Pages

Jun 19, 2013

የጁነዲን ሳዶ ባለቤት ወ/ሮ ሀቢባ መሐመድን ጨምሮ የ32ቱ ሰዎች ክስ ለሕዝብ ክፍት እንዲሆን ጠበቆቹ ጠየቁ

በዘሪሁን ሙሉጌታ
.ዐቃቤ ሕግ 197 የሰው ምስክር ለማቅረብ ጠይቆ 89 ምስክሮችን ብቻ አሰማ
በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢፌድሪየወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)(ለ)፣38(1) እና የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅቁጥር 652 /2001 አንቀፅ 3(1) (4)(6) እና 4 ስር የተመለከቱትንድንጋጌዎች በመተላለፍ የተከሰሱትንየቀድሞ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርየነበሩት የአቶ ጁነዲን ሳዶ ባለቤት ወ/ሮሀቢባ መሐመድን ጨምሮ ሌሎች 32ሰዎች ክስ ለሕዝብ ክፍት እንዲሆንጠበቆቹ ጠየቁ።ቀደም ሲል ዐቃቤ ሕግ በተጠርጣሪዎቹላይ የሰው ምስክር በሚያሰማበት ወቅትለምስክሮቹ ደህንነት ሲባል ችሎቱ በዝግእንዲካሄድ ፍርድ ቤቱ በመወሰኑ ችሎቱበዝግ ሲካሄድ ቆይቷል። ዐቃቤ ሕግ ለክሱ ዝርዝር ያስረዱልኛል ያላቸውን 197 የሰው ምስክሮች እንደሚያሰማ አስቀድሞለፍርድ ቤቱ ያመለከተ ቢሆንም 89 ምስክሮችን ካሰማ በኋላ ማጠናቀቁን ተከትሎ የፍርድ ሂደቱ ለጋዜጠኞችና ለዲፕሎማቶችእንዲሁም ጠበቆቹ ለተጠርጣሪዎቹ ዘመድ ወዳጆች ክፍት እንዲሆን ጠይቀዋል።ከተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች አንዱ የሆኑት ጠበቃ ተማም አባቡልጉ በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት፤ በመጪው ሐሙስ ሰኔ 13ቀን 2005 ዓ.ም የሚሰየመው ችሎት ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል ክፍት እንዲሆንና በቀጣይ በተከሳሾቹ ላይ ዐቃቤ ሕግአቀርበዋለሁ ያለው የኦዲዮና ቪዲዮ ቅጂ ለጠበቆች ቅድሚያ ሊደርስ ይገባል ብለዋል።በአሁኑ ወቅት የተጠርጣሪዎቹ ጉዳይ እየታየ ያለው የቀድሞ ቅንጅቶች ጉዳይ ይታይበት በነበረው በቃሊቲ ወረዳ 8 አዳራሽ ውስጥሲሆን፤ ጉዳዩ እየታየ ያለው በፌዴራል አራተኛ ወንጀል ችሎት ነው።በሌላ በኩል ከዚህ በፊት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት “ጅሃዳዊ ሀራካት” በሚል የቀረበው ዘጋቢ ፊልም በአሁኑ ወቅትጉዳያቸው እየታዩ ካሉ 12ቱ ተጠርጣሪዎች አለአግባብ ስማቸው መጥፋቱን በመግለፅ፤ በጠበቆቻቸው አማካኝነት በፕሬስ ሕጉአንቀፅ 43 መሠረት ፎቶና ምስሎችን አለአግባብ ታይቷል በሚል 8 ሚሊዮን ብር የካሳ ክስ አቅርበው እንደነበር ጠበቃ ተማምገልፀዋል። ነገር ግን የዳኝነት 83 ሺህ ብር ከፍለው ክሱን በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ለመክፈት ሲሞክሩ፤ ሬጅስትራሩ የክስፎርማሊቲ አልተሟላም በማለት ለዳኛ ሳይመራ፣ አቤቱታ አቅራቢዎች ሳይከራከሩ፣ ተከራካሪ ወገኖች መጥሪያ ሳይሰጣቸውአላግባብ በመዘጋቱ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ አቤቱታ ሰሞኑን እንደሚያቀርቡ አያይዘው ገልፀዋል።በተጨማሪም የመጅሊስ ምርጫውን በተመለከተ መጅሊሱ የተመረጠበት አካሄድ ሕገ-መንግስቱን፣ የኢትዮጵያ ፍትሐብሔርሕግን እና የመጅሊስ ሕገ-ደንብን የጣሰ ነው በሚል ያቀረቡትን ክስ የሥር ፍርድ ቤቶች ውድቅ ቢያደርጉም፤ ጉዳዩ ሰበር ሰሚመድረሱንና ለሰኔ 27 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱንም ጨምረው ገልፀዋል።
ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ

No comments:

Post a Comment

Total Pageviews

Translate