Pages

Feb 18, 2015

ለምንድን ነው ወጣቱ ዝም ብሎ ዹተቀመጠዉ ምንስ እስኪሆን ይሆን ትዕግስቱ አጀንዳ ??????? አንዱ ምን አለ

ዘመነ ወያኔ ወይም ዘመነ ኢሀዲግ ??? 
ለምንድን ነው ወጣቱ ዝም ብሎ ዹተቀመጠዉ ምንስ እስኪሆን ይሆን ትዕግስቱ አጀንዳ ???????
አንዱ ምን አለ
አትፍሚድ!! እኔን ለምሳሌ ውሰድ 1984 ነው ዚተወለድኩት በዘመነ ኢሀዲግ ካለ ኢሀዲግ ምን አውቄ እኔማ 1997 ያሃ ሁሉ ህዝብ ሲታሰር ሲገሚፍ ኹሃገር ሲሰደድ ሁሉ በቃ ሲያልቅ ምንም አልተሰማኝም እንደውም ህዝቡን ጥፋተኛ ነበር ያደሚግኩት ምክንያቱም ምርጫ አሾነፉ አይደል እንዎ እና ምን አድርጉ ይሏቾዋል ብዬ ነበር እንደገናም ደግሞ በኔ እድሜ ነው ባቡር ያዚሁት በኔ ዘመን ነው መንገድ ያዚሁት አዎ በኔ ዘመን ነው ፎቅ ያዚሁት በኔ ዘመን ነው ኮንዶሚንዚም ያዚሁት እና ለምን ኢሀዲግን ልጥላ ብዬ አስብ ነበር ይዅው አውን ደሚስኩ ተማርኩ ተመሚቅኩ ለወግ መአሹግ በቃሁ ይዅው ቜግሩን ዚትውልድ ዘመኔንም አዹው ለካስ ስው በራሱ ካልደሚሰበት አያውቅም ለካስ ሰው ወዶ አደለም ሊቢያ ጣልያን ብሎ በሹሃ ላይ ኩላሊት ልቡን እዚተነጠቀ ዹሚሞተው ለካስ ወዶ አደለም ባህር ላይ ዚሃሳ እራት ሆኖ ዹሚቀሹው ለካስ እህት ዓለም በዓሚብ ዓገር ዹዓገር ውርጅብኝ ዚሚወርድባት ዹማንም ዓሚብ መጫወቻ ዚሆነቜው ኹፎቅ ላይ ራሷን ዚምትኚሰክሰው ለዓመታት ያለምንም ክፍያ ጉልበቷን ዚምትበዘብዘው እናማ ታውቃለህ ለካስ ኣብሮ መብላት ኹሌለ መተማመን ኹሌለ ዘሚኝነት አገሪቱን ኹወሹሹ በሃገሬ ላይ ካልኖርክ ካልተናገርክ ካልበላክ ካልጠጣክ እንደ፯ተኛ ዜጋ ተቆጥሚክ ኹኖርክ ዲሞክራሲ ዹሃገር ዕድገት መንገድ ፎቅ ባቡር 11 % እድገት EBC ላይ ወይም ኹበደ ካሣ ብሎግ (LOL) ላይ ብቻ (ፌመስ አደሚግኩት አይደል ኚቀ ደስ ይበልክ ሎል ሎል) ኹሆነ ምኑ ላይ ነው ታድያ ኢትዮጵያ ውስጥ መኖሬ ጥቅሙ ምኑ ላይ ነው በኢሀዲግ ዘመን መወለዮ ዚሚያኮራኝስ ለምንድን ነው ኹነማን ጋር እንደቆመን ራስን እንድንመሚምር ዹሚገፋፋ ስለሆነ በሉ ኹግፉ ጚምሩበት እላለሁ። መገፋት አመጜን፣ አመጜ መሰባሰብንና ዚሀሳብ አንድነትን ይፈጥራልና፦
ለካስ በዘመነ ወያኔ መወለድም እርግማን ነበር ተሹግመን ነበር ማለት ነው
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኖራለቜ ሞት ለወያኔ
YAYAZUF

Jul 8, 2014

ETV Report Andargachew Tsege Detained in Ethiopia

አዎ አንዳርጋ቞ውን ያንኑ መኹሹኛ ዚሜብር ዶክመንተሪ ሊያሰሩት በሹሃ ለበሹሃ ሲያንኚራትቱት ፎቶና ቪዲዮ ሲያነሱት ሚስጢር አውጣ እያሉ ሲደበድቡት ኹርመው አድክመውታል። ዶክመንተሪውም ለዚያው ለድፍኑ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በ቎ሌቪዥን ይቀርብለት ይሆናል።
ዚተኚበሩ ዚነፃነት ታጋይ አቶ አንዳርጋ቞ው በኢቲቪ ታዩ! ኚዚያም እነዚህን አሹፍተ ነገሮቜ ሲቃ እዚተናነቀው ተናገሹና።
እኔ አሁን ኚራሎ ጋር ታርቄ ሰላም አግኝቻለሁ!
እውነ቎ን ነው ዹምልሕ ለእኔ እንደ ምርቃት ነው ዚተቀበልኩት
 áŠ¥áŠ” አሁን ምንም ዚሚያቻኩለኝ ነገር ዹለም... ጥሩ እሚፍት ማድሚግ እፈልጋለሁ
በጣም በጣም ደክሞኛል... በቅቶኛል
 áŠ¥á‹áŠá‰ŽáŠ• ነው ዹምልህ ተሚጋግቌ ያለሁበት ሁኔታ ነው
 áˆáŠ•áˆ አይነት ጥላቻ በውስጀ ዹለም
 áˆáŠ•áˆ አይነት ብስጭት ዹለኝም
 áˆáŠ•áˆ አይነት መጥፎ ስሜት አይሰማኝም
 á‰ á‰ƒ... ዚመጚሚሻ እርጋታና እሚፍት ውስጥ ነው ያለሁት

Jun 14, 2014

቎ዲ አፍሮና ውዝግብ ያልተለዚው ዝና

በአዲስ አበባ ታትሞ ኚተሰራጚው ቁምነገር መጜሔት ዹተወሰደ

ተወዳጁ ድምፃዊ ቎ዲ አፍሮ ወደ ሙዚቃው ዓለም ተቀላቅሎ ወደ ዝና ማማ መውጣት ኚጀመሚበት ጊዜ ጀምሮ መነጋገሪያ ኹመሆን ያመለጠ አርቲስት አይደለም፡፡ በ1993 ዓ.ም ማብቂያ ላይ ባወጣው ዚመጀመሪያ ‹áŠ á‰ŠáŒŠá‹³› አልበሙ ዹሙዚቃ አድማጩን ጆሮ ለመቆጣጠር ዚቻለው ቎ዲ አፍሮ በወቅቱ በአለቀ ሟው ፕሮግራም ላይ በእንግድነት ቀርቩ ‹25 ዓመቮ ቢሆንም ፍቅሹኛ ገና አልያዝኩም › ባለ ማግስት ዹኹተማው ወጣት ሎቶቜ አይን ማሚፊያ ሆኖ ነበር፡፡ ኹዚሁ ይፋ ካልወጣ ዚሎቶቜ አደን ጋር ተያይዞ ዚመጀመሪያውን ውዝግብ አስተናገደ፡፡ ‹á‰ áˆŽá‰µ ልጅ ጡት ላይ ፊርማ ፈርሟል› በሚል ተሰራጚው ወሬ ኹኹተማ ወሬነት አልፎ ዚአንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ገበያ መጥሪያና ማሻሻጪያ ሆኖ ነበር፡፡‹á‹šá‰°á‰£áˆˆá‹áŠ• ነገር አላደሚኩም፤ ኢትዮጵያውያን ሎቶቜ ኩሩዎቜ ናቾው፡፡ ይህንን ነገር እንዳደርግ አይጠይቁኝም ፤ እኔም አላደሚኩትም› ብሎ በወቅቱ ለታተመቜው ቅፅ 1 ቁጥር 1 ቁም ነገር መፅሔት ላይ ቢናገርም አድናቂዎቹን ኚማሳመን በቀር ዚወሬ ማጣፈጫነቱን አላስቀሚውም ነበር፡፡
TeddyAfro_NYC-12
቎ዲ አፍሮ ዚመጀመሪያ ውዝግቡን በዚሁ መልኩ ለመቋመጚት ጥሚት ቢያደርግም ኹዚሁ አልበሙ በፊት በሰራው ዚመጀመሪያ ካሎቱ ሳቢያ ለሌላ ውዝግብ ዚተዳሚገው ብዙም ሳይቆይ ነው፡፡ ዚመጀመሪያ ካሎቱን ሳያወጣ ለዓመታት አስቀምጊት ዹነበሹው ቮይስ ሙዚቃ ቀት ዚአቊጊዳ አልበሙ ዚአድማጭን ጆሮ መቆጣጠር ተመልክቶ አዲሱን አልበም ለገበያ ያቀሚበው ወዲያውኑ ነበር፡፡ በዚህ ሳቢያም ‹á‹šáŠ á‰ŠáŒŠá‹³áŠ• አልበም ሜያጭ ብቻ ሳይሆን አሁን ያለበሁበት ደሹጃ ፈፅሞ ዚማይመጥን› ያለውን ኚዓመታት በፊት ዚተሰራውን ካሎት ‹áˆ³á‹«áˆµáˆá‰…ደኝ መልቀቅ ዚለበትም› በሚል ሌላ ውዝግብ ተፈጥሯል፡፡ ተፈጠሹው ውዝግብ መሀል ጋዜጠኛ ሳምሶን ማሞ ገብቶ በሜምግልና ጉዳዩን እንዲፈታ እስኪያደርግ ድሚስ በመገናኛ ብዙሃን ዘንድ መነጋገሪያ ነበር፡፡
቎ዲ በሙዚቃ ስራው ብቻ ሳይሆን በማህበራዊ ህይወቱና በሚያደርጋ቞ው ቃለ ምልልሶቹ ዝናውን ኹፍ እያለ ቢመጣም ምርጫ 97 ተኚትሎ ገበያ ላይ በዋለሁ ሶስተኛ ‹áŒƒ ያስተሰርያል› አልበሙ ሳቢያ ውዝግቡ ኚግለሰብ ወደ መንግስት ዞሮ ነበር፡፡ ይፋዊ በሆነ መንገድ መንግስት ተቃውሞውን ባይገልፅም ዘፈኑ በማንኛውም ዚመንግስት መገናኛ ብዙሃን ላይ እንዳይተላለፍ ኹመኹልኹል ጀምሮ ለጉዳዩ ሌላ ፓለቲካዊ መልክ በመስጠት ዚውዝግቡን ጡዘት እንዳኚሚሚው እናስታውሳለን፡፡ ኚምርጫው ጋር ዚተያያዘው ውጥሚት ቀስ እያለ ቢሚግብም ኚመንግስት ጋር ያለው ውዝግበ ኚአንድ ዘፈን ወደ ሶስት አድጎ ኹ‹áŠ«á‰¥ ዳህላክና› እና ‹áˆŒ መንደፈርን› ጚምሮ ታይቷል፡፡ መንግስት በወቅቱ ኹነበሹው ፖለቲካዊ ራስ ምታት ተሚጋግቶ ሚሊኒዹሙን ለመቀበል ሜር ጉድ በሚልበት ወቅት ቎ዲ አሁንም ዚህዝቡን ዚልብ ትርታ ያዳመጠ ‹áŠ á‰ á‰£ አዚሜ ሆይ› ዹተሰኘውን ተወዳጅ ባህላዊ ዜማ ለእርቅ አውሎት ብቅ አለ፡፡ ኚፓለቲካ እስሚኞቜ መፈታት ጋር ተያይዞ ዚእርቅ መንፈሱ በሁሉም ሙዚቃ አድማጭ ጆሮ ማንቃጹል ቢጀምርም መንግስት ግን ዘፈኑን ዘወትር በዚሚዲያው ላይ ሲለቀቅ ሁኔታውን በዝምታ ኚመመልኚት ውጪ ‹áˆ† በል ኚበሮ ሆ በል አንተ ማሲንቆ ስታይ ሰው ታርቆ› በሚለው ስንኝ ኚህዝቡ ጋር እስክስታ ለመውሚድ ሳይቜል ቀርቷል፡፡ዚ቎ዲ አፍሮ ዚእርቅ መንፈስ ሚሊኒዹሙን ብቻ ሳይሆን ባህር ማዶ ተሻግሮ ለመዝፈንና ለማስጚፈር ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ኹሚሊኒዹሙ ጋር ታኮ በሚሊኒዹም አዳራሜ በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ ዹሙዚቃ ኮንሰርት ላይ ቢዮንሎ ኖውልስ በ቎ዲ አፍሮ ‹áŠ á‰ á‰£ አዚሜ ሆይ› ዜማ ወገቧን ይዛ ስትጚርፍር ታይታለቜ፡፡
቎ዲ በዘፈኑ ዚሀገሩን ልጆቜ አልፎ ዚውጪ ሰዎቜን ማማለል ቢቜልም ኚመንግስት ጋር ዚገባው ውዝግብ ኹዚህ ቀደም ኚግለሰቊቜ ጋር እንዳለው አይነት ተራ ዚሚባል አልነበሹምና ወደ እስር ቀት ዚሚገባበት ሁኔታ ተፈጠሹ፡፡ በብዙዎቹ አድናቂዎቹ ዘንድ አሁንም ድሚስ እንደሚታመነው ‹á‰Žá‹² አፍሮ በመኪና ሰው ገጭቶ አምልጧ› ዹሚለውን ዚአቃቀ ህግ ክስ ለመቀበል ዳግም መወለድ ዚሚያስፈልጋ቞ው ይመስላል፡፡ ‹á‹°áŒ‰ ይበልጣል› ዚተባለውን ዹ18 ዓመት ዚጎዳና ተዳዳሪ ገጭቶ ስለመግደሉና ስለማምለጡ በወቅቱ መነጋገሪያ ዹነበሹው ክስ ኚብዙ ዚፍርድ ቀት ቀጠሮና ምልልስ በኋለ ኚአንድ ዓመት ኚስድስት ወር በኋላ ሲቋጭ ‹á‰Žá‹² እንደ በፊቱ ተወዳጅ ሥራዎቹን ይሰጠን ይሆን ›á‹šáˆšáˆ ጥርጣሬ መኖሩ አልቀሹም፡፡ ዚፈጠራ ስራ ቜግር ዚሌለበት ቎ዲ ኚእስር ቀት በወጣ በሶስተኛው ወር ላይ በአዲስ አበባ ስታዲዚም ኮንሰርት በማዘጋጀት ገቢውን በልመና ሥራ ላይ ለተሰማሩ ወገኖቜ ማቋቋሚያ አደሹገ፡፡ በዚህ ኮንሰርት ላይም ያገኘውን ኚአንድ ሚሊዹንም ብር በላይ ገንዘብም ለኀልሻዳይ ዹበጎ አድራጎት ማህበር አስሚኚበ፡፡
ኚሚያወጣ቞ው አልበሞቜ ጋር ተያይዞ ውዝግብ ዚማያጣው ቎ዲ ኹሰይፉ ፋንታሁን ጋርም ውዝግብ ውስጥ መግባቱ ዹሚዘነጋ አይደለም፡፡ ኚዘፈኖቜ መመሳሰል ጋር በተያያዘ በሰይፉ ፕሮግራም ላይ በቀሹበ ዘገባ ሳቢያ ጉዳዩ በስምምነት እስኪፈታ ድሚስ ወደ ፍርድ ቀት ለመሄድ ጫፍ ደርሶ ነበር፡፡ ቎ዲ ዚሌሎቹን ያህል አይሁን እንጂ ኚሚዥም ጊዜ ማናጀሩ አዲስ ገሠሠ ጋርም ውዝግብ ውስጥ ገብቶ ዚተለያዩ ሲሆን በተደጋጋሚ ተሰርቀው በወጡ ነጠላ ዜማዎቹ ሳቢያም ዹመገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ዚ቎ዲ አራተኛ ካሎትም ውዝግብ መፍጠሩ አልቀሹም፡፡ ‹áŒ¥á‰áˆ­ ሰው› በሚል ርዕስ ያወጣው አልበም ኹፍተኛ ዹሙዚቃ ቜሎታውን ያሳዚበትና አዳዲስ ዹአዘፋፈን ስልቶቜን ያካተተበት ሥራው ቢሆንም ኚዳግማዊ አፄ ምንሊክ ፓለቲካዎ አቋም ጋር ተያይዞ ተቃውሞ ዹገጠመው ወዲያውኑ ነበር፡፡ ጉዳዩ ኚታሪክ አንፃር መታዚት ያለበትና ዚአድዋ ጀግኖቜን ለመዘኹር በሚል ዚተሰራ ሙዚቃ እንደሆነ ዚተለያዩ ሰዎቜ ዚዚራሳ቞ውን አስተያዚት በማኹል በዹመገናኛ ብዙሃኑ ላይ ለመኚራኚር መሞክሩም ፓለቲካዊ መልክ ዹተሰጠውን ውዝግብ ለማብሚድ ሳይቻል ቀርቷል፡፡ ኹዚህ ውዝግብ ቀጣይ ተደርጎ ሊወሰድ ዚሚቜለው ‹á‹ˆá‹° ፍቅር ጉዞ› ዹሚል ስያሜ ዹተሰጠው ዹሙዚቃ ኮንሰርትም በበደሌ ቢራ ስፖንሰር አድራጊነት ወደ ምስራቅ ኢትዮጵያ ክልሎቜ በመጓዝ ለማሳዚት ፕሮግራም ቢዘሚጋም ኚዳግማዊ አፄ ምንሊክ ጋር ተያይዞ ‹áˆ°áŒ › በተባለ ቃለ ምልልስ ሳቢያ በደሌ ቢራ ኮንሰርቱን ሰርዞታል፡፡ በደሌ ኮንሰርቱን ለመሰሹዝ ምክንያት ዹሆነው ቎ዲ ሰጠ በተባለው ቃለ ምልልስ ሳቢያ ዚተቆጡ ወገኖቜ ‹á‰ á‹°áˆŒ ቢራን እንዳይጠጡ!› ዹሚል ዚቅስቀሳ ዘመቻ በመጀመራ቞ው እንደሆነና ኚንግድ ስራ አንፃር ኮንሰርቱን መሰሹዝ አዋጭ ሆኖ በመገኘቱ እንደሆነ ይፋ አድርጓል፡፡ ቎ዲ ዚተባለውን ቃለ ምልልስ እንዳልሰጠ፤ ይልቁንም በመፅሔቱ ዹተፈጠሹ ተራ ስህተት እንደሆነ ገልጟ ለመኚራኚር ቢሞክርም ሰሚ
ያገኘ አይመስልም፡፡ ጉዳዩ ስር እዚሰደደ ዚመምጣቱ አንዱ ማሳያ ተደርጎ ዹሚወደሰደውም ዚዘመቻው ቀስቃሟቜ ዚ቎ዲን ኮንሰርት በማሰሹዝ ብቻ ሳይገቱ ሌላም ዚመልስ ምት መሰጠት እንዳለበት ዚሚያሳስቡ ቅስቀሳዎቜ ተጠናክሹው በመሰጠታ቞ው ዚጥቁር ሰው ተነፃፃሪ ተቃራኒ ነጠላ ዘፈን በአንድ አርቲስት
ተሰርቶ ተለቋል፡፡
ይህ ዚውዝግብ አዙሪት ባልተቋጚበት ሁኔታ ኮካ ኮላ ለብራዚሉ ዹዓለም ዋንጫ በዚሀገሩ ኚሚያሰራ቞ው አርቲስቶቜ መሀኹል አንዱ አድርጎ ቎ዲን እንደመሚጠው ተሰማ፡፡቎ዲም ኚሶስት ወራት በላይ በአዲስ አበባና በኬኒያ እዚተመላለሰ ዹሙዚቃ ስራውን ሰርቶ ቢያጠናቅቅም ተመሳሳይ ቜግር መኚሰቱ ተነግሯል፡፡ በደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ብራዚል እዚተካሄደ ዹሚገኘውን ዚዘንድሮውን ዹዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ጚዋታ ምክንያት በማድሚግ እንደተለመደው ግዙፍ ዚቢዝነስ ተቋም ዹሆነው ኮካ ኮላ በተለያዩ ድምጻውያን ሙዚቃዎቜን አዘጋጅቶ ራሱን እያስተዋወቀ ነው፡፡ ሙዚቃዎቹ ዚተሰሩት በብዙ ዓይነት ቋንቋዎቜና ኚተለያዩ ሀገራት በተውጣጡ ድምጻውያን ሲሆን ዚተቀሚጹት በኮካኮላ ስቱዲዮ /Coke Studio/ ነው፡፡ ኹ30 በላይ ኹሚሆኑ ሀገራት ዚተመሚጡ ድምጻዊያን ዚሠሩት ዚዘንድሮው ዹዓለም ዋንጫ አፊሲያላዊ ዚኮካ ኮላ ሙዚቃ ‹‹The world Is our›› /አለም ዹኛ ናት/ ዹሚል ርዕስ አለው፡፡ ይሄንን ሙዚቃ በድምፅ ለመስራት ኚተመሚጡት በርካታ ዘፋኞቜ መካኚል ኢትዮጵያዊው ቎ዲ አፍሮ ይገኝበታል፡፡ እ.ኀ.አ በ2013 መገባደጃ አካባቢ ቎ዲ ለሙዚቃ ኮንሠርት ወደ ኳታር ባቀናበት ወቅት ኚኮካ ኮላ ካምፓኒ ስልክ ተደውሎ በዓለም ዋንጫው ሙዚቃ ላይ እንዲሳተፍ ተጠዹቀ፡፡ በዚህ መሠሚት ኚሌሎቜ አፍሪካውያን ድምጻውያን ጋር በጋራ ካቀነቀነው ዘፈን በተጚማሪ በአማርኛ ቋንቋ ዚተሰራና በግሉ ዚተሳተፈበት ሙዚቃ በኮካ ኮላ ስቱዲዮ መቀሚጹ ተነገሹ፡፡ ሙዚቃውም በ2014 ዚመጀመሪያ ወራት ላይ ለህዝብ እንደሚቀርብ ተገልጟ ነበር፡፡ ይሁንና በተባለበት ጊዜ ዚ቎ዲ አፍሮ ዘፈን አልተለቀቀም፡፡
tedddyበሌሎቜ ሀገራት ድምጻውያን ዚተሰሩ ዘፈኖቜ ግን በይፋ ተለቀው እዚተደመጡ ይገኛሉ፡፡ በአማርኛ ቋንቋ ዚተሰራው ዚ቎ዲ ዘፈን ግን መዘግዚቱ ሳያንስ በቅርቡ ደግሞ ሙዚቃው ኚነአካ቎ው ኚስቱዲዮ እንደማይወጣ ተሰማ፡፡ ይህን ተኚትሎ ቎ዲ አፍሮ በድሚገጹ ላይ ወጣ በተባለ ጜሁፍ ድርጊቱን ኮነነ፡፡ ዚኮካ ኮላ ካምፓኒ ድርጊት ‹‹áˆ€áŒˆáˆ«á‰œáŠ• ያዋሚደ›› ጭምር መሆኑን በመግለጜ ጉዳዩን በኹፍተኛ ሁኔታ እንደሚኚታተለው ገለጾ፡፡ ዚኮካ ኮላ ዘመቻ በአብዛኛው ዹዓለም ክፍል ዚሚታወቀው ኮካ ኮላ በዓለም ላይ 200 ኚሚበልጡ ሀገሮቜ ውስጥ ፋብሪካውን ተክሎ በቀን ኹ1.7 ቢሊዮን በላይ ዹሚሆን ጠርሙስ ኮካ ይሞጣል፡፡ መመሚት ዚተጀመሚበትን 128 ኛ ዓመት በማክበር ላይ ያለው ኮካ ኮላ ካለፈው ጥር አንስቶ እስኚ መጋቢት ባለው ሶስት ወራት ብቻ 1.5 ቢሊዮን ዶላር አትርፏል፡፡ ኮካ ኮላ በዓለም ዙሪያ ዚተለያዩ ተቃውሞዎቜ ገጥመውት ዚሚያውቁ ሲሆን ሁሉንም በማይበገሹው ዚገንዘብ ሀይሉ አሞናፊነቱን አሹጋግጩ ነው ዚተወጣው፡፡ ኚአሚብ እስራኀሎቜ ጊርነት በኋላ በአሚቡ ዓለም በታዚው ዹፀሹ እስራኀል ዘመቻ ላይ ተሳታፊ ዹሆኑ ዚአብዛኛዎቹ አሚብ ሀገራት ኮካ ኮላን ባለመጠጣት ለፍልስጀሞቜ ያላ቞ውን አጋርነት ለማሳዚት ጥሚዋል፡፡ አሚቊቹ ኮካ ኮላን ባለመጠጣት ብቻ ሳይወሰኑ ፊታ቞ውን ወደ ፔፕሲ አዙሹዋል፡፡ ያም ሆኖ ግን ይህ ዘመቻ ዚኮካ ኮላን ገበያ ዚሚፈታተንና ኚገበያ ዚሚያስወጣ ስላልነበሚ በማስታወቂያው ላይ ባፈሰሰው ኹፍተኛ በጀት ዚዓለማቜን ቀዳሚ ለስላሳ መጠጥነቱን አስኚብሮ ለመቆዚት ቜሏል፡፡ እ.እ.አ በ1950ዎቹ አጋማሜ ላይም ዚህንድ ገበሬዎቜ ኮካ ኮላ ለማሳቜን ዚሚያስፈልገንን ውሃ ተሞማብን በማለት ኮካ ኮላን ባለመጠጣት ተቃውሟቾውን ለማሳዚት ሞክሹዋል፡፡ በዓመት 11 ቢሊዮን ዶላር ለማስታወቂያ ብቻ ዚሚያወጣው ኮካ ኮላ ንፁህ ዚመጠጥ ውሃን በማውጣትና ዙሪያ ለሚሰሩ ፕሮጀክቶቜ ዚሚመድበውን ማህበራዊ በጀት ወደ 50 ሚሊዮን ዶላር በማሳደግ ራሱን ኚህንድ አርሶ አደሮቜ ዘመቻ ተኹላክሏል፡፡
ዚኮካ ኮላ ዹአቀማመም ምስጢር ድብቅነቱን ተኚትሎ ሱስ አስያዥ ቅመም እንዳለውና ለጀናም አደገኛ ስለመሆኑ ዚተወራበት ጊዜ ነበር፡፡ ሌላው ቀርቶም ሰዎቜን ሱስ ዚሚያሲይዝ ዚኮኬይን ቅመም እንዳለው ሲነገር ኮካ ኮላ ግን ይህ መሰሹተ ቢስ ወሬ ነው ሲል አስተባብሏል፡፡ያም ሆኖ ኮካ ኮላ አሁንም
ድሚስ በብዙ ሀገሮቜ ውስጥ ተወዳጅ መጠጥ ቢሆንም እንደ ሰሜን ኮሪያ በርማና ኩባ አይነት ሀገሮቜ ኮካ ኮላ ፋብሪካ በሀገሮቻ቞ው እንዲቋቋም ያልፈቀዱ ሀገራት ናቾው፡፡እ.ኀ.አ በግንቊት 8 ቀን 1886 በአትላንታ ጆርጂያ ለራስ ምታት መድሃኒት ይሆናል ብሎ መድሃኒት ቀማሚው ጆን ኀስ ቮምበር ኚካካዋ ፍሬ በሶዳ ውሃ በጥብጊ ያዘጋጀው ኮካ ኮላ ዚተባለው መጠጥ ይኾው ዛሬ በመላው ዓለም ይጠጣል፡፡ በወቅቱ ድካምንና ራስ ምታትን እንዲሁም ድብርትንና ዚወንዶቜን ዚወሲብ ፍላጎት ያነሳሳል በሚል ዹተቀመመው ኮካ ኮላ በአዲስ መልኩ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ምስጢራዊነቱን ጠብቆ መመሚት ኹጀመሹ እነሆ ዘንድሮ 120 ዓመታት ሆኖታል፡፡
ዘመቻ ‹‹áŠ®áŠ« አትጠጡ››á‹šá‹µáˆáŒ»á‹Šá‹ አድናቂዎቜና በሁኔታው ስሜታቜን ተነክቷል ያሉ ሰዎቜ በማህበራዊ ድሚገፆቜ አማካኝነት በኮካ ኮላ ካምፓኒ ላይ መቀዹማቾውን ዚሚያሳዩ ምስሎቜንና ጜሁፎቜን ለጠፉ፡፡ ዚካምፓኒውን ምርቶቜ ባለመጠጣት ተቃውሞአቾውን ለማሰማት ዛቱ፡፡ በተግባር ጉዳዩ ለመፈጾሙ
ማሚጋገጫ ባናገኝም በ቎ዲና በኮካ ኮላ መካኚል ዹተፈጠሹው ውዝግብ አበሳጭቷ቞ው ኚኮካ ምርቶቜ ዚታቀቡ ሊኖሩ እንደሚቜሉ መገመት ግን አያዳግትም፡፡ በተለይ በማህበራዊ ገፆቜ ላይ በተደጋጋሚ ሲጻፍ ዹነበሹውን ‹‹á€áˆš-ኮካ›› ዘመቻ ዚቅስቀሳ መልዕክቶቜ ስንመለት ዚተባለው ድርጊት መጚሚሻው ዚት ነው እንድንል ይገፋናል፡፡ ዹሙዚቃው አለመለቀቅ ‹‹áˆ€áŒˆáˆ«á‰œáŠ• ኹመናቅ›› ዚመጣ ነው ኹሚል ሀሳብ ጋር አያይዞ ድምፃዊው ቅሬታውን መግለጹ ተቃውሞውን እንዲደምቅ አድርጎታል፡፡ በ቎ዲ አፍሮ ዹግል ድሚገጜ ላይ ወጣ ዚተባለው መግለጫ እንዲህ ይላል፡፡‹‹áˆµáˆˆ ዓለም ዋንጫ ዚኢትዮጵያ ቅጂ ሙዚቃ
ዹተሰጠ መግለጫ ባለፉት ወራቶቜ ቎ዎድሮስ ካሳሁን ወይም ‹‹á‰Žá‹² አፍሮ›› ኚኮካ ኮላ እና በስፋት ሲወራ ኹኹሹመው ዹዓለም ዋንጫ ዚኢትዮጵያ ቅጂ ሙዚቃ ጋር ስለነበሚው ግንኙነት ያለንን አቋም እንድንገልፅ ሚርፍልን ጥያቄዎቜ ምክኒያት ኹፍተኛ ጫና ሲደሚግብን ቆይተናል፡፡ በበኩላቜን በተገባው ዹውል ስምምነት ላይ ግንኙነቱን ሚጥራዊነት ለመጠበቅ ቃል ኪዳን ዚገባ እና ማክበር ዚነበሚብን ቢሆንም ቅሉ ዚ቎ዲ አፍሮ እና ዚኮካ ግንኙነት ወሬ እንዎት አፈትልኮ ወጥቶ ህዝብ እንዲያውቀወው እንደቻለ ቢያስገርመንም አሁን ለመገንዘብ እንደቻልነው ዚ቎ዲ ኚኮካ ጋር ያለው ግንኙነት ኢትዮፒካል ንክ
በተሰኘ ዹሀገር ውስጥ ዚኀፍ.ኀም ሬዲዮ ዹመዝኛ ፕሮግራም አዘጋጆቜ አማካኝነት ያወጀው እና በሚያስገርም ሁኔታ ለኮካ ዚቲቪ ሥራም አድናቆቱን በመስጠት ያሚጋገጠው ዚኮካ ኮላ ዚኢትዮጵያ እና ዚኀርትራ ብራንድ ሥራ አስኪያጅ ዹሆነው አቶ ምስክር ሙሉጌታ መሆኑን መሚዳት ቜለናል፡፡
ያለጥርጥር በኮካ ኮላ ስም ቎ዲ አፍሮ ለኮካ ዚ቎ሌቪዥን ስራ በማገናኘት እና በዓለም ዋንጫ ዚኢትዮጵያ ቅጂ ሙዚቃ ላይ ተሳታፊ እንዲሆን ተነሳሜነቱን ዹወሰደው ዚብራንዱ ሥራ አስኪያጅ ነበር፡፡ እኛም ጥያቄን ውድ አገራቜንን በመላው ዹዓም ዋንጫ ተመልካ቟ቜ ዘንድ አዎንታዊ ገፅታ ዚትኩሚት እይታ ስር ዚሚያውላት በመሆኑ እና በዚህ በጉጉት በሚጠበቀው ታላቅ ዓለም አቀፍ ዚስፖርት ኹንዋኔ ግዙፍ ቁጥር ያለው ዹዓለም ህዝብ ዘንድ ዚአገራቜንን እና ዚህዝባቜንን መልካም ገፆቜ ለማሳዚት ዚበኩላቜንን አስተዋፅኊ ኹተሟጠጠ በኋላ ነበር፡፡በመጚሚሻም ምንም እንኳን በጉዳዩ ጭብጥ ዙሪያ በሁለቱም ወገኖቜ ዘንድ ስለተያዘው አቋም ዹተወሰነ መግባባት ላይ መድሚስ ቎ሌኮንፈሚንስ ዚሚመለኚታ቞ው ወገኖቜ እንደሚገኙበት ቃል ተገብቶበት ዹተዘጋጀ ቢሆንም ውይይቱ ሙያዊ በሆነ መልኩ ያልተዘጋጀ፣ ግልፅነት ዹጎደለው፣ አለመግባባት እንዳይኚሰት ለማድሚግ ዚጋራ መፍትሔ ለመሻት ሳይሆን ቅንነት በጎደለው መልኩ ዹኛን ሐሳብ ለመሚዳት ነበር፡፡ ቎ሌኮንፈሚንሱ ሆነ ተብሎ ህጋዊ ወኪል ዹሆነውን ሥራ አስኪያጃቜንን በጭብጊቹ ላይ ለመወያዚት እንዳይሳተፍ በማግለል መካሄዱ በራሱ ሂደቱ በቅን ልቩና ላይ ያለተመሰሚተ መሆኑ ግልፅ ማስሚጃ ነው፡፡ በመሆኑም ዚአርቲስቱ አድናቂ ለሆኑት ኢትዮጵያዊያን እና ዚውጪ አገር ዜጎቜ በሙሉ ኚኮካ ኮላ ጋር ዹነበሹንን ግንኙነት ያቋሚጥን መሆናቜንን ለመግለፅ መገደዳቜን እያዘንን ስንገልፅ ዹዓለም ዋንጫ እስኚሚኚፈትበት ዕለት ድሚስ ኮካ ኮላ ዹወሰደውን እርምጃ በድጋሚ እንዲያጀነው ያደርግ ዘንድ በተደጋጋሚ ጥሪያቜንን ስናቀርብ ብሔራዊ ጠርዝ ባለው እና በውድ አገራቜን፤ በህዝባቜን እና አድናቂዎቻቜን ላይ ጭምር ዚተቃጣውን ዚፈሪ እና ሀገር ወዳድነት ዹጎደለው አሳፋሪ ዚክህደት እና ክብር ዚሚያጎድፈውን ተግባር ግን ይቅር ላለማለት ወስነናል፡፡
ኹዚህ በተጚማሪ አስኚመጚሚሻው ዕለት ድሚስ ኮካ ኮላ ዹተጠናቀቀውን ሥራ እንዲያሰራጚው እና እንዲለቀው ግፊት ማድሚጋቜንን እንደምንቀጥልበት ለአድናቂዎቻቜን እያሚጋገጥን ኹዚህ ጎን ለጎንም ኚሁኔታዎቜ ጋር አግባብነት ያላ቞ው ሰላማዊ እርምጃዎቜን በመውሰድ ዚሁለቱንም ወገኖቜ ገፅታን እና ጥቅምን ዚሚጎዳ ማናቾውም ውዝግብ በማስቀሚት በአድናቂዎቻቜን ዚተጣሉብንን አደራ መተማመን እና እምነት ለመመለስ ዚሚያስቜል እርምጃ ዚምንወስድ መሆናቜንን እንገልፃለን፡፡›› ቢቀር ምን ይቀርበታል? ድምፃዊ ቎ዎድሮስ ካሳሁን /቎ዲ አፍሮ/ ኚኮካ ኮላ ዚቀሚበለትን ጥያቄ በደስታ ተቀብሎ ዹዓለም
ዋንጫውን ዚኢትዮጵያ ቅጂ ሙዚቃ ናይሮቢ ኬንያ ውስጥ በሚገኘው ዚኮካ ኮላ ስቱዲዮ ተቀርጿል፡፡ ታድያስ መጜሔት ኚአሜሪካ እንደዘገበው ኹሆነ ደግሞ ሙዚቃው እንደማይለቀቅ ኹተነገሹ በኋላም ኮካ ለድምጻዊው ተገቢውን ዚካሳ ክፍያ ለመፈጾም መዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡ ዹተቀሹፀው ሙዚቃ ንብሚትነቱ ዹኔ ብቻ ነው ዹሚለው ግዙፉ ዚለስላሳ መጠጥ ካምፓኒ ለጊዜው ዘፈኑ ባይለቀቅም ለድምፃዊው ግን ተገቢውን ነገር እናደርጋለን ዹሚል መግለጫ አውጥቷል፡፡ ኹዚህ አንፃር ኚተመለኚትነው ቎ዲ ሙዚቃው ባለመለቀቁ ምንም አይቀርበትም ማለት እንቜላለን፡፡ ነገር ግን ድምጻዊው ኚሚያገኘው ገንዘብ ባሻገር ኢትዮጵያ በዓለም ፊት ዚምትታወቅበትን ዕድል አጥታለቜ፡፡ ቎ዲም ቢሆን ዚደኚመበት ሙዚቃ ኚስቱዲዮ አለመውጣቱ ም቟ት ይነሳዋል፡፡ ለምን ብሎ መጠዹቁም ተገቢ መሆኑን ዚብዙዎቹ አድናቂዎቜ ሀሳብ ነው፡፡
‹‹áˆŸáˆ‹ በድፍን››
ኮካ በዓለም ዋንጫ ውድድሮቜ ላይ ራሱን ለማስተዋወቅ ዚሚሚዱ ሙዚቃዎቜ ሲያዘጋጅ ዚዘንድሮው ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ ኹዚህ በፊት ደቡብ አፍሪካ ላይ ለተኹናወነው ዹዓለም ዋንጫ ‹‹waving Flag›› በሚል ርዕስ ሶማሊያዊው ድምጻዊ ኬናንን ጚምሮ በተለያዩ ሀገራት ድምፃውያን አሰርቷል፡፡
በወቅቱ ይህ ሙዚቃ ተወዳጅ እንደነበር ይታወሳል፡፡ዹዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር አጋር ዹሆነው ኮካ ለዘንድሮው ዹዓለም ዋንጫ ማጀቢያ ዹሚሆን ሙዚቃ በራሱ ስቱዲዮ መቅሚጜ ዹጀመሹው ባለፈው ዓመት ነበር፡፡ ሳምባ በሚባለው ዚብራዚሎቜ ባህላዊ ዹሙዚቃ ስልት ዚተሰራው ‹‹The World Is Our›› ዹተሰኘው ሙዚቃ በተለያዩ ሀገራት ሙዚቀኞቜና በተለያዩ ቋንቋዎቜ ተዘጋጅቷል፡፡ ዹዚህ ሙዚቃ ዋና አቀንቃኝ በትውልድ ብራዚላዊ በዜግነት ደግሞ አሜሪካዊ ዹሆነው ዎቪድ ኮሬይ ሲሆን ካለፈው መስኚሚም ጀምሮ ኹ90 በላይ በሚሆኑ ሀገራት ተዘዋውሮ ሙዚቃውን መድሚክ ላይ ተጫውቷል፡፡
በዲቪድ ኮሬይ በዋናነት ዚተሰራው ይህ ዚኮካ ኮላ ሙዚቃ በሌሎቜ ሀገራት ድምጻውያን በተለያዩ ቋንቋዎቜ ተቀርጟ ለጆሮ በቅቷል፡፡ ኚስቱዲዮ ያልወጣው ዚ቎ዲ አፍሮ ብቻ ነው፡፡ ለምን? እስካሁን መልስ ዹለውም፡፡ ዚኮካ ኮላ ሰዎቜ ኚአትላንታ ሰጡት በተባለው መግለጫና ቎ዲ አፍሮ በድሚ ገፁ ባሰፈሚው ጜሁፍ ሙዚቃው ስላለመለቀቁ እንጅ በምን ምክንያት እንደሆን አይጠቅሱም፡፡ ነገሩ ‹‹áˆŸáˆ‹ በድፍን›› ሆኗል፡፡ ስለዚህ ኹሁሉም ነገር በፊት ሙዚቃው ያልተለቀቀው በምን ምክንያት ነው? ብሎ መጠዹቅ አስፈላጊ ይሆናል፡፡
‹áŠ®áŠ« ሀገሪቷን ደፍሯል?›
቎ዲ አፍሮ በርካታ አድናቂዎቜ ካሏ቞ው አትዮጵያዊያን ዹሙዚቃ ሰዎቜ መካኚል አንዱ ነው፡፡ ለኮካ ኮላ ሙዚቃ ሊሠራ ነው ተብሎ ሲነገር እንደ አንድ በሀገር ኩራት ተቆጥሮ በመገናኛ ብዙሀን ሲዘወርለት ነበር፡፡ ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ተጠግቶ ኹነበሹው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ጋር ተነጻጜሮ ሲቀርብ ነበር፡፡ ‹‹áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹«áŠ• በብራዚሉ ዹዓለም ዋንጫ ዹሚወክለው›› ዹሚል መንደርደሪያ ኚስሙ በፊት መጠቀስ ጀምሮ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ሙዚቃው አለመለቀቁ በዚያ ሁሉ ሙቀት ላይ በሚዶ እንደመጚመር ነው፡፡ ለዚያምነው በማህበራዊ ድሚገፆቜ ‹‹áŠ®áŠ« ኮላ አትጠጡ›› ዹሚሉ ኢትዮጵያዊያን በብዛት ብቅ ማለታ቞ው፡፡ ቎ዲ አፍሮ ኢትዮጵያን ወክሎ ኹተጋዘበና ሙዚቃው በስቱዲዮ ኹተቀሹጾ በኋላ እዚያው ታፍኖ መቅሚቱ ‹‹áŠ­á‰¥áˆš ነክ›› መሆኑን እዚገለጹ ነው፡፡ ‹‹áˆ€áŒˆáˆ­ ተደፍራለቜ›› ዹሚሉ ሀሳቊቜ በስፋት እዚተነሱ ነው፡፡ በጉዳዩ ላይ መንግስት እጁንእንዲያስገባ ዹጠዹቁም ነበሩ፡፡ ጉዳዩ ግን ዚሁለት አካላት ስምምነት ዹሚጠይቅ ነው፡፡ ሀገራዊ አጀንዳ ለመሆን ግን አይበቃም፡፡ ተራ ዚቢዝነስ ስምምነትና ኚዚያ ጋር ተያይዞ ዹተኹሰተ ዹውል መፍሚስ ነው ዹሚሉም ወገኖቜ አሉ፡፡
ኮካ ኮላ እንደአንድ ዚንግድ ተቋም ኚድምጻዊ ቎ዲ አፍሮ ጋር ዚስራ ስምምነት አድርጓል፡፡ በስምምነቱ መሠሚት ተፈጻሚ ያልሆኑ ነገሮቜ ካሉ ቎ዲ አፍሮ ህጋዊ ጥያቄ ማንሳት ይቜላል፡፡ ይሄን ለማድሚግም ዝግጁ መሆኑን ገልጿል፡፡ እንዎት ተሠራ?ኮካ ኮላ ለዘንድሮው ዹዓለም ዋንጫ ሙዚቃ መሪ ድምጻዊ አድርጎ ዹመሹጠው ዎቪድ ኮሬይን ነው፡፡ ይህ ድምጻዊ ኚተለያዩ ሀገራት ድምፃዊያን ጋር ዚዚሀገራቱን ቋንቋ በመጠቀም በጋራ ሙዚቃውን ሰርቷል፡፡ ኹ30 በላይ ኹሚሆኑ ድምጻውያን ጋር በዚያው ቁጥር ልክ አንዱን ሙዚቃ ደጋግሞ ተጫውቷል፡፡ ይሄን ዕድል ካገኙ ድምፃዊያን መካኚል ቎ዲ አፍሮ አንዱ ነው፡፡ ዚኢትዮጵያ ቅጅ ዹሆነውን ሙዚቃ ዎቪድ ኮሬይና ቎ዲ በጋራ ቀርፀዋል፡፡ ኮካ ኮላ በተለያዩ ሀገራት ዹሙዚቃ ስቱዲዮዎቜ አሉት፡፡ ዚ቎ዲ አፍሮና ዚሌሎቜ አፍሪካውያን ድምጻዊያን ሙዚቃ ዹተቀሹፀው ናይሮቢ በሚኘው ዚኮካ ኮላ ስቱዲዮ ሲሆን ጉዳዩን ዚሚኚታተለውና ዚሚያስፈጜመው ደግሞ ማንዳላ ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያ ነው፡፡ ጣቢያው ግን ሙዚቃውን ‹á‹šá‹áˆ€ ሜታ› አደሹገው፡፡መጚሚሻው ምን ይሆን?
ለዚህ ጥያ቎ ምላሜ መስጠት ኚባድ ሊሆን ይቜላል፡፡ ሙዚቃው ኚስቱዲዮ እንዳይወጣ ዚተደሚገበትን ምክንያት አለማወቃቜን ኚግምት ያለፈ እንዳንናገር ያስገድደናል፡፡ኮካ ኮላ ትልቅ ዚንግድ ስም ነው፡፡ በሀገራቜን በብዛት ኚሚዘወተሩ ዚለስላሳ መጠጊቜ መካኚል አንዱ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ድምጻዊ ቎ዲ
አፍሮ ደግሞ ብዙ አድናቂዎቜ ካሏ቞ው ዹሙዚቃ ሰዎቜ አንዱ እንደመሆኑ መጠን ኮካ ኮላ በገበያው ላይ ዚሚደርስበትን ተጜዕኖ በመፍራት ቜግሩን እልባት ይሰጠዋል ብለን መገመት እንቜል ይሆናል፡፡በማህበራዊ ድሚገፆቜ ‹‹á€áˆš ኮካ›› ዘመቻ ዚጀመሩ ዚ቎ዲ አድናቂዎቜ ዚካምፓኒውን ስም ሊጎዱ ዚሚቜሉ ሀተታዎቜንም ደጋግመው እያስነበቡ ነው፡፡ ኮካ ለጀና ጠንቅ ዹሆነ ንጥሚ ነገሮቜ እንዳሉት በመግለጜና ዚ቎ዲ አፍሮ ሙዚቃ ያልተለቀቀው ካምፓኒው ለኢትዮጵያ ካለው ንቀት ዚተነሳ መሆኑን በመዘርዘር አድማ እዚቀሰቀሱ ነው፡፡
ይህን ስንመለኚት ካምፓኒው በኢትዮጵያ ያለውን ተቀባይነት ላለማጣትና ስሙን ለመጠበቅ ሲል ‹á‹šá‰³áˆáŠá‹áŠ• ሙዚቃ› ሊለቀው ይቜላል፡፡

Mar 1, 2014

ዚኢትዮጵያን ለኢትዮጵያ ወይም ዚወያኔን ለወያኔ

 á‰ áŠ áŠ•á‹µ ወቅትአንድ ዘጋቢ á‹šáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹«áŠ• á‰£áŠ•á‹²áˆ«  á‰ áˆšáˆ˜áˆˆáŠšá‰µ ተዘዋውሮ ካናገራ቞ው ዚመዲናይቱ ነዋሪዎቜ አንዱ፥ “እኛ አገራቜንን ዹምንወደው á‹ˆá‹«áŠ”á‹Žá‰œ ስለነገሩን አይደለም።  áŠ¥áˆ±áˆ› ባንዲራቜንን ባጥላሉበት ዘመንም አገራቜንን እንወድ ነበር፤ አሁንም እንወዳለን፤ ወደፊትም እንወዳለን። ይህ በደማቜን ውስጥ ያለና መቌም ቢሆን ኚልባቜን ሊወገድ ዚማይቜል ነገር ነው፤” ብለው áŠ¥áŠ•á‹°áŠá‰ áˆ­ áŠ áˆµá‰³á‹áˆ³áˆˆá‹ ።
ወያኔ ወደ ሥልጣን ዚመጣው ዚኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ እያጋዚ ነበር። በመጣም በነጋታው ሕገ-መንግሥ቎ ዹሚለውን መጹቆኛ መሣሪያ ለማጜደቁ ኑ ብሎ በጠራ቞ው ዚሱ ብጀ ዘሚኞቜ ስብሰባ ላይ ሰንደቅ ዓላማቜን፣ ሲዋሚድ፣ ሲብጠሚጠር እንደነበር ለታሪክ ዩ-ትዩብ በተባለው ዹዘመኑ ዚድምጜና ዚተንቀሳቃሜ ስዕል ማሳያ ዚድሚ ገጜ ማሳያ ላይ ለሕብሚተሰቡ ለዕይታ በቅቶ ይገኛል።
ሰንደቅ ዓላማቜን እንዳገራቜን እራሷ ባለታሪክ ናት። ሰንደቅ ዓላማቜን፣ እነሱ እንዳሏት “ጹርቅ” ብቻ ሳትሆን ስንት ደም ዚፈሰሰባት ወድቃ ዚተነሳቜ ልዩ ዚታሪካቜን መዘክርና ዚማንነታቜን ማብሰሪያ ሰንደቅ ናት።
ይቜን á‹«áŠ­áˆ áˆ°áˆˆá‰£áŠ•á‹²áˆ«á‰œáŠ• áŠ«áˆáŠ© áŠ¥áˆµá‰² áˆ›áˆˆá‰µ á‹ˆá‹°áˆáˆˆáŒˆáŠ©á‰µ áŠáŒˆáˆ­ áˆáˆ‚ድ ፦ áˆˆá‰¥á‹™ áŒá‹œ áˆ˜áˆáˆµ á‹«áˆ‹áŒˆáŠ˜á‹áˆˆá‰µ áŒ¥á‹«á‰„ áŠá‹ á‹­áˆ… á‰ á‹šáˆ… áˆáˆµáˆ áˆ‹á‹­
ዚሚታዚው. Ebbelsgata1,.0183Oslo.Norway á‹«áˆˆ á‹šá‹ˆá‹«áŠ” á‰µáŠ¬á‰µ áŠŠáŠáˆµ áŠá‹ ።
ባንዲራውንም áŒšáˆáˆ®  áˆ›áˆˆá‰µ áŠá‹ ። á‹šáˆ›áŠ• áŠá‹ á‹šáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« áŠ á‹šáˆ­ áˆ˜áŠ•áŒˆá‹µ á‹ˆá‹­áˆµ á‹šá‹ˆá‹«áŠ”áŠ á‹šáˆ­ áˆ˜áŠ•áŒˆá‹µ á‰£áŒ‹áŒ£áˆš á‰ á‹šáˆ… á‰ áŠ©áˆ á‰£áˆˆááŠ©
ቁጥር á‹«á‹ á‹šáˆšá‰³á‹šáŠ áŠáŒˆáˆ­ ቢኖር á‹šáŠ¥áŠá‹šáˆ… áŒšáŠ«áŠ á‹šáˆ°á‹ áŠ á‹áˆ¬ áˆ†á‹³áˆžá‰œ ኢትዮጵያን እዚመዘበሚና እዚገዛ á‹«áˆˆ ሌባ ቀማኛና ሰዶማዊ አገዛዝ  á‹ˆá‹­áŠ•áˆ á‹°áŒáˆž á‹˜áˆšáŠáŠá‰µ áŠ§áˆš áˆµáŠ•á‰± ነገር á‰°áŠáŒˆáˆ® á‹šáˆ›á‹«áˆá‰… áˆ˜áŒ¥áŽ á‰µá‹á‰³á‹Žá‰œ á‰¥á‰»
 ፦ áŠ¥áˆµá‰² áˆ˜áˆˆáˆµ á‰¥áˆˆáŠ• áŠ¥áŠ“áˆµá‰¥ á‹šá‹ˆá‹«áŠ” áˆ˜áŠ•áŒáˆµá‰µ á‰£áˆ³áˆˆááŠá‹23 á‹“መት á‹áˆµáŒ¥ á‰ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« áˆ…ዝብ áˆ‹á‹­ áˆáŠ• áŠ á‹­áŠá‰µ áŒ¢á‰£áŒ¢á‰€
 áŠ¥á‹šá‰°áŒ«á‹ˆá‰°á‰ á‰µ áŠ¥áŠ•á‹°áˆ†áŠ áˆ˜á‰Œáˆ á‰ á‹šá‰€áŠ‘ áŠ¥á‹«á‹°áˆšáŒˆ á‰£áˆˆá‹ á‹ˆá‹­áˆ áŠ¥á‹«á‹šáŠ•á‰£áˆˆá‹áŠáŒˆáˆ­ áˆ˜á‰Œáˆ áˆ³áŠ•á‰ áˆ³áŒ­ á‹šá‰€áˆšáŠ• áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹«á‹Š áˆá‹µáˆ© 
ይቁጠሹን áŒáŠ• áŠ¥áˆµáŠšáˆ˜á‰Œ  á‹µáˆšáˆµ áŠ¥áˆµáŠšáˆ˜á‰Œáˆµ áŠá‹ á‰ áˆ›áŠ“áˆáŠ•á‰ á‰µ áŠ¥áŠ“ á‰ áˆáŠ•áŒ áˆ‹á‹ áŠáŒˆáˆ­ áˆ‹á‹­ áˆ˜á‹ˆáˆ°áŠ• á‹šáˆ›áŠ•á‰œáˆˆá‹
-ወደ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« áˆˆáˆ˜áˆ„ድ á‹šáŒá‹µ á‹šá‹šáˆ… á‹šá‹ˆá‹«áŠ” á‰µáŠ¬á‰µ áŠŠáŠáˆµ á‰¥á‰» áŠá‹ á‹«áˆˆá‹ ?
-ወያኔን áˆ˜á‰ƒá‹ˆáˆ áŠ«áˆˆá‰¥áŠ•áˆµ á‰ áˆ›áŠ•áŠ›á‹áˆáŠ“ á‰ áˆáŠ•á‰œáˆˆá‹ áˆ˜áŠ•áŒˆá‹µ áˆ˜áˆ†áŠ‘áŠ• áˆšáˆµá‰°áŠá‹‹áˆ áˆ›áˆˆá‰µ ነው ?
-ወይስ á‹šáˆƒáŒˆáˆ­ áŠ¢áŠ®áŠ–áˆš áˆáŠ“ áˆáŠ•  áŠ§á‰£áŠ«á‰œáˆ áŠ¥áŠ•á‹³á‰µáˆ‰áŠ á‹ˆá‹«áŠ”á‹Žá‰œ áŒ¢á‰£áŒ¢á‰€ á‹šá‰°áŒ«á‹ˆá‰±á‰¥áŠ• á‹­á‰ á‰ƒáŠ“áˆ áˆˆáŠáŒˆáˆ©  áŠ¥á‹µáŒˆá‰µáŠ¥áŠ® 11% lol በመቶ ????
 á‰ á‰µáŠ•áˆ¹ áˆ›á‹µáˆšáŒ á‹«áˆá‰»áˆáŠá‹áŠ• áŠ¥áŠ•á‹Žá‰µ á‰ á‰µáˆá‰ áˆ›á‹µáˆšáŒ áŠ¥áŠ•á‰œáˆ‹áˆˆáŠ•?
እስኚ áˆ˜á‰Œ á‹µáˆšáˆµ áŠá‹ áŠ¥áŠá‹šáˆ… áˆ°á‹Žá‰œáˆµ á‰ áŠ¥áŠ•á‹°á‹šáˆ…áˆáŠ”á‰³ á‹šáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« áˆ…ዝብ  áŠ¥áŠ“ á‰£áŠ•á‹²áˆ«á‹‹ áˆ‹á‹­ á‰ áŠ¥áŠ•á‹²áˆ… áŠ á‹­áŠá‰µ መልኩ á‹šáˆšá‰€áˆá‹±á‰µ   áŠ¥áˆµá‰² á‰°áˆ˜áˆáŠšá‰±á‰µ áŠšá‹šáˆ… á‰ á‰³á‰œ á‹«áˆˆá‹áŠ• áŽá‰¶ á‹šáˆ›áŠ• áŠá‹ á‹šá‰„ሳርን áˆˆá‰„ሳር á‹šáˆ•ግዚኃብሔርን áˆˆáˆ•ግዚኃብሔር áŠ á‹­á‹°áˆ
እንግዲያውንስ á‹šáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹«áŠ• áˆˆáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« á‹ˆá‹­áˆ á‹šá‹ˆá‹«áŠ”áŠ• áˆˆá‹ˆá‹«áŠ”

 

Jan 23, 2014

Ethiopian stand on gay adoption !!



In a recent article in Times of Malta about gay couples adopting children, I discovered anew how pharisaical people’s ignorance and hypocrisy can be. One sentence reads: “Countries like Ethiopia had been closing doors on adoptions for Maltese because of fears that prospective single parents could be gay.”
Ethiopians, renowned for their inability to govern themselves and for living in the second poorest country in the world despite being one of the richest in mineral resources like gold, potash, copper, platinum and natural gas, are closing doors on adoptions by Maltese parents because these might be homosexual.
A country ravaged by illiteracy, corruption, child prostitution and political instability still has the damnable effrontery to pontificate on the sexual orientation of a few good souls willing to take starving Ethiopian foundlings into their care.
If this doesn’t win an award as one of the most banal acts of immorality ever to find its way into State policy, nothing will.
It is staggering that African nations only too willing to accept handouts and ‘aid’ from developed countries that endorse homosexuality will recoil in horror at one of their own being cared for by a gay couple.
Those African politicians who are so morally bankrupt that they will boast of being on the take and even hold ‘bribery auctions’ do not have the right to stand in the way of individuals whose only failings are being gay and wanting to give a few children a better life.

በሰብአዊ መብት አያያዝ አደጋ ላይ ዹወደቀው ዚኢትዮጵያ ገፅታ አሁን ደግሞ ተባብሷል ይለናል Human Right Watch በ2014



በሰብአዊ መብት አያያዝ አደጋ ላይ ዹወደቀው ዚኢትዮጵያ ገፅታ አሁን ደግሞ ተባብሷል ይለናል Human Right Watch በ2014 ዹዓለም ዚሰብአዊ መብቶቜ ሁኔታ ሪፖርቱ፡-ኢትዮጵያ

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እ.ኀ.አ በነሀሮ ወር 2012 ዓ.ም. መሞታ቞ውን ተኚትሎ በኢትዮጵያ ዚተተካው አዲሱ አመራር ሰብዓዊ መብቶቜን ዚሚመለኚቱ ማሻሻያዎቜ እንደሚያደርግ ተጥሎ ዹነበሹው ተስፋ ተዳፍኗል፤ በ2013 ዓ.ም ተጚባጭ ዹሆነ ዚፖሊሲ ለውጥ አልታዚም፡፡ ይልቁንም ዚኢትዮጵያ ባለስልጣናት ሃሳብን ዚመግለጜ፣ ዚመደራጀት እና በሰላም ዚመሰብሰብ ነጻነት ላይ ዚጣሉትን ጥብቅ ገደብ ማስፈጞማ቞ውን ዚቀጠሉበት ሲሆን ዚሲቪል ማህበራትን እና ነጻ መገናኛ ብዙሃንን እንቅስቃሎ ለማዳኚም አፋኝ ሕጎቜን ይጠቀማሉ፤ግለሰቊቜንም ፖለቲካዊ መነሟ ያላ቞ውን ክሶቜ በመመስሚት ዚጥቃት ዒላማ ያደርጋሉ።
መንግስት በሃይማኖታዊ ጉዳዮቻ቞ው ላይ ጣልቃ መግባቱን ዹተቃወሙ ሙስሊሞቜ ዓመቱን ሙሉ በጞጥታ ሃይሎቜ ዹዘፈቀደ እስር፣ እገታ፣ ድብደባ እና ሌሎቜ ተገቢ ያልሆኑ አያያዞቜ ተፈፅሞባ቞ዋል፡፡ በሐምሌ ወር 2012 ዓ.ም. ዚታሰሩት 29ኙ ዹተቃውሞው መሪዎቜ ዚፍርድ ሂደት ኚጥር ወር 2013 ጀምሮ ለህዝብ፣ ለመገናኛ ብዙሃን፣ እና ለቀተሰብ አባላት ዝግ ተደርጓል፡፡ እጅግ አወዛጋቢና መሠሚታዊ ግድፈት ያለባ቞ውን ድንጋጌዎቜ በያዘው ዚሃገሪቱ ዹጾሹ ሜብርተኝነት ህግ መሰሚት ጥፋተኛ ዚተባሉ ዹተቃዋሚ መሪዎቜ እንዲሁም አራት ጋዜጠኞቜ አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡
ኹሃገር ውስጥ በሚገኝ ገቢ እና ኹውጭ በሚመጣ እርዳታ በሚደገፉ ስፋት ያላ቞ው ዚልማት ፕሮግራሞቜ አፈጻጞም ምክንያት ዚአንዳንድ ማህበሚሰብ ተወላጅ ነዋሪዎቜ ያለበቂ ምክክር ወይም ምንም አይነት ካሳ ሳይኚፈላ቞ው ኚመኖርያ቞ው እንዲፈናቀሉ ይደሹጋል፡፡ ዚጞጥታ ሃይሎቜ ነዋሪዎቜን ኚመኖሪያ ቀያ቞ው አንስተው ወደ ሌላ ቊታ ለማስፈር ሃይል፣ ማስፈራሪያ እና ዛቻ ይፈጾማሉ፤ ለምሳሌ በታቜኛው ዹኩሞ ሾለቆ ዹሚገኙ ተወላጅ ነዋሪዎቜ ለዘመናት ዚኖሩበት መሬት መንግስት ለሚያካሂደው ዚስኳር መስኖ ልማት ይፈለጋል በሚል መፈናቀላቾው እንደቀጠለ ነው። በሰላም ዚመሰብሰብ ነጻነት ኹ2012 ዓ.ም. ጀምሮ ኚሀገሪቱ አጠቃላይ ህዝብ ቢያንስ 30 በመቶ ዹሚሆነውን ቁጥር ዚሚይዙት ዚኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበሚሰብ አባላት ተኚታታይ ህዝባዊ ተቃውሞ አድርገዋል፡፡ ዹተቃውሞው መነሻ ምክንያት መንግስት በእስልምና ጉዳዮቜ ኹፍተኛ ምክር ቀት ውስጥ እና በአዲስ አበባ በሚገኘው ዚአወሊያ መስጊድ ላይ ይፈጜማል ዚተባለውን ጣልቃ ገብነት በመቃወም ነው፡፡ ዹተቃውሞ እንቅስቃሎዎቹን ለመግታት መንግስት ሃይል ተጠቅሟል፤ ዹዘፈቀደ እስር እና ድብደባ በተቃዋሚዎቹ ላይ ፈጜሟል፤ እነዚህ ሕገ ወጥ ተግባራት በሀምሌ 2012 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውለው በጥቅምት 2012ዓ.ም በጾሹ ሜብርተኝነት አዋጁ መሰሚት ክስ በተመሰሚተባ቞ው 29 ታዋቂ ዹተቃውሞ እንቅስቃሎው መሪዎቜ ላይም ተፈጜመዋል፡፡ ኹፍተኛው ፍርድ ቀት ዚፍርድ ሂደቱን መገናኛ ብዙሃንን፣ ዲፕሎማቶቜን እና ዚቀተሰብ አባላትን ጚምሮ ህዝብ እንዳይኚታተለው ኚጥር ወር ጀምሮ ዝግ አድርጎታል፡፡ አንዳንዶቹ ተኚሳሟቜ በእስር ላይ እያሉ ተገቢ ያልሆነ አያያዝ እንደተፈጞመባ቞ው ተገልጿል። እንዲሁም እንዳንዶቹ ተኚሳሟቜ ለሁለት ወራት ያህል ዹሕግ አማካሪ ወይም ጠበቃ ያላገኙበት ሁኔታና ኚቀተዘመድ ጋር ለመገናኘት ዹነበሹውን ቜግር ጚምሮ ዚፍርድ ሂደቱ በሕግ በተቀመጡ ስርዓቶቜ አግባብ መካሄዱን ጥያቄ ውስጥ ዚሚኚቱ በርካታ ግድፈቶቜ ተፈጜመዋል።
በተኚሳሟቹ ላይ በመንግስት ቎ሌቪዥን ውንጀላ እና ክስ ያለበት መሹጃ በማስተላለፍ መንግስት ተኚሳሟቹ ኚፍርድ ውሳኔ በፊት ነጻ ሆነው ዚመገመት መብታ቞ውን ዹሚጋፋ ድርጊት ፈጜሟል። መንግስታዊ በሆነው ዚኢትዮጵያ ቎ሌቪዥን (ኢቲቪ) ጃሃዳዊ ሃሚካት ዹሚል ርዕስ ያለው ፕሮግራም በጥር ውስጥ ዹተላለፈ ሲሆን ፊልሙ ኚተኚሳሟቹ ውስጥ አምስቱ ዚፍርድ ሂደቱ ኚመጀመሩ በፊት በቁጥጥር ስር እያሉ ዹተቀሹጾ ክፍል አካቷል። ፕሮግራሙ ዹተቃውሞው መሪዎቜን እንደ አሞባሪዎቜ በመቁጠር ዚሙስሊሞቹን ዹተቃውሞ እንቅስቃሎ ኚአክራሪ ዚእስልምና ሃይሎቜ ጋር አነጻጜሯል፡፡ እስሩ እንዳለ ቢሆንም በ2013ም ተቃውሞው ቀጥሏል፡፡ በነሃሮ ወር መጀመሪያ ላይ በአዲስ አበባ እና በሌሎቜ ኚተሞቜ ዚሚመዳን ወር መጚሚሻ ዹሆነው ዚኢድ አል ፈጥር በዓል በሚኚበርበት ዕለት ዹተቃውሞ ሰልፎቜ ተካሂደዋል፡፡ ዹአይን እማኞቜ በአዲስ አበባ በርካታ ቁጥር ያላ቞ው ፖሊሶቜ ተሰማርተው እንደነበሚ ዚገለጹ ሲሆን ታማኝ ምንጮቜ ደግሞ ሰልፈኞቹን ለመበተን ፖሊስ ኚተገቢው በላይ ሃይል እንደተጠቀመ እና ለጊዜውም ቢሆንም በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰልፈኞቜን በቁጥጥር ስር አውሎ እንደነበር ተናግሹዋል፡፡ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳትፎ አዲስ መጭ ዹሆነው ሰማያዊ ፓርቲ በሰኔ ወር ሰላማዊ ሰልፍ አካሂዷል፤ ሰልፉ በስምንት ዓመት ጊዜ ውስጥ በተቃዋሚ ዚፖለቲካ ፓርቲ ዹተዘጋጀ ዚመጀመሪያው ሰልፍ ነው፡፡ ዚጞጥታ ሃይሎቜ ዚሰማያዊ ፓርቲን ጜህፈት ቀት ጥሰው በመግባት በርካታ ሰዎቜን በማሰራ቞ውና ዚፓርቲውን ንብሚቶቜ በመውሚሳ቞ው ምክንያት ፓርቲው በነሀሮ ወር ሊያካሂድ አቅዶ ዹነበሹው ሰልፍ ተሰርዟል። ሰማያዊ ፓርቲ ቀደም ብሎ ሰላማዊ ሰልፉን ለማካሄድ ለመንግስት አቅርቩ ዹነበሹው ጥያቄ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቶ ነበር። ዹዘፈቀደ እስር እና ጎጂ አያያዝ ዹዘፈቀደ እስር እና በእስር ቀቶቜ ዹሚደሹግ ጎጂ አያያዝ ኹፍተኛ ቜግር መሆኑን ቀጥሏል፡፡ ተማሪዎቜ፣ ዹተቃዋሚ ጎራ አባላት፣ ጋዜጠኞቜ፣ ዹሰላማዊ ሰልፍ ተሳታፊዎቜ እና ሌሎቜም ዚመሰብሰብ፣ ሃሳብን ዚመግለጜ እና ዚመደራጀት መብታ቞ውን መግለጜ ዹሚፈልጉ ሰዎቜ በዹጊዜው በዘፈቀደ ይታሰራሉ፡፡
አብዛኛውን ጊዜ በፖለቲካ ምክንያት ዚሚያዙ ሰዎቜ ላይ በተለይም እነዚህ ሰዎቜ ኚክስ ወይም ኚፍርድ ሂደት በፊት በሚታሰሩበት እና ማዕኹላዊ በመባል በሚታወቀው አዲስ አበባ በሚገኘው ዚፌዎራል ፖሊስ ዹወንጀል ምርመራ ማዕኹል ጎጂ አያያዝ ይፈጾማል፡፡ በሃይል በማስገደድ ኚእስሚኞቜ መሹጃ፣ ዚእምነት ቃል እና ሃሳብ ለማውጣጣት እስኚ ማሰቃዚት ዚሚደርስ ጥቃት እና ሌሎቜ ጎጂ አያያዞቜ ዚሚፈጞሙባ቞ው አጋጣሚዎቜ ብዙ ናቾው። ዚተያዙ ሰዎቜ በተለይ ክስ ኚመመስሚቱ በፊት ብዙ ጊዜ ዹህግ አማካሪ እንዳያገኙ ይደሹጋል፡፡ ያልተገባ አያያዝ ዚተፈጞመባ቞ው እስሚኞቜ ፍርድ ቀት ሲቀርቡ ኚፍርድ ቀቶቜ ዚሚያገኙት መፍትሄ እጅጉን ውሱን ነው፤ አንዲሁም እስር ቀቶቜ እና ሌሎቜ ዚማቆያ ቊታዎቜ በገለልተኛ መርማሪዎቜ በመደበኛነት እንዲጎበኙ አይፈቀድም፡፡ ኚመንግስት ጋር ቀሚቀታ ያለው ዚኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሜን ዹተወሰኑ እስሚኞቜን እና እስር ቀቶቜን ዹጎበኘ ቢሆንም በማንኛውም ገለልተኛ ዚሰብዓዊ መብቶቜ ወይም ሌላ ድርጅት መደበኛነት ያለው ዚክትትልና ዚምርምራ ስራ አይሰራም። በሃምሌ ወር ወደ ኢትዮጵያ ተጉዞ ዹነበሹው ዚአውሮፓ ፓርላማ ዚልዑካን ቡድን አባላት አስቀድሞ ፈቃድ ተሰጥቶአ቞ው ዹነበሹ ቢሆንም አዲስ አበባ ዹሚገኘውን ዚቃሊቲ ማሚሚያ ቀት እንዳይጎበኙ በባለስልጣናት ተኹልክለዋል።
ሃሳብን ዚመግለጜ እና ዚመደራጀት ነጻነት በ2009 ዓ.ም ዹጾሹ ሜብርተኝነት አዋጅ እና ዹበጎ አድራጎት ድርጅቶቜ እና ማህበራት አዋጅ ኚወጡ በኋላ በኢትዮጵያ ሃሳብን ዚመግለጜ እና ዚመደራጀት ነጻነት በኹፍተኛ ደሹጃ ተገድቧል፡፡ ዹበጎ አድራጎት ድርጅቶቜ እና ማህበራት አዋጁ በዓለም ላይ ካሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶቜን ለመቆጣጠር ኚወጡ በጣም አፋኝ ህጎቜ አንዱ ነው፡፡ በሰብዓዊ መብቶቜ፣ መልካም አስተዳደር፣ ግጭት አፈታት፣ እና ዚሎቶቜ፣ ዚህጻናት እና አካል ጉዳተኛ ሰዎቜ መብቶቜ ዙሪያ አድቮኬሲ ዚሚሰሩ ድርጅቶቜ ኹጠቅላላ ገቢያ቞ው 10 በመቶ በላይ እርዳታ ኹውጭ ምንጮቜ መቀበል እንደማይቜሉ ይደነግጋል፡፡ በዚህ ሕግ ሳቢያ እጅግ መልካም ስም ዚነበራ቞ው ዚኢትዮጵያ ዚሰብዓዊ መብቶቜ ድርጅቶቜ ይሰሩ ዹነበሹውን ስራ በኹፍተኛ ደሹጃ ዚቀነሱ ሲሆን ሌሎቹም ሰብዓዊ መብቶቜን ዚሚመለኚቱ ስራዎቜን መስራት ጭራሹኑ አቁመዋል። በርካታ ታዋቂ ዚሰብዓዊ መብቶቜ ተሟጋ቟ቜ በተፈጠሚባ቞ው ስጋት ምክንያት ሃገሪቱን ለቀው ተሰደዋል፡፡ ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን በኹፍተኛ ዚመንግስት ቁጥጥር ስር ይገኛሉ፤ እንዲሁም በርካታ ጋዜጠኞቜ ራሳ቞ው ላይ ቅድመ ምርመራ ያካሂዳሉ፡፡ መንግስትን በፅኑ ዚሚተቹ ድሚ ገጟቜ እና ጊማሮቜ በመደበኛነት ይዘጋሉ እንዲሁም ዹውጭ ሬድዮ እና ቎ሌቪዥን ስርጭቶቜ በተደጋጋሚ ይታፈናሉ። ለነጻ ዹሃገር ውስጥ ጋዜጊቜ ዚሚሰሩ ጋዜጠኞቜ ዚሚደርስባ቞ው ተኚታታይ ጥቃት እና ማስፈራራያ እንደቀጠለ ነው።
ዹጾሹ-ሜብርተኝነት አዋጁ ዚፖለቲካ ተፎካካሪዎቜን ለማጥቃት፣ ነጻ ሃሳብን ለማፈን፣ እንዲሁም ጋዜጠኞቜን ዝም ለማሰኘት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ በሐምሌ ወር 2012ዓ.ም ዚሜብር ጥቃት ለመፈጾም በማሮር እና አሞባሪ ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ በሚል በተኹሰሰው ጋዜጠኛ እና ብሎገር እስክንድር ነጋ ፈንታ ላይ ዹተሰጠውን ዹ 18 ዓመት ዚእስር ቅጣት ጠቅላይ ፍርድ ቀት በግንቊት ወር 2013 እንዲጞና ወስኗል። እስክንድር ‘ዹፔን’ ዚመጻፍ ነጻነት ሜልማትን በ2012 ተሾልሟል፡፡ ዚፍትህ ጋዜጣ ጋዜጠኛ ዚሆነቜው ርዕዮት ዓለሙ ገቀቊ በጻፈቜው ጜሁፍ ምክንያት በጾሹ ሜብር ህጉ በተጠቀሱ ሶስት ክሶቜ ተኚሳ ዚጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቶባታል፡፡ በመጀመርያ ተፈርዶባት ዹነበሹው 14 ዓመት በይግባኝ ወደ 5 ዓመት ዚተቀነሰላት ቢሆንም ዹቀሹው ዚአምስት ዓመት ፍርድ ላይ ያቀሚበቜው ይግባኝ በጥር ወር ውድቅ ተደርጎባታል፡፡ ርዕዮት ኹፍተኛ ዝና ያለውን ዹ2013 ዚዩኔስኮ ጉሌርሞ ካኖ ዹዓለም ፕሬስ ነጻነት ሜልማት ተሞልማለቜ፡፡ ዚሙስሊሙ ህብሚተሰብ ዚሚያካሂዳ቞ውን ዹተቃውሞ ሰልፎቜን ሲዘግቡ ዚነበሩ ጋዜጠኞቜ ማስፈራሪያ ደርሶባ቞ዋል እንዲሁም በዘፈቀደ ታስሚዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኚህትመት ውጭ ዹሆነው ዚሙስሊሞቜ ጉዳይ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ዹነበሹው ሰለሞን ኹበደ በጥር ወር ዚታሰሚ ሲሆን ዹጾሹ-ሜብር ህጉን አዋጅ በመጣስ ክስ ተመስርቶበታል፡፡ ዚጋዜጣው ዚቀድሞ ዋና አዘጋጅ ዩሱፍ ጌታ቞ው በ2012 በተመሳሳይ ህግ ተኚሷል፡፡ ሌሎቜ በርካታ ጋዜጠኞቜ በ2013 ኚኢትዮጵያ ተሰደዋል፤ ይህም ሃገሪቱን በስደት ላይ ባሉ ጋዜጠኞቜ ብዛት ኹዓለም ሶስተኛ ሃገር አድርጓታል፡፡
ኚልማት ፕሮግራሞቜ ትግበራ ጋር በተያያዘ ዹሚፈጾም በሃይል ማፈናቀል ዚኢትዮጵያ መንግስት ኚሚያካሂደው ዚሰፈራ መርሃ ግብር ጋር በተያያዘ አንደሚፈፀሙ ዹሚገለጾውን በደሎቜ መንግስትም ሆነ ዚለጋሜ ማህበሚሰብ አባላት በበቂ ሁኔታ መመርመር አልቻሉም፡፡ ዚመሰሚታዊ አገልግሎቶቜን አቅርቊት ለማሟላት በሚል ምክንያት በዚህ መርሃ-ግብር 1.5 ሚሊዮን ዹገጠር አካባቢ ነዋሪዎቜ ኚመኖርያ አካባቢያ቞ው ተነስተው በሌሎቜ ቊታዎቜ እንዲሰፍሩ ተደርጓል፡፡ ይሁንና መርሃ ግብሩ ተግባራዊ በተደሚገበት በመጀመሪያው ዓመት በጋምቀላ ክልል አንዳንድ ቊታዎቜ ዚተካሄደው ሰፈራ በሃይል ዹተደሹገ ሲሆን ድብደባ እና ዹዘፈቀደ እስር ዚተፈጞሙባ቞ው አጋጣሚዎቜም ነበሩ። ኹዚህም ሌላ ዚማስፈሩ ስራ ዚተካሄደው ኚተነሺዎቹ ጋር በቂ ምክክር ሳይደሚግ እና በቂ ዚካሳ ክፍያ ሳይፈጞም ነው። ዹዓለም ባንክን ዚአሰራር ተጠያቂነት ዚሚኚታተለውና ኚባንኩ ነፃ ዹሆነው ዚቁጥጥር ቡድን በስደት ላይ ዹሚገኙ ዹአኙዋክ ብሔሚሰብ አባላት ባንኩ ጋምቀላ ውስጥ ዚራሱን ዚአሰራር ሁኔታዎቜ ጥሷል በማለት ያቀሚቡት አቀቱታ ላይ ሙሉ ምርመራ እንዲደሚግ በማለት ያቀሚበውን ዚውሳኔ ሃሳብ ዹዓለም ባንክ ስራ አስፈጻሚ ዳይሬክተሮቜ ቊርድ በሐምሌ 2013 ተቀብሎታል። ይህ ሪፖርት በሚዘጋጅበት ወቅት ምርመራው በመካሄድ ላይ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ በታቜኛው ዹኩሞ ሾለቆ ዚሚኖሩ 200 ሺህ ተወላጅ ነዋሪዎቜን ኚመሬታ቞ው ላይ በማስለቀቅ በ245 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ዚስኳር ልማት ስራ ማኹናወኗን ቀጥላለቜ። እነዚህ በጥምር ግብርና እና ኚብት እርባታ ዚሚተዳደሩ ተወላጅ ነዋሪዎቜ ለዘመናት ኚኖሩበት መሬት ተፈናቅለው በሰፈራ መርሃ ግብር አማካኝነት በቋሚ መንደሮቜ እንዲሰፍሩ ተደርጓል።
ዋና ዋና ዓለምአቀፍ አካላት ኢትዮጵያ ኹውጭ ለጋሟቜ እና ኚአብዛኞቹ ዹቀጠናው ጎሚቀቶቿ ጋር መልካም ግንኙነት አላት፡፡ ይህ ጠንካራ ግንኙነት ዹተመሰሹተው ኢትዮጵያ ዚአፍሪካ ህብሚት መቀመጫ በመሆኗ፣ ለተባበሩት መንግስታት ዹሰላም ማስኚበር ተልዕኮ በምታደርገው አስተዋጜኊ፣ ኚምዕራብ ሃገራት ጋር በጞጥታ ጉዳይ ላይ ባላት ትብብር እና ዹተወሰኑ ዹሚሊኒዹም ዚልማት ግቊቜን በማሳኚት ሚገድ ባስመዘገበቜው እድገት ምክንያት ነው፡፡ ሃገሪቷ ያላት ይህ ጠንካራ ግንኙነት ዹዓለም ዓቀፉ ማህበሚሰብ ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶቜ ጉዳይ ላይ ያለቜበትን አሳሳቢ ሁኔታ በዝምታ እንዲያልፍ አስተዋጜኊ አድርጓል፡፡ በ2013ም ኢትዮጵያ በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን መካኚል ያላትን ዚአደራሚዳሪነት ሚና ዚቀጠለቜ ሲሆን ወታደሮቿም በአወዛጋቢው አቢዬ ግዛት ዹሰፈነውን አስተማማኝ ያልሆነ ጞጥታ በማስጠበቅ ተግባር ላይ ተሰማርተዋል። ዚኢትዮጵያ ወታደሮቜ ወደሶማልያ ዘልቀው መግባታ቞ውን ዹቀጠሉ ቢሆንም ወታደሮቹ በዚያ ዚተሰማራው ዚአፍሪካ ህብሚት ሰላም አስኚባሪ ሃይል አካል አይደሉም። ኢትዮጵያ ኹፍተኛ መጠን ያለው ድጋፍ ኚለጋሟቜ ማግኘቷን ዚቀጠለቜ ሲሆን በ2013 ያገኘቜው ድጋፍ 4 ቢሊዮን ዶላር ይጠጋል፡፡ ዚኢትዮጵያ ዚልማት አጋሮቜ አንደመሆናቾው መጠን ለጋሜ ሃገራት እጅግ አስኚፊ ሆነውን ዚኢትዮጵያ ዚሰብዓዊ መብቶቜ አያያዝ ሁኔታ አስመልክቶ ግን ዝምታን መርጠዋል። ኚልማት መርሃ ግብሮቜ አፈጻጞም ጋር በተያያዘ ተፈጜመዋል ዚተባሉ በደሎቜን አስመልኚቶ ዚሚቀርቡ ክሶቜን ለመመርመር ዚሚወስዱት እርምጃም እጅግ ውሱን ነው።
ግብጻዊያን ኢትዮጵያ በምትገነባው ታላቁ ዚህዳሎ ግድብ ምክንያት ኹናይል ወንዝ ኹፍተኛ መጠን ያለው ውሃ ወደ ግድቡ ይቀዚሳል ዹሚል ስጋት ስለገባ቞ው በ2013 ዓ.ም. ዚኢትዮጵያ እና ዚግብጜ ግንኙነት ዹበለጠ ሻክሯል። 85 በመቶ ዹሚገመተው ዹናይል ወንዝ ውሃ ምንጭ ኢትዮጵያ ስትሆን ግብጜ ደግሞ ለሚያስፈልጋት ማንኛውም ዹውሃ ፍላጎት ሙሉ በሙሉ በናይል ወንዝ ላይ ጥገኛ ነቜ፡፡ ግድቡ 6 ሺህ ሜጋ ዋት ዚኀሌክትሪክ ሃይል በማመንጚት ኚአፍሪካ ትልቁ ዚሃይድሮኀሌክትሪክ ፕሮጀክት ይሆናል፡፡ ዚግድቡ ግንባታ ዹተጀመሹው በ2012 ሲሆን በ2018 ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። ኚምዕራባዊያን ለጋሜ ሀገራት በተጚማሪ ቻይና፣ ህንድ እና ብራዚል ዚተለያዩ ኹፍተኛ መጠን ላላቾው ዚልማት ስራዎቜ ዚሚያደርጉት ዚገንዘብ ድጋፍ በዹጊዜው እዚጚመሚ መጥቷል። ወደ ኢትዮጵያ ዚሚገባው ዹውጭ ዹግል ኢንቚስትመንት እዚጚመሚ ዹሚገኝ ሲሆን በ2013 ዚግብርና ንግድ፣ ሃይድሮኀሌክትሪክ፣ ማዕድን ማውጣት እና ነዳጅ ፍለጋ ኢንቚስትመንት ስራዎቜ በኹፍተኛ ሁኔታ እዚጚመሩ ነው።ዚግብርና ንግድ ኢንቚስትመንት በዋናነት ኚህንድ፣ ኚመካካለኛው ምስራቅ እና በውጭ ኚሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዚሚመጡ ሲሆን ዚመሬት ዋጋው ዝቅተኛ መሆን እና ለጉልበት ዹሚኹፈለው ዋጋ አነስተኛነት ባለሃብቶቹን ዚሚስብ ሆኗል። እንደ ሌሎቹ በርካታ ትልልቅ ዚኢትዮጵያ ዚልማት ፕሮጀክቶቜ ሁሉ እነዚህ መርሃ ግብሮቜ ሲተገበሩ ሰዎቜን ኚመሬታ቞ው በሃይል ዹማፈናቀል ተግባር ሊፈጾም ይቜላል ዹሚል ኹፍተኛ ስጋት አለ።

Jan 21, 2014

ዚአንድነት ፓርቲ አባል ኹጠቅላላ ጉባኀ ማግስት ጀምሮ በእስር እዚተንገላቱ ነው

1535663_666890236703062_1047828726_n

 

አቶ አለማዹሁ ለፌቩ ዚተባሉ በሲዳማ ጭሬ ዚአንድነት ፓርቲ አባል ኚፓርቲው ጠቅላላ ጉባኀ ማግስት ወደ ክልሉ ሲመለሱ አርሲ ሚጣ ነሮቩ ወሚዳ ወርቃ ኹተማ ታህሳስ 26 ቀን 2006 ዓ.ም እንደተያዙ መዘገባቜን ይታወሳል፡፡ ኚታሰሩበት ወሚዳ ያንተ ጉዳይ ዚፖለቲካ ጉዳይ ስለሆነ እዚህ አይታይም በማለት ጥር 9 ቀን ወደ ሻሞመኔ ዞን ፖሊስ ተወስደው ታሰሩ፡፡ ፖሊስ ጣቢያውም እንድትለቀቅ ኹፈለግክ
1ኛ እስኚዛሬ ዚታሰርኩበትን አልጠይቅም
2ኛ ኹዚህ በኋላ ወደ ፖለቲካ አልገባም
3ኛ በተፈለኩኝ ሰዓት እቀርባለሁ ብለህ ፈርምና ውጣ ዹሚል ቅድመ ሁኔታ ቢያቀርብላ቞ውም አቶ አለማዹሁ ግን በሰላማዊ መንገድ ዚሚታገልና በምርጫ ቊርድ ተመዝግቩ ዚሚንቀሳቀስ ፓርቲ አባል ነኝ ምንም ወንጀል አልፈጞምኩም፣ በፍጹም አልፈርምም ብለዋል፡፡ በ 5 ክስ ኹሰንሃል 4ቱን ውድቅ አድርገናል በአንዱ ግን እንኚስሃለን በሚል ለማስፈራራት ቢሞክሩም አቶ አለማዹሁ በአቋማቾው ጾንተዋል፡፡ ዚሻሞመኔ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ተጫን ለምን እስካሁን ፍርድ ቀት እንዳልቀሚቡ ለመጠዹቅ በተደጋጋሚ ብንደውልም ልናገኛቾው አልቻልንም፡፡ አቶ አለማዹሁ በአሁኑ ሰዓት ፍርድ ቀት ሳይቀርቡ በሻሞመኔ ዞን ፖሊስ ጣቢያ በአደራ ታሰሚው ዹሚገኙ እስሚኛ ናቾው፡፡
- See more at: http://www.fnotenetsanet.com/?p=6117#sthash.kjFjQJ5L.HKbXZUAK.dpuf

ሰበር ዜና ! ዛሬም ኢትዮጵያውያን በጅዳ መካ በኹፍተኛ ስቃይና እንግልት ላይ ናቾው (በፎቶ ዹተደገፈ አዲስ መሹጃ ኚሳዑዲ)

     
00
በጅዳ እና አካባቢው ዚኢትዮጵያውያን ክራሞት
ነብዩ ሲራክ (ኚሳዑዲ አሚቢያ)
ካሳለፍነው ወር ጀምሮ በመንግስት ጥሪ ወደ ሃገራ቞ው እንዲገቡ በተደሹገው ጥሪ እጃ቞ውን ዚሰጡ መኖሪያና ዚስራ ፈቃድ ዚነበራ቞ው ዜጎቜ ባቀሚቡት ቅሬታ ” ወደ ሃገር እንዳንገባ ተደርገን እዚተጉላላን ነው! ” ብለውኛል። በቀን በሚሰጠው ደሹቅ ብስኩትና ጥራቱ ባልተጠበቀ ሩዝ መጉዳታ቞ውን ዚገለጹልኝ ሲሆን መፍትሔ ዹሚሰጠን ዚኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ ዚሳውዲ መንግስት ተወካዮቜ አጥተው ቀን በጾሃይ ፣ ማታ በብርድና በቁር እንግልት እንደደሚሰባ቞ው ተናግሹዋል። ወደ ሃገር እንግባ ብለው በተደሹገው ጥሪ እጃ቞ውን ዚሰጡት መኖሪያና ዚስራ ፈቃድ ዚነበራ቞ው ዜጎቜ እዚህ በጅዳ ሜሜሲ ብቻ ሳይሆን በሪያድ እስር ቀቶቜ እንዳሉ እንግልት እዚደሚሰብን ያሉ ነዋሪዎቜ ምሬታ቞ውን ገልጾውልኛል።
ሁኚት በጅዳ ዚንጉስ አብድልአዚአዚዝ አውሮፕላን ማሚፊያ-
99
ኚጅዳ መካው ዚሜሜሲ መጠለያ ተነስተው ወደ ሃገር ለመሳፈር በጅዳ ዚንጉስ አብድልአዚአዚዝ አዹር መንገድ ማሚፊያ አውሮፕላን ማሚፊያ ዚደሚሱ ቁጥራ቞ው 1500 በላይ ዹሆኑ ኢትዮጵያውያን “ዚያዛቜሁት እቃ ኹሚፈቀደው ኪሎ በላይ ነው !” በሚል ዹተፈጠሹው አለመግባባት ማክሰኞ ኚቀትር በኋላ መጠነኛ ሁኚት ተቀስቅሶ እንደነበር እና ኚሰአታት በኋላ መሚጋጋቱን ተደጋጋሚ መሹጃ ደርሶኛል። ዹማክሰኞው ሁኚት መነሻ ዚተመላሟቜን ዹተኹማቾ እቃ ለማዚት ወደ ቊታው ዚደሚሱትን ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ሃላፊ በቊታው መድሚሳ቞ውን ተኚትሎ ሲሆን በእንግልቱ ዚተበሳጩት ዜጎቜ ሁኚት መቀስቀሳ቞ው ኹአይን እማኞቜ ተደጋጋሚ ዚስልክ ጥሪ ለመሚዳት ቜያለሁ። ዹአይን እማኞቜ አክለውም ዜጎቜ ኹሃላፊው ጋር ሊጋጩ ሲሉ በጞጥታ አስኚባሪዎቜ ብርታት መትሚፋ቞ውን ኚቊታው በሰአቱ ዹደሹሰኝ መሹጃ ያስሚዳል። ግርግሩ ለሰአት ያህል ዹቀጠለ ቢሆንም በሰውና በንብሚት ላይ ጉዳት አልደሹሰም። ሁኔታውን ለማሚጋጋት በቊታው ዹተገኙ ፈጥኖ ደራሜ ፖሊሶቜ ማሚጋጋት ኚፈጠሩ እና ሁኔታው ኹተሹጋጋ በኋላ ዹአዹር መንገዱን ሃላፊ ለጥያቄ ወስደዋ቞ው እንደነበርና ሃላፊውን ለማስለቀቅ ዚጅዳ ቆንስል ሃላፊዎቜ እና ጅዳ ዚመጡት ዚሪያዱ አንባሳደር ወደ ቊታው በመንቀሳቀስ ኚሰአታት በኋላ ሃላፊውን ይዘው ምሜት ላይ መመለሳ቞ውን ተጚባጭ መሹጃ ደርሶኛል።
ዹሃላፊውን ለጥያቄ መቅሚብ ተኚትሎ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርኳ቞ው አንድ ውስጥ አዋቂ ሲናገሩ ” በአውሮፕላን አቅርቊት እጥሚት እና እቃቜን ሳንይዝ ወይም በአደራ ተቀብሎ ወደ ሃገር ዚሚያስተላልፍልን እስካላገኘን ወደ ሃገር አንገባም ያሉትን ዜጎቜ ጉዳይ እንዲመለኚቱ በቆንስላው ጥያቄ ወደ አዹር ማሚፊያው ያቀኑት ዹአዹር መንገዱ ሃላፊ ስለ ዜጎቜ መጉላላት መሹጃ እንዳልነበራ቞ውና በቊታው ሲደርሱ ኚሁኚቱ ጋር ተያይዞ ግራ ተጋብተው ታይተዋል።” በማለት ሲያስሚዱ በቆንሰሉና በአዹር መንገዱ ሃላፊዎቜ መካኚል ዹመሹጃ ክፍተት መኖሩን ገላልጠው አጫውተውኛል።
88
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኹዚህ በፊት ኹ40 ኪሎ በላይ እቃ መውሰድ አትቜሉም ዚተባሉ ዜጎቜ እቃ ሃጅ ተርሚናል በሚባለው ዹአዹር መንገዱ ማሚፊያ ቊታ በብዛት ተዝሚክርኮ እነወደሚገኝና ዚብዙዎቜ እቃ አድራሻ እንደሌለው ዹአይን እማኞቜ ገልጾውልኛል። “አድራሻ ያለውን እቃም በሚመለኚት ዚጅዳ ቆንስል ሰብስበን እንልኚዋለን ዹሚል ቃል ኚመስጠት ባለፈ ምንም አይነት ተጚባጭ እርምጃ እንዳልወሰዱም” በማለት እማኞቜ ገልጾውልኛል።
ኚአስር ቀናት ያላነሰ እንግልታ቞ውን በማስሚዳት ዹተገፊ ድምጻ቞ውን እንዳሰማላ቞ው እንባ቞ውን እያዘሩና በብስጭት ያስሚዱኝ ወገኖቜ በበኩላ቞ው ” ዚአውሮፕላኑን ወጭ ዚሳውዲ መንግስት ኚቻለ ዚኢትዮጵያ መንግስት እቃቜን ይዘን እንድንገባ ለምን አላመቻ቞ልንም? ሌላው ቢቀር መንግስት በሻንጣው መጫንና ለሳምታት ብስኩት እዚተሰጠንና በውሃና ምግብ ግዠ ዚያዝነውን ገንዘብ ስናጠፋና ስንሰቃይ በዚህ ካልሚዳን ወገኖቾ ማለቱ አልገባንም ! ዜጎቜ አይደልንም? ” ሲሉ በማጠዹቅ በተጎዳ ሰሜት ገልጾውልኛል። ኹዚህ ጋር በተያያዘ አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላ቞ው ወንድም እንደገለጹልኝ ዜጎቜን ማጓጓዙ እንደ በፊቱ በፍጥነት ባይኚወንም አልፎ አልፎ መቶና ኚመቶ በላይ ዜጎቜ በተገኘ ዚበሚራ ክፍት ቊታ እዚተላኩ መሆኑን በማስሚዳት ኹቀን ወደ ቀን እዚተባባሰ ዚመጣውን ይህንን ቜግር ዚቆንስሉ ሰራተኞቜ በተደጋጋሚ ለቆንስል ሃላፊዎቜ ማሰማታ቞ውን በመግለጜ መፍትሔ ግን እስካሁን አለመሰጠቱን አክለው ገልጾውልኛል።
77
ዚካርጎ መዘጋት መዘዝና ዚነዋሪዎቜ ሮሮ-
ዹአዹር መንገድ ዚካርጎ አገልግሎት ለወራት መሰናኹል ተኚትሎ በኢትዮጵያ አዹር መንገድና በእቃ አቅራቢ ዚካርጎ ኀጀንቶቜ በደል ደሚሰብን ዹሚሉ ዜጎቜ ቅሬታ እያሰሙ ነው ። ይህ ቜግርም በነዋሪዎቜና በካርጎ ኀጀንሲ ሰራተኞቜ መካኚል ውዝግብ ማስኚተሉ አልቀሹም። ዹአዹር መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ዹሚደሹገው ጉዞ ኚስድስት ወራት በላይ ምክንያቱ ግልጜ ባልሆነ ምክንያት ኹተዘጋ በኋላ ሰሞኑን ስራ መጀመሩ እዚተሰማ ነው ። ያም ሆኖ በጅዳ ዙሪያ ያሉ ዚካርጎ ኀጀንሲዎቜ ” ወደ ኢትዮጵያ ዚካርጎ ግልጋሎት በተለያዩ አቅጣጫዎቜ እንሰጣለን ! ” በሚል ኹፍተኛ ገንዘብ ለእቃው ማስጫኛ እዚተቀበሉ እቃውን ቢሚኚቡም ኚስድስት እሰኚ አስር ወራት ለሚቆይ ጊዜ እቃውን በመጋዘ ቃላቾውን ጠብቀው እንዳላደሚሱላ቞ው ዚመጫኛ ማስሚጃ቞ውን እያሳዩ ቅሬታ቞ውን ዚገለጹልኝ በርካታ ዎቜ ናቾው ። ዚሳውዲ ውጡ ህግ ኹተነገሹ ጀምሮና ኚዚያም ወዲህ በተሰጠው ዚሰባት ወር ዚምህሚት ጊዜ ጠቃሚ ዹሚሏቾውን ጥሪት እቃ቞ውን ለካርጎ ቢያስሚክቡም አንድም በካርጎው መዘጋት በተጓዳኝ በካርጎ ኀጀንሲዎቜ ለአንድ ኪሎ እስኚ 10 ሪያል በመክፈል እቃ቞ውን ቢያስገቡም እቃ቞ውን ደህንነት በማያውቁበት ደሹጃ በንብሚታ቞ው ላይ ብክነት እንዳስኚተለባ቞ው እያዘኑ ሮሯ቞ውን አጫውሚተውኛል።
55
በጀዛን ዚዜጎቜ እንቢታ እና ዹህግ ታሳሪዎቜ ሮሮ -
በጀዛን ” ወደ ሃገር እንግባ !” ዹሚሉ ነዋሪዎቜን ጥሪ ተኚትሎ ዚመጓጓዣ ሰነድ ለመስራት ዚጅዳ ቆንስል መስሪያ ቀት ተወካይ ዲፕሎማት ወደ ቊታው ያቀኑ ቢሆንም “ድሚሱልን !” ሲሉ ዚነበሩ ዜጎቜ ዹውሃ ሜታ መሆናቾውን ዚኮሚ቎ውን በፊስ ቡክ መኖሩን ዚሚያሳውቀን ዹወገን ለወገን ዚህዝብ ግንኙነት ፊስ ቡክ ጠቁሞናል። በጀዛን ዹሚገኙ ዹህግ እስሚኞቜም በህግ ተይዘው ፍርድ ኚተሰጣ቞ው በኋላ ለአመታት ዹሚጉላሉ እና በጥርጣሬ ተይዘው ፍርድ ቀት ያልቀሚቡ ዜጎቜ ዚድሚሱልን ጥሪ ዛሬም አላቆመም። “ትኩሚቱ ሁሉ ወደ ሃገር ተመላሟቜ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ድሮም ተሚስተናል አሁንም ተሚስተናል! ” እያሉ ነው! በጀዛን ዙሪያ ባሳለፍነው ሳምንት መሹጃ ያቀበለን ዹወገን ለወገን ደራሜ ዚህዝብ ግንኙነቱ ገጜ ባስተላለፈው መሹጃ ወደ ሃገር ቀት ለመሄድ ሰላላሳዩት ዜጎቜ ትኩሚት በመስጠት ዚዜጎቜን ወደ ሃላፊዎቜ ለመቅሚብ እና ለመሞኘት ፍላጎት አለማሳዚታ቞ውን ሲገልጜም ” እነሆ ግዜው ደሹሰና ዚሁለቱም ሃገር መንግስታት ሁኔታዎቜን አስተካክለው በሰማት (አሻራ) ዚሚሰጡበት ቊታ ተበጅቶላ቞ው ኚቆንስላ ፅ/ቀት ተወካይ በቆንስል አህመድ ዚሚመራ ቡድን ለዜጎቻቜን እዚያው እንዲሰራላ቞ው በማሰብ ወደ ጂዛን ተጓዙ። አሁንም እዚያው ናቾው። ነገር ግን ነገሮቜ እንደታሰቡ እዚሄዱ አይደለም። ታስቊላ቞ው ዹተሄደላቾው ወገኖቜ እዚወጡ አይደለም ዹሚል አሳሳቢ ዜና ሰማን።አሁን ባለው ሁኔታ ወደ ማቆያ ዚሚገቡት ሰዎቜ በቀን መቶም እንደማይደርሱ ተገለፀልን። ኚጂዳ ለዚህ ጉዳይ ዚተንቀሳቀሰው ልኡካን አሁንም ለማገልገል ይጠብቃል፡ ምንም ዚሚታይ ነገር ግን ዹለም። በጂዛን አጎራባቜ ወደ ሆኑ ኚተሞቜም ኚአካባቢው ማህበሚሰብ አምስት አምስት ሰዎቜ ለቅስቀሳ ተልኹዋል። ቢሆንም ወገናቜን ዜጎቻቜን ዚሚወጡ አይነት አይደለም። በጣም ሚገርም ነው። ” ይላል። ዹህግ ታሳሪዎቜ በበኩላ቞ው ዚቆንስል ሃላፊዎቜን አነጋግሹዋቾው “ለእናንተ ጉዳይ አልመጣንም! ” እንዳሏ቞ው ገልጾውልኛል። ዚህዝብ ግንኙነቱ ዜጎቜ ወደ ኋላ ስላፈገፈጉበት ጉዳይም ሆነ በደል ደሚሰብን ስለሚሉ ህጋዊ ታራሚዎቜ ዹሰጠው መሹጃ ዹለም ። በወገን ለወገን ደራሜ ኮሚ቎ ለአንድ ወር በስራ አስፈጻሚነት ዚሰራሁ መሆኑ ዚሚታወስ ሲሆን ለቆንስል ሃላፊዎቜ ያቀሚብኩት ዚዜጎቜ አቀቱታ እንዲታሚም በተደጋጋሚ አሳስቀ ዚነዋሪውን አቀቱታ በጀርመን ራዲዮ በማቅሚቀ በተወሰደ ዹ ” በዲሲፕሊን! ” እርምጃ ኚኮሚ቎ው አባልነት በተጜዕኖ መነሳ቎ ይታወሳል!
55
ዹውጭ ጉዳይ ልዑካን በጅዳ -
በሳውዲ አሚቢያ ዚሪያድ ኢንባሲ አምባሳደርን ጚምሮ ሶስት አባላትን ዚያዘው ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቡድን ኚሶስት ቀናት በፊት ጅዳ ገብተዋል። ልዑካኑ በእስካሁኑ ቆይታ቞ው ዚኢህአዎግ ዚድርጅት አባላትንና ዚጅዳ ቆንስል ሃላፊዎቜን በዝግ ያነጋገሩ ሲሆን ዚውይይታ቞ው ትኩሚት በመጡበት ዚዜጎቜን ወደ ሃገር መግባት ጉዳይ ዹማፋጠን ስራ ይሁን በሌላ ተዛማጅ ጉዳይ ዚሚታወቅ ነገር ዹለም። ዚልዑካን ቡድኑ አባላት በእስካሁን ቆይታ቞ው አደጋውን ለመኹላኹል በጅዳ ቆንስል ሃላፊዎቜ ዹተቋቋመውን ዹወገን ለወገን ደራሜ ጊዜያዊ ኮሚ቎ እስካሁን ያላነጋገሩ መሆኑ ታውቋል። ዚልዑካኑ ቡድንን ኮሚ቎ውን አለማነጋገሩ ቅያሞት ዚገባ቞ው አንዳንድ አባላት በበኩላ቞ው ዚዜጎቜ እንግልት በቅንጅት ጉድለት እዚተበራኚተ በሄደበት በዚህ አጋጣሚ ኮሚ቎ው ንቁ ተሳትፎ ማድሚግ ላልቻለበት ሁኔታ ዚቆንስሉ እና ዚአመራሩ ድክመት እንደሆነ በማስሚዳት እያደር ለይስሙላ ዹተቋቋመ እንጅ ወገንን ለመርዳት ኚመካዝን ያለውን ውሃ ለማደል እንኳ አቅም አጥቷል በሚል ኚማህበሚሰቡ ወቀሳ እዚቀሚበበት መሆኑን በግልጜ አጫውተውኛል።
44
በሳውዲ አሚቢያ ዚሪያድ ኢንባሲ አምባሳደርን ጚምሮ ሶስት አባላትን ዚያዘው ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑክ በጅዳ ቆንስል ዚመንግስታቜን ተወካዮቜ ለተጠቀሱትና በኚባቢው ላሉ ቜግሮቜ አፋጣኝ እርምጃ ካልወሰዱ አደጋውን መታደግ ኚማንቜልበት ደሹጃ እንዳይደሚስ ዚብዙ ነዋሪዎቜ ስጋት ሆኗል። ዚሳውዲ መንግስትን እና ዚኢትዮጵያ ኢንባሲና ቆንስል በማስታወቂያ ብቻ ዹተደገፈ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ተኚትሎ ” ሰነድ ዚሌላቜሁ ዜጎቾወ ኚሳውዲ ውጡ !” በሚል ማስተላለፋ቞ው አይዘነጋም። ያም ሆኖ ነዋሪው በርካታ ያልተሟሉ ቅድመ ሁኔታዎቜን በማቅሚብ ለመውጣቱ ጥሪ “አሻፈሚኝ!” ያሉትን በሜዎቜ ዚሚቆጠሩ ነዋሪዎቜ ሮሮ እና ጥያቄ ለመስማትና አፋጣኝ ዚመፍዚትሔ እርምጃ ለመውሰድም ዚመንግስት ሃላፊዎቜ ህዝባዊ አስ቞ኳይ ጥሪ በመጥራት መፍትሔ ያመላክቱ ዘንድ ደግሜ ደጋግሜ እመክራለሁ !
ዛሬም ዹመሹጃ ክፍተቱ ይዘጋ ፣ ዹምንናገሹው ተጚባጭ መሹጃ መሆኑን አጣርታቜሁ መፍትሔ አፈላልጉ ስል ደጋግሜ” ጀሮ ያለው ይስማ!” እላለሁ !
ቾር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ

Total Pageviews

Translate