜ በመፈጾሙ ሌላኛው አሳፋሪ እንዲሁም አስቂኝ ነገር ነው፡፡
ስለዚህም ለእውነት ያደሩ ሙያተኞቜ እንዲህ አይነቱን አሳፋሪ ተግብር ለህዝብ ኚማጋለጥ ባለፍ ለሙያ቞ው እና ለእራሰ቞ው እድገት ዹሚበጀውን ቀና መንገድ ለማምጣት ውጫዊ እና ውስጣዊ ሙያዊ ትግል ሊያካሂዱ ይገባል፡፡ በተጚማሪ በቀብር ስነስርአት ላይ ጥቁር ለብሶ እና በእመም ጊዜ ለመታኚሚያ ገንዘብ ለመሰብሰብ ኚመታዚት በለፈ በሙያ቞ው እውቅ ዚወኑትን አርቲስቶቜ በህይወት እያሉ በማሰብ እና በማበሚታታት ሙያዊ አጋርነታ቞ውን ለእውነት ዹቆሙ አርቲስቶቜ ሊያሳዩን ይገባል፡፡

እስክንድር ነጋ በአራት ጎብኚዎቜ ብቻ እንዲጎበኝ ተደሹገ

ታዋቂው ዚፖለቲካ ተንታኝና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በሚገኝበት ዚቃሊቲ ማሚሚያ ቀት አስተዳደር በተላለፈ ትዕዛዝ መሰሚት ዚጎብኚዎቹ ቅጥር መወሰኑን ዚማሚሚያ ቀቱ ምንጮቜ ለፍኖተ ነጻነት ገለጹ፡፡
ዚመስኚሚም 19/2006 ሰላማዊ ሰልፍ ብስጭት ኚፈጠሚባ቞ው አካላት መካኚል አንዱ ዹሆነው ዚቃሊቲ ማሚሚያ ቀት ብስጭቱን አደባባይ ያወጡበትን እርምጃዎቜ መውሰድ መጀመሩ እያነጋገሚ ነው፡፡ለአንዷለም አራጌ ዚጎብኚዎቹን ስም እንዲሰጥ ካልሆነ ግን በማንም እንደማይጎበኝ ዹነገሹው አስተዳደሩ ዚእስክንድርን ጠያቂዎቜ ቁጥር በአራት መወሰኑ ታውቋል፡፡
ህገ መንግስቱ በግልጜ እስሚኞቜ በወዳጅ ዘመዶቻ቞ውና ሊጠይቋቾው በሚፈልጓቾው ሰዎቜ መጎብኘት እንደሚገባ቞ው ቢደነግግም ዚቃሊቲው መንግስት ግን ህገ መንግስታዊውን ድንጋጌ በመጣስ በማን አለብኝነት ዚእስክንድር ጠያቂዎቜን በዝቅተኛ ቁጥር ገድቧል፡፡
ዚማሚሚያ ቀቱ ምንጮቜ እስሚኞቜ ጥፋት ሲፈጜሙ እንዲህ አይነት ህግ ለተወሰነ ግዜ እንደሚወጣባ቞ው በማስታወስ በእነ እስክንድር ላይ ዹተላለፈው ውሳኔ ግን ‹‹áŒ¥á‹á‰µ መፈጾማቾው ሳይነገራ቞ው ፣ፈጞሙት ለተባለው ጥፋትም ቀርበው መኚራኚሪያ ሳያቀርቡ መሆኑ ውሳኔውን ፖለቲካዊ ያደርገዋል››á‰¥áˆˆá‹‹áˆ፡፡
ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ በተመሳሳይ መልኩ ኚጥቂት ሰዎቜ ውጪ እንደማትጎበኝ እርሷን ለመጠዹቅ ዚሚፈቀድላ቞ው ሰዎቜም ለአስር ደቂቃ ብቻ እንደሚያገኟት ኹዚህ ቀደም መዘገቡ አይዘነጋም፡፡

ዚመንግሥት አመራር በኢትዮጵያ ውስጥ ዹለም::ሃገሪቱ ካለፈው ዚባሰ አደጋ ተጋርጊባታል:: MUST READ !!!

"አገሪቱ በልማት ጎዳና ላይ እዚነጎደቜ ...." ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ በትእዛዝ ዚካዱት
"ዚመንግሥት አመራር በኢትዮጵያ ውስጥ ዹለም::ሃገሪቱ ካለፈው ዚባሰ አደጋ ተጋርጊባታል::" ሪፖርተር ርእስ አንቀጜ 
ዹጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ዚሕወሓት ሪፖርተር መግለጫ ግጭት #1 ምንሊክ ሳልሳዊ

ኖሚናል ዚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዚተባሉት እና በህገመንግስት ዚተሰጣ቞ውን ስልጣን በትእዛዝ ብቻ ዚሚሰሩበት ምንም አይነት አገራዊ ፋይዳ ዚማያደርጉት ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ ዚሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እና ዚሕወሓት ታማኝ ዹሆነው ሪፖርተር ጋዜጣ ያሰፈሚው ርእስ አንቀጜ ዚሃገሪቷ ላይ ዹሰፈነው አብዮታዊ ዲሞክራሲ አምባገነንነት እያደሚሰ ያለውን ቜግር እና መጪውን አደጋ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል::

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሃገሪቱ ምንም አይነት ቜግር እንዳሌለ እና ሁሉም ነገር በመንግስት ቁጥጥር ስር እንዳለ በዲሞክራሲ እና በልማት እዚነጎድን ህዝባዊ ድሎቜን እዚተጎናጞፍን ..ምናምን...ዹሚሉ እና ሃሰትን ዹተሞሉ ዚማደናገሪያ እና ዚማስፈራሪያ ቃላት ፍርሃት በሚነበብበት ፊታ቞ው እያስገመገሙ ደስኩሚዋል:: ዚእርሳ቞ው ንግግር እንደተጠበቀ ዚሕወሓት ሪፖርተር ጋዜጣ ደሞ እንዲህ ብሎናል::ዚኢሕኣዎግ ባለስልጣናት ፕሮፓጋንዳ እና ዹሚኹተለውን ዚሪፖርተር ወቀሳ ይመዝኑት::ሪፖርተር እንደውስጥ አዋቂነቱ ያዚውን እና ዚታዘበውን ሃይለማርያም ደሳለኝ ግን በትእዛዝ ዚካዱት እኛ ደሞ ያነበብነውን ዹተኹፋፈልነው ዚታዘብነውን እንደራሳቜን እይታ እንደሚኚተው በዝርዝር ለማዚት እንፈቅዳለን::

ሰብሰብ፣ ጠንኹርና ነቃ ያለ ዚመንግሥት አመራር በኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሌለ እና እንደሚያስፈልግ በግልጜ አስቀምቷል:: ዚቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በሞት ሲለዩና አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሰዚሙ ምንም ቜግርና ብጥብጥ እንዳልነበር ይህ ማለት መሪ አልተተካም ሳይሆን ሰብሰብ፣ ጠንኹርና ነቃ ያለ መንግሥትና አመራር ስላሌለ አገራቜን ያያስፈልጋል እያልን ዓለም ዚኢኮኖሚ ቀውስ እኛንም እዚጐዳን ነው፡፡ ትላልቅና በርካታ ፕሮጀክቶቜ ተግባራዊ ሲደሚጉ በደመነፍስ ባጀት ተመድቊ ኹፍተኛ ፋይናንስ ሳይኖር ወደ ላማት ይገባል ፡፡ ኹዚህ በፊት ያልነበሚ ዚሃይማኖት ግጭትና ልዩነት እዚታዚ ነው፡፡ ቜግሩ ካልተፈታ አስጊ ነው፡፡ ዚኢትዮጵያን ዕድገት ዚማይሹና ዹማይመኙ ጠላቶቜ በእጅጉ እዚተፈታተኑን ናቾው፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ጠንካራ መንግሥትና ጠንካራ አመራር ዚግድ ይላል፡፡በኢትዮጵያ ውስጥ ተንካራ መንግስት እና አመራር እንደሌለ በግልጜ ሪፖርተር አስቀምጧል::

ገዥው ፓርቲ እርስ በኀርሱ እዚተዋኚበ እና እዚተፈሚካኚሰ በውስጡ መተማመት እንደጠፋ በገሃድ መካሪ መስሎ ዹመሰኹሹው ሪፖርተር ኢሕኣዎግ ውስጣዊ አንድነቱን ማጠናኹር አለበት፡ሲል በአደሚጃጀቱ ምክንያት አራት አባል ድርጅቶቜ ቢኖሩትም ሲሠራና ሲንቀሳቀስ እንደ አንድ መሆን አለበት፡፡ኢሓዎግ አራት ድርጅቶቜን አክፎ በተለያዩ አሰራሮቜ በመጠመድ እርስ በራሱ እዚተዋጋ እና እዚተሞበር መሆኑን ሪፖርተር ፍንትው አድርጎ አሳይቶናል::ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን ዚጠላት ወሬ ሲሉ ክደዋል::በኢሕኣዎግ ድርጅቶቜ መካኚልመራራቅ እና መፈሚካኚስ እዚታዚ ነው ዹሚለው ይሄው ዘገባ እንኳን እዚተራራቁ አንድ ተሁኖም ለመፍታት ዚሚያስ቞ግሩና ዚሚፈታተኑ ቜግሮቜ እያጋጠሙ ናቾው፡፡ሲል ጠላቶቜና አንዳንድ ተቃዋሚዎቜ እንደሚሉት ተጣሉና ተሰነጣጠቁ እንደሚባለው ሳይሆን ካለው ተጚባጭ ሁኔታ አኳያ ተገቢና ዹሚጠበቅ አንድነት፣ መቀራሚብ፣ ዹዓላማ ፅናትና ለመስዋዕትነት ዝግጁነት እዚታዚ አይደለም፡፡በማለት መክሯል ሆኖም ያለው ገዢ ፓርቲ እዚሞተ እዚተበታተነ እና እዚተልፈሰፈሰ መሆኑን ሰብሰብ ነቃ እና ጠንኹር በሚሉ ቃላቶቜ ተክቶ አቅርቊታል::


ዹጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ዚሕወሓት ጋዜጣ ሪፖርተር ግጭት === #2 ምንሊክ ሳልሳዊ
 
-ገዢ ፓርቲ እዚሞተ እዚተበታተነ እና እዚተልፈሰፈሰ መሆኑን ዚሚያሳብቁ ተተኪ ቃላቶቜ ሰብሰብ ነቃ እና ጠንኹር
-ሙሰኞቜን ማደን - ‘እንትና ይደናገጣል እኚሌ ያኮርፋል’ ተብሎ ዹሚቆምና ዹሚቀዘቅዝ ትግል
-ዚትም ሥፍራ፣ ዚትም መሥሪያ ቀት በማንኛውም ጊዜ መልካም አስተዳደር እዚተጣሰ፣ ፍትሕ እዚጠፋ፣ ዚሕዝብ ጩኞትና ጥሪ ተቀባይ አልባ ሆኗል፡፡

ገዥው ፓርቲ እርስ በእርሱ እዚተዋኚበ እና እዚተፈሚካኚሰ በውስጡ መተማመት እንደጠፋ በገሃድ መካሪ መስሎ ዹመሰኹሹው ሪፖርተር ኢሕኣዎግ ውስጣዊ አንድነቱን ማጠናኹር አለበት፡ሲል በአደሚጃጀቱ ምክንያት አራት አባል ድርጅቶቜ ቢኖሩትም ሲሠራና ሲንቀሳቀስ እንደ አንድ መሆን አለበት፡፡ኢሕኣዎግ አራት ድርጅቶቜን አቅፎ በተለያዩ አሰራሮቜ በመጠመድ እርስ በራሱ እዚተዋጋ እና እዚተሞበር መሆኑን ሪፖርተር ፍንትው አድርጎ አሳይቶናል::

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን ዚጠላት ወሬ ሲሉ ክደዋል::በኢሕኣዎግ ድርጅቶቜ መካኚል መራራቅ እና መፈሚካኚስ እዚታዚ ነው ዹሚለው ይሄው ዘገባ እንኳን እዚተራራቁ አንድ ተሁኖም ለመፍታት ዚሚያስ቞ግሩና ዚሚፈታተኑ ቜግሮቜ እያጋጠሙ ናቾው፡፡ሲል ጠላቶቜና አንዳንድ ተቃዋሚዎቜ እንደሚሉት ተጣሉና ተሰነጣጠቁ እንደሚባለው ሳይሆን ካለው ተጚባጭ ሁኔታ አኳያ ተገቢና ዹሚጠበቅ አንድነት፣ መቀራሚብ፣ ዹዓላማ ፅናትና ለመስዋዕትነት ዝግጁነት እዚታዚ አይደለም፡፡በማለት መክሯል ሆኖም ያለው ገዢ ፓርቲ እዚሞተ እዚተበታተነ እና እዚተልፈሰፈሰ መሆኑን በሚያሳብቁ ተተኪ ቃላቶቜ ሰብሰብ ነቃ እና ጠንኹር በሚሉ ተክቶ አቅርቊታል::

ሙስናው በስፋት ተንሰራፍቷል ያልው ዚሪፖርተር ጋዜጣ "አገር በሙስና እዚተጚማለቀቜ ናት" ሲል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኚተናገሩት በተቃራኒ ጎኑ መጭውን አደገኛ ዹሃገር ኢኮኖሚ ዚዳግም ስርኣተቀብር ሙስናው እያሳዚን መሆኑን ጠቁሟል:: ሙስናን ለመዋጋት ዹሚደሹጉ እንቅስቃሎዎቜ ዚውስጥ ዚፖለቲካ ባላንጣዎቜን ለማፈን እና ለማስወገድ ዚእጅ አዙር መጥሚቢያነት ኹማገልገል ውጭ ምንም አይነት እርምጃ በሙሰኞቜ ላይ ሲወሰድ አልታዚም ይባስ ሙስና በሃገሪቱ እዚተስፋፋ እና እያበበ ነው::‘እንትና ይደናገጣል እኚሌ ያኮርፋል’ ተብሎ ዹሚቆምና ዹሚቀዘቅዝ ትግል እንደሆነ ይጠቁማል::ሙስና ኢትዮጵያን እያጚማለቀ ሲሆን ኚስርቆትና ኚዝርፊያ በፊት ሙስናን ዚሚያስቆሙና ዚሚያጋልጡ አሠራሮቜ፣ ሕጐቜ፣ መዋቅሮቜና ዚሥነ ምግባር ደንቊቜ እንዳይወጡ ዚመንግስት ባለስልጣናት እንቅፋት ሁነዋል::ዚመንግስት ባለስልጣናት በራሳ቞ው ለሙስና ዚሚያመቜ ሁኔታ እዚፈጠሩ ሙስናን እንዋጋለን ማለት አያስኬድም፡፡ ኚአሿሿም ጀምሮ፣ ኚቁጥጥር ጀምሮ፣ ኚቅጥር ጀምሮ አሠራሩ ሁሉ ሙስናን ዚሚያስወግድ ሳይሆን ዚፖለቲካ ታማኝነትን ዹጠበቀ ነው፡፡

አገሪቷ በሙስና መጹማለቋ ዚመልካም አስተዳደር እጊት ፈጥሯል:: ጠቅላያቜን እንዳሉን ማንጫውንም ነገር መልካም አስተዳደርን ጚምሮ እዚተሰሩ ያሉ ስራዎቜ መኖራ቞ው እና በሂደት እዚተሻሻሉ እንደሚሄዱ ነግሹውናል ይህ ነገር ላለፉት 22 አመታት ሲነገሚን ዹነበሹ እና ምንም አይነት ለውጥ ኚማዚት ይልቅ በካድሬዎቜ ብልሹ አሰራር እና ቢሮክራሲ ዚመልካም አስተዳደሩ እዚተበላሞ ገደል መግባቱን ብቻ ነው::ዚመልካም አስተዳደር እጊት ሕዝቡን ተስፋ እያስቆሚጠ ነው ብሎናል ለገዢው ፓርቲ ቅርብ ዹሆነው ሪፖርተር- አዎን ገዥው ፓርቲ መልካም አስተዳደር አለመኖሩን እያመነ ነው፡፡ ዕርምጃም እወስዳለሁ ቢባልም ለስልጣኑ ማራዘሚያ ዚሚጠቀምባ቞ው በጥቅም ዚተተበተቡ ካድሬዎቹ ይገለበጡብኛል በሚል ፍራቻ ምንም አይነት ርምጃ ሳይወስድ ዚመልካም አስተዳደር እጊቱ እንደቀጠለ ነው ፡፡

መልካም አስተዳደር ይኑር ይስፋፋም ዹሚሉ ዚመንግስት ሚዲያዎቜም ይሁኑ ፕሮፓጋንዲስቶቜ ቃላቶቜን ህዝብን ለማጭበርበር እዚተጠቀሙበት ነው ፡፡ በቃላት ላይ ቜግር ዹለም፡፡ በተግባር ግን መልካም አስተዳደር እውን ሊሆን አልቻለም፡፡ ዚትም ሥፍራ፣ ዚትም መሥሪያ ቀት በማንኛውም ጊዜ መልካም አስተዳደር እዚተጣሰ፣ ፍትሕ እዚጠፋ፣ ዚሕዝብ ጩኞትና ጥሪ ተቀባይ አልባ ሆኗል፡፡ ሕገ መንግሥቱና ዚተለያዩ ሕጎቜ ተግባር ላይ ዚሚያውላ቞ው አጥተዋል፡፡ ዚሙስና ተጠርጣሪዎቜ ታሰሩ ቢባልም ፈጥሚውታል ዚተባለው በደል ግን ሲስተካኚል አይታይም፡፡ ይህ ቜግር በእጅጉ አደገኛ ነው፡፡ ዜጋ አገሩን እንዲጠላና ተስፋ እንዲቆርጥ እያደሚገ ያለ ቜግር ነው፡፡ 


#3 ምንሊክ ሳልሳዊ 
በአንድ አገር ላይ ሁለት አገር ዹለም ሃይለማርያም ደሳለኝ ስለ ዚትኛው አገር መግለጫ እንደሰጡን አሁንም አልገባንም::ሪፖርተር ጋዜጣ ደሞ ዚታዘብኩት ያዚሁት ዚሰማሁት በሚል አበይት ብሎ ያለውን ዚሃገርቱን እውነታዎቜ በኚፊት አስቀምጧል:: በርግጥ ዹተሾፋፈነ ቢሆንም ፍንጭ ግን አገሪቷ አደጋ ላይ እንዳለቜ ጋዜጣው መስክሯል:: እኛም ያዚነውን ዹምናውቀውን ጀቅላይ ሚኒስትሩን እና ጋዜጣውን ይዘን ተንትነናል ::

ዚሃይለማርያም ደሳለኝ መግለጫ እና ዚሪፖርተር ጋዜጣ ግጭት
- ዚመንግስት ዚጥንቃቄ ጉድለት እና ዚፖለቲካ አጀንዳ ሃይማኖቶቜን እዚበሚዘ ነው:;
- ዚኢኮኖምው ድቀት አገ

ሪቷን ወደማትወጣበት አደጋ ውስጥ ዹኹተተ ሲሆን ኹፍተኛ ስራ አጥነት ፈጥሯል::
- በወያኔ መንግስት ዚመወያዚት ዹመነጋገር ዚመቀራሚብ መንገዶቜ ስለተዘጉ ቜግሮቜ እዚበሚኚቱ ነው::

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ዚድርጅታ቞ው ዹበላይ አካሎቜ በሰጧቾው ኊሚን቎ሜን መሰሚት አጥንተው ገብተው በሃገሪቱ ዚተኚሰቱ ዚሃይማኖት ነጻነት ጥያቄዎቜን እና መሰሚታዊ ዚዲሞክራሲያዊ መብት ጥያቄዎቜን በተለመደው አሞባሪ አክራሪ እና ጜንፈኛ በሚሉ ወያኔያዊ ቃላት ተጠቅመው ሲያስፈራሩ ... ይህን መሰል ዚመንግስት ማስፈራሪያ በህዝቊቜ መብት ላይ መስጠት በሃገሪቱ ያሉ ሃይማኖቶቜ ነጻነታ቞ውን መጋፋት ሲሆን ዋናው ዚቜግሩ ፈጣሪ ወያኔ ዹፈጠሹው ዚስልጣን ማስሚዘሚያ ዹወንጀል ቃላቶቜ መሆናቾውን ፍንትው አድርጎ ያሳያል :: ሃይማኖቶቜ በመርሃቾውም ይሁን በተግባራ቞ው አይጋጩም፡፡ ሁሉም ፍቅርን፣ መተሳሰብንና ሰላምን ዚሚሰብኩ ናቾው፡፡ ቜግሩ ያለው እምነት ላይ አይደለም፡፡ ቜግሩ ያለው ዹዚህ ሃይማኖት ጠበቃና አለኝታ እኔ ብቻ ነኝ፣ አንተ ወይም ያኛው አይደለም በሚል ሃይማኖትን ተገን በማድሚግ በሚደሹግ እንቅስቃሎ ነው፡፡ ስለዚህ ዚቜግሩ መንሮ ዹሆነው ወያኔ ዚሃይማኖቶ ጠበቃ በመምሰል በህገመንግስት ንግድ ውስጥ ተጀቡኖ እጁን ወደ ሃይማኖቶቜ በማስገባት ራሱን ዚሃይማኖት አለኝታ በማስመሰል ሃይማኖቶቜን ለፖለቲካ ፍጆታ ማዋሉ ዚህዝብ ጥያቄዎቜ በአደባባይ መሰማት ኚጀመሩ አመታት ተቆጥሚዋል::
ዚክርስትና፣ ዚእስልምናና ዚአይሁድ እምነቶቜ በጋራ በሚኖሩበት አገር ውስጥ፣ ጋብቻ ፈጜመውና ተፋቅሹው መኖር ዚሚቜሉ ዚተለያዩ ዚሃይማኖት እምነት ተኚታዮቜ ያሉበት አገር አለን እያልን፣ ዚወያኔ መንግስት በፈጠሹው ዚፕሮፓጋንዳ እና ዹኹፋፍለህ ግዛ ድርጊት ተጋጹ፣ ጠንካራ ዹነበሹን ሕዝብ ተፋጀ ወደሚል አሳፋሪ ታሪክ እዚቀዚርነው ነው፡፡ ወያኔ ለስልጣን ማስሚዘሚያ ብሎ ዚተጀቀመበት ስልት ነገ ለቁጭት ዚሚዳርገን እና ወደማንወጣበት ውድቀት ዹሚኹተን ሲሆን ታሪካቜንን፣ ማንነታቜንና ደኅንነታቜንን ለአደጋ እያጋለጠ ነው::

ዚሃገሪቷ ኢኮኖሚ በወያኔ ባለስልታናት እና በብሄራዊ ጥቅም በታወሩ ምእራባውያን እንደሚወራል ሳዮን እጅግ በጣም እዚተንኮታኮተ መሆኑ እሙን ነው::በመንግስት ካዝና ውስጥ ኚባድ ዹሆነ ዚገንዘብ ቜግር አለ:: ዚመንግስት ካዝና ባዶ ነው ቢባል ዚሚያስኬድበት ደሹጃ ላይ ተኩኖ ዚሃገሪቷን በጀት ማጜደቅ እንደት እንደሚቻል ግራ እዚገባን ነው:: በጀት ሲጞድቅ እንጂ ሲለቀቅ ዚማይታይባት ኢትዮጵያ አስደንጋጭ ዚኢኮኖሚ ውጥንቅጥ ውስጥ እዚዳኚሚቜ ነው:: ዚፓርቲ ዚንግድ ድርጅቶቜ ብቻ ኚጥቂት ነጋዎዎቜ እና ብሄርተኞቜ ጋር በሙስና ተጹማልቀው ዚሚሰሩት ዹአዹር በአዹር ንግድ ዚሃገሪቷ ኢኮኖሚ አይደለም ዹመንደር ኢኮኖሚ ሊባይ አይቜልም::ክፍያ አፈጻጞም ላይ እንኳን ግለሰብ መንግሥትም እዚተ቞ገሚ ነው፡፡ ዹግል ባንኮቜ እዚተዳኚሙ ናቾው፡፡ ዚብድርና ዹውጭ ምንዛሪ ቜግርና እጥሚት አለ፡፡ ግሜበትን ለመቆጣጠር ዹሚወሰደው ዕርምጃ ዚራሱን ቜግር እዚስኚተለ ነው፡፡ ዚኀሌክትሪክ ኃይል መቋሚጥ፣ ዹውኃ መጥፋት፣ ዚኔትወርክ አለመኖር፣ በሁሉም ዘርፍ ቜግር እያስኚተለ ነው፡፡ ገንዘብ ማሞሜና መደበቅ እዚታዚ ነው፡፡ ሌባው ሲፈራ ባይገርምም፣ ንፁኃን ሲሞማቀቁና ብታሰርስ እያሉ በመፍራት ኚቢዝነስ እንቅስቃሎ ሲቆጠቡ እዚታዚ ነው፡ ይህንን ወያንኀ አምኖ ሊቀበለው አይደለም ጭራሜ በጠላይ ሚኒስትር ደሹጃ መካድ ተጀምሯል:: ኚሕዝብ ብዛትና ኹሚመሹቁ ተማሪዎቜ አንፃር በቂ ዚሥራ ዕድል አልተፈጠሹም፡፡ ሥራ ለማግኘት ወደ ዓሚብ አገሮቜ ዹሚደሹገው ስደት በአስፈሪ ሁኔታ እዚታዚ ነው፡፡ ወደ ወንጀል እዚተገባ ነው፡፡ ለባለ ገንዘብ ራስን ለሜያጭ ማቅሚብ እዚተስተዋለ ነው፡፡ ይህ ቜግር ካልተፈታ አደጋ ሊያስኚትል ይቜላል፡፡ ያሰጋል፡፡ ልዩ ትኩሚትና መፍትሔ ይደሚግበት፡፡ ዚተራበ ሆድ አደገኛ ነውና፡፡

በወያኔ መንግስት ዚመወያዚት ዹመነጋገር ዚመቀራሚብ መንገዶቜ ስለተዘጉ ቜግሮቜ እዚበሚኚቱ ነው:: በኢትዮጵያ እዚታዩ ያሉ ቜግሮቜ ኢትዮጵያዊያን ሊፈቱዋ቞ው ዚሚቜሉ ናቾው፡፡ በመንግሥትና በሕዝብ፣ በመንግሥትና በተቃዋሚ ፓርቲዎቜ፣ በመንግሥትና በግሉ ዘርፍ፣ በመንግሥትና በሲቪል ማኅበሚሰቡ፣ በመንግሥትና በተለያዩ ዚሙያ ዘርፎቜ መካኚል መቀራሚብ፣ መወያዚትና መመካኚር ስለሌለ በቀላሉ ዚሚፈቱ ቜግሮቜ እዚተባባሱ ናቾው፡፡ ቜግሮቜን ለመንግሥት ማቅሚብ አልተቻለም፡፡ መንግሥትም ዚሕዝብን ቜግርና ስሜት ማወቅ አልቻለም፡፡ በዚህ ምክንያት ቀላል ቜግሮቜ እዚተካበዱና ወደማያስፈልግ አቅጣጫ እዚተሞጋገሩ ናቾው፡፡ መንግሥት በአስ቞ኳይ ቲንክ ታንክ ያቅድ፣ ዚጋራ መድሚክ ይፍጠር፣ ዚሕዝብና ዚመንግሥት፣ ዚመንግሥትና ዚባለሙያዎቜን ግንኙነት ያጠናክር፡፡ 

   ምንሊክ ሳልሳዊ

 

Oct 12, 2013

Africa vs ICC: Quotes on court before Kenya trial

By JASON STRAZIUSO and TOM ODULA
The Associated Press

FILE - In this Thursday, Jan. 3, 2008 file photo, a young girl cries as she is carried by a man and woman fleeing an area of wooden kiosks which was set on fire by supporters of Raila Odinga's party, the Orange Democratic Movement (ODM), during post-election violence in the Kibera slum area of Nairobi, Kenya. Kenya's foreign minister Amina Mohamed said at a news conference Wednesday, Oct. 9, 2013 that no sitting president in the world has had to appear before a court, a statement that comes as Kenya appears to be laying the groundwork to avoid having President Uhuru Kenyatta appear at the International Criminal Court next month. BEN CURTIS, FILE — AP Photo Read more here: http://www.adn.com/2013/10/10/3119796/africa-vs-icc-quotes-on-court.html#storylink=cpyFILE – In this Thursday, Jan. 3, 2008 file photo, a young girl cries as she is carried by a man and woman fleeing an area of wooden kiosks which was set on fire by supporters of Raila Odinga’s party, the Orange Democratic Movement (ODM), during post-election violence in the Kibera slum area of Nairobi, Kenya. Kenya’s foreign minister Amina Mohamed said at a news conference Wednesday, Oct. 9, 2013 that no sitting president in the world has had to appear before a court, a statement that comes as Kenya appears to be laying the groundwork to avoid having President Uhuru Kenyatta appear at the International Criminal Court next month.
BEN CURTIS, FILE — AP Photo
ADDIS ABABA, ETHIOPIA — Foreign ministers from around Africa on Friday meet at the African Union headquarters in Ethiopia to discuss Africa’s relationship with the International Criminal Court.
The meeting comes a month before Kenyan President Uhuru Kenyatta is scheduled to appear in The Hague, Netherlands court to answer charges of crimes against humanity for his alleged role in Kenya’s 2007-08 post-election violence that killed more than 1,000 people.
Kenya’s parliament, in a nonbinding resolution, voted last month to pull out of the treaty that created the ICC, amid indications Kenyatta may not show up in The Hague for his November court case. Kenya has petitioned the court for Kenyatta to appear by video link.
There is growing criticism inside Africa that the ICC has only prosecuted Africans. On Saturday African heads of state and government meet on the ICC issue. Below are different views on Africa’s relationship to the ICC and Kenyatta’s judicial dilemma.

— “Why should the Kenyan flag be dragged into the court? Kenyatta should not leave the country. If the president goes to the ICC it’s like the whole country is being prosecuted. … Kenyatta wants to go but his advisers are telling him not to go.” — James Gakuya, Kenyan member of parliament from Kenyatta’s political party.
— “Needless to say, the work and functioning of the ICC should not be beyond scrutiny and improvement. However, considerations of withdrawal risk grave consequences for civilians in Africa, who tend to bear the brunt of serious crimes committed in violation of international law.” — Statement by 130 African and international civil society organizations.
— “Instead of promoting justice and reconciliation and contributing to peace and stability, (the ICC) has degenerated into a political instrument targeting Africa and Africans. This is totally unacceptable and that is why Africa has been expressing its serious reservation against the ICC.” — Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn, in his role as chairman of African Union, as told to the U.N. General Assembly last month.
— “He has cooperated fully with the court up until now. … Are the circumstances different? Absolutely. Totally. Completely different. Before he wasn’t the head of state of the republic. … It’s going to be the first time that a sitting head is brought before any court of any time, not just here but anywhere in the world.” — Kenyan Foreign Minister Amina Mohamed, speaking on Wednesday.
— “He won’t go.” David M. Crane, professor at Syracuse University College of Law, on whether Kenyatta will report to the ICC.
— “Whatever its merits as an institution of international law, the ICC is apparently tone deaf to growing public perception in Africa … that the tribunal has it out for Africans, given that all eight of its current investigations involve Africans. … Nevertheless, I doubt that President Kenyatta will blow off the ICC entirely; that would be overplaying his hand.” — J. Peter Pham, director of the Africa Center at the Atlantic Council.
— “This trial could well sound the death knell for the ICC. … Kenya is a fully functioning democracy, more than capable of prosecuting violators of its laws. Not only have no charges been brought against Kenyatta and Ruto in Kenya, they were recently elected in a free and fair election to run the country. That should be the only verdict that matters.” — Charles Stith, director of Boston University’s African Presidential Center, former U.S. ambassador to Tanzania.
— “Impunity for politically-motivated violence has been the norm in Kenya for far too long and, so far, the Kenyan authorities have failed to undertake any domestic accountability process to address the crimes committed during the post-election violence that rocked the country in late 2007 and early 2008.” Statement by No Peace Without Justice, a group promoting human rights and international justice.

MIGRANT BOAT SINKS 10 DEAD, EXCEPT 200IN

A ship carrying about 250 people capsized Friday off the coast of Sicily, according to the Maltese military and the Italian news agency ANSA.
The ship is believed to have been carrying migrants.
The incident occurred in international waters about 60 nautical miles south of Lampedusa, Italy, according to a posting on the Armed Forces of Malta Facebook page.
Malta's military Rescue Coordination Centre has assumed control of what it called a "major search and rescue incident," according to the Facebook posting.
According to the Maltese military, the ship was being followed by military chase planes and "appeared unstable."
"A few minutes later, the aircraft reported that the boat had capsized and that numerous persons were in the water. Initial assistance was provided by the aircraft, which dropped a life raft in close proximity of the persons in distress," according to the Facebook posting.
The fate of those aboard the capsized ship was not immediately clear.
It is the second such incident this month in the region.
Earlier this week, a boat carrying more than 500 African migrants sank off the coast of Lampedusa, killing 309 people in what Lampedusa Mayor Giusi Nicolini called "the biggest sea tragedy in the Mediterranean Sea since World War II."
That ship originated in Libya, caught fire off the Italian coast and sank.
Survivors, many of them from Eritrea, told CNN they used bodies to keep themselves afloat until they were rescued.
The incident sparked calls for efforts to reform migration policies in the region.
A week ago Friday, the United Nations' human rights office urged the European Union to work to prevent another such incident.
The agency called on authorities to work to reduce migrant trafficking and address economic and security issues that have driven thousands of African residents to make the risky voyage to Europe in search of a better life.

MIGRANT BOAT SINKS 10 DEAD, EXCEPT 200IN
In the Strait of Sicily, a boat full of migrants sank. On board were about 250 people. At least a dozen dead, as confirmation that the Navy with ships and helicopters took part in the rescue. The survivors rescued so far are 200, about 150soccorsi by Maltese vessels and about 50 from Italian means, including ten children.
The tragedy occurred in Maltese waters, on the border with Libya, 70 miles from Lampedusa, where a week ago died 339 refugees.

አያ ጅቩ ሳታመካኝ ብላኝ !!!

ኃይለማሪያም ደሳለኝ በአንድ ወቅት ዉሞትን ዚማያዉቅ ጠንካራ ክርሰቲያን ነዉ ተብሎ ሲነገርለት ሰምተን ነበር፤ ታድያ ይህ ሰዉ መለስን ሲተካ ብዙዎቜ በጥርስ ዚለሜ አንበሳነቱ ቢስማሙም ዉሞት እንደ ንጉስ በነገሰባት ኢትዮጵያ ዉስጥ ዉሞት ዚማያዉቅ መሪ መጣ መባሉ ብዙዎቻቜንን ነጻነት ዹተገኘ ያክል አስደስቶን ነበር። ሆኖም ኚወያኔ ጋር ዹዋለ ሰዉ እራሱን ሆኖ መክሹም አይቜልምና ኃይለማሪያምም ባስቀመጡት ቊታ ዹማይገኝ ዹሌላ መንደር ሰዉ ሆኖ ተገኘ። በዚህም ዚዜጎቜን ተሰፋ አመኹነ፤ ደስታ቞ውንም ወደ ኃዘንና ትካዜ ለወጠው።
ባለፈዉ ሳምንት መጚሚሻ ላይ በመገናኛ ብዙኋን ፊት ያዚዉን አላዹሁም፤ ዹሰማዉን አልሰማሁም፤ ያልሆነዉን ሆነ ዹሆነዉን ደግሞ አልሆነም እያለ ሜምጥጥ አደርጎ ዚካደዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝ፤ በእርግጥም ጎበዝ ዚመለስ ዜናዊ ተማሪ መሆኑን በተግባር አስመስክሯል። ኃይለማሪያም ባለፈዉ ዓርብ አንድ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። ይህ ግለሰብ በዚህ ጋዜጣዊ መግለጫዉ ኢትዮጵያን ያክል ትልቅ አገር ኚሚመራ ሰዉ ቀርቶ ኚአንድ ተራ ዚቢሮ ተላላኪ እንኳን ዹማይጠበቅ መልስ ሲመልስ ተስተዉሏል።
ኃይለማሪያም በጋዜጣዊ መግለጫዉ ወቅት ኚቀሚቡለት ብዙ ዲሪቶ ጥያቄዎቜ ውስጥ አንዱ አገር ቀት ውስጥ እዚተደሚገ ያለው ሠላማዊ ሰልፍ ጉዳይ ነበር። ኃይለማሪያም አገር ቀት ዹሚደሹጉ ዹተቃውሞ ሰልፎቜ “በራሳ቞ው ዹሚደሹጉ ሳይሆኑ ኹኋላ ባሉ ሌሎቜ ኃይሎቜ መሪነት ዹሚደሹጉ” ናቾው ሲል ተናግሯል። ኃይለማሪያም ጌቶቹ ፊቱን በጹርቅ አስሚዉት ዚኢትዮጵያ ህዝብ ቜግር፤ መኚራና ስደት አልታይ ብሎት ነዉ አንጂ ወያኔን ዹመሰለ ነብሰ ገዳይ ባለበት አገር ዉስጥ ዚህዝብን ብሶት ዚሚያስጋቡ ጥያቄዎቜ በዹቀኑ ይመነጫሉ አንጂ ኹዉጭ አገርማ አይመጡም። በሌላ በኩል ደግሞ ይሄዉ ኢትዮጵያ በቅርቡ ያፈራ቞ዉ ዋሟ ሰዉ ዚእስልምና እምነት ተኚታዮቜ ዚሚያደርጉት ሠላማዊ እንቅስቃሎ ዚአሞባሪዎቜ እጅ ያለበትና፤አማኞቹ ሃይማኖታ቞ውን ዚወደዱ መስሏ቞ው ሳያውቁ ዚገቡበት ስለሆነ እንዲታሚሙ እንመክራ቞ዋለንም” ብሏል። እዚህ ላይ በግልጜ እንደምናዚዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝ እመራዋለሁ ዹሚለዉን ህዝብ ጥቅምና ፍላጎት ፈጜሞ ሊሚዳ አልቾለም፤ ስለዚህ ምክር ዚሚያስፈልገዉ መብትና ነጻነት ምን እንደሆኑ ገብቶት ዚሚታገለዉ ዚአትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን ኃይለማሪያም እራሱ ነዉ።
እኛ ግንቊት ሰባቶቜ ወያኔን ዹመሰለ ጚካኝ እና ምንም አይነት አገራዊ ኃላፊነት ዹማይሰማውን ዘራፊና ዘሹኛ ቡድን በሠላማዊ መንገድ ዚሚጋፈጡ ወገኖቻቜንን እናደንቃለን። እነዚህ ወገኖቻቜን ኃይለማሪያም ደሳለኝ እንደሚለው ዹማንንም አጀንዳ ዹተሾኹሙ ሳይሆኑ ዚራሳ቞ው ዹሆነ አጀንዳ ያላ቞ውና ኃይለማሪያም በዉክልና ለሚያስሚግጣ቞ዉ ወገኖቻቜዉ መብትና ነጻነት ዚሚታገሉ ጅግኖቜ ናቾዉ። አጀንዳ቞ውም ዹተደበቀ ወይም ኚጀርባውም ሌላ ነገር ያለው አጀንዳ አይደለም።አጀንዳ቞ው ግልጜ እና ዚታወቀ ዚነፃነት፤ ዚእኩልነት፤ዚፍትህና ዹሠላም አጀንዳ ነው። ኃይለማሪያም ደሳለኝ ዚዜጎቜን ጥያቄ አድምጊ መልስ መስጠት ሲገባው እነዚህን ዚኢትዮጵያን ህዝብ አጀንዳ ተሾክመው ዚሚታገሉ ወገኖቜ ደካሞቜ አድርጎ ለመሳል ዚሚያደርገዉ ሙኚራ አንድም በተቃዋሚዎቹ ዙሪያ ዚተሰባሰበውን ዹሰው ኃይል ካለማወቅ፤ አለዚያም ደግሞ “ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ይሏታል ጅግራ” እንደሚባለው ነገር ነው።
ሌላው ኃይለማሪያም ዹሚናገሹዉ ቃል ጠፍቶት በተደጋጋሚ ሲንተባተብ ዚታዚዉ በሜብርተኝነት አካባቢ ዹተጠዹቀዉን ጥያቄ ሲመለስ ነዉ። በእኛ እይታ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዋነኛው አገር በቀል አሞባሪ ህወሃት እና ህውሃት ብቻ ነው። ህወሃት ስልጣን ላይ ያቆዚኛል ብሎ ኹገመተ ዹማይመሰርተው ዚክስ ዓይነት፤ ዚማያፈሰው ዚንጹህ ሰው ደም ፤ዚማያፈነዳው ዚቊንብ እና ዹፈንጂ ዓይነት እንደሌለ ኹሃውዜን እስኚ አዲስ አበባ ያሉ መንገዶቜ ቋሚ ምስክሮቜ ናቾው። ይህንን እኩይ ተግባሩን ዓለም ሁሉ እንደሚያውቀው በዊክ-ሊክ ላይ ዚወጣው መሹጃም አሳይቷል።
ዚህውሃት ታማኝ ሎሌ ዹሆነዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሠላማዊ ትግሉን ለማፈን ኹፈለገ በትግሉ ዙሪያ ዚተሰባሰቡትን ዜጎቜ ኹሌላ ኹማንም ጋር ማነካካት አያስፈልገውም። ኢትዮጵያ ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ዚሚታገሉ ሁሉ አንደ ኃይለማሪያም ሞቶ ዹተቀበሹን ሰዉ ራዕይ ዹተሾኹሙ ዚአመለካኚት ደሃዎቜ ሳይሆኑ ዚራሳ቞ው አስተሳሰብና ህያዉ ራዕይ ያላ቞ው ዜጎቜ ናቾው። አነዚህን ሠላማዊ ታጋዮቜ ኹማይገናኝ ሌላ ኃይል ጋር አቆራኝቶ ለመምታት መሞኹር ለኃይለማሪያምም ሆነ ለጌቶቹ አይበጃቾዉም። ዛሬ በወያኔ ነብሰ ገዳይ ወታደሮቜ ተኚብቊ እዩኝ እዩኝ ዹሚለዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝም ዚኢትዮጵያ ህዝብ ቁጣ ዹነደደ ቀን ደብቁኝ ማለት ይመጣልና ያ ቀን ኚመምጣቱ በፊት ዹበደለዉን ህዝብ ይቅርታ ጠይቆ ዚነጻነት ኃይሎቜን እንዲቀላቀል ወገናዊ ምክራቜንን እንለግሳለን።
በመጚሚሻም ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ስለ ግንቊት ሰባት ተጠይቆ ሲመልስ ግንቊት ሰባት “በህልም ውስጥ ያለ ድርጅት” ነው ብሏል። ታድያ ምነዉ ተኝቶ ህልም ዚሚያልም ድርጅት ኃ/ማሪያምንና ጌቶቹን እንዲህ ያቃዣ቞ዋል? ለምንስ ይሆን ወያኔና ታማኝ ሎሌዉ ኃ/ማሪያም ያገኙትን ሁሉ ግንቊት ሰባት እያሉ ዚሚያስሩት፤ ዚሚደበድቡትና ዚሚገድሉት? ያገኛቜሁትን ሁሉ ዚግንቊት ሰባት አባል እያላቜሁ ትኚሳላቜሁ? ለምንስ በግንቊት ሰባት ስም ታስራላቜሁ? ትገርፋላቜሁ? ትገድላላቜሁ? ተኝቶ ለሚያንቀላፋ ድርጅት ለምን ትሞበራላቜሁ፤ ለምንስ እንቅልፍ አጥታቜሁ ትባዝናላቜሁ? ግንቊት ሰባት እናንተ አልገባቜሁም አንጂ መነሻውንና መድሚሻውን አጥርቶ ዚሚያውቅ፤ ኹደመናው ባሻገር ፍንትው ያለ ዚነፃነት ዉጋገን ዚሚታዚው ባለ ታላቅ ራዕይ ድርጅት ነው። አስኪ ምናልባት ቢገባቜሁ ተሚት ቢጀ እንንገራቜሁ፤
“አንዲት ሚዳቋ ነበርቜ አሉ። ሚዳቆ ኚመሬት ገንዘብ ተበድራ ሲትኖር ኚእለታት አንድ ቀን መሬት አፍ አውጥታ ብድሬን መልሜ አንጂ ብላ ትጠይቃታለቜ። ሚዳቆዋም ደንግጣ ኚነበሚቜበት ቊታ ፈትለክ ብላ ወደ ተራራ ጫፍ ላይ ወጥታ እፎይ ያንን ድምጜ ኹአሁን በኋላ አልሰማም አለቜ። መሬትም በይ ብሬን ክፈይኝ ስትል ዳግም ጠዚቀቻት። እንዎ ይህቜ መሬት ዚሌለቜበት ዬት አገር ሊሂድ ብላ ሚዳቆ ወደ ማይታወቅ ቊታ ተፈተለኚቜ። ኚዚያም እያለኚለኚቜ በቃ አሁንስ አታገኚኝም ስትል አሁንም መሬት ብቅ ብላ እዚጠበኩሜ ነውኮ ብድሬን ክፈይ እንጂ ስትል ጠንኹር አድርጋ ጠዚቀቻት። ሚዳቆዋም መሬት ዚሌለቜበት ልትደሚስ ስትበር ስትበር ሳንባዋ ፈንድቶ ሞተቜ”ይባላል።
ዚፍትህ፤ ዚእኩልነት፤ ዚነፃነትና ዚዲሞክራሲ ጥያቄዎቜ እንደ መሬት ናቾው። ዚትም ሂዱ፤ ዚትም ግቡ ይኚተሏቜኋል። መስጊድ ዉስጥ አሉ፤ ቀተክርስትያናት ውስጥ አሉ። ቀተመንግሰት ዉስጥም አሉ። ዚሌሉበት ቊታ ዹለም። መፍትሄው እንደ ሚዳቆዋ መሞሜ አይደለም። መፍትሄው ዜጎቜ ዚሚያነሷ቞ውን ዚፍትህ፤ ዚእኩልነ፤ ዚነፃነትና ዚዲሞክራሲ ጥያቄዎቜን አድምጊ ትክክለኛ መልስ መስጠትና ኚዕዳ ነጻ መሆን ብቻ ነዉ ። ኹዚህ ዉጭ ጥያቄን ላለመስማት ወይም ሰምቶ ለመደፍጠጥ ዹሚደሹገው ኚንቱ ሩጫ መጚሚሻው እንደ ሚዳቆዋ መፈንዳት እንጂ ህይወት አይሆንላቜሁም።
እኛ ግንቊት ሰባቶቜ ዘሹኛዉንና አሞባሪውንና ዚወያኔ ስርዐት ለመደምሰስና ህዝብ በነፃነት ያለፍርሃት ዚሚኖርበትን አገር ለመፍጠር ቆርጠን ተነስተናል። ኚእንግዲህ ዚሚያቆመን ምንም ነገር ዹለም። ዚምንታገለዉ ለህዝብ ጥያቄያቜንም ህዝባዊ ጥያቄ ነዉና እኛም አንደጥያቄዉ በዚመስጊዱ፤ በዚቀተክርሲቲያኑና በዚሰፈሩ ዉስጥ አለን።እኛ ዚሌለንበት ስፍራ ዹለም። በዚህ አጋጣሚ ዚዘመናት ትግላቜን ፍሬዉ ዚሚታይበት ቀን እጅግ በጣም ቅርብ ነዉና ዚኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም አገር ተሚካቢ ዹሆነዉ ወጣቱ ትዉልድ እራሱን፤ ወገኖቹንና እናት አገሩን ለማዳን ዹሚደሹገዉን ዚነጻነት ትግል እዚመጣ እንዲቀላቀል ወገናዊ ጥሪያቜንን አቅርበናል። ኑ እና ተቀላቀሉን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Total Pageviews

Translate