Pages

Jan 5, 2013

በኬንያ ስደተኞቜ ኹተማ ልቀቁ ተባሉ ኢትዮጵያውያኑ እንታፈናለን ብለው ሰግተዋል


ወቅቱ 2003 አጋማሜ ላይ ነው። ሁለት ዚኢህአዎግ ሰዎቜ ድንበር አቋርጠው ናይሮቢ ይገባሉ። በናይሮቢ አድርገው ወደ ሌላ አገር ለመኮብለል ጊዜያዊ ማሚፊያ መጠነኛ ሆቮል ይኚራዩና ለሁለት አንድ ላይ ያርፋሉ። አንደኛው ኚሰዎቜ ጋር ቀጠሮ እንዳለው አስታውቆ ወደ ጉዳዩ ይሄዳል። ቀጠሮው ቊታ ቆይቶ ለጓደኛው ስልክ ሲደውል “እንዳትመጣ፣ ጓደኛህን ኚተኛበት ገብተው ዚማይታወቁ ሰዎቜ ወስደውታል” ዹሚል መልዕክት ይደርሰዋል። ኚዚያን ቀን ጀምሮ ስለጓደኛው ሰምቶ አያውቅም። እሱም አገር ቀይሮ በስደት በመንኚራተት ላይ ይገኛል።
ኬንያ ሶስት ዓይነት ስደተኞቜ አሉ። በኢኮኖሚ ድቀት ዚዕለት ጉርስ ፍለጋ ዚሚሰደዱ፣ በፖለቲካ ሳቢያ ኢህአዎግን ሜሜት አገር ለቀው ዚወጡ፣ በኢህአዎግ ልዩ ተልኮ ስደተኛ መስለው ኬንያ ዚሚኖሩ፤ ኚናይሮቢ በስልክ ለጎልጉል መሹጃ ዚሰጡት ወገኖቜ እንደደሚሉት በዹጊዜው እዚታፈኑ ወደ አገርቀት ዚሚላኩ ጥቂት አይደሉም። ይህ ዹሚሆነው ደግሞ በኬንያ ውስጥ ኢህአዎግ እጀ ሹጅም በመሆኑ ነው። በዚህም ሳቢያ ለፖለቲካ ስደተኞቜ እያንዳንዷ ቀን ዹሰቀቀን ነቜ። ራስን ዹመጠበቅ!!
ዚኬንያ መንግስት “ለደህንነቮ ቅድሚያ” በሚል ሰሞኑንን ያስተላለፈው መመሪያ በስደት ናይሮቢ ዚሚኖሩትን ወገኖቜ ያስደነገጣ቞ውም ለዚሁ ነው። በኬንያ ዚሚኖሩ ስደተኞቜ ኹተማ ለቅቀው ወደ ካምፕ እንዲገቡ በተላለፈው ትዕዛዝ መሰሚት መመሪያው ዚሚመለኚታ቞ው ኢትዮጵያዊያን ዚመፍትሄ ሃሳብ ዹላቾውም። ግን ጭንቀታ቞ውን ለማሰማት ያህል ይናገራሉ።
በናይሮቢ ዹዓለም ዚስደተኞቜ ኮሚሜንን ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ካሉት ስደተኞቜ መካኚል አንዱ ብርሃኑ በዹነ ይባላል። በዝዋይ ማሚሚያ ቀት ታስሮ ተገርፏል። እሱ እንደሚለው ዚኬንያ መንግስት ሁሉንም ስደተኞቜ ባንድ መነጜር ሊመለኚት አይገባም። በጅምላ ኹዘጠኝ አገሮቜ ተሰድደው ኬንያ ለገቡት ጥገኝነት ጠያቂዎቜ በግል ዹፋይል ቁጥራ቞ው ወደ ካምፕ እንዲገቡ መመሪያ ተላልፏል።
በአዲሱ ዓመት ግርግር ጉዳዩ ተጓተተ እንጂ መመሪያው ተግባራዊ መሆኑ አይቀሬ ነው። ዚስደት ማመልኚቻ቞ውን አስገብተው በተባበሩት ዚስደተኞቜ ኮሚሜን እውቅና ናይሮቢ እንደፍጥርጥራ቞ው ተቀምጠው ጉዳያ቞ውን ዚሚኚታተሉም ሆኑ፣ በስደት ካምፕ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ኹቀላል ዚርስ በርስ ጞብ በስተቀር በወንጀል፣ በግድያና በጞያፍ ተግባር አይታወቁም። ኹዚህም በላይ ለናይሮቢ ነዋሪዎቜ ስጋት ዚሚሆኑበት አንድም አግባብ እንደሌለ ብርሃኑ ያስሚዳል።
በኬንያ ስደት ካምፖቜ ሙቀታ቞ው ኹፍተኛ፣ ለመኖሪያ ዚማያመቹ፣ ለአካባቢ ወለድ በሜታዎቜ ዚተጋለጡ፣ በቂ ዚመኖሪያ ግብአት ያላሟሉ ኹመሆናቾው በላይ ትልቁ ቜግር ዚደህንነት እንደሆነ ያመለኚተው ብርሃኑ አብዛኞቜን ስጋት ላይ ስለጣለው ጉዳይ “ተመሳስለው በስደተኛ ስም ኬንያ ዚገቡት ዚኢህአዎግ ዚስለላ ሰዎቜ በዹቀኑ ሰዎቜን ያድናሉ። ወደ ኢትዮጵያ ይወስዳሉ። በዚህ መልኩ ዚታፈኑ በርካታ ናቾው። አንድ ላይ ተሰባስበን እንዎት እንቀመጣለን? ይህ እጅግ አሳሳቢና ኹፍተኛ መዘዝ ዚሚያስኚትል ዚሰብአዊ መብት ጥሰት ነው” ሲል ዚኬንያ መንግስት ውሳኔውን ሊያጀን እንደሚገባው ያሳስባል።
ይህ ብቻ አይደለም በኬኒያ ያለው ሙስናም ሌላው ስጋት ነው። “በኬንያ ገንዘብ ካለ ሁሉንም ማድሚግ ይቻላል። ኢህአደግ ገንዘብ አለው። ገንዘብ ኹተኹፈለ ዋስትናቜንን አሳልፎ ዚመስጠት ውሳኔም ሊወሰን ይቜላል” ዹሚለው ግርማ ጉተማ “ኩነግን ፍርሃቻ በዚስርቻው ዚሚንቀሳቀሰው ኢህአዎግ ይጥቀመው እንጂ ማንኛውንም ነገር ዚማድሚግ ሞራል ስላለው ዋስትናቜን ዹተመናመነ ያህል ይሰማኛል” ይላል።
ሁሉም እንደሚሉት ዚኬንያ መንግስት ውሳኔውን ተግባራዊ ኚማድሚጉ በፊት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቜ ድምጻ቞ውን በያሉበት ሆነው ሊያሰሙ ይገባል። በዚአቅጣጫው ጉዳዩን በማስመልኚት ለኬንያ መንግስትና ለሚመለኚታ቞ው ክፍሎቜ ዚስጋቱን ደሹጃ ማሳወቅ ለነገ ዚማይባል አንገብጋቢ ጉዳይ እንደሆነ አበክሹው ያስሚዳሉ። በኬንያ ኚደቡብ ኢትዮጵያ፣ ኚአማራና ኚኊሮሚያ ዚሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር አብላጫውን ቁጥር ይይዛል።
Dadaab refugee camp, Kenya
ዳዳብ ዚስደተኞቜ ካምፕ ኬኒያ ሐምሌ 2003(ፎቶ:AlertNet)
በኬንያ በተደጋጋሚ በደሹሰ ዚቊንብ ጥቃት ሳቢያ ዜጎቜ ኚስደተኛ ዚሶማሌ ዜጎቜ ላይ ጥቃት መሰንዘራ቞ውና፣ ዚሶማሌ ዜጎቜን በመቃወም ዚኬንያዊያን ጥያቄ ገፍቶ በመምጣቱ መንግስት ሁሉም ስደተኞቜ ወደ ካምፕ እንዲገቡ ዚሚያስገድድ መመሪያ አውጥቷል። ዚኬንያ ዚመኚላኚያ ሃይል በሶማሌ ዚአልቃይዳንና ዚአልሞባብን ሃይል ኚዩጋንዳ፣ ኚብሩንዲና ኚኢትዮጵያ ሰራዊት ጋር በመሆን ማጥቃቱ ለቊንብ አደጋው እንደ ምክንያት ቢገለጜም፣ ዚኬንያ መንግስት ውሳኔውን ያሳለፈው አጠቃላይ አገሪቱ ውስጥ ለገቡት ስደተኞቜ ሁሉ ነው።
በዓለም ትልቁ ዚሚባለውና አብዛኛዎቹ ኚሶማሊያ ዚሚመጡት ስደተኞቜ ዚሚገኙበት ዚዳዳብ ካምፕ ኚግማሜ ሚሊዮን በላይ ስደተኞቜን ዹሚገኙ በመሆናቾው ተጚማሪ ስደተኞቜን ሊጹምር ባይቜልም ሌሎቜ አዳዲስ ካምፖቜን በማሰራት ስደተኞቜን ወደዚያው ለማጎር እዚታሰበ እንደሆነ ኚኬኒያ ዚሚወጡ ዜናዎቜ ይጠቁማሉ፡፡

ተስፋ መቁሚጥ ዹወለደው እርምጃ – መስጊድ ነጠቃ!


ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞቜ መሠሚታዊ ዚእምነት ነፃነት መብታቜን ተጥሶ ለተቃውሞ አደባባይ ኚወጣን ድፍን አንድ አመት ሞላን፡፡ ይህ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞቜን አንድ ላይ ያስተሳሰሚ ተቃውሞ መነሻውም ሆነ መድሚሻው ዚመንግስት በሐይማኖታቜን ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነትና ዹህገ መንግስቱ ድንጋጌዎቜ በይፋ መጣሳ቞ው ነው፡፡ አሕባሜ ዹተሰኘውን አንጃ ኚሊባኖስ በማስመጣት በሙስሊም ዜጎቜ ላይ በኃይል ለመጫን ዹተደሹገው ሙኚራ ለዚህ ዹኹፋ ድርጊት ዋነኛ ማሳያ ነው፡፡ተስፋ መቁሚጥ ዹወለደው እርምጃ - መስጊድ ነጠቃ!
አሕባሜ በኹፍተኛ መዋዕለ ነዋይ ታጅቊ በመንግስት ጋባዥነት ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ሊፈፅማቾው ያሰባ቞ው በርካታ ፕሮጀክቶቜ ነበሩት፡፡ በሃሮማያ ዩኒቚርሲቲ ዚአህባሜ ዚግዳጅ ጠመቃ ላይ በወጣው ባለ 15 ነጥብ ዹአቋም መግለጫ መሰሚት ኢትዮጵያ ውስጥ ዹሚደሹግ ማንኛውም ዚሙስሊሞቜ እንቅስቃሎ በአህባሜ ዚመጅሊስ አስተዳደር ጥብቅ ቁጥጥር ስር እንዲውል፣ ማንኛውም ዚመስጂድ ኢማምም ሆነ ዳዒ ይህንን ዚአሕባሜን ስልጠና እንዲሳተፍ፣ ዚአሕባሜን ስልጠና ያልወሰደ ማንኛውም ኢማም ማሰገድ እንደማይቜልና ስልጠናውን ያልወሰደ ኢማም ቊታም ስልጠናውን በወሰደ ሌላ ሰው እንደሚተካ፣ ዚአህባሜን ስልጠና ያልወሰደ እና ኚአህባሜ ዚመጅሊሱ አስተዳደር ሰርተፊኬት ያልተሰጠው ማንኛውም ዳዒ በዚትኛውም መድሚክ ዚኃይማኖት ትምህርት እንዳይሰጥ፣ በሕብሚተሰቡ ጉልበት፣ ሀብትና ጥሚት ዚተገነቡ ማንኛውም ኢስላማዊ ተቋማት ለአሕባሜ እንዲሰጡ… አዋጅ መታወጁ ይታወሳል፡፡
ይህ አዋጅና በኹፍተኛ ዚመንግስት ሁለንተናዊ እገዛ ዹተደሹገው ዚአሕባሟቜ እንቅስቃሎ ዚህዝብን ቁጣ ቀስቅሶ እነሆ መብሚጃ ወዳልተገኘለት ቀውስ ውሰጥ ገብቶ ይገኛል፡፡ ሕዝበ ሙስሊሙ በወሰዳ቞ው ቆራጥ ዹተቃውሞ እርምጃዎቜ ዚአሕባሜ ፕሮጀክቶቜ አንድ ባንድ ተንኮታኚተዋል፡፡ ዛሬ ስለ አህባሜና አደገኛ ሎራው ያልተሚዳ እና ራሱንም ቀተሰቡንም ኹአደጋው ያልጠበቀ ሙስሊም ግልሰብ ማግኘት አዳጋቜ ነው፡፡ ይሁንና መንግስት በዚህ ተፀፅቶ እርምት ሊወስድ ሲገባው አላስፈላጊ እልህ ውስጥ በመግባት እነሆ ዚብዙ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞቜ እጣ ፋንታ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም መሠሚት ዚአህባሜ ፕሮጀክት ዚመጚሚሻ ተግባራትን ዚፖለቲካ ኃይሉን ተገን አድርጎ ለማስፈፀም እዚተጋ ይገኛል፡፡
መንግስት ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ያደራጃ቞ውን ቡድኖቜ ስትራ቎ጂካዊ ቅርጫ በማድሚግ ነባሩን ዚአሕባሜ አመራር በሌላ ዚአሕባሜ አመራር አካላት ተክቷል፡፡ ይህም ለቀጣይ ዚመጚሚሻ ዚአህባሜ ፕሮጀክት አፈፃፀም እንደሚሚዳው በመተማመን እነሆ በአሁኑ ሰዓት ይህንኑ ድፍሚት ዚተሞላበትን እርምጃ መውሰድ ጀመሯል፡፡ በሕዝብ ንፁህ ሀብት፣ ጉልበት፣ ደምና መስዋዕትነት ዚተገነቡ ኢስላማዊ ተቋማትም ሆኑ መስጂዶቜ ለሙስሊሙ ሕዝብ ትርጉማ቞ው ኹ‹‹áŒáŠ•á‰¥›› ኹ‹‹áˆ•ን›› በላይ ነው፡፡ አይደለም ዛሬ ዚመጣበትን አደጋ ለመኹላኹል እጅ ለእጅ ተሳስሮ አንድነቱን ይፋ ባደሚገበት ወሳኝ ጊዜ ላይ ይቅርና ያኔም በቀደመው ጊዜ በነኚህ ሀብቶቹ ላይ ዚመጣውን አካል ያለምንም ማቅማማት ሲጋፈጥ ቆይቷል – በዚህ ጉዳይ ተደራድሮም አያውቅም፡፡
ሰሞኑን በአንዳንድ አካባቢዎቜ በተለይም እዚህ በመዲናቜን አዲስ አበባ እና ደሮ ኹተማ እዚተደሚገ ያለው አደገኛ አካሄድ አፀፋ ኹማውገዝም በላይ ሊሆን እንደሚቜል ማንም ጀነኛ አእምሮ ላለው ሰው ዹሚጠፋው አይደለም፡፡ ህዝብ ጥሮ ግሮ ያፈራ቞ውና ለዘመናት ጠብቆ ያቆያ቞ውን መስጂዶቜ በፖሊስና በወታደር ኃይል በማስፈራራት፣ በመኚብበብና በማገት ለመንጠቅና እና ለአሕባሟቜ አሳልፎ ለመስጠት ኹፍተኛ ጥሚት እዚተደሚገ ይገኛል፡፡
በተለይም በደሮ ኹተማ እዚተስተዋለ ያለው ሁኔታ ትእግስትን ዚሚፈታተን ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው፡፡ ዹዚህ ዚመንግስት አካሄድም ተልዕኮውም ግልፅ ነው፤ ህዝብን ለአመፅ በማነሳሳት እልቂትና ፍጅትን መጋበዝ ነው፡፡ መስጂዶቻቜንን መንጠቅ፣ ኢማሞቻቜንን በማባሚር በአሕባሟቜ መተካት በዚትኛውም ሐይማኖት ተኚታዮቜ ላይ ታስቊ እንኳን ዚማይታወቅ ድፍሚት ነው፤ ዹዚህን ድርጊት መቀጠል ተኚትሎ ለሚኹሰተው ማንኛውም ጥፋት መንግስት ራሱ ተጠያቂ እንደሚሆን ቀድሞ ሊያምንበት ይገባል፡፡ መስጂዶቻቜን ዚህልውናቜን ጉዳዮቜ ናቾው፡፡
አሕባሟን ኚማደራጀትና በሌላው ላይ በግድ ኚመጫን ያልተቆጠበው መንግስት ዚህዝብ ንብሚት በሆኑት መስጂዶቻቜን ላይ ወሚራ ኚማካሄድ ዚራሳ቞ውን መስጂድ ሊገነባላ቞ው ይቜላል፡፡ ኹዚህ ቀደም በኚሞፉት ዚአሕባሜ ፕሮጀክቶቜ፤ በተለይም ሕብሚተሰቡ በአንድ ድምጜ ዚአሕባሜን አስተሳሰብ ኚእውቀት በመነሳት አንቅሮ በመትፋቱ በመበሳጚትና በተስፋ መቁሚጥ ስሜት ተውጩ ያለ ዹሌለ ሃይልን በመጠቀም በተጚባጭ እዚተደሚገ ያለው እንቅስቃሎ መዘዙ ዹኹፋ እና ዚአገራቜንንም ገፅታ እስኚመጚሚሻው ድሚስ ሊያበላሜ እንደሚቜል ሊታሰብበት ይገባል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙም መቌም ቢሆን መስጂዶቹን አሳልፎ እንደማይሰጥ ቢታወቅም በተዘጋጀለት ወጥመድም ላይ እንደማይወድቅም ሊታወቅ ይገባል፡፡
አላሁ አክበር!

Jan 4, 2013

ዹለንደኗ ማሪያም ቀ/ክን ወዎት እያመራቜ ነው? – ኚታምሩ ገዳ (ጋዜጠኛ)




ዹለንደኗ ማሪያም ቀ/ክን ወዎት እያመራቜ ነው?

ኚታምሩ ገዳ (ነጻ እና ዹግል አሰተያዚት)

በምድሚ እንግሊዝ በለንደን ኹተማ ዚምትገኘው ዚርእሰ አድባራት ደብር ጜዮን  á‰…ድስት ማሪያም  á‰€á‰°áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ• ፈታኝ ዹሆኑ ቜግሮቜን
በመጋፈጥ  áˆ‹á‹­ ትገኛለቜ፡፡
ዚቀተክርስቲያኒቱን  áˆµáˆ በግል ስማ቞ው  áˆˆáˆ›á‹›á‹ˆáˆ­  áŒ¥áˆšá‰µ አድርገዋል ዚተባሉ ሁለት  áˆáŠ¥áˆ˜áŠ“áŠ•   ኚአባልነት  á‰³áŒˆá‹±፡
ዚስብኚተ ወንጌል አገልግሎት ለመስጠት ወደ ቀተክርስቲያኔቱ  áŒá‰¢ ያቀኑ  áˆáˆˆá‰µ አገልጋዮቜ  á‰°á‰ƒá‹áˆž ገጠማቾው ፡
ዚጞጥታ ሃይሎቜ  á‰ á‰€á‰°áŠ­áˆ­á‰²á‹«áŠ’á‰± ጉዳይ   ሰሞኑን ሁለት ጊዜ ተጠርተዋል፡፡
ኚተመሰሚተቜ  áŠšáˆ¶áˆµá‰µ አስርት አመታት በላይ  á‹«áˆµá‰†áŒ áˆšá‰œá‹  á‹šá‹°á‰¥áˆš ጜዮን  á‰…ድስት  áˆ›áˆªá‹«áˆ  á‰€á‰°áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ•   በሺዎቜ ለሚቆጠሩ
በለንደን እና  á‰ áŠ áŠ«á‰£á‰¢á‹‹ ለሚገኙ ዚኢ/ኩ/ተ/ ቀ/ክን አማኞቜ  áŠ áˆá‰£ እና  áˆ˜áŒ áŒŠá‹«  á‰ áˆ˜áˆ†áŠ•  áˆµá‰³áŒˆáˆˆáŒáˆ  á‰†á‹­á‰³áˆˆá‰œ ፡፡ዚድንግል ማሪያምን
አምላጅነት  áŠ áˆáŠá‹  á‹šá‰°áˆ›áŒžáŠ—á‰µ  á‰ áˆ­áŠ«á‰³  áˆáŠ¥áˆ˜áŠ“áŠ•  áŠ á‹«áˆŒ  á‰°áŠ áˆáˆ«á‰µ ሲሰራላ቞ው  áŠ¥áŠ•á‹°á‰†á‹©  á‰ á‰°á‰ƒáˆ«áŠ”á‹  á‹µáŒáˆž ዚማሪያምን  áŒ¥á‰…ሟን
ዚነኩ   ወገኖቜ   አይወድቁ አወዳደቅ እንደገጠማ቞ው  áŠ¥áŠá‹šáˆ  áˆ›áŠ¥áˆ˜áŠ“áŠ•  á‹šáˆ˜áˆ°áŠ­áˆ«áˆ‰፡፡ ይህቺ ለአብዛኛው ስደተኛ  áˆ›áˆ…በሚሰብ  á‰ áˆƒá‹˜áŠ•
ሆነ በደስታ ጊዜያት መሰባሰቢያ እና  áˆ˜áŒœáŠ“áŠ›  á‹šáˆ†áŠá‰œ ቅድስት ቀ/ክን  áŠšáŠ áˆ«á‰µ አመት  á‰ áŠá‰µ  á‰ 1,700, 000 ዚእንግሊዝ  á“ውንድ
(47,600,000 ብር ) ዚራሷ ዹሆነ ህንጻ ቀ/ክን  áŒá‹¢ ሲፈጞም  á‰¥á‹™á‹Žá‰œ ህልማቾው እውን መሆኑን በማዚታ቞ው ዚደስታ  áŠ¥áˆá‰£á‰žá‹áŠ•
አምብተዋል፡፡ ሁኔታውንም በጊዜው  á‰ áŒáŠ•á‰£áˆ­  á‰°áŒˆáŠá‰Œ ለተለያዩ ድህሚ ገጟቜ ዘግቀዋለሁ ::
ኚቅርብ ጊዚያት  á‹ˆá‹²áˆ… ግን  á‰€áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ”á‰± በምን  áˆ˜áˆáŠ© ትተዳደር?፡ ዹ ጊዜ ገደቡ ያለፈው ዚሰበካ ጉባኀው  áˆ˜á‰Œ ነው  á‹ˆáˆ­á‹¶ አዲስ
አባላት ዚሚመሚጡት?  ፡ ቀክርስቲያኔቱ ኚዚትኛው   ቅዱስ  áˆ²áŠ–á‹¶áˆµ  áŒ‹áˆ­ ትሁን ?(በአገር ቀት   ካለው ሲኖዶስ ? ወይስ  á‰ á‹áŒª ካለው
ሲኖዶስ?  á‹ˆá‹­áˆµ   አሁን ባለቜበት በገለልተኛነት አቋሟ ትጜና?...  á‹ˆá‹˜á‰°) ዹሚሉ ሃሳቊቜ ዙሪያ  á‹šá‰°áŠ«áˆšáˆ© እሰጣ ገባዎቜ በሃሳቊቹ ደጋፊዎቜ
እና በተቃዋሚዎቜ  áˆ˜áŠ«áŠšáˆ በአውደ ምህሚት ላይ: በኪራይ አዳራሟቜ  áŠ¥áŠ“  á‰ á‰°áˆˆá‹«á‹© ደህሚገጟቜ  áŠ áˆ›áŠ«áŠáŠá‰µ ሲንሞራሞሩ   ተስተውለዋል፡፡
ወደ ዋና ዚጜሁፊ  áˆ˜áŠáˆ»  á‹ˆá‹°áˆ†áŠá‹  á‹ˆá‰…ታዊ ዚቀተክርስቲያኒቱ ቜግሮቜ  áˆ°áˆ˜áˆˆáˆµ  áŠ áŠ•á‹µ ወር ባልሞላ  áŒŠá‹œ ውስጥ  áˆ°áˆˆá‰°áŠšáˆ°á‰± አንኳር
ዚቀተክርስቲያኒቱ  á‰œáŒáˆ®á‰œ  áˆ˜áŠ«áŠšáˆ በሁለቱ ጉዳዮቜ  á‹™áˆªá‹« ትንሜ ዹግሌን አሰተያዚት  áˆáˆ°áŠ•á‹áˆ­ ፡፡
ባለፈው ታህሳስ 13 ቀን 2005 አ/ም (22 ታህሳስ   2012 እኀአ )ዚቀተክርስቲያኒቱ አሰተዳደር ጉባኀ  á‰  Ref DTM 568 Ext-Msl
00568/ 12 ያወጣው  á‹°á‰¥á‹³á‰€  áŠ¥áŠ•á‹°áˆšá‹«áˆ˜áˆˆáŠ­á‰°á‹  “አቶ ግርማ  á‰°áˆŠáˆ‹  áŠ¥áŠ“  áŠ á‰¶ ጥላዬ ዚሻነው   ዚተባሉ ምእመናን በመስኚሚም 2
2012 እ ኀ አ ዚቀተክርስቲያኒቱን  áˆµáˆ በመጠቀም ኩባንያ  áŠ«áˆá“áŠ” ቁጥር 8200045 ዹሚል  á‰ áŠ á‰¶ ግርማ  á‰°áˆŠáˆ‹  á‹šáˆ˜áŠ–áˆªá‹« ቀታ቞ው
አድራሻ  á‰ áˆ›á‹áŒ£á‰µ  áˆ‹áˆˆá‰á‰µ  áˆ¶áˆµá‰µ  á‹ˆáˆ«á‰µ  á‹«áˆ…ል  áŒ‰á‹³á‹©áŠ•  á‹°á‰¥á‰€á‹  áŠ áŠ•á‹°á‰†á‹©  á‰ áˆ˜á‹°áˆšáˆ± ሁለቱ ግለሰቊቜ   ኚቀተክርስቲያኒቱ
አባልነታ቞ው  áˆˆáŒŠá‹œá‹ እነደታገዱ” ይፋ አድርጎ ወደፊትም  á‰ áˆ…ግ እንደሚጠዚቁ  á‹šá‰€/ክኗ ማህተም እና ፊርማ  á‹«á‹˜áˆˆá‹  áˆ˜áŒáˆˆáŒ«
ያትታል፡፡  á‹­áˆ… መግለጫ ባለፈው እሁድ እለት (ኚሁለት ሳምንት በፊት ) ለምእመናኑ   በአውደ ምህሚት ላይ ይፋ በተደሚገበት  á‹ˆá‰…ት
“ዚሁለቱ ግለሰቊቜ  áˆƒáˆ³á‰£á‰œá‹ መደመጥ አለበት በሚሉ እና ዚለበትም” በሚሉ ወገኖቜ መካኚል  á‹šá‰°áŠ«áˆšáˆš አስጣ ገባ  áŠ¥áŠ•á‹°áŠá‰ áˆ­ ፡
ሁኔታውንም ለማርገብ ዚጞጥታ ሃይሎቜ  áŒ£áˆá‰ƒ እንደገቡ በእለቱ ዹተገኙ ምእመናኖቜ ሁኔታውን በሃዘኔታ አጫውተውኛል ፡፡ጉዳዩም
በህግ ዚተያዘ በመሆኑ  áˆˆáŒŠá‹œá‹  á‰¥á‹™  áŠ áˆµá‰°á‹«á‹šá‰µ መስጠት ባይቻልም  áˆáˆˆá‰±  “ተወቃሜ ግለሰቊቜ” በ 19 ታህሳስ  2012 እኀአ  á‰  ኀ-ሜል
አማካኝነት አሰተላለፉት ዚተባለ እና ስማ቞ው  á‹šáˆ°áˆáˆšá‰ á‰µ  áŠáŒˆáˆ­ ግን ፊርማቾውን ያላካተተ   ጾሁፍ አንዳመለኚተው ኹሆነ
“ቀተክርስቲያኔቱን  á‰ á‰»áˆªá‰°áŠ¥á‰¥áˆŒ  áŠ«áˆá“áŠ’á‹­   ሊሚትድ ባይ  áŒ‹áˆ«áŠ•á‰²   ለማቋቋም ወራት ዹፈጀው  áŠ¥áŠ“  áŠ¥áˆµáŠšáŠ áˆáŠ• ድሚስ  áŠ¥áˆá‰£á‰µ  
ያላገኘው ድርድር ባለመቋጚቱ  áˆˆá‰€á‰°áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ’á‰±  á‰°áŒˆá‰¢á‹  á‹šáˆ†áŠá‹áŠ• ሰው ሌላ ግለሰብ ወይም ድርጅት  áŠ¥áŠ•á‹³á‹­á‹ˆáˆµá‹µá‰£á‰µ  á‰ áˆ›áˆ°á‰¥
ዚቀተክርስቲያኒቱን ስም ተጠቅመናል ፡፡ሁኔታዎቜ  áˆ²áˆšáŒ‹áŒ‰  á‹«áˆµáˆ˜á‹áŒˆá‰¥áŠá‹áŠ•  á‹µáˆ­áŒ…ት በነጻ  áˆˆá‰€á‰°áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ’á‰±  á‰ á‰»áˆªá‰°á‰¥áˆ ካምፓኒ
ሊሜትድ ባይ ጋራንቲ  áŠ á‰µáˆ˜á‹˜áŒˆá‰¥áˆ   ኚተባለ በስማቜን  á‹«áˆµáˆ˜á‹˜áŒˆá‰¥áŠá‹  á‹µáˆ­áŒ…ትን   ወዲያውኑ  áŠ¥áŠ•á‹°áˆáŠ•á‹˜áŒ‹  áˆˆáˆ°á‰ áŠ« አሰተዳደር
ለማስተዋወቅ እንወዳለን::” ይላል፡፡  áˆáˆˆá‰± ግለሰቊቜ  áŠ¥áˆµáŠš አሁን ድርስ ለምን ዝምታን መሚጡ? እነርሱን ይህንን ታላቅ ሃላፊነት በግል

እንዲቀበሉ ማን መሚጣ቞ው? ቀተክርስቲያኒቱ   ዚውሳኔ መግለጫ ካወጣቜ በሁዋላ  áˆˆáˆáŠ• ዚማስተባበያ    á‹°á‰¥á‹³á‰€ ማውጣት አሰፈለገ
?ለሚሉት እና  áˆ˜áˆ°áˆ ጥያቄዎቜ ተጠቃሟቹ ግለሰቊቜ ሆኑ በእነርሱ ስም ዚጻፉት ወገኖቜ ለጊዜው ያሉት ነገር ዹለም፡፡  á‹šáŠ¥áŠá‹šáˆ…áŠ• ሁለት
ግለሰቊቜ ተግባር “እንደግፋለን”  á‹šáˆšáˆ‰ ነገር ግን ሰማቾውን እና ማንነታ቞ውን በውል ያልገለጹ ወገኖቜ ያሰራጩት  áˆ˜áˆáŠ¥áŠ­á‰µ  á‰ á‰ áŠ©áˆ‰
አንደሚያትተው ኹሆነ  “ሁለቱ ግለሰቊቜ ዚኚፈቱት  á‹µáˆ­áŒ…ት  áŠšáˆˆáŠ•á‹°áŠ— ጜዮን  áˆ›áˆªá‹«áˆ   ቀ/ክን  áŒ‹áˆ­ አይገናኝም”  á‹šáˆšáˆ መልእክት ያዘለ
ሲሆን  á‹­áˆ„ው ጜሁፍ  á‹ˆáˆšá‹° ብሎ “ሁለቱ  áŒáˆˆáˆ°á‰Šá‰œ  ( አቶ ግርማ እና አቶ ጥላዮ)  á‹­áˆ…ንን አርምጃ ዚወሰዱት  áˆŒáˆŽá‰œ  áŒáˆˆáˆ°á‰Šá‰œ
ዚቀተክርስቲያኒቱን   ስም  áŠ¥áŠ•á‹³á‹­áŒ á‰€áˆ™ ወይም እንዳይወስዱ  áˆˆáˆ›á‹µáˆšáŒ  áŠ áˆµá‰ á‹ ነው::” ዹሚል ድጋፍ  áŠ á‹­áŠá‰µ  áˆ˜áˆáŠ­á‰µ
እስተላልፏል፡፡
ሌላኛው   አራሳ቞ው ዚቀተክርስቲያኔቱ  áŠ«áˆ…áŠ“á‰µ እና ምእመናን በሚል ሰም  á‰ áŠ€-ሜል አማካኝነት  áˆ°áˆžáŠ‘áŠ• ዚተሰራጚ ዚቅስቀሳ  áŠ¥áŠ“
ማስጠንቀቂያ   መልእክት  á‹šá‰°áˆ°áˆ«áŒš ሲሆን ዹዚህ  á‹ˆá‰€áˆ³ ሰለባዎቜ መካኚል  á‹šá‹°á‰¥áˆ© አሰተዳዳሪ  á‹šáˆ†áŠ‘á‰µ ቆሞስ አባ  áŒáˆ­áˆ› ኹበደ   አንዱ
ሲሆኑ   ይሄው  áŒœáˆá “ዚማሪያም ቀ/ክን   ኚስላሎ ቀ/ክን ጋር ያላትን ዹአቋም ልዩነት  á‹ˆá‹° ጎን አደርገው  áŠšáˆµáˆ‹áˆŽ ቀ/ክን  áŠ¥áŠ“  áŠšáˆŒáˆŽá‰œ
ዚሟቹ ፓትሪያርክ አባ ጳውሎስ  á‹°áŒ‹áŠá‹Žá‰œ  áŒ‹áˆ­  á‰ áˆ˜á‹ˆáŒˆáŠ• ዚቀተክርስቲኗን  áˆ…ልውና  áŠ áˆ³áˆáŽ ዚሚሰጥ  á‰°áŒá‰£áˆ­  áŠ¥á‹šáˆáŒžáˆ™ ሲሆን  á‹­áˆ…
ድርጊታ቞ው   በቀተክርስቲያኒቱ  áŠ á‰£áˆ‹á‰µ  áˆáŒ¥áŠ– ካልተገታ  á‰€á‰°áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ“á‰œáŠ•áŠ•  áŠšáŠ¥áŒƒá‰œáŠ• ወጥታ ልትቀር አንደምትቜል በሚገባ መሚዳት
ያሰፈለጋል… ወዘተ፡፡ “  á‹­áˆ‹áˆ፡፡  á‹­áˆ„ው  á‹šá‰…ስቀሳ ኢ-ሜል ጜሁፍ አንገብጋቢ ቜግር ነው ያለውን ጉዳይ  áˆ²á‹«á‰¥áˆ«áˆ« “ በርእሰ  áŠ á‹µá‰£áˆ«á‰µ
ለንደን ጜዮን  áˆ›áˆªá‹«áˆ ቀ/ክን  á‹šáˆšá‹°áˆšáŒˆá‹ ቅዳሎ:  á‰áˆ­á‰£áŠ•:  áŠ­áˆ­áˆµá‰µáŠ“  áˆáˆ‰ ዚማይሰራ እና   ዹተወገዘ ነው በማለት  á‰€á‰°áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ“á‰œáŠ•áŠ•
ዚኮነነ  áŠ¥áŠ“  áˆµáˆŸáŠ•   ያሚኚሰ   ዲያቆን  á‰¥áˆ­áˆƒáŠ‘  á‹šá‰°á‰£áˆˆ ሰባኪን ኚስላሎ ቀ/ክን  á‰ 16 ታህሳስ   2012 እኀአ   በማምጣት   ዲ\ን ብርሃኑ ዚአባ
ግርማ ኹበደን  áŠ áˆ‹áˆ›áŠ•  áˆŠá‹«áˆ³áŠ«   ዚሚቜል ስብኚት  áŠ¥áŠ•á‹²á‹«á‹°áˆ­áŒ  áŠ á‰£ ግርማ ጥሚት  á‰ áˆ›á‹°áˆšáŒ ላይ ናቾው…  á‹ˆá‹˜á‰°፡፡ “ዹሚል  áŠá‹
በአጭሩ፡፡
እውን አባ ግርማ ኹበደ  360 ዲግሪ ተቀዚሩ?
  ዚቀተክርስቲያኒቱ አስተዳዳሪ ዚሆኑት ቆሞስ አባ ግርማን እስኚ ቅርብ ጊዜ እስኚ ማቃቾው ድሚስ በኢትዮጵያ ያላውን ዚሰብአዊ መበት  áŠ¥áŠ“
ዚሃማኖታዊ ጭቆናን በተመለኹተ   በርካታ ወገኖቜ ኹአገዛዙ ጋር ያላ቞ው ዚጥቅም እና ዚቅርርቊሜ ትስስር እንዳይቋሚጥቧ቞ው   ዘምታን
በመሚጡበት በአሁኑ ወቅት   አባ ግርማ  áŒáŠ• ድርጊቱን   በአደባባይ በማውገዝ በተለያዩ ሃዝባዊ ዹተቃውሞ  áˆ°áˆáŽá‰œ እና ስብሰባዎቜ ላይ
በመገኘት ለጾሹ- ዚሰባዊ መብት ዘመቻው አጋርነታ቞ውን  á‰ áŒˆáˆƒá‹µ  á‹šáŒˆáˆˆáŒ¹ መነኩሎ ናቾው፡፡  á‹šá‰€á‰°áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ’á‰±áŠ•  áŠ¥áŠ•á‰…áˆµá‰ƒáˆŽ  á‰ á‰°áˆ˜áˆˆáŠšá‰°
ደግሞ መሹጃን እንኳን ለዜና ሰዎቜ ለመስጠት  áˆ™áˆ‰ ነጻነት  á‹šáˆŒáˆ‹á‰žá‹   አባት  áˆˆáˆ˜áˆ†áŠ“á‰žá‹  áŠšáŠ áŠ•á‹²áˆ ሁለት ጊዜ ላነጋግራ቞ው  áˆžáŠ­áˆ¬  
“ጥያቄህ ማእኚላዊነቱን መጠበቅ  áˆµáˆ‹áˆˆá‰ á‰µ በጜሁፍ አቅርብ…ወዘተ”   ያሉኝ  á‹šá‰…ርብ ጊዜ ትዝታዪ ነው ፡፡ ታዲያ  áŠ¥áŠ› በቀተክሚስቲያኒቱ
አስተዳደራዊ  áŒ‰á‹³á‹®á‰œ ዙሪያ እንቅስቃሲያ቞ው  áˆ†áА አነጋገራ቞ው  á‰ áŠ áˆ˜á‹›áŠ™ ውሱን መሆኑ ዚሚታወቀው አባ  áŒáˆ­áˆ›áŠ• አንዳንድ ወግኖቜ
በቅርቡ “አቩይ ግርማ “አስኚ ማለት  á‹°áˆšáˆ°á‹ ሲጠሯ቞ው  áˆµáˆ°áˆ›  áŠ¥á‹áŠ•  á‰†áˆžáˆµ አባ ግርማ  áˆ˜áˆ°áˆšá‰³á‹Š ዹአቋም  áˆˆá‹áŒ¥ አሳዩ?   ወይስ
በታላቁ መጜሃፍ ቅዱስ  á‹áˆµáŒ¥  á‰ á‹šá‹‹áˆ…ነት ዹተመሰለው በጉ ካመሚሚ… ዹሚለውን  á‰ƒáˆ ተግባራዊ አደሚጉት?  áˆµáˆ ኚእይምሮዩ ጋር ሙግት
ገጥሜ ስንብቻልሁ፡፡ በነገራቜን ላይ አባ ግርማ ፍጹም  áˆ°á‹ ናቾው ዹሚል  áŠ¥áˆáŠá‰µ ዹለኝም ፡፡አርሳቜውም ቢሆኑ  “ፍጹም  áŠáŠ “ዹሚሉ
አይመስለኝም፡፡ ታዲያ  á‰ áŠ á‰ á‹›áŠ›á‹ ዹለንደን  áˆ°áˆ‹áˆ›á‹Š እና ህዝባዊ ስብሰባዎቜ እና  á‹šá‰°á‰ƒá‹áˆž ሰልፎቜ  áˆ‹á‹­ ዚማይጠፉት አባ ግርማ  áˆáŠ•
አይነት “ዚሚያማልል   አለማዊ”   ነገር አገኙ ተብሎ ነው “ቀተክርስቲያኒቱን እያመሷት ናቾው …ወዘተ” ዹሚሉ በሚካታ ወቀሳዎቜ
ሰሞኑን ዚሚሰነዘሩባ቞ው?
ኹላይ ዹቀሹበውን  á‹šáŠ€-ሜል  áŒœáˆá በመንተርሰስ  á‰ áˆáˆµáˆ«á‰… ለንደን ኹተማ  áˆˆáˆá‰°áŒˆáŠ˜á‹ እና በአብዛኛው ዚካሪቢያን ተወላጆቜ    áŠ¥áŠ“
ዚኢ/ኩ/ተ/ቀ/ክን  á‰°áŠšá‰³á‹®á‰œ ዹሆኑ ዹ ጞራጌዮን ማሪያም ቀ/ክን  á‰ á‰…ርቡ ለገዙት  áŠ á‹²áˆµ ህንጻ ቀ/ክን ዚማስፋፊያ  á‹šáŒˆá‰¢ ማሰባሰቢያ
ፕሮግራም ኚአዲስ አበባ ለስበኚት ወንጌል  áŠ áŒˆáˆáŒáˆŽá‰µ ተጋብዘው ወደ ለንደን ዚመጡት ዲ/ን መምህር ብርሃኑ   አድማስ እና ዘማሪ ዲ/ን
ምንዳዮ ብርሃኑ  á‰ áŠ á‰£ ግርማ ኹበደ ዹግል ጥሪ ወይስ  á‰ áˆ«áˆ³á‰žá‹ መንገድ ወደ  áˆ›áˆªá‹«áˆ ቀ/ክን ሄዱ? ዹሚል ጥያቄ በአይምሮዬ ውስጥ
ተጭሮ ነበር ፡፡ ለጥያቄዬም ያገኘሁት ምላሜ  áˆáˆˆá‰± አገልጋዮቜ (ዲ/ን በርሃኑ እና ዲ/ን ዘማሪ  áˆáŠ•á‹³á‹® ) በለንደን አና በአካባቢዋ ዹሚገኙ
ዚኢትዮጵያ  ፡ዚካሪቀያን  áŠ áŠ“ ዚኀርትራ ተወላጆቜ ዹሆኑ ዚኊርቶዶክስ  á‰°á‹‹áˆ…á‹¶ ቀተክሚሰቲያኖቜ  á‰ áˆ˜á‹˜á‹‹á‹‹áˆ­ ዚስብኚተ ወንጌል  á‰µáˆáˆ…ርት
እና አገልግሎት  á‰ áˆ˜áˆµáŒ á‰µ  áŠ¥áŠ“  áŠŠáˆ­á‰¶á‹¶áŠ­áˆ³á‹Š መዝሙር በህብሚት በማዜም መሰንበታ቞ውን  á‹šá‰°áˆšá‹±  á‰ áˆˆáŠ•á‹°áŠ•  á‹°á‰ áˆš ጜዮን ማሪያም
ቀተክርስቲን ዹሚገኙ  áˆáŠ¥áˆ˜áŠ“áŠ•   ለቀተክርስቲያኒቱ ዚካህናት  áŒ‰á‰£áŠ€á‹ ባቀሚቡት ጥያቄ መሰሚት አንደተጋበዙ እና  á‹šáˆáˆˆá‰±áŠ•áˆ አገልጋዮቜ
ወደ ማሪያም ቀ/ክን   መምጣት በመቃወም ሚገድ  áˆ˜áˆª ጌታ   አዲስ  áŠ á‹±áŠ›   ዚተባሉ ዚቀተክርስቲያኒቱ አገልጋይ   ብቻ ሲቃወሙ ዚመሪ
ጌታ አዲስ ተቃውሟቾው ተመዘግቩ  á‹šáŒá‰¥á‹£ ሃሳቡ በድምጜ ብልጫ  á‰°á‰€á‰£á‹­áŠá‰µ ማግኘቱን  áˆˆáˆ›á‹ˆá‰… ቜያለሁ፡፡

ሁለቱ አገለጋዮቜ (ዲ/ን በርሃኑ እና ዲ/ን ዘማሪ  áˆáŠ•á‹³á‹® )  á‰ áŒá‰¥á‹£á‹  áˆ˜áˆ°áˆšá‰µ ወደ ማሪያም ቀ/ክን ሲያመሩ  á‹šáŒ á‰ á‰ƒá‰žá‹ ዚዘንባባ
ዝንጣፊ ሳይሆን ሁለቱ አገልጋዮቜ “ ወደ ቀ/ክኗ ይገባሉ… !! አይገቡም…!!  “ዹሚሉ ዚሁለት ወገኖቜ ዹኹሹሹ  áŠ áˆˆáˆ˜áŒá‰£á‰£á‰µ ዚታዚበት እና
ሁኔታውን ለማርገብ እና ለምቃኘት ዚጞጥታ ሃይሎቜ  á‹ˆá‹° ቀተክርስቲያኒቱ  á‹šáŒ‹á‰ á‹˜  áˆáŠ”á‰³  á‰°áˆµá‰°á‹áˆáˆ፡፡ ለሶስት ቀናት ይካሄዳል
ዚተባለው ዚስብኚተ ወንጌል ፕሮግራሙ ሁለቱ  áˆ°á‰£áŠªá‹«áŠ‘ ኚነበራ቞ው ዚተጣበበ  á•ሮግራም ዚተነሳ ለሁለት ቀናት  á‰¥á‰»  á‰°áŠ«áˆ„á‹·áˆ፡፡
ዲ/ን ብርሃኑ  áŠ á‹µáˆ›áˆµ ማናቾው ?
በዚህ ሰብኚተ ወንጌል ላይ ዚተገኙት ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ  “ሰለ ማሪያም  á‰€áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ•  áˆ˜áŒ¥áŽ  áˆµá‰¥áŠšá‰µ  áˆ°áŒ¥á‰°á‹‹áˆ”  á‰°á‰¥áˆŽ   ወቀሳ
ዚተሰነዘሚባ቞ው ሲሆን   በመሰሚቱ  á‹²/ን ብርሃኑ  á‰ áŠ áŒˆáˆ­ ቀት ምን አይነት ስብኚት እንደሚሰጡ ለመታዘብ አጋጣሚውን ባላገኝም በባህር
ማዶ ሰብኚታ቞ው  áŒáŠ•  á‹˜á‹ˆá‰µáˆ­  á‰ áˆµá‰¥áŠšá‰° ወንጌል ትምህርታቜ  áˆ‹á‹­   ጥቁሩን  áŒ¥á‰áˆ­:  áŠáŒ©áŠ•  áŠáŒ­ : ጎባጣውን ጎባጣ :ቀጥ ያለውን
ሞንቃጣ  á‰¥áˆˆá‹ በስሙ   ኚሚጠሩ ጥቂት ዚዘመናቜን  á‹ˆáŒ£á‰µ ሰባኪያን መካኚል አንዱ እንደሆኑ  áŠ¥áŠ“   በተለያዩ ጉባኀዎቜ ላይ
አሰሹገጠው ሲናገሩ ኹሰማሁዋቾው  áˆ˜áˆáŠ­á‰¶á‰»á‰žá‹  áˆ˜áŠ«áŠšáˆ  “ዚኢ/ኩ/ተ/ቀ/ክን  á‹šáˆ«áˆ· ዹሆነ ሰርአት እና  á‹°áŠ•á‰¥ ያላት :  á‹šáˆ›á‰µáŠšá‹áˆáˆ
ሃይማኖታዊ ተቋም በመሆኗ  á‹­áˆ…ንን  áˆ°áˆ­áŠ á‰·áŠ•  á‰ áˆ›á‹ˆá‰…ም ይሁን ባለማወቅ ዚሚያፈርሱ ወይም  á‹šáˆšáŒ»áˆšáˆ­ መንገድ  áˆ‹á‹­ ዹቆሙ
በዹተኛውም  áŒŽáˆ« ዹተሰለፉ ፖለቲኚኞቜ ሆኑ ዚሃይማኖት መሪዎቜ ነን  á‹šáˆšáˆ‰ ወገኖቜ  áŠ áŠ«áˆ„á‹³á‰žá‹áŠ• ሊመሚምሩ ይገባል  ፡
ቀተክርስቲያኒቱም  á‹šáˆ°áˆ‹áˆ እና  á‹šáá‰…ር መድሚክ  áŠ¥áŠ•áŒ‚  á‹šáŒžá‰¥ እና ዚንትርክ ቊታ  áˆáŠ“á‹°áˆ­áŒ‹á‰µ  áŠ á‹­áŒˆá‰£áˆ ፡ በቀተክርስቲያናቜን ህግ እና
ደምብ መሰሚት   ጳጳስ ካልባሚኚው በሰተቀር  áŠ áŠ•á‹µ ቄስ ተነሰቶ አዲስ ቀ/ክን  áˆŠáŠšáá‰µ ወይም ዚድቁና ማእሚግ ለአገልጋዩቜ ሊሰጥ በፍጹም
አይቜልም …ወዘተ “ በማለት   አስሚግጠው ሲሰብኩ  áŠ á‹³áˆáŒ«áˆˆáˆ፡፡ ይህ ሰብኚታ቞ው   ሁሉንም ምእምናን ሊያስድስት  á‹šá‰œáˆ‹áˆ ማለት
ባይቻልም ኚስርአተ  á‰€/ክን አንዱ አካል በመሆኑ መቀበል አለመቀበለ  á‰ áŠ¥á‹«áŠ•á‹³áŠ•á‹± ምእመን  á‹šáˆƒá‹­áˆ›áŠ–á‰³á‹Š ግንዛቀ  á‹°áˆšáŒƒ  áˆ‹á‹­ ይወደቃል
፡፡ ዛሬ አውነታውን ፍርጥርጥ አደርግው ለምናገር ዚሞራል ብቃቱ ሆነ ብልሃቱ ዹጎደላቾው  á‰ áˆšáŠ«á‰³  áˆ˜áˆªá‹Žá‰œ  áˆ†áŠ‘ ሰባኪያን
በተበራኚቱበት አለም ውስጥ ስንገኝ  áŠšá‹ˆáŒˆáŠ•á‰°áŠáŠá‰µ ዚጞዳ ስብኚት  áŠ¥áŠ“ ስርአተ ቀ/ክን ትምህርት  á‹šáˆšáˆ°áŒ¡ ወገኖቜን እንዲያው  á‰ á‹°áˆáŠ“á‹
ማሳጣቱ ወይም ለወቀሳ መዳሚጉ ልዪነቶቜን ኚማስፋቱ በተጚማሪ  áŠ¥áŠ•á‹Ž ጎብዝ ምን አይነት ዘመን ላይ ደሹሰን? ፡ወዎትስ እያመራን ነው?
ዹሚል ጥያቄ ማስነሳቱ  áŠ á‹­á‰€áˆ­áˆ ፡፡ይህ ማለት ግን    á‹šáŠ áŒˆáˆ­ እና  á‹šáˆƒá‹­áˆ›áŠ–á‰µ ጉዳይ ዚጥቂት  áŠ á‹‹á‰‚á‹Žá‰œ ወይም መሪዎቜ   ብቻ ስለሆነ ዝም
በሉ ወይም  á‹šáˆšáˆ°áŒ£á‰œáˆáŠ•  áˆ˜áˆáˆªá‹« ሆነ ውግዘት አሜን ብላቜሁ ተቀበሉ ማለት  áˆ³á‹­áˆ†áŠ•  áˆˆáˆáˆˆá‰µ ሺህ  áŠ áˆ˜á‰³á‰µ ስርአቷን  áŠ¥áŠ“ ትውፊቷን
ጠብቃ ዚቆዚቜ  áˆƒá‹­áˆ›áŠ–á‰µáŠ•   “ዚእነ አባ እገሌ ደጋፊዋቜ  áŠ¥áŠ“ ተቃዋሚዋቜ  á‹ˆá‹­áˆ  áŠšá‹šá‹« ዝቅ ሲል ዹዚህ እለት  áŠ¥áŠ“  á‹šá‹šá‹«áŠ›á‹ እለት
ጉባኀተኞቜ…  á‹ˆá‹˜á‰°”   በሚሉ  áˆá‹©áŠá‰¶á‰œ በመተብተብ  á‹ˆá‹° ማያባራ  áˆá‹©áŠá‰µ ለመውስድ መሯሯጡ   በዚትኛውም  áˆ˜áŠ•áŒˆá‹µ ሊደገፍ
ዚሚገባ አይመስለኝም፡፡ ቢቻል ልዩነቶቜን  áˆˆáˆ›áŒ¥á‰ á‰¥  áˆ˜áˆžáŠšáˆ­ ብልህነት  áŠ¥áŠ“ ዚሚያጞድቅ ስራ ሲሆን ካልሆነ ደግሞ ጊዜ ፈቅዶ ወደ
አንድነት እስኪመጣ ድሚስ  áŠ¥áŠ•áŠ³áŠ•  áˆ‹áˆˆáˆ˜áŠá‰‹á‰†áˆ­  áŠ¥áŠ“áŠ³áŠ•  á‰ áŒšá‹‹ ደንብ ተወያይቶ መለያዚት ሲቻል   ነጋ ጠባ  á‰ áŠáŒˆáˆ­ ቁርቃሶ
መውነጫጚፉ  áŒ‰á‹³á‰± ለተፋላሚ ወገኖቹ ብቻ ሳይሆን ሃይማኖቱን  áˆƒá‹­áˆ›áŠ–á‰Ž ብሎ   ኚፈጣሪው ጋር ለመገናኘት ዘወትር ማልዶ  á‹ˆá‹°
ቀተክርስቲያን ዹሚሄደውን ህዝበ ክርስቲያንን  áˆ›áˆ³á‹áŠ• እና ኚሃይማኖቱ አንዲርቅ  áŠ¥áŠ•á‹°áˆšá‹«á‹°áˆ­áŒˆá‹  áˆ˜á‹˜áŠ•áŒ‹á‰µ ዚለብንም ፡፡
ፖለቲካኛ ገዢዎቜ በተፈራሚቁ ቁጥር  á‹šáŒšááˆá‰€áˆ… ወይም ዹኹፋፍለህ ግዛው ፖሊሲያ቞ውን ለማሳካት ሲሉ ዛሬ ድርሰ  áŠ¥áŒƒá‰žá‹áŠ•
ያላነሱባት ቅድስት  á‰€á‰°áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ•áŠ• ኚተደቀነባት ዹመኹፋፈል እና ዚመለያዚት አደጋ  áˆˆáˆá‰³á‹°áŒ ዹህዝበ ክርስቲያኑ  á‹šáŒ‹áˆ« ጟም ፡ጞሎት እና
ስርአት ያለው ዹተቃውሞ ድምጜ ማሰማት  áŠ áŒá‰£á‰£áŠá‰µ  á‹«áˆˆá‹ እና  áˆŠá‹°áŒˆá ዚሚገባው መንገድ  áˆˆáˆ˜áˆ†áŠ‘ ጥርጥር ዹለውም ፡፡ ይህ ሳይሆን
ቀሚቶ  “አኛ ካልነው  áˆƒáˆ³á‰¥ ውጪ  áˆáŠ•áˆ አይነት  áˆƒáˆ³á‰¥  áŠ á‹­á‰ áŒ€áŠ•áˆ  ፡ ኚዚትኛው ወገን ይሁን ወደ ቀተክርስቲያን ዚሚመጡ  á‹ˆáŒˆáŠ–á‰œáŠ•
ዘወትር በጥርጣሬ  áŠ á‹­áŠ• ማዚቱ … ወዘተ “ ቀተክርስቲያን  áŠšá‰°áˆ˜áˆ°áˆšá‰°á‰œá‰ á‰µ   ሃዋሪያዊ ተልእኮዎቜ   መካኚል አንዱ ዹሆነው   ጠላትህን
እንደ ራስህ አድርገህ ውደደው  á‹šáˆšáˆˆá‹áŠ•  áŠšá‰£á‹µ ትእዛዝን  áˆˆáˆ˜á‰°áŒá‰ áˆ­ ቀሚቶ  “ዹገዛ ወንድምህን  áŠ¥áŠ•á‹°áˆ«áˆµáˆ…  áˆˆáˆ›á‹šá‰µ ሞክር “ በሚል
እንኳን ብንተካው  áŠšáŠá‰³á‰œáŠ•  á‰ áˆ­áŠ«á‰³ ዚቡድን እና ዹግል ፈተናዎቜ   ዚተደቀኑብን  á‹­áˆ˜áˆµáˆˆáŠ›áˆ ፡፡   ( tamgeda@gmail.com)

በኢትዮጵያ አንድም ዚፖለቲካ እስሚኛ አለመኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በድፍሚት ተናገሩ


ስመራ ለመሄድና ለመደራደር ፈቃደኛ ኹሆኑ፥ ዚመድሚክ ተወካዮቜ እርሳ቞ው ቢሮ ድሚስ በመሄድ እንዲደራደሩ እንዲፈቅዱ ተጠይቀዋል። በኢትዮጵያ ያለውን እስርና እንግልት፣እንዲሁም “ዹውንጀላ” ቅንብር ኚንጹህ ህሊና እንዲመሚምሩ በትህትና ዹልመና ያህል ቀርቩላቾዋል። በምትሰጠዋ አጭር ዚመናገሪያ ደቂቃ መነጋገሪያ ዹሚሆኑ ጥያቄዎቜ ተሰንዝሹዋል። ዚእያንዳንዱን ቀት ዚሚያንኳኳ ሰብአዊነትን ዚሚፈታተን ጥያቄዎቜ በማንሳት አቶ ግርማ ሰይፉ ተሳክቶላ቞ዋል። በትህትና ያቀሚቡዋ቞ው ጥያቄዎቜ በተለይም ዶ/ር ደብሚጜዮንን በተደጋጋሚ ሲስቁ እንድንመለኚት ኹመጋበዙ በላይ ኹጠቅላይ ሚኒስትሩ ነጻነት ዹተሞላው መልስ አልተሰጠባ቞ውም። አቶ ሃይለማርያም ቀሪዋን ሁለት ዓመት ለመጚሚስ ውለታ አስቀማጭ በመሰሉበት ዹፓርላማ ውሏቾው ፖለቲካ ውሞትና ክህደት ዚሚበዛበት ዹአይነ ደሚቆቜ ጚዋታ ነው ቢባልም፣ እሳ቞ው ግን ክህደታ቞ው ኹልክ ያለፈና ፖለቲካዊ ቃና ዹሌለው ሆኖ ታይቷል።

ዚአቶ ግርማ አካሄድ በምዕራቡ ዓለም በሚካሄድ ዚፍርድቀት ቜሎት አንዳንድ ጊዜ ጠበቆቜ መናገር ዚማይገባ቞ውን ነገር እያወቁ ዚሚናገሩትን ሁኔታ ይመስላል፡፡ እማኝ ዳኞቜን (ጁሪ) እንዲሰሙት ዚሚያስፈልግ ነገርግን በፍርድቀቱ ውስጥ ለመናገር ዚማይፈቀድ ሃሳብ/መሹጃ ጠበቆቜ ሆን ብለው ይለቃሉ፡፡ ይህ ልክ እንደተሰማም ተኚላካይ ጠበቃ ዹተቃውሞ ድምጜ ያሰማል፤ ዳኛውም ንግግሩ እንዲሰሚዝ ያዛሉ ሆኖም ኚሰሚዎቹ እማኝ ዳኞቜ ጭንቅላት ውስጥ መሠሹዝ ማንም አይቜልም፡፡ ለአቶ ግርማ መሠሚታዊ ጥያቄዎቜ አቶ ሃይለማርያም እጅግ መስመር ዹለቀቀ ምላሜ በመስጠት ጥያቄዎቹን ለመሰሹዝ ቢሞክሩም ዚአቶ ግርማን ጥያቄዎቜ ኚህዝብ ጆሮ መልሰው መውሰድ አይቜሉም፤ ኚህዝብ ልብ ውስጥ ማጜዳት አይቜሉም፤ ኚአዚሩ ውስጥ መምጠጥ አይቜሉም፡፡

በንግግር ማጣፈጥ ሳይሆን ባነሱት ቁም ነገር በተለይም በኢትዮጵያ አንድም ዚፖለቲካ እስሚኛ ዹለም ሲሉ መናገራ቞ው ኚዳር አስኚዳር ዚሚወጡባ቞ውን ሪፖርቶቜ፣ አገርና ህዝብ ዚሚያውቁትን እውነት፣ ዚፈጠራ ክስ ሰለባ ዹሆኑ ቀተሰቊቜ ለፈጠራው ክስ ምስክር ዹሆኑ፣ያቀነባበሩ፣ እንዲኚሱ ዚሚያዙ፣ ዚሚፈርዱትና ፍርድ ዚሚያስፈጜሙት ሁሉም ባንድነት ዚህዝብ ወገኖቜ ናቾውና ዛሬ አቶ ሃይለማርያም በሰጡት ደሹቅ ዚክህደት መልስ ስቀውባ቞ዋል። ቢያንስ “በስህተት ዚተሰራ ስራ ካለ አጣራለሁ” በሚል አውገርግሹው ማለፍ ሲገባ቞ው፣ አንድም ዚፖለቲካ እስሚኛ ዹለም በማለት አፋቾውን ሞልተው መናገራ቞ው በግል ዚሚያኚብሩዋ቞ውን ሁሉ አሳዝኗል። ዚሃዋሪያት ቀተክርስቲያንን ስምና ዲሲፒሊንም ገደል ኚተውታል። እምነታ቞ውንና ዚእምነት ቀታ቞ውን አስመልክቶ ዹተሰጠ አስተያዚት ቢኖርም ለጊዜው ኹማተም ተቆጥበናል።

ቀተሰቊቻ቞ው ኩነግ ተብለው ዚታሰሩባ቞ው፣ በፖለቲካ እምነታ቞ው በጹለማ ቀት ዹሚማቅቁ፣ በፈጠራ ክስ ዹተወነጀሉ፣ ዚተደፈሩ፣ ሃብታ቞ውን ዹተቀሙ፣ ስለመኖራ቞ው ባደባባይ እዚታወቀና በዹቀኑ ቶር቞ር (torture) ሲደሚጉ ሲቃ቞ው ዹሚሰማ ዜጎቜ ቁጥር በሺህ እንደሚቆጠር ይታወቃል። ዹፈሹንጅ እማኝ እንኳን ካስፈለገ ሁለቱ ዚስዊድን ጋዜጠኞቜ ዚቅርብ ጊዜ ምስክር ናቾው። ሁለቱ ስዊድናዊያን ጋዜጠኞቜ ዹማንም ብሄርና ዚፖለቲካ ድርጅት አባል ባለመሆና቞ው “መሹጃና ማስሚጃ” ስለሚባለው ዚክስ ድራማ ዚተናገሩት ኚሚታመነው በላይ ነው። እንግዲህ አቶ ሃይለማርያም ይህንን ሁሉ እያወቁ ነው “ድኜበታለሁ” በሚሉት አምላክ ፊት እንዲህ ያለ ጥያቄ ማንሳት “በእሳት ዚመጫወት ያህል ነው” ያሉት። አናትመውን ካልነው አስተያዚት ውስጥ “… ልጆቻ቞ውና ባለቀቶቻ቞ው ሳይቀሩ ይታዘቡዋ቞ዋል” ዹሚል ይገኝበታል።

ብ቞ኛው ተቃዋሚ “አንኚራኚርበትም ህዝብ ይፍሹደው”

በኢትዮጵያ አንድም ዚፖለቲካ እስሚኛ አለመኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በድፍሚት ተናገሩ። ዚመንግስታ቞ውን ፍርድ ቀቶቜና ዚፍርድ ሂደት እንደማስሚጃ ጠቅሰዋል። በተወካዮቜ ምክር ቀት ብ቞ኛው ዚመድሚክ ተወካይ ለጥያቄያ቞ው ዚሚሰጣ቞ውን መልስ አስቀድመው በመገመት “አንኚራኚርበትም ህዝብ ይፍሹደው” ብለዋል። ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ ዚጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኊባንግ ሜቶ ንግግሩን “ፍጹም ቅጥፈት ዚተሞላበት” በማለት ሲኮንኑት በእስር ዚሚማቅቁት ኚቁጥር በላይ “ስም፣ ቀተሰብ፣ ልጅ … ያላ቞ው ዹምናውቃቾው ሰዎቜ ናቾው” በማለት ተናግሹዋል፡፡

ታህሳስ 23 ቀን 2005 ዓ ም በተካሄደው ዹ10ኛው ዚተወካዮቜ ምክር ቀት መደበኛ ስብሰባ ላይ ለሚቀርቡላ቞ው ጥያቄዎቜ መልስ ለመስጠት ዚተገኙት ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ ኚመድሚኩ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ ዹቀሹበላቾው ጥያቄ ኚወትሮው በተለዹ ህሊናንና ውስጣዊ ማንነትን በሚፈታተን መልኩ ነበር።

ዚፖለቲካ እስሚኞቜን አስመልክቶ “መቌም ዚታሰሚ ዘመድ ዚለዎትም” በማለት ነገሩን “በኔ ላይ ቢደርስ” ብለው እንዲያስቡ በመማጾን አቶ ግርማ አንድ ሰው ኚማያውቀው ቊታና ድርጅት በግል ሞባይሉ መልዕክት ቢላክለት እንዎት አልቃይዳ ሊባል እንደሚቜል፣ ኚማያውቀው ድርጅት ወይም ኚማያውቀው ዚአልቃይዳ አባል መልዕክት ቢላክለትና መልስ ሳይለዋወጥ ዹተገኘ ሰው እንዎት ወንጀለኛ እንደሚባልና እንደሚፈሚድበት በመግለጜ ጥያቄ ሰነዘሩ።

ኹኩነግ ጋር ግንኙንት አለሜ ተብላ ኹ3 ለጆቜዋ ተነጥላ 10 ዓመት ጜኑ እስራት ዚተፈሚደባት ሌሊሮ ወዳጆ

“አልቃይዳ ሞባይላ቞ውን እንዎት እንደሚያገኘው ባይገባኝም” በማለት ወገኖቻ቞ውን ባስፈገጉበት መልሳ቞ው ቀድመው ዚተናገሩት አቶ ሃይለማርያም፣ “አንድም ዚፖለቲካ እስሚኛ ዹለም” በማለት ነበር። ዚፍታብሔርና ዹወንጀል ጉዳዮቜና፣ በዚሁ አግባብ ዚተፈሚደባ቞ው ካልሆኑ በስተቀር ዚፖለቲካ እስሚኛ ዚሚባል እንደሌለ አስሚግጠው በመግለጜ ዚመንግስታ቞ውን ዚፍትህ አሠራር ደሚታ቞ውን በመንፋት አሞካሜተዋል።

በፖለቲካ ሜፋን ወንጀል ዚሚሰሩ፣ ዚአሞባሪ መሳሪያ ዹሚሆኑ፣ ዚፖለቲካ መሪና አባል በማስሚጃ መኚሰሳ቞ውን ዚጠቆሙት አቶ ሃይለማርያም “መሹጃ ቢኖሚንም ማስሚጃ ያላገኘንባ቞ውና ወደ ህግ ሳይቀርቡ ዚተቀመጡ አሉ” ሲሉ ዹ“ቢጫ” ካርድ ማስጠንቀቂያ በመሳብ ዹህሊናን ነገር ወደ ጎን በመተው በደሹቁ በመሞምጠጥ አቶ መለስን በልጠው ታይተዋል። በድጋሚ ጥያቄ ዹመጠዹቅና ዚመሟገት እድል አለመኖሩ ጠቀማቾው እንጂ “ዚሚፈለጉትን ሰዎቜ ስልክ ኹቮሌ ወይም ኚጓደኞቻ቞ው በመውሰድ በሶማሊያ አገር በተመዘገበ ስልክ ኚሜብር ጋር ዚተያያዘ መልዕክት ኢህአዎግ እንደላኚው እናውቃለን በማለት አቶ ግርማ ቢኚራኚሩ መልሳ቞ው ምን ሊሆን ይቜል ነበር?” በማለት ስርጭቱን ሲኚታተል ዹነበሹ አስተያዚት ሰንዝሯል።

ዕውቁ ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋቜና ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ ዚጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኊባንግ ሜቶ ይህንን ዚአቶ ሃይለማርያም ምላሜ በተመለኹ በተለይ ኹጎልጉል ዚድሚገጜ ጋዜጣ በስካይፕ ለተጠዚቁት ሲመልሱ “በእውነቱ ይህ ፍጹም ቅጥፈት ዚተሞላበትና አጞያፊ ነው” በማለት ምላሻ቞ውን ሰጥተዋል፡፡ “እነዚህ እስሚኞቜ እኮ በቁጥር ዚሚታወቁ ብቻ ሳይሆኑ ስም፣ ቀተሰብ፣ ልጅ፣ ዘመድ፣ ወዘተ አላቾው፡፡ እናውቃ቞ዋለን፤ ዓለም ያውቃ቞ዋል፤ እንግዲህ ጠ/ሚ/ሩ ለእነዚህ ልጆቜና ቀተዘመዶቜ ነው አባታቜሁ/እናታቜሁ/ዘመዳቜሁ ወንጀለኛ አሞባሪ ነው እንጂ ዚፖለቲካ እስሚኛ አይደለም እያሉ ነው ያሉት፤ … ሥነምግባር ዹጎደለው ንግግር ነው” ብለዋል፡፡

አቶ ኊባንግ ሲቀጥሉም “ዚጋራ ንቅናቄያቜን አቶ ሃይለማርያም ሥልጣን እንደያዙ ደብዳቀ ልኹን ነበር፤ በደብዳቀውም ቀዳሚ ተግባራ቞ው ሊሆን ዚሚገባው በዕርቅ ዙሪያ ላይ መሥራት ሲሆን ይህም ዹሚጀምሹው ዚፖለቲካ እስሚኞቜን በመፍታት እንደሆነ ጠቅሰን አጜዕኖት ሰጥተን ጜፈን ነበር” በማለት ድርጅታ቞ው ኚሊስት ወራት በፊት ለጠሚ/ሩ በስም ዚጻፈውን ደብዳቀ አስታውሰዋል፡፡ ሆኖም እስካሁን ምንም ምላሜ ያላገኙ እንደሆነ ዚጠቀሱ ሲሆን በደብዳቀው ላይ አቶ ሃይለማርያም በአሁኑ ጊዜ ዚህወሃት/ኢህአዎግ ሥራአስፈጻሚ ሳይሆኑ ዚኢትዮጵያ ህዝብ መሪ በመሆናቾው ለሚደግፏቾው ብቻ ሳይሆን ለሚጠሏቾውም ጭምር በቅንነት ማገልገል እንደሚጠበቅባ቞ው መጥቀሳ቞ውን ተናግሹዋል፡፡ “ይህ ዓይነቱ ማሳሰቢያና ጥያቄ ግን እንዲሁ ሲቀጥል አይኖርም፤ እኛም ሆነ ሕዝብ በቃኝ ዚሚልበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፤ ለዘመናት አምባገነኖቜ ተመሳሳይ ጥሪ ሲቀርብላ቞ው ቆይተው ሁሉም ንቀው በመጚሚሻ ዚውርደት ጜዋ እንደተጎነጩ ታሪክ ምስክር ነው፤ ህወሃት/ኢህአዎግ ኹዚህ ዚታሪክ ክስተት ፍጹም ዹተለዹ ሊሆን አይቜልም” በማለት አቶ ኊባንግ ዚማስጠንቀቂያ ተግሳጜ ሰጥተዋል፡፡

ስኳሩን እዚላሱ በሞቀ ቀታ቞ው ስለተቀመጡ “ዚመንግስት ሌቊቜ” ለተጠዚቁት “ለጾሹ ሙስና ኮሚሜን መሹጃውን በማቅሚብ ቢተባበሩን ራሎው ተኚታትዬ ለማስፈጞም ቃል እገባለሁ” ዹሚል መልስ ዚወሚወሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም፣ መንግስታ቞ው ማስሚጃ ባገኘባ቞ው ላይ ርምጃ እዚወሰደ እንደሆነ አመላክተዋል።

አቶ ሃይለማርያም “ለህሊናቾው ይቀርባሉ” በሚል ይመስላል አቶ ግርማ በዹቀበሌው ያሉ ዚኢህአዎግ ካድሬዎቜ “ኢህአዎግ ኹሌለ አገሪቱ አትቀጥልም” በማለት ስለሚያስፈራሩ ህዝብ ዹፈለገውን ዚመምሚጥ መብት እንዳለው በግልጜ ማሚጋገጫና መመሪያ እንዲሰጡላ቞ው በተማጜኖ ጠይቀው ነበር።

ዚአቶ ግርማ ጥያቄ እንደተነሳ አቶ መለስ አማራ ክልል ቡግና ወሚዳ በሚገኘው አባላ቞ው ላይ አቶ ልደቱ ላቀሚቡት አቀቱታ ዚሰጡትን ዓይነት ምላሜ ዹጠበቁ ነበሩ፤ በ2002 ምርጫ አቶ ልደቱ አዲስ አበባን ለቀው በትውልድ ስፍራ቞ው ቡግና ለመወዳደር ሲቀሰቅሱ ኚሃይማኖት ጋር በተያያዘ ዚስም ማጥፋት ተካሂዶባ቞ው እንደነበር ጠቅሰው ይኚሳሉ። አቶ መለስም “… እንዲህ ያለ ወራዳ፣ እንዲህ ያለ ቆሻሻ… እደግመዋለሁ እንዲህ ያለ ወራዳና ቆሻሻ ዚድርጅታቜን አባል ሊሆን አይገባም…” በማለት ዚስድብ ናዳ አወሚዱ። አራዳው ኢቲቪ አቶ ልደቱ ተደስተው ፈገግ ሲሉና አንጀታ቞ው መራሱን ዚሚያሳብቀውን ፊታ቞ውን አሳዚ።

አቶ ሃይለማርያም አቶ ግርማ ላቀሚቡት ተመሳሳይ ጥያቄ “አባሎቻቜን ይህን አይፈጜሙም” በማለት ባጭሩ መልሰዋል። ህዝብ ዹሚመርጠውን ስለሚያውቅ እንዲህ አይነቱ ጥያቄ ዚህዝብን ዚምርጫ ልምድና ንቃተ ህሊና አሳንሶ ዚማዚት ያህል እንደሚቆጠር በመናገር ቀጥተኛውን ጥያቄ ዚፖለቲካ እርሟ ለማድሚግ ሞክሹዋል።

በማተሚያ ቀት ቜግር ዚፓርቲያ቞ው ጋዜጣ ኚህትመት መውጣቱን በመጥቀስ አንድ ኹፍተኛ ጉዳይ አንስተው ነበር። ፓርቲያ቞ው ኚአባላቱ፣ ኹደጋፊውና ኚህዝብ ጋር ዚሚገናኝበትን ብ቞ኛ ሳምንታዊ ጋዜጣውን በግል ማተሚያ ቀቶቜ ለማሳተም ሲሞክር በስልክ በሚሰጥ ማስፈራሪያ አታሚዎቹ እዚፈሩ እንደማይተባበሯ቞ው፣ ዚህትመት ጥያቄያ቞ውን ሙሉ በሙሉ እንደማይቀበሉ በመግለጜ በስልክ ማስፈራሪያ ለሚደርሳ቞ው ዹግል አታሚዎቜ በግልጜ ህዝብ እዚሰማ ሳይፈሩ ስራ቞ውን መስራት እንዲቜሉ እንዲነግሩላ቞ው አሁንም ዚተማጞኑት አቶ ግርማ ያገኙት መልስ ለጠዚቁት ዚሚመጥን አልነበሹም።

አቶ ሃይለማርያም “ማተሚያ ቀቶቹ ስራ቞ውን ጠንቅቀው ስለሚያውቁ በስልክ ማስፈራሪያ ስራ቞ውን ያቆማሉ ብዬ አላስብም” በማለት ኹደመደሙ በኋላ “ማተሚያ ቀቶቹ ስለመፍራታ቞ው መሹጃ ዹለኝም። እንደጭራቅ ለምን ፈሩን ዹሚለውን ራሳቜሁን ጠይቁ” ዹሚል ኚጥያቄው ጋር ግንኙነት ዹሌለው ምላሜ ሲሰጡ ተደምጠዋል። አያይዘውም ቜግሩ አጋጥሞም ኹሆነ ዚአታሚዎቜ ማህበር አለ በዚያ በኩል ሊቀርብ እንደሚቜል አመላክተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህገወጥ ደላሎቜ ምክንያት ኹአገር ስለሚወጡ ዜጎቜ ሲናገሩ፣ አንድ ሰው ዹሚኹፍለው 50ሺህ ብር መሆኑን በማመልኚት ይህን ገንዘብ በመያዝ አገር ውስጥ በመደራጀት ስራ መፍጠር እንደሚቻል ጠቁመዋል። ይህንን ገንዘብ ራሳ቞ውን ለማጥፋት ኚሚያውሉት ራሳ቞ውን ወደሚጠቅም ስራ እንዲቀይሩት ሰፊ ስራ እንደሚሰራም ተናግሹዋል። ይህን ያህል ብር በመክፈል መሰደድን ስለሚመርጡበት ዹተለዹ ነገር ግን ዚተናገሩት ነገር ዹለም። ዹጠዹቀም ወገን አልታዚም።

አስመራ በመሄድ ለመደራደር ፈቃደኛ እንደሆኑ ለአልጃዚራ ቎ሌቪዥን ተናግሹው ዚነበሩት አቶ ሃይለማርያም፣ ኀርትራን በተመለኹተ አስመራ ለመሄድ ፈቃደኛ ኹመሆናቾው ጋር ተያይዞ በራሳ቞ው አባል ለቀሹበላቾው ጥያቄ ቀደም ሲል ዹነበሹው ዚኢትዮጵያ ፖሊሲ አልተቀዹሹም፣ ይህ ኢትዮጵያ ዚያዘቜው ዹሰላም ፖሊሲ ወደፊትም ዚሚቀጥል ነው በማለት መልስ ሰጥተዋል። ዚኀርትራ መንግስት በተለይም ዚመሪዎቹ ባህሪ ዚሚታወቅና ዚአስመራ መንግስት ኢትዮጵያን ዚማተራመስ ስራውን እንዳላቆመ ዚተናገሩት አቶ ሃይለማርያም፣ ዚኀርትራ መንግስት ለሚፈፅማቾው እኩይ ተግባራት ዚኢትዮጵያ መንግስት ዹዓለም አቀፍ ህግጋትን መሰሚት በማድሚግ ተመጣጣኝ እርምጃ ለመውሰድ ዚተያዘው አቋም እንደማይቀዚር አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ ዚአስመራው መንግስት ለድርድርና ለሰላም ራሱን ዚሚያስገዛ ኹሆነ በሩ ክፍት መሆኑን ተናግሹዋል። በሌላም በኩል ዹሰላምና ፍላጎት እንደሌለው ለዓለም ማስታወቃ቞ውን ለጠዹቋቾው ገልጾዋል።

ዚምዕራብ አገሮቜ በስፋት ኢንቚስትመንት ላይ ያልተሰማሩት በመንግሥት ቜግር ሳይሆን በራሳ቞ው ዚኢኮኖሚ ቀውስ መሆኑንን በማመልክት አስተያዚት ሰጡት አቶ ሃይለማርያም፣ ቻይናና ህንድ በኢትዮጵያ ኹፍተኛውን ዚኢንቚስትመንት ዘርፍ እንደተቆጣጠሩት፣ በአነስተኛ ደሹጃም ቢሆን ዚቱርክ ባለሃብቶቜ እዚገቡ መሆኑን ገልጾዋል። ቻይናና ህንድ እያስመዘገቡ ያለው እድገት ኹፍተኛ በመሆኑ በአሁኑ ሰዓት በተለያዩ ዹዓለም ክፍሎቜ በስፋት ኢንቚስትመንት ላይ መሳተፋ቞ውን አስታውቀዋል። ዚኢትዮጵያ ዚኢኮኖሚ እድገት 11.4 በመቶ መሆኑንን ዹዓለም ባንክ ማመኑንና ዚተጀመሩት ኹፍተኛ ዚልማት ስራዎቜ በተያዘላ቞ው ዚአምስቱ ዓመት እቅድ መሰሚት በርብርብ እንደሚሰራ አስታውቀዋል። በቀቶቜ ግንባታ “በአፍሪካ በዓመት 100ሺህ ቀቶቜ ዚሰራው ኢህአዎግና ኢህአዎግ ዚሚመራው መንግስት በቻ በመሆኑ ልንደነቅ ይገባል” ሲሉ በቀቶቜ ግንባታና ግንባታውን ለመቆጣጠር ዹተጀመሹው አካሄድ በተጀመሹው መልኩ ይቀጥላል ብለዋል። መንግሥታ቞ው ይህንን “ግንባታ” ሲያደርግ በዹጊዜው ስለሚያፈርሰው ዚዜጎቜ ንብሚትና ህይወት ኚእርሳ቞ው ዹ“ልማትና ግንባታ” ንግግር ጋር ዚሚሄድ ባለመሆኑ ሳይጠቅሱት አልፈውታል፡፡

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድሚስ በጎልጉል ዚድሚገጜ ጋዜጣ® ላይ ዚሚወጡት ጜሁፎቜ በሙሉ ዹጎልጉል ዚድሚገጜ ጋዜጣ®áŠ•á‰¥áˆšá‰µ ናቾው፡፡ ይህንን ጜሁፍ ለመጠቀም ዹሚፈልጉ ሁሉ ዹዚህን ጜሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም ዚድሚገጻቜንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብሚው መለጠፍ ኚጋዜጠኛነት ዹሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

ሀሹር ኹተማ ኹጁምዓ ፀሎት በኋላ ፖሊሶቜ አንድ ህፃን ልጅ ገደሉ

ሀሹር ኹተማ ኹጁምዓ ፀሎት በኋላ በተፈጠሹው ዚሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ፖሊሶቜ አንድ ህፃን ልጅ ገደሉ። (እኔ “አንድ ህፃን ገደሉ” ዹሚለውን ስፅፈው በምን አይነት ሀዘን ውስጥ ሆኜ አንደሆነ ዹላይናው ይወቀው… ዚገደሉትስ ምን ተሰምቷ቞ው ይሆን…!?)
ጎበዝ መንግስታቜን ወዎት እዚሄደ ነው…? ባለፈው ቀታቜን አለ አግባብ ፈሹሰ ብለው አቀቱታ ሊያሰሙ ዚወጡ ዚአዲሳባ ነዋሪዎቜ ላይ ፖሊስ ጥቃት ሰንዝሮ ታዘለቜ ህፃን ገደለ። ሲባል ሰማን አሁን ደግሞ ሌላ መዓት ሰማን… አልገባንም “ዚቀተሰብ ምጣኔ” ሲባል ዹተወለደን መግደል መስሏ቞ው ይሆን እንዎ!? ዚት ሄደን እንፈንዳ…! ልል ነበር ለካስ በዚሄድንበት ሰዎቻቜን እያፈነዱን ነው… አንዮም በሳቅ አንዮም በእንባ… አንዮም በቜግር አንዮም በዱላ… አሹ መላ መላ…!






ESAT Breaking News Muslim Protest Jan 04, 2013

በአንዋር መስጊድና በአዳማ ዹተቃውሞ ሰልፉ በሰላም ሲጠናቀቅ በሐሹር አንድ ሰው ተገደለ

ፎቶ ኹፋይል áˆˆáŒáŠ•á‹›á‰€፡ ዚሙስሊሙ ዚትግል መነሟና á‹šáŒ¥á‹«á‰„ዎቻ቞ው እንድምታ

(ዘ-ሐበሻ) በአራት ሳምንታት ተደልድሎ እዚተዘኚሚ ያለው ‹‹365 ቀናት ለእምነት ነጻነት›› ዚመጀመሪያ ሳምንት ዹጁምዐ ተቃውሞ መርሐ ግብር በበርካታ
ዚአገሪቱ ኚተሞቜ ዚኢትዮጵያ ሙስሊምቜን አገራዊ አንድነት በጉልህ ባሳዚ መልኩ መካሄዱ ተሰማ። በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ በኹፍተኛ ጥበቃ ታጅቊ
በተደሹገው በዚሁ ዹተቃውሞ ሰልፍ ሙስሊሙ ማህበሚሰብ በአንድነት ድምጹን ጮክ ብሎ አሰምቷል። በአዳማ ኹተማም እንዲሁ በርኚት á‹«áˆ‰ ሙስሊሞቜ
ወጥተው ‹‹365 ቀናት ለእምነት ነጻነት›áŠ• ዚመጀመሪያ ሳምንት መርሃ ግብር ያጠናቀቁ ሲሆን መብታ቞ው እንዲኚበርና ዚታሰሩት መሪዎቻ቞ው እንዲፈቱ
ጠይቀው ዹተቃውሞው ሂደት በሰላም ተጠናቋል።
ዚሙስሊሙ ማህበሚሰብ ሰላማዊ አካሄድ አስደናቂ መሆኑን ዚሚገልጹት ዹዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎቜ መንግስት በአንዋር መስጊድም ሆነ በደሮ ሕዝቡን ለማበጣበጥ
ትንኮሳዎቜን ቢያደርግም ሰላም ፈላጊው ሕዝብ ግን ሰላምዊውን ጥያቄውን ወደ ግጭት እንዳያመራ በጥንቃቄ ይዞ ዚዛሬውን ውሎውን ቢያጠናቅቅም፡ በተለይ
በሃሹር ኹተማ ግን ዚሙስሙን እንቅስቃሎ ሰላማዊ “ኚአሞባሪነት ጋር ለማስመሰል” መንግስት ሆን ብሎ ባስነሳው ዚጞጥታ ቜግር ተፈጥሮ ሰዎቜ መታሰራ቞ውንና
አንድ ወደ ወጣትነት ዕድሜ እዚደሚሰ ያለ ሙስሊም መገደሉን ኹሐሹር አካባቢ ለዘ-ሐበሻ ዚደሚሱን መሚጃዎቜ ያመለክታሉ።
በደሮና በወልዲያም ይህ ተቃውሞ ቀጥሎ ዹዋለ ሲሆን በተለይ በወልድያ አልበሲጥ መስጊድ ለተቃውሞ ኚወጡ ሙስሊሞቜ መካኚል ቁጥራ቞ው በውል
ያልታወቀ ሰዎቜ መታሰራ቞ውን ኹደሹሰን መሹጃ ለመሚዳት ቜለናል።
                   
ኚድምጻቜን ይሰማበአላህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ á‰ áŒ£áˆ አዛኝ በሆነው፡- á‰ áŠ á‹ˆáˆŠá‹« ሙስሊም ሚሜን ት/ት ተማሪዎቜዚተጀመሚውና ወደ ሀገር አቀፍ ደሹጃ ያደገው
‹‹á‹µáˆáƒá‰œáŠ• ይሰማ›› ዚኃይማኖት ነፃነት ጥያቄ እና
ዚመንግስት ጣልቃ ገብነትና ዚመብት ጥሰት ተቃውሞ
እነሆ አንድ ዓመት ሞላው፡፡ በዚህም አመታዊ ጉዞው
ውስጥ ኹደርዘን በላይ ሙስሊሞቜ ህይወታ቞ውን
መስዋዕት አድርገዋል፤ ዚመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚ቎
አባላትን ጚምሮ 29 ሙስሊሞቜ ታስሚዋል፤
በሜብርተኝነትም ተኹሰዋል፤ በብዙ ሜህ ዚሚቆጠሩ
ንፁሃን ሙስሊሞቜ በመላ ሀገሪቱ እስር ቀቶቜ እዚማቀቁ
ይገኛሉ፤ ብዙ ምዕመናን አካላ቞ውን አጥተዋል፤ ብዙ
ሙስሊሞቜ ዚሚወዷት ሀገራ቞ውንና ቀተሰቊቻ቞ውን
ትተው ተሰደዋል፤ ብዙ ዚሙስሊም ልማት ድርጅቶቜ፣
ዚገንዘብ፣ ኢኮኖሚና ዚንግድ ተቋማት፣ ዚዚቲሞቜ
መሚዳጃና ማሳደጊያ ተቋማት፣ ዹምርምር ማዕኚላት
ተዘግተዋል፣ ዚባንክ ሂሳባ቞ው ታግዷል፣ ገንዘባ቞ው
ተወርሷል፤ ዚሙስሊም ጋዜጊቜና መፅሄቶቜ ላይመለሱ
ተኚርቜመዋል፡፡ ዚእምነት ማዕኚላትና መድሚሳዎቜ
ተዘግተዋል፤ መስጂዶቜ ፈርሰዋል፤ ዚግዳጅ ሰልፎቜ ተስተውለዋል፤ ሰላማዊ ትግሉ ዚተለያዩ ስልቶቜን በመቀያዚር ሀገሪቱ ሰፍኗል፤ወዘተ…
ዹዚህ ምልኚታ ዓላማም ዚትግሉን ጉዞ ሂደት ማለትም መነሻ ምክንያቶቜ፣ ስኬቶቜ፣ ድክመቶቜ፣ ስጋቶቜና ተግዳሮቶቜ እንዲሁም ዚወደፊት አቅጣጫዎቜን
ለመጠቆም ያለመ ነው፡፡
ዚቜግሩ ቁልፍ መነሻ
ዚኢ.ህ.አ.ዮ.ግ መንግስት ኹ1987ቱ ዹአንዋር መስጅድ ጭፍጹፋ በኋላ ኚመጅሊስ እጁን አንስቶ ባያውቅም እስኚ ቅርብ ጊዜ ድሚስ ግን ይፋዊ ዹሆነ አስገድዶ
ዚማጥመቅ ዘመቻ አልጀመሹም ነበር፡፡ ኹሀምሌ ወር 2003 ጀምሮ ግን አዲስ ጥፋት ተጀመሹ፡፡ መንግስት በፌደራል ጉዳዮቜ ሚኒስ቎ር በኩል አስፈላጊውን
ቅድመ ዝግጅት ካደሚገ በኋላ በዚሁ ወር በሀሮማያ ዩኒቚርሲቲ ሀሹር ካምፓስ ውስጥ በ1980ዎቹ አካባቢ በሊባኖስ ርዕሰ መዲና ቀይሩት እንደተጀመሚ
ዚሚነገርለት አል-አህባሜ ዚሚባል እምነት በመንግስትና በመጅሊሱ ቅንጅት ኚሊባኖስ በመጡ 200 መምህራን በይፋ ማጥመቅ ተጀመሹ፡፡ በዚህም 1300
አካባቢ ዹሚሆኑ ዚፌደራልና ዹክልል ዚመጀሊስ ቢሮዎቜ አባላት ተካፋይ ሆነዋል፡፡ ኹዚህ በኋላም በተኚታታይ ቀጥሎ ዹነበሹው ዚአስገዳጅ ስልጠና በዚአካባቢው
መሰጠቱ ሲቀጥል፣ ስልጠናውን ዹተቃወሙ ሙስሊሞቜ ኚኃላፊነታ቞ው እንዲነሱ ተደርገዋል፡፡ ዚአሞባሪነት ስያሜም እዚተሰጣ቞ው ለማሾማቀቅ ተሞክሯል፡፡
እንዲሁም ሁሉም ዚመስጂድ ኢማሞቜና ሙዓዚኖቜ በአህባሟቜ አቀንቃኞቜ እንዲቀዚሩ፣ ሁሉም ዚሙስሊም ትምህርት ቀቶቜና ማዕኚላት በአህባሜ አስተምህሮ
እንዲቀዚሩ ካልሆነም እንዲዘጉ በሚለው ዚመንግስት ዕቅድ መሰሚት ብ቞ኛው ዚሙስሊሞቜ ኮሌጅ ዹሆነው አወሊያም እጣው ደርሶት በ2004 ታህሳስ 21 ቀን
ዚኮሌጁ 50 ዚአርብኛ መምህራን እና ዚመስጂዱ ኢማምና ምክትላ቞ውን ጚምሮ በመጅሊሱ ቀጭን ትዕዛዝ በአንድ ሌሊት እንዲባሚሩ ተደሹገ፤ በዚህ ምክንያት
ኮሌጆም ተዘጋ፡፡ ይህ ያስቆጣ቞ው ዚአወሊያ ኮሌጅና ሁለተኛ ደሹጃ ት/ቀት ተማሪዎቜ ታህሳስ 24 ቀን ‹‹áŠ¢áˆ›áˆ™áŠ“ መምህራኖቜ ይመለሱልን፣ ኮሌጁም
ይኚፈት!›› በማለት ዹተቀውሞ ድምጜ ማሰማት ጀመሩ፡፡ ይህ ቜግር በቀላሉ ሳይፈታ ቀርቶ ወደ ሀገራዊ አጀንዳነት በማደጉ ‹‹á‹šáˆ˜áŒ…ሊስ አመራሮቜ
ይውሚዱ!›› ዹሚል ጥያቄ ተነሳ፡፡ ዚቜግሩ ቁልፍ መነሻ ዚኃይማኖትና እምነት ነፃነት በሚፃሹር፣ ዚኢትዮጲያን ህገ-መንግስታዊ አንቀፅ 27 እንዲሁም ዹዓለማቀፍ
ዚሰብዓዊ መብቶቜን በሚጥስ ሁኔታ መንግስት በኃይማኖት ጉዳዩቜ ጣልቃ መግባቱና አስገድዶ ዚማጥመቅ ዘመቻ መጀመሩ ነበር፡፡ ነውም፡፡

ዹሰላማዊ ትግሉ ህጋዊ አካሄድ
ይህ ዚተማሪዎቜ ጥያቄ ወደ ሀገራዊ አጀንዳነት ኹተቀዹሹ በኋላ በብዙ ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሙስሊሞቜ ዹተቃውሞ ድምፃ቞ውን ማሰማት ሲጀምሮ ህገ-መንግስቱ
በሚፈቅደው መሰሚት ኚሁለት ሳምንታት በኋላ ጥር 11 ቀን ወኪሎቜን በመምሚጥ 17 አባላት ያሉት ኮሚ቎ ተዋቀሹ፡፡ ይህ ኮሚ቎ም ዘርፈ-ብዙ ኚሆኑት ኚህዝቡ
ኚተነሱ በርካታ ጥያቄዎቜ ውስጥ ሶስት ጥያቄዎቜን ብቻ በመለዚት ለመንግስት ለማቅሚብ ተሰናዳ፡፡ በመቶዎቜ ኚሚቆጠሩ ኚህዝብ ኚቀሚቡ ጥያቄዎቜ እነዚህ
ሶስቱ ሲመሚጡ በርካታ ነጥቊቜን ኚግንዛቀ በማስገባት ነበር፡፡ በቀጥታ ተቃውሞው እንዲነሳ ምክንያት ዚሆኑት ላይ ብቻ በማተኮር፣ ኚእምነት ነፃነትና
ዚህገመንግስታዊ መርህን ሙሉ ድጋፍ ዚሚያገኙትን፣ በሃይማኖታቜንና በመንፈሳዊ ተቋማቜን ብቻ ዚታጠሩትን፣ መንግስት ኚመመለስ ውጭ ምክንያት ሊያቀርብ
እድል ዚማያሰጡትን፣ በፅንሰ ሃሳብና አሻሚ በሆኑ ነገሮቜ ላይ ዚተገነቡ ሳይሆን ግልፅና በተግባር መመለሳ቞ው ሊሚጋግጥ ዚሚቜሉ፣ ቀላሎቹን፣ አፋጣኝ መፍትሄ
ዚሚሹትን፣ ፣ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ዚሚያሳምኑትን፣ ፍፁም ኢትዮጵያዊ ባህሪ ያላ቞ውን፣ 3 ጥያቄዎቜን በመለዚት ነበር ዚመንግስት ባለስልጣናትን ለማስሚዳትና
መፍትሄ ለማፈላለግ ስራውን ዹጀመሹው፡፡
ሊስቱ መሰሚታዊ ዚትግሉ ጥያቄዎቜም፡-
1. ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ም/ቀት አመራሮቜ በሙሉ ዹሕዝበ ሙስሊሙ ውክልና ዹሌላቾው በመሆኑ በሙስሊሙ ኅብሚተሰብ በነጻነት
በሚመሚጡ አመራሮቜ ይተኩልን
2. በመጅሊሱ አማካኝነት በኢትዮጵያ ሙስሊሞቜ ላይ በግድ እዚተጫነ ያለው ዚአሕባሜ ዚማጥመቅ ዘመቻ ይቁምልን እና
3. አወሊያ ዹህዝበ ሙስሊሙ ነጻ ተቋም ሆኖ እንዲቀጥል መጅሊስ እጁን ኚአወሊያ ያንሳ ዹሚሉ ነበሩ፡፡
በዚህም መሰሚት ዹሰላማዊ ትግሉ ዓላማና ግብ ኚመንግስትና መጅሊስ እጅ ነፃ ዹሆነና ህትሃዊ ምርጫ ይካሄድ፤ እንዲሁም ሙስሊሙ ተቋማት በራሱ
በሙስሊሙ ፍላጎት ይመሩ ዹሚል ማለትም ዚኃይማኖታዊ ተቋማትን ዚማደራጀት፣ ኃይማኖታዊ ዚመምሚጥና ዚመመሚጥ መብቶቜ መኹበር ላይ ዚሚያተኩር
ነበር፡፡ ሌላኛው ደግሞ አስገድዶ ዚማጥመቅ ዘመቻው ይቁም ሲል ዚኃይማኖት፣ ዚእምነትና ዚአስተሳሰብ መብትና ነፃነት ይኹበር፣ መንግስት እጅህን አንሳልን
ዹሚል ትልቅ እንድምታ ያለው ነበር፡፡ ዚትግሉም ውጀትና ስኬት ዚሚለካው ኹዚሁ ዓላማና ግብ አንፃር ነው፡፡
ኮሚ቎ውም እነዚህን ጥያቄዎቜ ይዞ ኚመንግስት አካል ኹሆነው ዚፌደራል ጉዳዮቜ ሚኒስ቎ር ጋር ባደሚገው ኚሶስት ያላነሱ ውይይቶቜ መሰሚት ዚካቲት 26
መንግስት ‹‹áˆ˜áˆáˆŽ ነው›› ያለውን ዚመጚሚሻ አቋሙን እንደሚኚተለው አሳወቀ፡-
1. ዚመጅሊስ ምርጫ በቅርቡ ይካሄዳል፤ እንዎት በማንና በምን መስፈርት ዚሚሉት ግን ዝግ ነበሩ
2. አወሊያና መሰል ዚሙስሊሙ ማዕኚላት በመጅሊሱ በሚመሚጥ ቊርድ ይመራሉ እና
3. ዚአህባሜ ስልጠናም ይቀጥላል ዹሚሉ ነበሩ፡፡
ምንም እንኳን ጥያቄዎቹ በሀገሪቱ ህገ-መንግስት፣ በዓለማቀፋዊ ዚሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎቜ በግልፅና በማያሻማ መልኩ ዚተቀመጡ ቢሆንም ዚመንግስት ምላሜ
ግን ሰብዓዊነትን ዹሚጋፋ፣ ዚኃይማኖት ነፃነት መብትን በእጅጉ ዚሚጥስና ኢትዮጲያ ዚፈሚመቻ቞ውን ዓለማቀፋዊ ስምምነቶቜ በሙሉ ቅርቃር ውስጥ ዚሚኚት
ነበር፡፡ ኮሚ቎ውም ሰላማዊነትንና ህጋዊነትን ብቻ በመላበስ ዚፌደራል ጉዳዮቜ ዹሰጠው ምላሜ ትክክለኛና ጥያቄዎቹን በደንብ ያላገናዘበ መሆኑን በፅሁፍ ጭምር
በማሳወቅ ወደ ኹፍተኛ ዚመንግስት አካላት እስኚ ጠቅላይ ሚኒስ቎ር ቢሮ ድሚስ በደብዳቀ በማስሚዳት እንዲሁም ለውይይት በመጋበዝ ብዙ ዹተጓዘ ቢሆንም
ሳይሳካና ምላሜ ሳያገኝ ቀርቷል፡፡
ኚዚካቲት 26ቱ ምላሜ በኋላ መንግስት በሚቆጣጠራ቞ው መገናኛ ብዙኃን ሰላማዊ ትግሉንና ጥያቄውን በአክራሪነትና በአሞባሪነት በመፈሹጅ ዚማጠልሞት
ፕሮፓጋንዳውን በይበልጥ ተያያዘው፡፡ ኮሚ቎ውም ለወቅታዊ ክስተቶቜ ማብራሪያዎቜን እዚሰጠ እንዲሁም በዹክልሉ ዚትግሉንና ዚጥያቄዎቹን ምንነት በህዝብ
ዘንድ ለማስሚፅ እንዲሁም ዚህዝብን አንድነትና ሰላማዊ አካሄድ ብቻ ለማስሚፅ ብዙ ተጉዟል፡፡ መንግስት ዚመጅሊስ አመራሮቜን ለመቀዹር ቢፈልግም
ምርጫወውን ግን ለራሱ ቁጥጥር በሚያመ቞ው መልኩ በመንግስት አስተዳደራዊ ቊታዎቜ ማለትም በቀበሌ እንዲሆን በማድሚጉ ምክንያት ህዝበ-ሙስሊሙ
‹‹áˆáˆ­áŒ«á‰œáŠ• በመስጅዳቜን›› እያለ ቢቃወምም በእምቢተኝነት ህዝብ ያልተሳተፈበት ዚምርጫ ድራማ በመስኚሚም ወር አድርጎ በአዲስ ዚመንግስት ካድሬዎቜ
ተክቷል፡፡ እስካሁንም በሀገሪቱ ውስጥ ያሉትን መስጅዶቜና መድሚሳዎቜ በመጅሊሱ ቁጥጥር ስር ለማስገባት ሩጫውን እንደቀጠለ ነው፡፡ ዚተቃወሙትን እስር
ቀቶቜ በማጎር ላይ ይገኛል፡፡
ሙስሊሙ ህብሚተሰብ ላነሳ቞ው ጥያቄዎቜ ኹ 365 ቀን በኋላ ዛሬም ፍትሓዊ መልስ ይጠብቃል፡፡ መስማት ዚነበሚባ቞ው አካላት ጆሮ ዳባ ልበስ ቢሉም
ለመስማት እስኪገደዱና መልስ እሰኚሚያገኝ ድሚስ ያለ መሰል቞ት ድምፁን ኹፍ አድርጎ ያሰማል፡፡ ድካሙም ኚንቱ እንደማይቀር በአላህ ላይ ሙሉ እምነት ጥሎ
ወደፊት ይጓዛል፡፡ መሰሚታዊ መብቱ እዚተጣሰ እንዳላዚ ሆኖ ዝም ዚሚልበት ጊዜ በአላህ ፈቃድ ላይመለስ ተሞኝቷል፡፡

ዳዉሮ ህዝብ አመጜ እንደገና ሊያገሚሜ ነው

“እውነትና ፍትህ በሌለበት ሀገር ኑር አትበሉኝ!”

ሚ/ሳጅን ሜታዬ ወርቁ ሺበሺ
ዚዳውሮ ዞን ፖሊስ ባልደሚባ
(ዋካ ኚስዊድን)
መግቢያ
ዚዳውሮ ሕዝብ ዚደሚሰበትን ዚመልካም አስተዳደር እጊት፤ በአቅራቢያው ማህበራዊ አገልግሎቶቜን ለማግኘት አለመቻል፤ በዹደሹጃው ዹሚገኙ አመራሮቜ ሕዝቡ ለሚያቀርበው ዚመብትA memorial service for Yenesew Gebre á‹šáá‰µáˆ…ና ዚዎሞክራሲ ጥያቄ ተገቢ ምላሜ ያለመስጠት፤  á‰ á‹šá‹ˆá‰…ቱ በሚፈራሚቁ ዚሥልጣን ተሹኛ በሆኑት ዚህወሐት/ ደኢህዎን ካድሬዎቜ ዹግል ፍላጎትና ውሳኔ ብቻ ዚወሚዳ ማዕኹል እዚተወሰነ ኹመንደር ወደ መንደር በመዘዋወሩ ዚተነሳ ማሕበራዊ አገልግሎቶቜን ለማግኘት አለመቻል አበሳጭቶት ወደ አምጜ ማምራቱን በመዘርዘር ኹዚህ በፊት በሊስት ክፍሎቜ ያዘጋጀሁትን ጜሑፍ ማስነበቀ ይታወሳል።
አሁንም በሕወሃት/ ደህዮን ካድሬዎቜ ተንኳሜነት ዚተነሳ ዚሕዝቡ ቁጣ እንደገና እያገሚሞ መጥቷል። እስሩ ማንገላታቱ ኚሥራ ማባሚሩ ተጀምሯል። ዚሕዝቡ ጥያቄ ዚሚታወቅና ግልጜ ነው። ኚሚዲያና ኚካድሬዎቜ ዹሚነገሹውን ዚሀገሪቱን  ዚኢኮኖሚ ዚልማትና እድገት ፕሮፓጋንዳ ባሻገር ድርሻውን ማግኘት ቀርቶ በአይኑ ለማዚት አለመቻል፤ ወጣቶቜ ዚሥራ ዕድል ለማግኘት ያለመቻላ቞ውና ዚሥራ አጥ ወጣቶቜ ቁጥር ኹጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ እዚናሚ መምጣት፤ አንድ አርሶ አደር ወደ ወሚዳ ማዕኹል ለመድሚስ ኚአንድ ቀን በላይ ለሚፈጅ ጊዜ በእግሩ መጓዝ ዚግድ እዚሆነበት ስለመጣና ይህም ስላሰለ቞ው፤ ያላግባብ እንዲርቀው ዹተደሹገው ዚወሚዳ ማዕኹል በሚፈልገውና ወደ ሚቀርበው ሥፍራ እንዲዛወርለት ያቀሚበው ተደጋጋሚ አቀቱታ ሰሚ ሊያገኝ አለመቻሉ፤ ጥያቄውን ለመንግሥት በዹደሹጃው  በተደጋጋሚ አቅርቩ መፍትሄ አለማግኘቱ ሕዝቡን በጣም አሳዝታል። በዚህም ዚተነሳ ዚዳውሮ ዋካን ሕዝብ ጥያቄ ያነገበው ጀግናው ሰማዕት መምህር ዹኔሰው ገብሬ በህዝቡ ላይ እዚደሚሰ ያለውን በደልና ዚመልካም አስተዳደር እጊት በመቃወምና ድርጊቱን በማውገዝ ራሱን በእሳት በማቃጠል መስዋዕትነት መክፈሉ ይታወቃል። ይህም ሆኖ ዚዳውሮ ሕዝብ በደል መፍትሄ እስካሁን ሊያገግኝ አልቻለም።
ዹተቃውሞው እንደገና መቀስቀስ ምክንያት
ህወሐት/ ደኢህዎን በደቡብ ክልል በአንዳንድ ዞኖቜ ውስጥ በተደጋጋሚ ዚሚነሳበትን ዚህዝብ ተቃውሞ መቀነስ ስለሚቜልበት ሁኔታ ተወያይቶ ነበር። በዚህ ውይይት ላይ በዋናነት ዚተነሳውና ዚታመነበት ነጥብ ዚተጚማሪ ወሚዳ ጥያቄና ዚወሚዳ ማዕኹል ጉዳይ ሆኖ በውይይቱ ጎልቶ ወጣ። በመቀጠልም እንዎት አድርገው ዚህዝቡን ቁጣ ማርገብ እንደሚቻልና ምንም ተጚማሪ ወሚዳ ሳይሰጥ ሕዝቡን ዚማሳመን ሥራ መሥራት እንደሚገባ ታምኖበት ለአፈጻጞም ለሚመለኹተው ዚፖለቲካ ኃላፊዎቜ እንዲያስፈጜሙት ስልጠና ተሰጥቶ ወደ ሕዝቡ እንዲወርዱ ተደርጓል።
በውይይቱ ላይ በአንክሮ ዚተነሳው ዚቀድሞው ሰሜን ኩሞ ዞን ሥር ዚነበሩት ዞኖቜ መካኚል ዹጋሞጎፋና ዚዳውሮ ዞኖቜ ህዝብ ጉዳይ ነበር። በዚህ መነሻነት ዹዞን አመራሮቜ ሕዝባ቞ውን ዚማሳመን ሥራ እንዲሰሩ ዚሚያስገድድ መመሪያ ለዞኑ ዚፖለቲካ አመራርቜ ይወርዳል። አመራሮ቞ እንዲያስፈጜሙ ታዘዙ። በዚህ መነሻነት ነው እንግዲህ   በእስርና በእንግልቱ ሳቢያ ዝም ያለና ጊዜ ዚሚጠብቅ፤ ግን ውስጥ ውስጡን እዚፋመና እዚጋመ ዹነበሹን ዚህዝብ ብሶት እንደገና ቀሰቀሱት።
ዚዳውሮ ህዝብ ያቀሚበው ዚፍትና ዚመብት ጥያቄ በመሆኑ ኚዛሬ ነገ ይመለስልኛል ብሎ በሚጠበቅበት ወቅት  áˆ˜áŠ•áŒáˆ¥á‰µáŠ“ ገዢው ፓርቲ ጥያቄውን ለማድበስበስና ኚሕዝቡ ዚተሻለ ለሕዝቡ አሳቢ በመምሰል ወሚዳ ምን ያደርግላቜኋል? ልማት ነው ዚሚያስፈልጋቜሁ! ኚልማትና ኚወሚዳ ምሚጡ! ተጚማሪ ወሚዳ አይጠቅማቜሁም! ዚወሚዳ ርእሰ ኹተማ ቢርቅባቜሁም ራቀብን አትበሉ! ዝም በሉ! እንዲያውም ፍትህ ፍለጋ ስንቅ ተሞክማቜሁ በእግራቜሁ ሹጅም ሰዓት በመጓዛቜሁደስ ደስ ሊላቜሁ ይገባል! ዹሚል ስሜት ያዘላ አድራቂ ፕሮፓጋንዳ ሕዝቡን ለማወናበድ እዚተሞኚሚ ይገኛል። ዚመንግሥት ሠራተኛው ዚህዝብ ልጅ እንዳልሆነና ዚሕዝብ በደልን ዚማይሚዳ በማስመሰል ኚሕዝቡ ሓሳብ በተቃራኒው ኚአመራሮቜ ጎን እንዲቆም ለማድሚግ በዚወሚዳው ካድሬ ተመድቊ ተግቶ እንዲሰራ ይደሹጋል።
ካድሬዎቜ በሕዝቡ መካኚል እጅግ ዹሚገርምና ፍጹም ኃላፊነት ዹጎደለው ሥራ ጀመሩ። ዹማሹቃ ዋካ ወሚዳ ዋና ኹተማ ዋካ ይሁንልን ዹሚልን ዚህዝብ ጥያቄ ለማፈን ዚማይቻል መሆኑ ግልጜ ነው። በማሰር በማፈን በሐሰት በመክሰስና በመወንጀል በማስፈራራት ጥያቄውን ምላሜ እንዳያገኝ ማድሚግ አምና ተቜሏል። ይህ ማለት ግን ሕዝቡ ጥያቄውን ትቶታል ወይም መልስ አግኝቷል ማለት አይደለም። ዚወሚዳው ማዕኹል አያማክለንም ዹሚለውን ዚሕዝብ ጥያቄ ለማፈንና ምላሜ ላለመስጠት ሲባል ለዘመናት አብሮ ዹኖሹንና ቀተሰብ ዹሆነውን ዚማሪና አካባቢውን ሕዝብ በመቀስቀስና በዋካ ኹተማ ሕዝብ ላይ ለማነሳሳት መቀስቀስ ቀጠሉ።
ዹማሹቃ ወሚዳ ሕዝብ ኚቆዳ ስፋቱና ኚሕዝብ ቁጥር አንጻር እንዲሁም ጂኊግራፊያዊ አቀማመጡ ዚተነሳ ሁለት ወሚዳ ሊሆን ይገባል ዹሚል ጥያቄ ማንሳት ተገቢነት ያለው ነው። በዚህ ዚተነሳ ዋካና ማሪ ሁለት ዚተለያዩ ወሚዳዎቜ መሆን ይገባ቞ዋል ዹሚል ሐሳብ ይዞ መነሳት ነው ዚተጚማሪ ወሚዳ ጥያቄ ማለት። ነገር ግን ቀድሞ ዹነበሹን ወሚዳ ዚወሚዳው ማዕኹል ይርቀናል አያማክለንም ዹሚልን ጥያቄ ለማፈን ሌላ ተገቢ ያልሆነ ቅስቀሳ ሕዝብ ውስጥ መርጚት ተጀመሹ።
በምንም ዓይነት ሁኔታዚኢትዮጵያ ዋና ኹተማ ኬንያ ጠሹፍ ዹሚገኝ ቀበሌ ሊሆን አይቜልም። ዚትግራይ ክልል ዋና ኹተማ ደሮ አልተደሹገም። ዳውሮ ውስጥ ብትመለኚቱ ግን ሁኔታው ዹተለዹ ነው። ዚሎማዲሳ ወሚዳ  ዋና ኹተማ ገሳ ጚሬ ይባላል። ይህ አዲስ ዹተቆሹቆሹ ኹተማ ያለው በአጎራባቹ ዹጌና ቊሳ ወሚዳ ውስጥ ነው። ዹሎማ ዲሳ ወሚዳ ሕዝብ ዹጠዹቀው ዚወሚዳቜን ዋና ኹተማ ኚአጎራባቜ ወሚዳ ወጥቶ ቢያንስ እንደቀድሞው ወደ ወሚዳቜን መሐል አካባቢ ተመልሶ በሚያማክለን ሥፍራ ይደሹግልን ነው። ይህንን ጥያቄ አይቶና ሰምቶ መፍትሔ ዚሚሰጥ አመራር ዹለም።
በመንግሥት ውሳኔ ዚተጣመሩ ወሚዳዎቜ ዳግም በመንግሥት ውሳኔ ተለያይተው ቀድሞ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ሲደሚግ ዚወሚዳው ማዕኹል ጉዳይ ወደ ሕዝቡ ወርዶ ውይይት ተደርጎበት ሊወሰን ሲገባ ይህ ሳይሆን ቀርቷል። ታዲያ ይሄ ስህተት ዹማነው? ዚሕዝቡ ነው ወይስ ዚአመራሩ ነው? ኚዲሳ አካባቢ ለምሳሌ ቃኢ ጌሬራና ኚዚያ ርቆ ዹሚኖር አንድ አርሶ አደር ዚወሚዳውን አስተዳደር ፍለጋ አንድ ቀንና ኚዚያ በላይ መጓዝ አለበት ዹሚል ዚወሚዳና ዹዞን አመራር እውነት ለህዝቡ ዹቆመ ነው? አመራሩ ለምንድነው ዚሚመራውን ሕዝብ  ዹማይሰማው? እውነት አሁን ዚዲሳ አካባቢ ህዝብ ወደ ገሳጚሬ እንዲመላለስ ተገቢ አይደለም ያለ ዚመንግሥት ሠራተኛ ሊዋኚብ ሊታሰርና ኚሥራ ሊታገድ ተገቢ ነው?
ዚዳውሮ ህዝብ ዚወሚዳ ማዕኹል ለአቀቱታ ሲሄድ እንደ ዘመነ ምንሊክ ኚቀቱ ስንቅ ቋጥሮ በእግሩ ኚአንድ ቀን በላይ በመጓዝ ላይ ይገኛል። በሎማ ወሚዳ ዲሳ አካባቢ አገልግሎት ማለት ጋሞ ጎፋ ዞን አዋሳኝ አካባቢዚሚገኝ ቀበሌ ማለት ነው። ኚዚያ ተነስቶ አንድ አርሶ አደር ዚወሚዳው ማዕኹል ወደተሰደደበት ሌላ ወሚዳ ማለትም ጌና ቊሳ ወሚዳ ኚአንድ ቀን በላይ መጓዝ ግድ ይለዋል። ኚዚያ በኋላ ተጚማሪ ዚመኪና ጉዞ አድርጎ ነው ገሳ ጚሬ ዹሚደርሰው። ይህ ነው እንግዲህ እውነቱ። ልዩነቱ ጥቂት ዚእግር ጉዞ ሰዓታት ልዩነት ካልሆነ በስተቀር ቜግሩ በቶጫም ሆነ በማሹቃ ወሚዳዎቜ ተመሳሳይ ነው።
ዹሎማን ወሚዳ ምሳሌ አነሳሁ እንጂ ዚቶጫ ወሚዳም ቢሆን ተመሳሳይ ነው። ተርጫ አጠገብ ዋራ አካባቢ ዹሚኖርን አንድ አርሶ አደር ኚጪ ድሚስ ተጉዞ ፍትህ እንዲያገኝ ማስገደድ ምን ይባላል? ኚጪ ኢሰራ ወሚዳ አጠገብ ነው። ቀደም ሲል ኢሰራና ቶጫ ወሚዳዎቜ እንዲጣመሩ በተደሹገ ጊዜ ሁለቱን ወሚዳዎቜ እንዲያማክል በሚል ዹተመሰሹተ ኹተማ ነው። ወሚዳዎቜ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ሲወሰን ዚኢሰራ ወሚዳ ኹተማ ወደ ቀድሞው ማዕኹል ሲመለስ ቶጫ ወሚዳ ግን ቀደም ሲል ወደ ነበሚበት ሥፍራ ሳይመለስ እዚያው እንዲቀጥል ተደሹገ።
ይህ ዚሕዝብ ጥያቄ ሕብሚተሰቡን ኚመቌውም ጊዜ ዹበለጠ ያስተባበሚና እያጠናኚሚው ዚመጣ ሲሆን በገዢው ፓርቲ  áˆ‹á‹­ ያለው ጥላቻ እያደገና እዚኚሚሚ መጥቷል። ለዚህ አስተዋጜኊ ያደሚጉት ካድሬዎቜ ናቾው። ጀግናው ዚነጻነት ታጋይና ሰማዕት ዹሆነው መምህር ዹኔሰው ገብሬም “ ዚወሚዳና ዚልማት ጥያቄ በማቅሚቡ ወህኒ ቀት ሲያስሩት ጀነኛ ዹነበሹ፤ ሲፈቱት ያልታመመና በሳምንቱ ራሱን በብሶት በቀንዚን አቃጠለ። በተቃጠለ በሊስተኛው ቀን ሞተና ኹሞተ በኋላ ደግሞ ፖለቲኚኞቹ እንዲሉት ታዘውና ተገደው እብድ ነበር አሉት።  á‹šáŠšáˆáˆˆá‹ መስዋዕትነት ዹዚሁ ትግል አካል ነበር።  áˆŒáˆŽá‰œáˆ ለሚዲያ ያልበቁ በዚወሚዳው ፍትህና መልካም አስተዳደር እጊት ለቜግራ቞ው መፍትሄ ዚሚሰጥ አካል አጥተው በተለያዚ መንገድ ራሳ቞ውን ያጠፉ ሰዎቜ ቁጥራ቞ው ጥቂት አይደለም። ጊዜና ወቅት ሲፈቅድ ዚሚታወሱበት ሁኔታ ሊኖር ይቜላል።
እኛ አመራሮቹ ዹምንፈልገውን አስተጋቡልንም? ዚወሚዳ ጥያቄ ለህዝቡ አይጠቅምም እያላቜሁ ሕዝቡን ቀስቅሱልን! ዚህዝቡን ጥያቄ ለማፈን ኚገዢው ፓርቲ ጋር ሁሉም ዚመንግሥት ሠራተኛ መተባበር ግዎታው ነው! ይህን ካላደሚግህ ጥገኛ ነህ!  á‰ áˆŒáˆ‹ አባባል ህዝቡን ለማፈን መብቱን ለመንፈግ ተነስተናልና ዚመንግሥት ሠራተኛውም ኚእኛ ይተባበር ዹሚል አስገዳጅ ውሳኔ ወስነው ለመንግሥት ሰራተኛው ጥሪ አደሹጉ። ለዚህ ያልተባበሚውን ዚመንግሥት ሠራተኛ ኚሥራ በማገድ በማባሚር በማሰር ወዘተ ለማስገደድና አንገቱን ለማስቀርቀር ብሎም ዝም ለማሰኘት ይቻላል በሚል እርምጃ መውሰድ ጀመሩ።ይህም ዚሕዝቡን ቁጣ እዚቀሰቀሰው ይታያል። ሚዳት ሳጅን ሜታዬ ወርቁም ታህሳስ 17/ 2005 ዓ.ም በገሳ ጚሬ ኹተማ ዹተደሹገው ዚመንግሥት ሠራተኞቜ ስብሰባ ላይ አካሄዱን ያወገዘው። ሕዝቡን ማፈን ተገቢ አይደለም ያለው።
ዚሚዳት ሳጅን ሜታዬ ወርቁ ጥያቄና ላቀሹበው ዎሞክራሲያዊ ጥያቄ ዹተሰጠው ምላሜም ዹዚሁ ውሳኔ አካል ነው። በደሚሰበት ጫናና እስራት ዚተነሳ ነው ነጻነት በሌለበት ሁኔታ ለመኖር መ቞ገሩን ያስታወቀው። ይህንን ዚሚያደርጉ ካድሬዎቜ ነገ ኚሕዝቡ ጋር ዚሚኖሩ ናቾው ወይስ አይደሉም? እያልኩ ራሎን ስጠይቅ ምላሜ አጣለሁ። መንግሥትም ዚዳውሮ ሕዝብ ቜግርን በመናቅ ጉዳዩ ለስልጣኑ ምንም ዚሚያሰጋው ስላልሆነ ይመስላል እስኚዛሬ እያስለቀሰው ይገኛል።
ይህንን ዚዳውሮን ሕዝብ በደል ለማስቆም ትልቁ ጉልበት ያለው በመንግሥት እጅ መሆኑ ግልጜ ነው። መንግሥት ግን ስለ ሕዝቡ መበደል አልተገነዘበም ወይም ንቆታል አሊያም ኚአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝና ዳውሮ ውስጥ ኚፈጠራ቞ው አሜኚሮቹ ዹሚቀርበውን ዚሐሰት መሹጃ በመቀበል ሕዝቡን እንደጠላቱ ፈርጆታል ብዬ እገምታለሁ። በመሆኑም ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመለወጥና ዚሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዚሚመለኚታቜሁ ዚሕብሚተሰቡ አካላት ዚዚድርሻ቞ውን መወጣት እንደ አለባ቞ው በማመን መልዕክቮን አስተላልፋለሁ።
መልዕክት ለሕወሀት አመራሮቜ
ዚዳውሮ ሕዝብ በደል እጅግ ተባብሷል። ለመንግሥት ያቀሚበው ጥያቄ ተገቢውን ምላሜ ያገኛል ብሎ ተስፋ ያደርግ ነበር። ዚሕዝቡ ጥያቄ በአጭሩ፤ ዚወሚዳ ማዕኹል ቊታ እንዲሆን ዹተመሹጠው ሥፍራ ዚወሚዳውን ሕዝብ አያማክልም፤ ዚወሚዳ ዋና ኹተማ ዝውውር ዹተወሰነውና ዹተኹናወነው በአንድና ሁለት ካድሬዎቜ ዹግል ፍላጎትና መነሻነት ነው፤ ስለዚህ በሕዝቡ ፍላጎትና ሕዝቡን በሚያማክል ሥፍራ ይደሹግልኝ ነው። ቅን መሪ ቢኖርና ዹመወሰን ኃላፊነት ኚተመጣጣኝ ሥልጣን ጋር ዹተሰጠው ዜጋ ይህን ጥያቄ ለመመለስ እንደማይ቞ገር ግልጜ ነው። ይህ ባለመሆኑ ሕዝቡ ተበደለ።
ዚሕወሀት/ ደህዮን ኃላፊና ዹአሁኑ “ ጠቅላይ ሚንስትር ” ዚሆኑት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ዚሰሩትና ዚሚያኚናውኑት ድርጊት ዚዳውሮ ሕዝብ ጥላቻ቞ው እስካሁን እንዳልበሚደላ቞ው ያሳያል። ዚዳውሮ ሕዝብ እምነት ያለውን ጠንካራ አመራር ጠራርገው አስወግደው፤ በቀጣይም ሌላ ዚተሻለ መሪ እንዳይፈጠር አምክነው በግል አሜኚሮቻ቞ው ተክተውታል። እሳ቞ው በስልጣን እስካሉ ድሚስ ዚዳውሮ ሕዝብ ለማንኛውም ፍትሐዊ ጥያቄው ምንም ምላሜ እንደማያገኝ እሳ቞ውም ያውቃሉ፤ አሜኚሮሻሞውም ለዚሁ ሳይታክቱ ይሰራሉ፤ ዚዳውሮ ሕዝብም ይህንኑ በሚገባ ያውቃል። ይቃወሙናል በሚል ዚዳውሮ ኹፍተኛ ባለሙያዎቜ በተለያዚ ሰበብ ኚሥራ ገበታ቞ው እዚተወገዱ ይገኛሉ።
ዚእርሳ቞ው ዓላማ ዚዳውሮ ሕዝብን ጥቅም ሥልጣና቞ውን ተጠቅመው ነጥቀው ዚራሎ ነው ለሚሉት ብሔር አሳልፈው ዚመስጠትና ዚመጥቀም ራዕይ ነው። ለምሳሌ ያህል በዳውሮ ውስጥ ዚተካሄደውን ዚሰፈራ ፕሮግራም ዚሥራ ክንውን፤ በግልገል ግቀ ቁጥር ሊስት ዚኃይድሮ ኀሌክትሪክ ኃይል ምንጭ ግንባታ ሥራ ኚባለሙያና ኚአስተዳደር ሠራተኞቜ ቅጥር ጀምሮ ኹኃይል ማመንጫው ሥራ ጋር በተያያዘ ዹሚኹናወኑ ዹተኹላ ሥራ እንቅስቃሎዎቜ ድርጊቱን መመልኚት በቂ ማስሚጃ ነው። በወላይታ በኩል ብቻ ግንኙነት እንዲኖሚው በማሰብ ዚዳውሮ ጠንባሮን ዹገጠር መንገድ ፕሮጀክት ሥራ ሥልጣና቞ውን ተጠቅመው አስዘግተውበታል። ዚዳውሮ ሕዝብ ዚወሚዳ ጥያቄም እስኚ አሁን መፍትሔ እንዳያገኝ ያደሚጉ እሳ቞ው ለመሆናቾው ዚዳውሮ ሕዝብ ጥርጥር ዹለውም።አሜኚሮቻ቞ውም ለሚቀርባ቞ው ሁሉ ይህቜን ለሕዝቡ አሹጋግጠዋል።አቶ ሺፈራው ሜጉጀ ዚደቡብ ክልል አስተዳዳሪ በዋናነት በዳውሮ ዚወሚዳ ጥያቄ ጉዳይ አቶ ኃይለማርያም ያሳሚፉትን በደል ጠንቅቀው ያውቃሉ። ለሕዝቡ ወሚዳ በመስጠት ቜግሩን ለመፍታት እንኳ እንዳይቜሉ ተደርገዋል።
ህወሀቶቜ ኚአቶ ኃይለማርያምና ኹግል አሜኚሮቻ቞ው ጡጫና በደል ዚዳውሮን ሕዝብ ታደጉ አላቅቁትም። ታግላቜሁ ዚደማቜሁት እናንተ ናቜሁና እናንተው ብትበድሉት ይሻላል እሳ቞ው ኚሚበድሉት። በደልን ማንም በደለ ያው ነው። ግን ዚእሳ቞ው በደል ባሰበትና ነው። እርሳ቞ው እንደሚሉት ዚዳውሮ ሕዝብ አሞባሪ፤ ጥገኛና ጾሹ ልማት አይደለም። ዹሚጠቅመውንም ዚማያውቅ ሕዝብ አይደለም። ዚወሚዳና ዚልማት ጥያቄን ልዩነትና አንድነት ጠንቅቆ ያውቃል። ለወላይታ ሕዝብ አምስት ተጚማሪ ወሚዳ ሲሰጡት አቶ ኃይለማርያም ዚወላይታን ሕዝብ ጥገኛ ነው አላሉም። ጭቁን ሕዝብ ነው ብለው ነበር ዚሰጡት። ዛሬ ዚዳውሮ ሕዝብ ዚወሚዳ ጥያቄ ኚወላይታ ሕዝብ ቀድሞ ያቀሚበ መሆኑን እያወቁ ዚተዛባ ሥም ሊሰጡት አይገባም። ይህንን ለምን ታደርጋለህ? ዹሚል ሰው ዹለም! እርሳ቞ውና ዚአሜኚሮቻ቞ው ዹግፍ አገዛዝ ዘመን በዳውሮ ምድር ሊያበቃ ይገባልና ዚዳውሮን ሕዝብ ኚእሳ቞ው ጡጫ አውጡት።
ዚወሚዳ ጥያቄን ለማምኹን ሲባል ወሚዳውን በሁለትና በሊስት መንደር ኹፋፍሎ ዚአንዱን መንደር ሕዝብ በሌላኛው ላይ ጥገኛ ሕዝብ ነው ታገሉት ብሎ መቀሰቀስ ፍጹም ኃላፊነት ዹጎደለው አካሄድ ነው። ሕዝብ ሁልጊዜ አብሮ ዹሚኖር ነው። መንግሥት እንደነባራዊ ሁኔታው ሊቀያዚር ግድ ነው። ዹሚቀዹርና ዚሚያልፍ መንግሥትና ገዢ ፓርቲ ለዘመናት ዹኖሹንና ወደፊትም አብሮ ዚሚቀጥል ሕዝብን ጥገኛ ነው፤ ዚጥገኛ ሐሳብ ተሞካሚ ነው፤ ጠላትህ ነው! ወዘተ በሚል ሕዝብን በጥላቻ እንዲተያይ ማድሚግ አይጠቅምም። ይህንን ኃላፊነት ለጎደላቾው ኹፍተኛ አመራሮቜ ንገሯ቞ው።
መልዕክት ለዳውሮ ዞንና ለዚወሚዳዎቹ ካድሬዎቜ
ዚዳውሮ ወሚዳዎቜ ዹማዕኹል ጥያቄ ዚተነሳው አሁን በእናንተ ዘመነ ሥልጣን አይደለም። አሁን በስልጣን ላይ ያሉት አመራሮቜም ሆኑ ካድሬዎቜ ለቜግሩ መነሻዎቜ እንዳይደላቜሁ እሚዳለሁ። ዚቜግሩ ምንጭ ቀደም ሲል ዚወሚዳዎቜ መታጠፍና እንደገና መዘርጋት ጥሎ ያለፈው ቜግር እንደሆነም አስተውላለሁ። ቜግሩን ለመፍታት ኚጪ፤ ገሳ ጚሬና ተርጫ ቀት ዚሠሩና ዚንግድም ሆነ ሌሎቜ ዹግል ድርጅቶቜን ዚመሰሚቱ ኹፍተኛ ካድሬዎቜ ዚሚያሳርፉት ቀጥተኛ ያልሆነ ግፊትና ጫናም እንዳለ ይሰማኛል። በዚወሚዳው ማዕኹል ዚተሰሩ ዚአመራሮቜና ዚካድሬዎቜ ዹግል መኖሪያ ቀቶቜ፤ ዚመንግሥት መስሪያ ቀቶቜ ለዚህ ዚወጣው ወጪ ወዘተ ቀላል እንዳይደለም አልዘነጋም። ይህ ሁሉ ግን ኚምንመራው ህዝብ መብት ዚሚበልጥ አይደለም።ተጠቃሚው ሕዝብ አይመቾኝም ሲል ያለው አማራጭ መቀበልና በሕዝብ ውሳኔ መገዛት ይገባቜኋል።
ይህንን ዚቀት ሥራና ዚዳውሮ ዚወሚዳዎቜን ዹማዕኹል ጥያቄ በቀላሉ መመለስ ሲቜል ዹሰሜን ኩሞ ዞን መዋቅር ፈርሶ በ1993 ዓ.ም መግቢያ አካባቢ ዳውሮ እንደ ዞን ሲዋቀር በወቅቱ ዚነበሩ ዚፖለቲካ አመራሮቜ ይህንን ቜግር በሚገባ አስተውለው መወሰንና በቀላሉ ማስተካኚል ሲገባ቞ው ይህንን ቜግር ተክለው እንዳለፉ ይሰማኛል። ይህ ዚዛሬው ዚዳውሮ ዚአያማክለኝም ጥያቄና ቜግር በሂደት ሊመጣ እንደሚቜል አስቀድመው ማዚት ዚቻሉ ዚዳውሮ ምሁራንና ባለሙያዎቜ ነበሩ። አስተያዚታ቞ውን አቅርበው እንደነበር አውቃለሁ። ወሚዳዎቜ እንዎት በአዲስ መልክ ቢካለሉ ዚተሻለ ሊሆን እንደሚቜል አጥንተው ያቀሚቡት ነገር ነበር። ይህንን ጥናት አስፍቶ ሕዝብን ማወያዚትና ዚተሻለ መፍትሄ ማምጣት አልተቻለም። ዚዚያኔ  áŠ áˆµáˆáˆ‹áŒŠ ዹነበሹው ወሚዳና ዚወሚዳ ማዕኹል ጉዳይ እንደተራ ነገር ታይቶ መፍትሄ ሳያገኝ ቀርቷል። ሕዝብ ተንቋል።
ዚቶጫ ወሚዳ ሕዝብ ዚመኪና መንገድ በመቆፈር ግንኙነት መቁሚጡን አትዘነጉትም። ይህን  ያደሚገ ህዝብ አቅም ቢኖሚው ኖሮ ለደሚሰበት በደል ዚተሻለ እርምጃ አመራሩ ላይ ይወስድ እንሰነበር ለመገመት ዚሥነ ልቡና ትምህርት አይጠይቅም። ተቃውሞውን አሳይቷል። በተመሳሳይ ዚዋካንና አካባቢውን  áˆ•ዝብ ዚወሚዳ ማዕኹል ጥያቄ ባለፈው ዓመት አይታቜሁታል። ዚዲሳን ሕዝብ ብሶት ደግሞ ሰሞኑን እያያቜሁት ነው።
ጋሞ ጎፋና ዳውሮ ዚተለያዩ ናቾው። አቶ ታገሰ ጫፎ ወደ ደጋማው ዹጋሞ አካባቢ ተንቀስቅቅሶ ዚሕዝብ ፍላጎት ዹነበሹውን ዚተጚማሪ ወሚዳ ጥያቄ ለማምኹን ባደሚገው ጥሚት ውጀታማ ሥራ ሰርቷል በሚል ተሞክሮ ይህ ሂደት በዳውሮ ሕዝብም ላይ ይሞኹር በሚል ዚዳውሮ ሕዝብ እንደላቮራቶሪ እንዲሞኚርበት አሥራ አንድ ገጜ ወሚቀት ለውይይት ዹቀሹበ ሰነድ በሚል ተዘጋጅቶ ተሰጥቷቜሁ ዚሕዝቡን ጥያቄ ለማፈን እዚሰራቜሁ ትገኛላቜሁ። ለዚሁም አፈጻጞም እንዲመቜ አስተያዚት እንዲሰጥ ዹመናገር ዕድል ለማን እድል መስጠት እንዳለባቜሁ ጭምር ተነግሯቜሁ በነጻነት መናገር ለሚቜሉ አርሶ አደሮቜ ዹመናገርና ሀሳባ቞ውን መግለጜ እንዳይቜሉ በሕዝብ ስብሰባው ላይ እድል በመኹልኹል፤ እንቢ ብለው ኚተናገሩ አቅራቢያቜሁ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ በማሰር ማፈን፤ ዚመንግሥት ሠራተኛ ኹሆነ ደግሞ በተጚማሪ ማስፈራራት ኚሥራ ማገድ እንዲሁም ኚሥራ ማባሚር ወዘተ ተግባራዊ በማድሚግ ዚህዝብን ጥያቄ መቀልበስ እንደሚገባ ኚሰነዱ ላይ ሰፍሯል። እዚሰራቜሁ ያላቜሁትም ይህንን ተግባራዊ ለማድሚግ ነው። በዋናነት ዹጋሞጎፋ ሕዝብ ጥያቄ ዚተጚማሪ ወሚዳ ጭምር እንጂ በጉልህ ዚወሚዳ ማዕኹል ጥያቄ አልነበሹም።
ባለሙያዎቜ ዚሆናቜሁ አመራሮቜና ካድሬዎቜ በሙያቜሁ ሰርታቜሁ በቀላሉ መኖር ዚምትቜሉት ዜጎቜ ናቜሁ። እውነትን ሰርቶ ማለፍ ዹህሊና ቁስል ዹለውም። እስቲ ዚሚኚተሉትን ጥያዌዎቜ ልጠይቃቜሁ። ሲዳማ ዘጠኝ፤ ወላይታ አምስት፤ ቀንቜ ማጂ ሊስት፤ ስልጢ ሁለት፤ ጎፋም እንደዚሁ አዳዲስ ወሚዳዎቜ ለሕዝቡ ሲሰጥ ለምን ዹነዚህ ዞንና ወሚዳዎቜ አመራሮቜ ህዝቡን ወሚዳ አያስፈልገውም ልማት ይጠቅመዋል ብለው ወሚዳውን ያላስኚለኚሉትና ሕዝባ቞ውን ያልቀሰቀሱት ለምንድነው? ምናልባት አመራሩ ጥገኛ ስለሆነ ነው ትሉኝ ይሆናል። ለሲዳማ አቶ ሺፈራው፤ ለወላይታ አቶ ኃይለማርያም፤ ለስልጢ አቶ ሬድዋን፤ ለቀንቜ ማጂ አቶ ጞጋዬ ዹክልሉ ኹፍተኛ አመራሮቜ ዚነበሩት ለሕዝባ቞ው አዳዲስ ወሚዳዎቜን ሰጧቾው። እርግጠኛ ነኝ እነዚህን አመራሮቜ ጥገኛ ናቾው እንደማትሉ! ታዲያ ዳውሮ ውስጥ ተጚማሪ ወሚዳ መጠዹቅ ይቅርና ዚወሚዳ ማዕኹል ይስተካኚልልኝ ብሎ ማሰብ መናገርና መጠዹቅ ምነው ጥገኝነት በሚል ፍሹጃ ውስጥ ዚሚያስገባ ሆነ? ዚዳውሮ ዚወሚዳ ማዕኹል ጥያቄ ለምን ኚልማት ጋር ይያያዛል? እናንተ ለህዝባ቞ው ወሚዳ ኚሰጡት ባለስልጣናት ዚምታንሱት ሕዝባቜሁን ስለማትወዱና ራሳቜሁንና ዚሥልጣን ዘመናቜሁን ለማስሚዘም ብላቜሁ ነው ዹሚል ጥያቄ ቢነሳባቜሁ መልሳቜሁ ምን ይሆን? ቀድሞውኑ ማን ጠይቋቜሁ!
በቀድሞዎቹ ዚንጉሡና ዹደርግ መንግሥታት ዘመን ያገለገሉትና ሕዝብን በድለዋል ተብለው ብዙ ባለስልጣናት ታስሚዋል ተቀጥተዋል። እነዚህ ባለሥልጣናት አብዛኛዎቹ ያገለገሉበት መንንግሥት ዚሰጣ቞ውን ሥራ በሕዝቡ ላይ አስገድደው አስፈጜመዋል። ትልቁ በደላቾውና ስህተታ቞ው ይህ እንደሆነ ሲገለጜ ሰምተናል። ዚመንግስትን ዕቅድና ፍላጎት በጉልበት ማስፈጞም፤ ዚግለሰብን ዹመናገርና ዚማሰብ ነጻነት መንፈግ፤ ያለምንም ጥፋትና በደል ሰውን በመናገሩ ብቻ እንደወንጀለኛ ማሰር ማንገላታት ኚሥራ ማባሚር ወዘተ ማድሚግ ኚቻላቜሁ ታዲያ እናንተ ኚእነርሱ ዚምትለዩት በምንድነው? እናንተስ ነገ ተመሳሳይ ጥያቄ እንደማትጠይቁ እርግጠኞቜ ናቜሁ?
አትቀበሉኝ ይሆናል ግን ልምኚራቜሁ።‘‘ጻድቃን ሥልጣን ሲይዙ ሕዝብ ሐሀት ያደርጋል፤ ክፉዎቜ ሲገዙ ግን ሕዝብ ያቃስታል፡፡’’ ምሳሌ 29፡2  እናንተንን ክፉዎቜ ናቜሁ ለማለት ባልደፍርም ዚዳውሮ ሕዝብ እያለቀሰ ነው። እውነቱን ደግሞ ውስጣቜሁ ያውቀዋል። እናንተም ነገ ታልፋላቜሁ። ለሚያልፍ ሥልጣን ብላቜሁ ዚማያልፈውን ወገናቜሁን በዋናነት ዳውሮንና ሕዝባቜሁን አትበድሉ። ዹመሰለውን ስለተናገሚ ሰውን አላግባብ ጎትታቜሁ አትሰሩ። ዹደርግ ባለሥልጣናት እንኳን እንደናንተ ለሕዝብ እንዲዋሜ ትብብር ጠይቀው እንቢ አልተባበርም ያላ቞ውን ግለሰብ ስለማሰራ቞ው እርግጠና አይደለሁም። ዚእናንተ ባስ እኮ!
ዚመንግሥት ሠራተኛ ዹግል ሠራተኛቜሁ አይደለም። እንደእናንተ ሕዝብን አልዋሜም ስላለ ኚሥራም አንዲባሚር እንዲጎሳቆል አታድርጉ። ቢቻላቜሁ ዚህዝቡን ጥያቄ በምትቜሉት ሁሉ መልሳቜሁ ምኑም ቀርቶባቜሁ በሰላምና በፍቅር ኚወገኖቻቜሁ ጋር ብትኖሩ ይሻላቜኋል። ነገ ኚስልጣን ስትወርዱ ዚምትኖሩት ኚዳውሮ ሕዝብ ጋር ነው። ብትሞቱ ዚሚቀብራቜሁ ይህ ህዝብ ነው። ቃሉን አክብራቜሁ ብትሰሩ ይጠቅማቜኋል። ወደዳቜሁም ጠላቜሁ ዚህዝብ ጥያቄ ምላሜ ማግኘቱ አይቀርም። አሁን በሥልጣን ያላቜሁት ግለሰቊቜ ዚሕዝቡን ጥያቄ በተገቢው መልሳቜሁ ምርቃቱ ቢቀርባቜሁ እንኳ ሳትሚገሙ ብታልፉ ይሻላቜኋል። ነገ ኚነገወዲያ እግዚአብሄር ሲፈቅድለት በእናንተ ማግስትም ቢሆን ዚህዝብ ጥያቄ በተገቢነት መመለሱ እንደማይቀር ለማዚት ዕድሜ ያድላቜሁ!
ለመንግሥት ሠራተኞቜ
ሚዳት ሣጅን ሜታዬ ወርቁ በሎማ ዲሣ ወሚዳ አካባቢ ዚዲሣ ኹተማ ፖሊስ በመሆን ለዓመታት ማገልገሉንና በቅርቡ ወደ ሎማ ገሣ መዛወሩን፤  á‰ á‹²áˆ£ አካባቢ ቆይታዉ ወቅት ዚዲሣን ወሚዳ ጥያቄ ዚሚያንቀሳቅሱ ሊስት ግለሰቊቜን እንዲያስር ኚዳዉሮ ዞን ዚፖለቲካ ጉዳዮቜ ሀላፊ መመሪያ ተሰጥቶት ያለ አንዳቜ በቂ ማስሚጃና ጥፋት ሰዉ እንዲሁ ኚሜዳ አላስርም በማለቱ በዞኑ ኹፍተኛ ባለሥልጣናት በሁኔታው አልተደሰቱም ነበር፡፡ ዚዲሣን ወሚዳ ጥያቄ ያንቀሳቅሳሉና መታሰር አለባ቞ዉ ተብለዉ ኹዞኑ ፖለቲካ ኃላፊ ትዕዛዝ ዚተላለፈባ቞ዉ ግለሰቊቜ አቶ አባ቎ አሰፋ ዚትምህርት ባለሙያ፤ አቶ መስፍን ማሞ አርሶ አደር፤ እና አቶ ደስታ ቶልባ ዚግብርና ባለሙያ ነበሩ። አሁን እዚህ ላይ ዚፖለቲካ ኃላፊውንና ፖሊሱን አወዳድሩ። ዚትኛው ነው ለሕዝብ ዹቆመውና እውነተኛ ዚህዝብ ጥቅምና መብት ዚታገለው? ልዩነቱን ተመልኚቱ።
ይህንን ያነሳሁት በዚወሚዳው እዚተደሚገ ያለው  ዚሕዝብን እውነተኛ ዚተጚማሪና ዚወሚዳ ማዕኹል ይስተካኚልልኝ ጥያቄ ዚመንግሥት ሰራተኛው እንዳይደግፈው ለማድሚግ እዚተካሄደ ያለውን ሁኔታ ለማመላኚት ነው። ዚመንግሥት ሠራተኛው ዚራሱም ሆነ ዚቀተሰቡ ህይወት መንግሥት በሚኹፍለው ዹወር ደመወዙ ላይ ዹተመሰሹተ በመሆኑ ካድሬዎቜ ይህቜን እንጀራውን እንደማስያዣ ዕቃ ቆጥሚው አንድን ዚመንግሥት ሠራተኛ እነርሱ ዚፈለጉትን እንደ ቎ፕሪኚርደር ሲዲ ያሻ቞ውን ሞልተው ለማናገር ዹወሰኑ ይመስላል።ልጅን በአባቱና በቀተሰቡ ላይ ለመቀስቀስ እዚሰሩ ነው።
ኃላፊነት ዹጎደለው ሥራ እያተሰራ ይስተዋላል። ዚህዝብን ጥያቄ ለማፈን ለመንግሥት ኚባድ አይደለም። እንደተለመደው ማሰር ማንገላታት ማስፈራራትና ጥያቄህን አንመልስም እንቢ ምን ታመጣለህ? በሚል በተለመደው መንገድ ማስቆምና መግታት ይቻላል። ተቜሏልም። ነገር ግን አንድ ወሚዳ ውስጥ ያለን ዹኖሹንና ዹሚኖርን ሕዝብ እርስ በራሱ ለማጋጚት በአንድ ወሚዳ ውስጥ ዚዋካንና ዙሪያውን ህዝብ ጥያቄ ዚማሪ ዙሪያ ህዝብ እንዲቃወመው ሕዝብን ማነሳሳትና መቀስቀስ፤ ዚዲሳን አካባቢ ሕዝብን ዚወሚዳ ማዕኹል ጥያቄን ለመቀልበስ ዚገሳጚሬ አካባቢ ሕዝብን መቀስቀስ፤ ዚቶጫ አካባቢን ሕዝብ ጥያቄ ለማፈን ዚኚጪ አካባቢ ሕዝብን መቀስቀስ ዚዛሬን ዚሕዝብን ዚወሚዳ ጥያቄ ለመግታት እዚተሰራ ያለው ኃላፊነት ዹጎደለው ሥራ ለነገ አብሮነታ቞ው ዚሚያሳድሚው ዹነገር ቁርሟ እንዳይኖር በተማሩትና አርቀው ማስተዋል ዚሚቜሉት ዚሕብሚተሰቡ ወገኖቜ ሊያስቡበትና ሊነቁበት ይገባል። ካድሬዎቻቜን ምን እንደነካ቞ው አላውቅም። እኛ በስልጣን ላይ ዛሬን እንቆይ እንጂ ዚሕዝብ ጉዳይ ዹነገ ጉዳይ ወዘተ አያገባንም ያሉ ይመስላልና እንድናስብ አደራ እላለሁ። እነርሱ ለሕዝባ቞ውና ለዳውሮ ጥሩና ዚሚቜሉትን አድርገው ለማለፍ ዚታደሉ አይደሉም።
በ1998 ዓ.ም እና በ1999 ዓ.ም ዚሌሎቜ አካባቢዎቜ ዹዞንና ዹክልል አመራሮቜ ዚነበሩ ለህዝባ቞ው ልማትና ዕድገት ሲሉ ዚራሳ቞ውን ጥቅም ዚማያስቀድሙ፤ ህዝባ቞ውን ዚሚወዱና ዚሚያኚብሩ፤ በተሰጣ቞ው ዚስልጣን ክልል ዚህዝባ቞ውን ዚልማትና ዚወሚዳ ጥያቄ አንግበው ዚታገሉና ጾንተው ዹቆሙ፤ ዹወኹለኝ ህዝብ ጥያቄ ዚእኔም ጥያቄ ነው ያሉ አመራሮቜ በሌሎቜ ዞኖቜና አካባቢዎቜ በተለያዚ ቊታና ደሹጃ አሉ። ዚሲዳማን ዚስልጢን ዹጎፋን ዚቀንቜንና ዚወላይታ አመራሮቜን ዚሥራ ተግባር ማዚት እንቜላለን። እነዚህ ህዝባ቞ውን ጠቅመዋል። ዹወኹላቾውን ሕዝብ ጥያቄ በሆዳ቞ው አልለወጡትም። በዚህ ዚተነሳ ኹፍተኛ ዚሞራል ዚበላይነት ሊሰማቾው ይገባ቞ዋል። ሕዝባ቞ውና አካባቢያ቞ው ሲዘክራ቞ው ይኖራል።
ለጊዚያዊ ዹግል ጥቅማ቞ው ዹቆሙ፤ ነገ ሳያውቁትና ሳይመሰገኑበት አሊያም ታስሚው ወይም ተባርሚው ለሚጥሉት ሥልጣን ትኩሚት ዚሰጡ፤ ለጊዜው  á‹šá‹«á‹™á‰µáŠ• ሥልጣን ማጣት ዚሚያስጚንቃ቞ው፤ ራስ ወዳዶቜ፤ ጥሩ ነገር ለህዝባ቞ው ሰርተው ለማለፍ ያልታደሉና አድርጉ ዚተባሉትን ለማድሚግ ተሜቀዳድመው ኚመሮጥ ባሻገር ቆም ብለው ይህ ሕዝባቜንን አካባቢያቜንን ይጠቅማል ወስ አይጠቅምም? ሕዝቡስ ምን ይላል ማለት ዚማይቜሉ ዚህዝብ ተቃራኒዎቜ ደግሞ አሉ።። ዚዳውሮ ዞን አመራሮቜን በዚህ ቡድን አስገብቶ መውቀስ ተገቢ ነው። ጠንካራ አመራሮቜ ለህዝባ቞ውና ለዞናቾው ተጚማሪ ወሚዳ ታግለው አስገኙ። እኛ ለህዝብ ዹቆመ አመራር በዞን ደሹጃ ስላልነበሚን ዚዳውሮ ህዝብ እያነባ እያለቀሰ ይገኛል። ኚእሱ ዹተሰበሰበው ግብርና ታክስ እዚተኚፈለው ዚሚሰራ አመራርና ካድሬ ህዝቡ ወሚዳ አያስፈልገውም አልጠዹቀም እያለ እዚዋሞ እኛም ዚሱን ግጥምና ዜማ ተቀብለን እንድናዜም ሊያስገድደን ይታገለናል። አለመታደል እኮ ነው ወገኖቌ! በፍጹም እንቢ ልንል ግድ ይለናል። ተቃውሟቜሁን በግልጜ አድርጋቜሁ ጥቂቶቜን ሰለባ ማድሚግ ባያስፈልገንም ዚሕዝብ አጋርነታቜንን በምንቜለው ሁሉ በቀጥታም ሆነ በተቃራኒ መግለጜ ዚሞራል ግዎታቜን ነው።ይህ አመራር ጥቅሜ ኹሚጓደልና ዚመኪና ጋቢና ኚሚቀርብኝ ኚዳውሮ ሕዝብ ምኑም ይቅርበት ብሎ ዹወሰነ ይመስላልና ያቅማቜንን ዚማበርኚት ግዎታ ይጠብቀናል።
ለዳውሮ አርሶአደሮቜ፤ ነጋዎዎቜና ሌሎቜ ዹዹኹተማው ነዋሪዎቜ
ለዳውሮ ዞን ሕዝብ መንግሥት ተገቢውን  ምላሜ እንደሚሰጣቜሁ በተስፋ ስትጠብቁ ቆይታቜኋል። ነገሩ መፍትሄ ሊሰጠው እንደሚገባ ዚሚታወቅ ቢሆንም ዚህዝቡ ጥያቄ ምላሜ ሊያገኝ ይገባል ዹሚል ዚፖለቲካ አመራር በዹደሹጃው ባለማኖሩ እስካሁን ተገቢውን ምላሜ ማግኘት አልተቻለም። እንዲያውም እያደር ጥያቄው ዚጥገኞቜ ነው፤ ዚጥቂቶቜ ነው፤ ዚብዙኋኑ ዚዳውሮ ሕዝብ ጥያቄ አይደለም፤ ሕዝቡ ልማት እንጂ ወሚዳ አይጠቅመውም በሚል ዚሕዝቡን ጥያቄ ለመቀልበስና አቅጣጫውን ለማስቀዚር ብሎም ህዝቡ ተጚማሪ ወሚዳ እንዲያጣና ዚሚሻውን ዚወሚዳ ማዕኹል ወደሚቀርበው ሥፍራ ዹማዛወር መብት እንዳይኖሚው ለማድሚግ ተግተው እዚሰሩ ይገኛሉ።
ዹገዛ ልጆቜህ ናቾው ጥያቄህን ለመድፈቅ አሲሚው አንተን ለማፈን ተግተው እዚሰሩ ዚሚገኙት። ዹሚናገሹውን ለማስፈራራትና እንዳይናገር በማድሚግ እድል በመኹልኹልና በማሾማቀቅ፤ ለምን መብታቜንን ትነኩብናላቜሁ ብለው ዹሚጠይቁ ኹተገኙ ለማስፈራሪያነት በማሰር ለማስፈራራት ዕቅድ ተሰጥቷ቞ው ይህንን ለመተግበር ይሰራሉ። በመንደርና በአገልግሎት በመኹፋፈል ጥያቄህን ለማሳነስና ዚጋራ ጥያቄ አይደለም ዚጥቂቶቜ ነው ለማለት እዚተባበሩ ነው። ስለዚህ በአገልግሎትና በመንደር መኹፋፈል አያስፈልግህም። ልማትና ወሚዳ አይነጣጠልም።
አንድ ምሳሌ ላንሳላቜሁ። ዚወሚዳ ማዕኹል ጥያቄ ዚእኛ አይደለም ዚጥቂቶቜ ነው እኛ ወሚዳ አንፈልግም በሉ፤ እንቢ ካላቜሁ ሁለተኛ ደሹጃ ት/ቀቱን ኹዚህ እናነሳለን፤ ዚጀና ጣቢያ ሥራ አይኹናወንም ወዘተ ዹሚል ተራ ማስፈራሪያ አንድ ሆድ አደር ካድሬ ሲናገር ሰምተው ኚተሰብሳቢዎቹ መካኚል አንዱ አርሶ አደር (በማሹቃ ወሚዳ ጌንዶ አገልግሎት አካባቢ ውስጥ ነዋሪ ናቾው ) ካድሬውን በሚያሳዝን መልኩ ሚግመውት አሁን ዚእኛን ወሚዳ ጥያቄ ለማስጚንገፍ ብለህ ለሆድህ አድሚህ ህሊናህን ሜጠህ በል ዚተባልኚውን እያልክ ነው ብለዉት ይህንን ተራ ወሬ ይዞ ወደ መጣበት እንዲመለስና እሳ቞ውም ሆነ ሕዝቡ ዚሚሻለውን ጠንቅቀው ዚሚያውቁ መሆኑን አስተምሚውት አሳፍሚውት መልሰውታል።
ይህንን ዚተናገሩት አርሶ አደር በፖለቲካዊ ንቃተ ህሊና አንጻር ኚካድሬው ጋር አነጻጜራቜሁ ዚቱ ዚተሻለ ደሹጃ ላይ እንዳለ አስተውሉ። ማነው ዹህሊና ነጻነት ያለው? ልማትና ወሚዳ አይነጣጠሉም። ወሚዳ ሲመጣ ኚወሚዳው ጋር አብሮ ልማትም ይመጣል። ዳውሮ ዞን ባይሆን አሁን ዚደሚሰበት ዚልማት ደሹጃ ላይ ይደርስ ነበር ዹሚል ካድሬ ሊመጣ እንደሚቜል አትጠራጠሩ ግን አትመኑት። ዹሰሞኑ ካድሬ ድንጋይ ዳቊ ነው ለማለት ዚሚታቀብ ስለመሆኑ ያጠራጥራል። እያኚናወነ ያለው ክብሩን ህሊናውን ሞራሉን ሁሉ ትቶት ነው።
ዚዳውሮ ሕዝብን ዚወሚዳና ዚልማት ጥያቄውን ለመቀልበስ ዚሚሰሩ ሁሉ ዚዳውሮ ልማትና ዚዳውሮ ህዝብ ጠላቶቜ ናቾው! ሕዝብ ዹሚበጀውንና ዚሚሻለውን ያውቃል። ዚካድሬ ሰበካና ዚሐሰት ቀላጀ አያስፈልገውም። ዚካድሬው ዓላማ ዚህዝብን ጥያቄ ወደ ጥቂቶቜ ጥያቄነት ለመቀዹርና ጥያቄውን ለማምኹን ነውና ሁላቜንም በምንም ሳንኚፋፈል አብሚን ቆመን ጥያቄያቜንን በጋራ በአንድ ድምፅ ማስተጋባት ይጠበቅብናል።
ዚዳውሮ ምሁራን ዚሆናቜሁ በሙሉ!
ኹላይ በዝርዝር ያስቀመጥኩትን እውነታ ተመልክታቜኋል። ዚዳውሮ ዞን አመራሮቜ ኹክልል አመራሮቜ ተጭነው ዚመጡትን ዚሕዝቡን ዚወሚዳና ዚወሚዳ ማዕኹል ጥያቄ ለማምኹን ምን ያህል ተግተው እዚሰሩ እንዳለ ተመልኚቱ። ኚራሳ቞ው አልፈው ዚወሚዳ አመራሮቜንና ካድሬዎቜን አስገድደው ዚተጫኑትን መልሰው ጭነውባ቞ው ኚህዝቡ ጋር እያላተሟ቞ው ይገኛል። እኔ በግሌ ዚወሚዳ አመራሮቜ ላይ ብዙ አልፈርድም። ለአብዛኛዎቹ ዚእንጀራ ጉዳይም ሆኖባ቞ው ሳይወዱ በግድ ዚተጫኑትን ማራገፊያ አጥተው እንደሚሰቃዩ ይሰማኛል። ኚሕዝቡም እዚደሚሰባ቞ው ያለው ነገር እያሰቃያ቞ው ነው። በድርጊቱ ኹዞን ጀምሮ ያለው አመራር በሕዝባቜን ላይ ለሚደርሰው ማንኛውም በደልና እንግልት ተጠያቂ መሆናቾውን ልብ ልንል ይገባል።
ምሁሩ ዚሕዝብ ወገን አመራሩ ለምንድነው እንዲህ ዚሚያደርጉት? ምን ይሻሻል? ኚእኔ ምን ይጠበቃል? በሚል ማሰብ እንደሚገባቜሁና እንቅስቃሎውንም በአንክሮ መኚታተል እንደሚጠበቅባቜሁ አሳስቀ ጜሁፌን በዚሁ እቋጫለሁ።

Jan 3, 2013

Breaking News: Protest erupts at Addis Ababa University

                                                                       Addis Ababa University main campus

Awramba Times (Addis Ababa) – Protest sparked at the College of Natural Sciences, Arat Kilo Campus of the Addis Ababa University. According to our sources in Addis Ababa, The main cause of the protest is due to an ethnic derogatory poster against Oromo-ethnic students placed at the College’s main Library and two other places.
So far, more than 20 students from the conflicting ethnic groups were wounded and were taken to government hospitals. On the other hand Police have accused several students of causing damage to university property, including broken windows and doors. More details to come…

ዚኀርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ዚኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ ያቀሚበውን ዹመነጋገርና ዚመታሚቅ ጥያቄ ውድቅ አደሹጉ


ኢሳት ዜና:-ኚኀርትራ ቎ሌቪዥን ጋር ቃል ዚተመላለሱት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ኀርትራ ስልጣን ላይ ካሉ ግለሰቊቜ መቀያዚር ጋር ዚምታያይዘው አንዳቜም ነገር ዹለም ካሉ በሆላ ዝንባሌው እራሱ ኚኀርትራ ባህልና እሎት ዹሚቃሹን መሆኑን ገልጠዋል::
እንነጋገር ዹሚለው አባባል ምንጩ ኚዚት እንደሆነ እንሚዳልን ያሉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ይህ አይነት አካሄድ ትኩሚት ኚማስቀዚር በቀር ምንም አይነት ጥቅም እንደሌለውና ኀርትራም ዚምትገባበት ድራማ እንዳልሆነ አመልክተዋል::
ዚድንበር ኮምሜኑ ውሳኔ ተግባራዊ ላለመሆኑ ዚአሜሪካ መንግስት ተጠያቂ ነው ያሉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ውስጥ ኹፍተኛ እንቅስቃሎ እዚተካሄደ መሆኑን ኚሀገራ቞ው ቎ሌቪዥን ጋር ባደሚጉት ቃለምልልስ አስታውቀዋል::
ፕሬዚዳንቱ ዚአሜሪካ መንግስት በሀገራ቞ው ላይ ዚጣለውን መአቀብ በመቆቆም አንድነቱንና እድገቱን በማጠናኹር መዝለቁንም በዚሁ ቃለምልልስ ገልጠዋል::
ኚአልቃይዳና ኚአልሞባብ ዚተሰጣ቞ውን ግዳጅ ለመፈጾም ሲንቀሳቀሱ ተገኝተዋል ዚተባሉ 10 ተኚሳሟቜ ጥፋተኛ ተባሉ ::  አንዱ በነጻ ተለቀቀ::
በተያያዘ ዜና በሱማሊያ ኹሚገኙ እስላማዊ ሀይሎቜ ጋር ያላ቞ውና በኢትዮጵያ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዹተዘጋጁ ያላ቞ውን 15 ተጠርጣሪዎቜ  ዚኢትዮጵያ መንግስት መያዙን ሮይተርስ ዘገበ:፡ ዚፌደራል አቃቢ ህግ ክስ ዚመሰሚተባ቞ውና በዕስር ላይ ሆነው ክሳ቞ውን ሲኚታተሉ ኚነበሩት መካኚል በሜር ሀጂ እስማኀል ዚተባለው ተኚሳሜ ነጻ ሲወጣ ሌሎቜ 10 ተኚሳሟቜ ጥፋተኛ ተብልዋል::
አቃቢህግ ዹወንጀሉ ጠንሳሜ ዚአልቀኢዳና ዚአልሞባብ ዋና ተላላኪ ያለውን ነዋሪነቱ በሶማሊያ ሞቃዲሟ ዹሆነውን ሀሰን ጋርሶ ስቶላ ክሱ እንዲኚብድና በእድሜ ልክ እስራት እንዲቀጣለት ጠይቆል::
ጥፋተኛ ዚተባሉት 10 ተኚሳሟቜ በህቡ በመደራጀትና በመንቀሳቀስ በኢትዮጵያ ዚፖለቲካና ዚሀይማኖት አላማ ለማራመድ በማሰብ በመንግስት ላይ ተጜዕኖ ለማሳደር ህብሚተሰቡን በማስፈራራት ህገመንግስታዊ ስርአቱን ለማፈራሚስ በአሞባሪነት ኚተፈሚጁት ኚአልቃይዳና ኚአልሞባብ ጋር ሲንቀሳቀሱ እንደነበር አቃቢ ህግ በክሱ ላይ አስሚድቶል::
በዚህ መሰሚት ግለሰቊቹ ሊፈጜሙት ዹነበሹው ወንጀል ኚባድ እንዲባል አቃቢ ህግ ፍርድ ቀቱን ጠይቆል::
በተያያዘ ዜና ዚኢትዮጵያ ዚደህንነትን ዚጞጥታ አገልግሎት 20 ሰአት በፈጀ ዘመቻ በሀገሪቱ ላይ ጥቃት ለመፈጞምምያቀዱ 15 ሰዎቜን መያዙን ሮይተርስ ዘግቩል::
እንደዘገባው ኹሆነ ተጠርጣሪዎቹ በሱማሊያ ኹሚገኝ እስላማዊ ቡድን ዚተቀጠሩ፡ዹሰለጠኑና በኢትዮጵያ ላይ ጥቃት እንዲፈጜሙ ዚተሰማሩ ናቾው ብሎል  ዚኢትዮጵያ ዚደህንነትን ዚጞጥታ አገልግሎት:፡
ዚተያዙት 15 ሰዎቜ ዜግነት አልተገለጠም ያለው ሮይተርስ ኚሱማሊያና ኚኬኒያ አቆርጠው ኢትዮጵያ መግባታ቞ውን ግን ዘግቩል:፡

በመቀሌ ኹተማ ዹግል ጋዜጣና መጜሄት አዞሪዎቜና ሻጮቜ ስራ቞ው ህገወጥ በመሆኑ ኚስራ መታገዳ቞ው ተገለጠ




ኢሳት ዜና:- በኹተማዋ በቆሚነት ደርድሚውና እያዞሩ ጋዜጣና መጜሄት ዚሚሞጡ በመኹልኹላቾው ህዝቡ ጋዜጣ ማግኘት አለመቻሉን ዹመቀሌ ኹተማ ነዋሪዎቜና ዚቅርብ ምንጮቜ ያላ቞ውን ጠቅሶ ሪፖርተር ዘግቩል::
ስማ቞ው እንዳይገለጜ ዹጠዹቁና በአካባቢው ጋዜጣና መጜሄት በመሞጥ ዚሚተዳደሩ ወጣቶቜ ዹጠቀሰው ዘገባ ዹኹተማዋ ወያኔ ወሚዳ ንግድና ኢንዱስትሪ አስተዳደር ስራው ህገወጥ መሆኑ ተገልፆላቾው ኚታህሳስ 5፣2005 ጀምሮ በአካባቢው ዹገል ጋዜጣና መጜሄት ዚመሞጥ ስራ እንዳይሰራ መታገዱን አመልክቶል::
ይህንን ትእዛዝ ተላልፋቜሁ ጋዜጣና መጜሄት እያዞራቜሁ ተገኝታቜሆል ዚተባሉ አምስት ወጣቶቜ በፖሊስ ተይዘው መታሰራ቞ው ዚታወቀ ሲሆን ሲያዞሩት ዹነበሹው ጋዜጣና መጜሄት መወሚሱ ተዘግቩል::


ESAT Daliy News-Amsterdam Jan. 03 2013 Ethiopia

Ethiopian woman in Kuwait died after falling from a building


KUWAIT CITY (Arabtimes) — An Ethiopian woman died when she fell from the window of a domestic employment agency in Hawally.
According to security sources, when the Operations Room of Ministry of Interior received information from the building guard about a woman lying on the ground and bleeding, police and paramedics rushed to the location and found the woman bleeding profusely from the head.
Paramedics examined her and discovered she had succumbed to severe head injury.
Officers from General Department for Criminal Evidences rushed to the location and referred the corpse to the Forensics Department.
Preliminary investigations by authorities revealed that the victim fell from the window of a domestic employment agency in the building. They also noticed that the victim was wearing ‘abaya’ without any underclothes. They were informed that the woman was at the agency with three other Ethiopian women.
Police summoned the three women and the owner of the agency to the police station where they said that they were sleeping at the time of the incident and were not aware of her death until the police notified them about it.
A case was registered for further investigations.

ኢሳያስ አፈወርቂ በጩር ወንጀለኝነት ሊጠዹቁ ይገባል ተባለ


ር ያ ዕቆብ ኃይለማርያም ኢሳያስ አፈወርቂ “በጩር ወንጀለኝነት ሊጠዹቁ ይገባል” አሉ። ዚፖለቲካ ኢኮኖሚ
ባለሙያ ዚሆኑት ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በርሄ በበኩላ቞ው “ዚኢትዮጵያ መንግስት ኢሳያስን እና ዹጩር ጀኔራሎቹን በጩር
ወንጀለኝነት ሊኹሰው ዚሚቜልበት ዕድል አለ” ይላሉ።

በፋኑኀል ክንፉ
ዚኀርትራው ፕሬዝደነት ኢሳያስ አፈ ወርቂ ያቀሚቡት ዹሰላም ድርድር ጥያቄ ተኚትሎ ዚኢትዮጵያ መንግስት ያለቅድመ ሁኔታ እደራደራለሁ ማለቱ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡
በተለይ ኚኢትዮ-ኀርትራ ጊርነት ጋር በተያያዘ በሃይደር ት/ቀት ላይ ዹተፈፀመው ዚቊንብ ድብደባ እና በምርኮ በተያዙት በኮሎኔል በዛብህ ጎጥሮስ ላይ ዹተፈፀመው áˆ°á‰¥á‹“ዊነት ዹጎደለው አያያዝ በጀኔቫ ዹጩር ወንጀል ስምምነት መሠሚት ኢሳያስ አፈወርቂና ዹጩር ጀኔራሎቻ቞ው በጩር ወንጀለኝነት ዚሚያስጠይቅ መሆኑ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹«á‹Šá‹«áŠ• ባለሙያዎቜ እዚጠዚቁ ነው፡፡
በዓለም አቀፉ ሕግ ኹፍተኛ ባለሙያና ተመራማሪ ዚሆኑት ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለጜት፤ “ዹጩር ወንጀለኝነትን በተመለኹተ በጄኔቫ áŠ®áŠ•á‰¬áŠ•áˆœáŠ• ዚሠፈሩ ሁለት ፕሮቶኮሎቜ አሉ፡፡ በእነዚህ ፕሮቶኮሎቜ ትንታኔ ውስጥ ዹጩር ወንጀል፣ ዚሚያስኚትለው ክስ በፍትሐብሄርና በወንጀል ዚሚያስጠይቅ áˆ˜áˆ†áŠ‘፣ ኚጊርነት ቀጠና ውጪ ስለሆኑ ሰዎቜ እንዲሁም ዹጩር ምርኮኞቜን በተመለኹተ በዝርዝር ሰፍሯል፡፡ ኚፕሮቶኮሎቹ ስንነሳ በሃይደር ት/ቀት በአስመራ áˆ˜áŠ•áŒáˆµá‰µ ዹተፈፀመው ዚቊምብ ድብደባ በግልፅ ኚጊርነት ቀጠና ውጪ ዹተፈፀመ ዹጩር ወንጀል መሆኑ ግልፅ ሆኖ እናገኛዋለን፡፡”
አያይዘውም “ዹኰሎኔል በዛብህ ጎጥሮስ ዹጩር ምርኮኛ ሆነው ኚተያዙ በኋላ ዚተፈፀመባ቞ው ሰብአዊነት ዹጐደለው አያያዝ ዚጄኔቫ ዹጩር ምርኮኞቜ ፕሮቶኮል áˆ˜áˆ áˆšá‰µ በጩር ወንጀል ዚሚያስኚስስ ነው፡፡ ፕሮቶኮሎቹ ወንጀልና ካሳን ለይተው ነው ዚሚያስቀምጡት፡፡ ካሳን በተመለኹተ ዚአልጀርሱ ዚድንበር ኮሚሜን ስምምነት áŠ¥áŠ“ ዹሄግ ፍርድ ቀት ውሣኔ ሰጥተውበታል፡፡ ለኢትዮጵያ 110 ሚሊዮን ዶላር ሲቆሚጥላት፣ ኀርትራ 100 ሚሊዮን ዶላር ተወስኖላታል፡፡ ኹዚህ ውስጥ ለሃይደር
ት/ቀት ተብሎ ዹተሰጠ ዚካሳ ክፍያ አለ፡፡ ይህ ግን በፍትሐብሔር ዹተፈፀመ ዚካሳ ክፍያ እንጂ በተማሪዎቹ ላይ ስለተፈፀመው ዹጩር ወንጀል ዹተሰጠ ብይን áŠ á‹­á‹°áˆˆáˆ፡፡ ዚፍርድ ውሣኔ ግን በፍትሐብሔር ላይ ዹተመሠሹተ በመሆኑ ሃይደር ት/ቀትን በተመለኹተ ዹተኹፈለ ዚገንዘብ ክፍያ መኖሩን ዚፍርድ ውሣኔ ሰነድ á‰¢á‹«áˆ³á‹­áˆ፤ ዹወንጀል ድርጊቱን በተመለኹተ ያለው አንዳቜ ነገር ዹለም፡፡ ኹዚህም በተጚማሪ ወንጀል በቅጣት እንጂ በካሳ አይታለፍም፡፡ በእስር ያስቀጣል፡፡ áˆµáˆˆá‹šáˆ…ም ኢሳያስና ዚእሱ ዹጩር ጀነራሎቜ ዚፈጞሙት ዹጩር ወንጀል በመኖሩ ሊጠዹቁ ይገባል” ብለዋል፡፡ “ኢትዮጵያ ዹዓለም አቀፉ ዹወንጀል ፍርድ ቀት አባል ሀገር አይደለቜም፡፡ ይህን መሰል ክስ ዚት ልትመሰርት ትቜላለቜ ተብሎ ለቀሹበላቾው ጥያቄ በሰጡት ምላሜ፤
“ኢትዮጵያ ዹዓለም አቀፉ ዹወንጀል ፍርድ ቀት አባል ባትሆንም ዹተፈፀመውን ዹጩር ወንጀል ዚሚያሳይ መሹጃ ለፀጥታው ም/ቀት በማቅሚብ በኢሳያስ ላይ ዹጩር á‹ˆáŠ•áŒ€áˆ ክስ ምርመራ ማዘዣ ማስወጣት ትቜላለቜ፡፡ ምክንያቱም ዚፀጥታው ም/ቀት ዹዓለም አቀፉ ዹወንጀል ፍርድ ቀትን ዹማዘዝ ስልጣን አለው፡፡ ቁም ነገሩ ግን፤ á‹­áˆ…ን ዹጩር ወንጀል ድርጊት በባለቀትነት ዚያዘውም ዹጠዹቀውም በኢትዮጵያ በኩል አለመኖሩ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን አሁንም በጩር ወንጀል ኢሳያስን ለመክሰስ á‹šáˆšá‰»áˆá‰ á‰µ እድል ተዘግቷል ማለት አይደለም፡፡ አሁንም ኢሳያስ አፈወርቂ በጩር ወንጀል ሊጠዹቁ ይገባል” ሲሉ አፅንኊት ሰጥተው ተናግራዋል፡፡”
ዚፖለቲካ ኢኮኖሚ ባለሙያ ዚሆኑት ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በርሄ በበኩላ቞ው፤ “ዚኢትዮጵያ መንግስት ኢሳያስን እና ዹጩር ጀኔራሎቹን በጩር ወንጀለኝነት ሊኹሰው á‹šáˆšá‰œáˆá‰ á‰µ ዕድል አለ፡፡ ኹዓለም አቀፉ ሹጅም ቢሮክራሲ አንፃር ምን ያህል ያስኬዳል ዹሚለው እንደተጠበቀ ሆኖ፤ አሁን ያለው ነገር በአልጀርሱ ስምምነት መሠሚት  á‹ˆá‹° ሁሉን አቀፍ ዹሠላም ድርድር ውስጥ ለመግባት ዚታሰበው መስለኝ፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ዚምትቀበለውም ዚምትሰጠውም ነገር ይኖራል፡፡ ቜግሩ ሁለቱም ሀገሮቜ
ዚአልጀርሱን ስምምነት አለመቀበላቾው ነው፡፡ ቁምነገሩ ድርድሩ ቢጀመር በምንድነው ዹሚጀመሹው? ዚድንበር ኮሚሜኑ ውሣኔ ትክክል ነው? ዚኢትዮጵያ መንግስት á‰£á‹µáˆ˜áŠ• ለኀርትራ አሳልፎ ቢሰጥ በቀጣይ ምን ዓይነት ዚፖለቲካ ሁኔታ ሊገጥመው ይቜላል? ኹ70 ሺ በላይ ዹሰው ህይወት ዹቀጠፈው ጊርነት ለምን ተጀመሹ?  áˆˆáˆšáˆ‰á‰µ ጥያቄዎቜ በቂ ምላሜ ሊሰጥባ቞ው” ይገባል ብለዋል፡፡
ዶክተሩ አያይዘውም ፤ “ዚጊርነቱ መጀመር ዚባድመ ጉዳይ አይደለም፡፡ ናቅፋ ዚኀርትራ ገንዘብ ሆኖ መቅሚቡ ነበር፡፡ በኀርትራ ውስጥ ሶስት ቢሊዮን ብር ዹሚጠጋ áŒˆáŠ•á‹˜á‰¥ ነበር፡፡ ይህን ገንዘብ ዚኀርትራ መንግስት ኚኢትዮጵያ መንግስት በዶላር እንዲኚፈል ጥያቄ ቢያቀርብም ውድቅ ተደሚገበት፡፡ ሌላው፤ ዚኢትዮጵያ መንግስትም áŠ€áˆ­á‰µáˆ«áŠ• ለማቋቋም ዹሰጠው ሶስት ቢሊዮን ብር እና ለኀርትራ ንግድ ባንክ ማቋቋሚያ ተብሎ 2 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በብድር ሰጥቶ ዚነበሚበት ሁኔታ ነበር á‹šáŠá‰ áˆšá‹፡፡ በወቅቱ ኀርትራ ትጠቀምበት ዹበሹውን ዚኢትዮጵያን ብር ወደ ናቅፋ ስትቀይሚው፤ ዚኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ ነባሩን ብር በአዲስ ብር ተክቶ ስራ ላይ áŠ á‹‹áˆˆ፡፡ ስለዚህም ኀርትራ ውሰጥ ዹነበሹው ዚኢትዮጵያ ብር ኚአገልግሎት ውጩ ሆነ፡፡ ይህ በመሆኑ ዚኀርትራ መንግስት ንዎት ውስጥ ወደቀ፡፡ ዚነበራ቞ው ግምት  á‰ áŠá‰ áˆšá‹ ግንኙነት በመጠቀም ወይም በጉልበት ፍላጐታ቞ውን ማሳካት ዚሚቻል መስሏ቞ው ነበር፡፡ ዹሆነው ግን ኚጠበቁት ውጪ ነው፡፡ ጠብ ዹተጀመሹው ኹዚህ áŠá‰ áˆ­ ማለት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም ዚኢትዮጵያ መንግስት ኀርትራን ዚሚያክል መሬት ኹሰጠ በኋላ 20 ኪሎ ሜትር ለማይሞላ በባድመ መሬት ጊርነት ውስጥ ሊገባ
አይቜልም፡፡ አሁንም ሊደሹግ ዚታሰበው ድርድር ባድመን ማዕኹል ያደሚገ ነው ተብሎ መውሰድም ኚባድ ነው ዹሚሆነው፡፡ ኀርትራዊያን ባድመን ቢወሰዱትም á‹šá‰»á‹­áŠ“ ግንብ አይሰሩበትም፡፡ ባድሜ ያለውም ሕዝብ ኀርትራዊ ነኝ ብሎ ዚሚያምን ቢሆን ኖሮ፤ እስካሁን ዚድንበር ውዝግቡ መቋጫ ያገኝ ነበር፡፡ መሬቱን ኀርትራ á‰µáŒ á‹­á‰ƒáˆˆá‰œ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ነኝ ይላል፡፡ እዚህ ላይ ነው ጚዋታው ያለው፡፡›› ብለዋል፡፡ á‹šáŠ€áˆ­á‰µáˆ« መንግስት ኚኢትዮጵያ ጋር ያለውን ቁርሟ በእርቅ ለመጚሚስ በደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫኪር በኩል በይፋ ጥያቄ ማቅሚቡን ተኚትሎ ዚኢትዮጵያ
መንግስት አዎንታዊ ምላሜ መስጠቱ ዚተለያዩ ምንጮቜ መዘገባ቞ው ይታወሳል፡፡
ምንጭ፡ ሰንደቅ ጋዜጣ

ኢህአዎግ ዹአ.አ. መራጮቜን A, B, C በሚል መክፈሉ አንድነት ፓርቲን አስቆጣ


በዘሪሁን ሙሉጌታ

በመጪው ሚያዚያ ወር ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደርን ጚምሮ በመላው ሀገሪቱ ዚአካባቢ ምርጫ መካሄዱን ተኚትሎ ኢህአዎግ ዚአዲስ አበባ መራጮቜን በሊስት
መክፈሉ ዚአንድነት ፓርቲን አስቆጣ።
ኢህአዎግ በበኩሉ ኹ2002ቱ ዹተለዹ አዲስ ዚምርጫ ስትራ቎ጂ ግብ እንደሌለው አስታውቋል። ምርጫው በሕዝቡ ዘንድ ተአማኒነቱን ጠብቆ እንዲሄድ አባላቱን
በተለያዚ መንገድ እያነቃነቀ መሆኑን ግን አልካደም።
ቀደም ሲል ለ2002ቱ ምርጫ ኢህአዎግ ዚገነባው ዚምርጫ ሰራዊት (አንድ ለአምስት) አደሚጃጀት እንዳለ ቢሆንም ግንባሩ በተለይ ዚአዲስ አበባ መራጮቜ በሊስት
ደሹጃ በመክፈል ለአባላቱ አዲስ ቅፅ አሳትሞ ማሰራጚቱ ታውቋል። በዹቀበሌው ዹተበተነው ቅፅ መራጮቹን ‘‘ኀ’’፣ ‘‘ቢ’’ እና ‘‘ሲ’’ በሚል በመክፈል ዚምርጫ
ቅስቀሳው በዚሁ ቅደም ተኹተል ዹሚፈፀም መሆኑን ዚሚያመለክት ነው።
‘‘ቅፁ በእጃቜን ገብቷል’’ ያሉት ዚአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዋና ፀሐፊ አቶ አስራት ጣሎ በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ቅፁ ዚኢህአዎግ አርማ
ያለበት ሆኖ ዹቀበሌውን ስም፣ መዝጋቢውን፣ ዚመራጩን ስምና ዚሚኖርበትን ቀበሌ፣ ዚቀት ቁጥር ዚተመዘገበበት ቀን ዚመሳሰሉትን መጠይቆቜ ዚያዘ መሆኑን
ገልፀዋል። ቅፁን በመያዝ ዚኢህአዎግ አባላት ሕዝቡን መመዝገብ መጀመራ቞ውን ገልፀዋል።
በቅርቡ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕሹግ ዚማኀበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ሆነው ዚተመሚጡት አቶ ሙክታር ኚድር በስራ቞ው ዹሚገኙ 22 ዚመንግስት ሚኒስ቎ር
መስሪያ ቀቶቜንና ኀጀንሲዎቜ ላይ ግምገማ ካካሄዱ በኋላ ዚመንግስት መስሪያ ቀት ሰራተኞቜ አንድ ለአምስት መደራጀት እንዳለባ቞ውና አደሚጃጀቱም በሊስት
ዘርፎቜ እንደሚሆን መግለፃቾው፣ እነዚህም ሶስት ዘርፎቜ ዚኢህአዎግ ዘርፍ፣ ዚመንግስት ዘርፍ እንዲሁም ሶስተኛው አንድ ለአምስት ኚሚያደራጀው መስሪያቀት
ወይም ኚኀጀንሲው ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያለው ዚህብሚተሰብ ክፍል እንዲሆን መወሰኑ አቶ አስራት አስታውሰዋል።
ለምሳሌ ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ሰራተኞቜ በአንድ ለአምስት አደሚጃጀት በኢህአዎግ ዘርፍ፣ በመንግስት ሰራተኛ ዘርፍ ኚተደራጁ በኋላ ኚትምህርት ሚኒስ቎ር ጋር
ቀጥታ ግንኙነት ያላ቞ው ተማሪዎቜና ወላጆቜ መሆናቾው በመጥቀስ ኢህአዎግ ዚአደሚጃጀት አካሄድ ሀገሪቱን ዚአንድ ፓርቲ ስርዓት ኚማድሚግ ባለፈ በመንግስትና
በኢህአዎግ መዋቅር መካኚል ያለው ልዩነት ተደምስሷል ሲሉ ቅሬታ቞ውን ገልፀዋል።
ኢህአዎግ በሚያዚያ ወር በሚካሄደውም ምርጫ መሰሚት በማድሚግ መራጮቜን በሶስት መክፈሉ ምርጫውን ይበልጥ ያወሳስበዋል ያሉት አቶ አስራት ‘‘ኀ’’፣ ‘‘ቢ’’
እና ‘‘ሲ’’ ዹሚለው መዋቅራዊ አካሄድም ዚመራጩን ስነ-ልቩና ዚሚነካ እንደሆነም ነው ዚገለፁት።
በስትራ቎ጂው መሰሚት በ‘‘ኀ’’ ስር ዚሚመደቡ መራጮቜ በአስተማማኝ ኢህአዎግን ዚሚመርጡ በመሆኑ ኚእነዚህ መራጮቜ ላይ ብዙ መስራት አያስፈልግም፣
በ‘‘ቢ’’ ስር ዹተፈሹጁ ደግሞ በኢህአዎግ እና በተቃዋሚ መካኚል ዹሚዋልሉና መጠነኛ ቅስቀሳ ዚሚካሄድባ቞ው ሲሆን በ‘‘ሲ’’ ስር ዹተፈሹጁ መራጮቜ ደግሞ ሙሉ
በሙሉ ተቃዋሚ ዚሚመርጡ በመሆኑ ዹበለጠ መስራት ዹሚል እንደሆነ ተጠቁሟል።
ዚኢህአዎግ ዚውጪ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተመስገን ጥላሁን ስለ ጉዳዩ ተጠይቀው ግንባሩ ለአዲሰ አበባ አስተዳደር እና በመላው ሀገሪቱ ለሚካሄደው ዚአካባቢው
ምርጫ ዹተለዹ ዚምርጫ ስትራ቎ጂ እንደሌለው ተናግሹዋል። ምርጫው በሕዝቡ ዘንድ ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና በሕዝቡ ዘንድ ተአማኒ እንዲሆን ግንባሩ እዚሰራ
እንደሆነም አሹጋግጠዋል። ግንባሩ በምርጫው ስኬታማ ለማድሚግ ነባር መዋቅሩን መሰሚት በማድሚግ አባላቱን እያነቃነቀ መሆኑን በመግለፅ ስብሰባ እዚመሩ
በመሆኑ በቀጣይ ጊዜ ወስደው በጉዳዩ ላይ ተጚማሪ ማብራሪያ እንደሚሰጡበት ገልፀዋል።

ምንጭ፡ ሰንደቅ ጋዜጣ

Total Pageviews

Translate