Pages

Dec 28, 2012

ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብሚ ጜዮን ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያን ኹዘሹኛው ዚወያኔ አገዛዝ ተጜዕኖ ዚጞዳቜ፤ በUK ለሚገኘው ስደተኛ ዚእምነቱ ማዕኹልና ኢትዮጵያው ጭምር ናት!! አደጋ ላይ ነቜ፤ አድኑኝ ትላለቜ


ዚዘመናት ታሪክ ባለቀትና ኚትውልድ ወደ
ትውልድ
በመተላለፍ፤ ወደፊትም ለዘለዓለም ዚምትኖር
ዚኢትዮጵያ
ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን እውነተኛ
ዚክርስቶስ
ማደሪያ ዚምትባለው ዛሬ ኖሮ ነገ ለማይኖሹው
አምባ ገነንና
ዘሹኛ አገዛዝ መሣሪያ ሳትሆን ኹተበደለውና
መብትና
ነጻነቱን ኹተገፈፈው ዚኢዮጵያ ሕዝብ ጎን መቆም
ዚቻለቜ
እንደሁ ብቻ ነው።ደን ደብሚ ጜዮን ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያን አደጋ ላይ ነቜ፤ አድኑኝ ትላለቜ -(Erope-Churchደን ደብሚ ጜዮን ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያን አደጋ ላይ ነቜ፤ አድኑኝ ትላለቜ

ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብሚ ጜዮን ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያን ኹዘሹኛው ዚወያኔ አገዛዝ ተጜዕኖ 
ዚጞዳቜ፤ በUK ለሚገኘው ስደተኛ ዚእምነቱ ማዕኹልና ኢትዮጵያው ጭምር ናት!! 
አደጋ ላይ ነቜ፤ አድኑኝ ትላለቜ
ዚዘመናት ታሪክ ባለቀትና ኚትውልድ ወደ ትውልድ
በመተላለፍ፤ ወደፊትም ለዘለዓለም ዚምትኖር ዚኢትዮጵያ
ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን እውነተኛ ዚክርስቶስ
ማደሪያ ዚምትባለው ዛሬ ኖሮ ነገ ለማይኖሹው አምባ ገነንና
ዘሹኛ አገዛዝ መሣሪያ ሳትሆን ኹተበደለውና መብትና
ነጻነቱን ኹተገፈፈው ዚኢዮጵያ ሕዝብ ጎን መቆም ዚቻለቜ
እንደሁ ብቻ ነው።
ላለፉት 21  á‹“መታት ይህንን እውነተኛ ክርስቲያናዊ ሥራ
ተግባራዊ በማድሚግ ኚወያኔ ተጜዕኖ ነጻ በመሆን በዓለም
ሁሉ ተዘርቶ ለሚገኘው ኢትዮጵያዊ መኩሪያና መመኪያ
ተበለው ኚሚጠቀሱት ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ
ክርስቲያን ውስጥ ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብሚ ጜዮን
ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያን አንዷ ነቜ።
ኢትዮጵያ ውስጥ ዚተንሰራፋው ዘሹኛው ዚወያኔ አገዛዝ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ዹበላይ፤ ሕግ
አውጪና ወሳኝ ዹሆነው ዚቅዱስ ሲኖዶስን መንፈሳዊ ዓላማና ውሳኔ በሥራ ላይ እንዳይውል፤ እውነት ዚሚናገሩ አባቶቜን
በማስፈራራት፤ በማስደብደብ፤ በጠመንጃና በደህንነት ኃይል በማስገደድ በሃገሪቱ ዚመንግሥት መዋቅር ውስጥ እንደሚፈጞመው
ሁሉ በቀተ ክህነትም ሆነ በዚአብያተ ክርስቲያኑ ወሳኝ በተባሉ ቊታዎቜ ሁሉ ዹአገዛዙን ዚጎሳ አባላትና ደጋፊዎቜ በመሰግሰግ ቀተ
ክርስቲያንም ዹዘሹኛ አገዛዝን ሥርዓትን ተኚትላ እንድትዋቀር አድርጓት እንደሚገኝ ይፋ ኹሆነ ወራትና አመታት ተቆጥሚዋል።
ዹዘሹኛው ቁንጮ ዚሆኑት መለስ ዜናዊና አባ ጳውሎስን ሞት ቢወስዳ቞ውም ዘሹኛው ሥርዓት በቅድስት ቀተ ክርስቲያን ላይ
ዚሚያደርገው ተጜዕኖና መኹፋፈል በኹፋ ሁኔታ ቀጥለ እንጂ ሲሻሻል አልታዚም።
ለንደን ደብሚ ጜዮን ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያን ላለፉት 21 ዓመታት በአባ ጳውሎስ አማካኝነት ዚተቃጣባትን ዚወያኔን አገዛዝ
ጣልቃ ገብነት በሙሉ በመመኚትና በመኹላኹል በዘሹኛው አገዛዝ አቀነባባሪነት በጅማ፤ በአሩሲ፤ በአሰቊትና በሌሎቜም ቊታዎቜ
በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያንና በተኚታዮቿ ላይ ጥቃት ሲደርስ ማንንም ሳትፈራ በነፃነት ድርጊቱን አጋልጣለቜ፤
ተቃውሞዋን ለዓለም አሰምታለቜ፤ አቅም በፈቀደም ለተጎዱት ክርስቲያኖቜ ድጋፍ አድርጋለቜ።
በቅርቡም ዚዋልድባ ገዳም በአገዛዙ ሲደፈርና ሲጠቃ፤ መነኮሳት ሲታሰሩና ሲሰቃዩ ሌሎቜ እንግሊዝ ሃገር ያሉ በወያኔ አገዛዝ ጫና
ሥር ያሉ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያናት ፀጥ እሚጭ ሲሉ ቀተ ክርስቲያናቜን ግን በድፍሚትና በነፃነት ታላቅ
ሰላማዊ ሰልፍ በማካሄድ አገዛዙ በእምነት ውስጥ ጣልቃ በመግባት ዚሚፈጜመውን በደል አጋልጣለቜ ተቃውሞዋንም ለዓለም
አሰምታለቜ።
ይህ ዚቅርቡ ትዝታ ሲሆን እንደ አውሮጳ አቆጣጠር በ2005 ዘሹኛው ዚወያኔ አገዛዝ ወንድ ሎት ሳይለይ ህጻን ወጣት፤ ጎልማሳና
አዛውንት ሳይቀር በአሰቃቂ ሁኔታ በጚፈጚፈበት ወቅት ቀተ ክርስቲያናቜን ኹፍተኛ ተቃውሞ ኚማሰማት ባሻገር በአገዛዙ
ዚተገደሉት ኢትዮጵያኖቜ እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ውሻ ተቆጥሚው ፍትሐትም ሆነ ጞሎት አይደሹግላቾው ተብሎ በአባ ጳውሎስ
አማካኝነት ሲታገድ ለንደን ደብሚ ጜዮን ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያን ግን በግፍ ለተገደሉት ኢትዮጵያኖቜ መሉ ጞሎት
አድርጋለቜ።
ኹዚህም በማስኚተል ብጹ ወቅዱስ በማለት ዚአባ ጳውሎስ ሥም በቀተ ክርሲያኗ ውስጥ አይጠራም በማለት ቀተ ክርስቲያኗ
ዚወሰደቜውን ዚጠራ ዹአቋም ባሉት ሚዲያዎቜ ተጠቅማ ለዓለም ሁሉ አሳውቃለቜ። ይህንን ተኚትሎ በቀተ ክርስቲያኗ ውስጥ
ዚነበሩ ዹዘሹኛው ወያኔ አገዛዝ ደጋፊዎቜ ቀተ ክርስቲያኗ ውስጥ ለሞቱት መጞለዩንና በአባ ጳውሎስ ላይ ዹተወሰደውን አቋም
በመቃወም ኚቀተ ክርስቲያኗ ተለይተው ስላሎ ቀተ ክርስቲያንን ሊያቋቁሙ ቜለዋል።
ዹተፈጠሹው ዹአቋም ልዩነት እንጂ ዚሃይማኖት ልዩነት ባለመሆኑም በአንድ ሃይማኖት ጥላ ሥር ሆኖ በአቋም ልዩነት ሕዝብ ኚህዝብ
ኹሚቃቃርና ኹሚናቆር ተለያይቶ ማምለኩ መፍትሔ ሰጪ ሊሆን ቜሏል።

በእርግጥ ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብሚ ጜዮን ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያን እ.አ.አቆጣጠር በ1993 ዹዘሹኛ ሥርዓት አራማጅ
ተወካይ ዚሆኑት አባ ጳውሎስ ዚቀተ ክርስቲያኗ አባላት ሳይጋብዟ቞ው መጥተው በማሳፈርና በማዋሚድ መልሳ አባራ቞ዋለቜ ያም
ሆኖ ግን ዚአባ ጳውሎስን ስም ብጹዕ ወቅዱስ ብላ ትጠራ ስለነበር መልሰን በእጃቜን እናገባታለን በሚል ተስፋ ዚተለያዩ ዚተንኮል
ሙኚራዎቜ ይደሚግባት ነበር እንጂ በለዚለት ጠላትነት ተፈርጃ ዹኹፋ ጥቃት ሳይሰነዘርባት ቆይታ ነበር።
እ.አ.  áŠ á‰†áŒ£áŒ áˆ­ ኹ2005  á‰ áŠ‹áˆ‹ ግን ቀተ ክርስቲያኗ በመንበሹ ፓትርያርኩኗ በአባ ጳውሎስ በለዚለት ጠላትነት ተፈርጃ በርካታ
ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቃት ዚደሚሰባት ሲሆነ ኹዚህም ውስጥ ዹማይዘነጋው ቀተ ክርስቲያኗ ዚምትገለገልበትን ህንፃ ቀተ ክርስቲያን
ለመግዛት ሕዝበ ክርስቲያኑ ገንዘብና ጉልበትን በማስተባበር ደፋ ቀና ሲል በአባ ጳውሎስ ዹተፈሹመና ኹመንበሹ ፓትሪያርክ
ለእንግሊዝ ቀተ ክርስቲያን በተጻፈ ደብዳቀ ቀተ ክርስቲያኑ በእንግሊዝ ሃገር በስደት ላይ ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን
እንዳይሞጥላ቞ው ዚወጣው ማገጃ ነው።
ይህንን ማገጃ ግን በስደት ላይ ያለው ሕዝበ ክርስቲያን እንዲሻር በማድሚግ ዚቀተ ክርስቲያኑንና በግቢው ውስጥ ዹሚገኘውን
ዚቪካሬጅ ህንፃ በ£1.700.000 (አንድ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሺህ ፓውንድ) በመግዛት ዚስደተኛው ኢትዮጵያዊ ዘላለማዊ ሃብትና
ቅርስ እንዲሆን አድርጎታል።
ይህንን ሕዝብ ጥሮና ግሮ ያፈራውን ቅርስ ነው ዛሬ አባ ግርማ ኹበደና (በግራ)
መሪጌታ ዓለማዹሁ ደስታ (በቀኝ) በተባሉ ካህናት አስተባባሪነት ቀተ
ክርስቲያኗም ሆነቜ ሃብትና ንብሚቷ ዚቅዱስ ሲኖዶስና ዹመንበሹ ፓትርያርክ ነው
በማለት በቅዱስ ሲኖዶስ ስም ለዘሹኛው ዚወያኔ አገዛዝ ሥርዓት አራማጆቜ
በኀምባሲ አማካኝነት ለማስሚኚብ ኹፍተኛ ትግል በማድሚግ ላይ ዚሚገኙት።
ይህንን ዚክህደት ተግባራ቞ውን ዚቀተ ክርስቲያኗ አባላት እንዳማይደግፉት ሲሚዱ
ዚወያኔ ሥርዓት ደጋፊ ዹሆኑ ሰዎቜን በተለያዚ ዘዮ ወደ ቀተ ክርስቲያኗ በመጥራት
ዚቀተ ክርስቲያኗ አባላት በብዛት እንዲዋጡና እዚተስፈራሩ ኚቀተ ክርስቲያን እንዲባሚሩ በማስደሚግ ላይ ይገኛሉ።
ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ሰብዓዊ መብቱ በወያኔ ተሹገጠ፤ ፍትሕ በኢትዮጵያ ጠፋ፤ ዘሚኝነትና ዚአንድ ጎሳ ዚበላይነት በኢትዮጵያ ነገሰ፤
ዹሃገር ሃብትና ንብሚት በዘሚኞቜ እጅ ወደቀ እያልክ ዚምትቆሚቆርና ድምጜ ለሌለው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጜ ዹሆንክ ሁሉ ዘሹኛው
ወያኔ ኚኢትዮጵያም አልፎ በጥቂት ካህናትና ደጋፊዎቻ቞ው አስተባባሪነት እዚህ እንግሊዝ ሃገር ዹሚገኘውን ዚስደተኛው
ኢትዮጵያዊ ንብሚትና ቅርስ  áˆŠá‹ˆáˆ­áˆµ እዚጣሚ ነውና አንዳቜም ማመንታት ሳታደርግ ወደ ቀተ ክርስቲያን በመምጣት በተለመደውና
በምትታወቅበት ወኔ ወያኔን አዋርደህ እንድታባርር ቅድስት ማርያም ጠርታሃለቜና አታሳፍራት!!
ላለፉት 21 ዓመታት ኹዘሹኛው ዚወያኔ አገዛዝ ተጜዕኖ ነፃ አድርገህ በነፃነት እንዳኖርካት ዛሬም ቀተ ክርስቲያንህ በጥቂት ዹግል
ጥቅም አሳዳጅ ካህናት አማካኝነት በወያኔ ደጋፊዎቜ እጅ እንዳትወድቅ መጥተህ ታገልላት።
ዚፊታቜን አሑድ 30/12/12  áŠ­á‰€áŠ‘ ሰምንት ሰአት፤ በቀተ ክርስቲያናቜን ውስጥ ዓዲስ አመራር ኮሚቲ ለመምሚጥ ስብስባ 
ጠርተዋል። ስሞኑን ብዙ ዹማናውቃቾው ስወቜ ወደ ቀተ ክርስቲያናቜን መምጣት ጀምሹዋል። ይህም ‘አባላትን”  áˆ•ጋዊ ባልሆነ 
መንገድ በማብዛት፤ ቀተ ክርስቲያናቜንን፤ ንብርተዋንና አስትዳደርዋን፤ አሳልፎ፤ ለወያኔ፤ ለመስጠት ነው። ስለዚህ፤ በእለቱ 
ተገኝታቜሁ፤ ቀተ ክርስቲያናቜሁን አድኑ። ወደፊትም በቀተ ክርስቲያናቜን ውስጥም ሆነ ኚቀተ ክርስቲያናቜን ውጭ በሚደሹጉ 
ስብሰባዎቜ ላይ ተገኝታቜሁ፤ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብሚ ጜዮን ቅድስት ማርያምን አድኑ!!!
ኃይልም ድልም ዚእግዚአብሔር ነው!!ent/uploads/2012/12/Church-Under-Attack1.pdf

ይቅርታ ዹደወሉላቾውን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይቜሉም” ቎ሌኮም ቀመስ ልቊለድ!


ይቅርታ ዹደወሉላቾውን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይቜሉም” ቎ሌኮም ቀመስ ልቊለድ!

ናፍቃው ናፍቃው አሁንም ናፍቃው ደወለቜለት።
ነግሯታል። በእርሱ ውስጥ ዚተሟመቜ ባለስልጣን እርሷ ነቜ። ና ስትለው ይመጣል ሂድ ስትለው ይሄዳል። ግባ ስትለው ይገባል ውጣ ስትለው ይወጣል።
ለዚህም ነው ዚወደደቜው ታዛዥነቱን ትህትናውን “ጠብ እርግፍ” ማለቱን አይታ ነው  በፍቅሩ “ጠብ እርግፍ” ያለቜው።
ናፍቃው ናፍቃው አሁንም ናፍቃው ደወለቜለት።
“ይቅርታ ዹደወሉላቾውን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይሉም!”  በተስሚቅራቂ ድምፅ ኚወዲያኛው መስመር ዚሆነቜ ሎትዮ መለሰቜላት። ቅናት አይሉት አንዳቜ ሰይጣናዊ ስሜት ሲሰማት ታወቃት። ሰውነቷ በበስጭት ጋለ። ኹዛም ምን ነካኝ… ብላ በሀፍሚት ሳቅ ብላ…
ደግማ ደወለቜ…
቎ሌዎቜ በዚስኩ ላይ ያስቀመጧት ሎትዬ ዹሰዉን አባወራ ሁሉ “ይቅርታ ዹደወሉላቾውን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይቜሉም” ስትል “ኹኔጋ ዚሚቆይበት ጉዳይ አለው” ዚምትል ትመስላለቜ፤ እንጂ ምክንያቱን አትገልፅም። አነጋገሯ ደግሞ ኚሌሎቹ ዹተለዹ ቅላፄ አለው። “ያልዎት ቀሪ ሂሳብ አነስተኛ ነው…” ኚምትለው እና ቀልቀል ባለ ድምፅ “The network is busy now” ኚምትለው ሎትዬ ዚተለዚቜ ናት። ማሜን ላዹ ዚተገጠመቜ ሳይሆን ኹሰዉ ወዳጅ ጋር አጓጉል ዚገጠመቜ ነው ዚምትመስለው።
ዹገዛ ፍቅሹኛዋን ያለ በቂ ምክንያት “አሁን ማግኘት አይቜሉም” መባሏ እያብኚነኚናት ደግማ ደወለቜ…
ኹዛኛው መስመር ቆጣ ያለ ዚሎት ድምፅ ሰማቜ፤
“ሁለተኛ በዚህ ስልክ ባትደውይ ደስ ይለኛል ነገርኩሜ አይደል እንዎ!”
ተሳስታ ዚደወለቜ መስሏት ስልኳን አዚት አደሚገቜው። በፍፁም አልተሳሳተቜም። ዚእርሱን ስልክ መሳሳት ስሙን ዚመሳሳት ያክል ኚባድ ነው።
ማናት ይቺ…?
እንደቅድሙ ማሜኗ በሆነቜ… ስትል እዚተመኘቜ… ቀሰስ ባለ ድምፅ “ሃ…ሎ” አለቜ፤ ቅስሟ ስብር ሲል ታወቃት። ቅስም ዚቱጋ ነበር…? እንጃ ብቻ ኚወገብ ስብራት ዹበለጠ ያማል። ታመመቜ…
በተሰበሹ ቅስም እና በተሰበሹ ድምፅ ድጋሚ “ሃ…ሎ” አለቜ። ዚእርሱን ድምፅ ሰማቾው። ግን አልገባትም… “በቃ እንደነገሚቜሜ አድርጊ ዹኔ እመቀት”
ራሷ ሊፈነዳ ነው።
————————————————————————————-
“በቃ እንደነገሚቜሜ አድርጊ ዹኔ እመቀት” አለና፤
ተጣድፎ ስልኩን ዘጋው። አንዳንድ ደንበኞቜ ይገርሙታል  ኚሰራተኞቜ ዚተሰጣ቞ውን መሹጃ ድጋሚ ኚእርሱ ካልሰሙ ደስ አይላቾውም። እርሱም “እነርሱ እንደነገሯቜሁ አድርጉ” ብሎ ይሾኛል።
ስልኩን ገና ሳይዘጋው ሌላ ጥሪ መጣ… ውዱ ናት። ገብሚክርስቶስ ደስታ ኚገጠመላት በላይ ሚካኀል በላይነህ ካዜመላት ዹበለጠ ዚሚወዳት ውዱ…
“ዹኔ ናፍቆት…” ብሎ ሲጀምር፤ “ማንነቷን ብቻ ንገሹኝና እዘጋልሃለሁ።” ዹሚል ዹተሰበሹ ድምፅ ዚእንባ ሳግ እዚተናነቀው ኚጆሮው ደሹሰ።
አልገባውም…
“እሷ እንደነገሚቜኝ አደርጋለሁ… ግን ማናት…!?”
ዚት ነበርሜ…? ይሄ ቃል እርሷ ኹመደወሏ በፊት ዹተናገሹው ነው…! ዚት ሆና ሰማቜው… ደግሞስ ምን ክፋት አለው… ዚስራ ጉዳይ ነው… “እርሷ እንደነገሚቜሜ አድርጊ ዹኔ እመቀት…” እመቀት ማለቮ ይሆን ያስኚፋት…
እያሰበ እያለ ሃይሏን አሰባስባ አምባሚቀቜበት።
“ማናት?”
“ደንበኛቜን ናት…” አለ። ኹዛኛው ጫፍ ውዱ ኚምትገኝበት ጫፍ ስቅስቅታ… ተሰማው… አዎ አለቀሰቜ ሆዷ ባባ… ስልኩንም ዘጋቜበት።
———————————————————————-
ግራ ተጋብቶ በተቀመጠበት አንድ ወዳጁ ቢሮውን ላመል ያህል “ኳኳ..” አድርጎ ገባና… “ሰሞኑን ቮሌ ዚሰዎቜን ዹፍቅር ተቋማት ለማፈራሚስ ቆርጩ ተነስቷል” አለው።
“እንዎ….ት” አለ ሙትት ባለ ድምፅ፤
“ዚአንዱን ስልክ ለአንዱ እያጠላለፈ ዹሰዉን ፍቅር እያናጋው ነዋ” አለው።
ይሄኔ “ኚትክት ብሎ ሳቀ” ወዳጁ ዹነገሹው ነገር ይሄን ያህል ዚሚያስቅ መሆኑ አልገለጥልህ አለው። ጭራሜ ተነስቶ፤ “ተጠልፎ ነው ተጠልፎ ነው… ተጠልፎ ነው” እያለ እንደቀውስ ብቻውን እዚጮኞ በሩጫ ወደ “ውዱ” ሄደ አንገቷን ደፍታ አይኗ ቀልቶ አገኛት…
“ተጠልፎ ነው! ተጠልፎ ነው! ተጠልፎ ነውኮ…”

Dec 27, 2012

ለእርቅ ጉባኀ አሜሪክ ቆይተው ወደ ኢትዮጵያ ዚተመለሱት አባቶቜ በሜምግልና ኮሚ቎ ላይ ጠንኹር ያለ መግለጫ አወጡ


ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባና በውጭ ሀገር ዹሚገኙ አባታቶቜን በሶስት ዙር ሲያደራድር ዹቆዹውና ለአሹተኛ ዙር ቀጠሮ ይዞ ዚተነሳው ዚሜምግልና ቡድን ባለፈው አርብ ያወጣው መግለጫ እንዳስቆጣ቞ው ዚገለጹት አባቶቜ ይቅርታ ካልተጠዚቁ በተያዘው ዚእርቅ ንግግር እንደማይቀጥሉ አሹጋግጠዋል::
በቀተክርስትያኒቱ መካኚል እርቅ ለማውሚድና ሰላምን ለማውሚድ ሲንቀሳቀስ ዹቆዹው አስታራቂ ቡድን አዲስ ፓትሪያርክ ለመምሚጥ ኮሚ቎ መሰዹሙን በመቃወም ባለፈው አርብ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል::
ለእርቅ ንግግር ወደአሜሪካ ዚተጎዙት ልኡካን ባልተመለሱበትና  á‰€áŒ£á‹­ ንግግር ለማድሚግ ቀጠሮ በያዙበት ወቅት በአንዳንድ አባቶቜ ግፊት እ  እርምጃ ተገቢአይደለም ሲል ነበር ሞምጋዩ ቡድን መግለጫ ያወጣው::
እንደ ሜምግልና ቡድኑ ሁሉ ፓትርያርክ ለመምሚጥ አስመራጭ ኮሚ቎ መሰዹሙን በመቃወምና እንደማይቀበሉ በማሚጋገጥ ለአሜምጜ ሬዲዮ ዚአማሪኛው አገልግሎት መግለጫ ዚሰጡት አባቶቜ አዲስ አበባ ኚደሚሱ በሆላ ሞምጋዮቹን በመውቀስ ያወጡት መግለጫ አነጋጋሪ ሆኖል::
በሞምጋዩ ቡድን አርብ ታህሳስ 23/2005 መግለጫውን ሲያወጣ በአሜሪካ ዚነበሩትና ታህሳስ 15/2005 ወደ ኢትዮጵያ ዚተጎዙት አባቶቜ ኚአዲስ አበባ ያወጡትን መግለጫ አሜሪካ በነበሩበት ቀን ታህሳስ 13/2005 እንደሆነ መደሹጉ ግልጜ አልሆነም::
ዚልኡካን ቡድኑ አባላት ብጹእ ወቅዱስ አቡነ ገሪማ፡ ብጹእ አቡነ አትና ቲዎስ ፡ ብጹእ አቡነ ቀውስጊስ ፡ ንቡሚ እድ ኀሊያስ አብርሀ ባወጡት መግለጫ ሞምጋዩ ቡድን ቅዱስ ሲኖዶሱን ተዳፍሮል በማለት ወቅሶል:: በሜምግልናውም ሂደት ወገንተኝነት ይንጞባሚቅበት ነበር ሲሉ አክለዋል::
ዚሜምግልናው ኮሚ቎ ይህንን ስህተቱን አምኖ ይቅርታ ካልጠዚቀ ኚዛሬ ጀምሮ በዚህ ኮሚ቎ አማካኝነት በሚደሹግ ንግግር አንሳተፍም ብለዋል::
ለሰላም ያለን ፍላጎት ግን አይታጠፍም ሲሉም አጠቃልዋል::

ያለው አማራጭ ሕገ-መንግስቱን ማሻሻል ብቻ ነው ሲሉ አንጋፋው ዚሕውሀት ታጋይ አቶ ስብሐት ነጋ ገለጹ


ኢሳት ዜና:-አቶ ስብሐት ነጋ በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ኹተማ ለንባብ ለበቃው ሰንደቅ ጋዜጣ በሰጡት ቃለ ምልልስ ዚመለስ ራዕይ ዚሚባለው ነገር ትክክል እንደማይመስላ቞ውና ያለው ዚጋራ ራዕይ መሆኑን ገልጠዋል::
ሊስት ምክትል ጠ/ሚኒስትር መሟም ያስፈለገው ክፍት ዚአመራር ቊታ ስለነበር እንደሆነ ያወሱት አቶ ስብሐት ነጋ: መደሹግ ዚነበሚበት ነገር መኹናወኑን አስሚድተዋል::
ይህ እርምጃ ሕገ-መንግስቱን ይጥሳል በሚል ዚሚነሳውን ተቃውሞ በተመለኹተ እኔ ዹማውቀው ነገር ዹለም ያሉት አቶ ስብሐት ነጋ ሕገ-መንግስቱ ኚተጣሰም ያለው አማራጭ ሕገ-መንግስቱን ማሻሻል ወይንም ሌላ አማራጭ መፈለግ እንጂ አዲሱ አደሚጃጀት መቀጠል አለበት ብለዋል::
ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ሕውሀት)ን ኹ1971 እስኚ1981 በመሪነት ያገለገሉትና አሁን ይፋዊ ዹሆነ ዚፓርቲ አመራር ስፍራ ዹሌላቾው አቶ ስብሐት ነጋ በሐገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ተጜዕኗ቞ው ዹጎላ መሆኑ እዚተገለጞ ይገኛል:: በተለይ ዚአቶ በሚኚት ሥምዖን ሚና ኹቀነሰ ወዲህ ይበልጥ እያንሰራሩ መሆናቾው ዹተገለጾው አቶ ስብሐት ነጋ በዚህ ሚገድ ለተነሳባ቞ው ጥያቄ እኔ ተራ አባል ነኝ ያለ ሃላፊነቮ ምንም ዚምሰራው ነገር ያለም ብለዋል::
እኔ ሥርዓት ኚጣስኩ ኚግንቊት 7: ኊብነግ እና ኩነግ በምን እለያለሁ:: በማለት ጠይቀው ምንም ሚና ዹለኝም ዹሚል ምላሜ ሰጥተዋል::
ዚአቶ መለስ ራዕይ በሚል ዚሚነሳውን በተመለኹተም “በግለሰብ ብቻ ዹተቀመጠ ራዕይ ሳይሆን ዚሁላቜንም ዕሎት ዹሆነ ዚጋራ ራዕይ ነው” በሚል ምላሜ ሰጥተዋል:: ሆኖም አቶ መለስ ወሳኝ ሰው እንደነበሩ በቃለ ምልልሱ አንስተዋል::
በድርጅቱ ውስጥ ክፍፍል ስለመፈጠሩ ለተነሳባ቞ው ጥያቄ “እስኚአሁን በኢሕአዲግ ውስጥ ይሁን በአባል ድርጅቶቹ መኹፋፈል ዚሚባል ነገር  ገጥሞ አያውቅም:: በዚህ ሂደት በተለያዩ መለኪያዎቜ ለኢሕአዲግ ብቁ ያልሆኑ ሰዎቜ ተባሚዋል ወይንም በራሳ቞ው ለቀው ወደ ሚመጥና቞ው ድርጅት ሔደው ይወድቃሉ” ያሉት አቶ ስብሐት ነጋ “አሁን በኢሕአዲግ ውስጥ ዚሚታይ ዹሚሰማ ዚፖለቲካ ጥያቄ ያለ አይመስለኝም ብለዋል:: ካለም እንዳለፈው ጾጋ ነው:: በአፈጻጞም ዙሪያም ጥያቄዎቜ ሊኖሩ ይቜላሉ” ሲሉ ምላሜ ሰጥተዋል::

በደቡብ ክልል ዚዳውሮ ወሚዳ ዞን ም/ቀት አባላት ዛሬ ኚጠሩት ስብሰባ 1500 ሰራተኞቜ ስብሰባውን ሹግጠው መውጣታ቞ው ተገለጠ


ኢሳት ዜና:- ዚኢሳት ምንጮቜ  ኹዞኑ እንዳመለኚቱት ዚክቢኒ አባላቱ ዚምሚጡን ስብሰባ አድርገው በነበሹ ጊዜ ህዝቡ ዹኔሰው ገብሬ ዚተሰዋበትን ዹሎሜ ኹተማ ዋና ኹተማ ዋካ ትሁን ጥያቄ ሳይመለስ ስለምርጫ  አናወራም ብለው ስብሰባውን ሹግጠው መውጣታ቞ው ተመልክቶል::
ዚዳውሮ ዞን ዋና ኹተማ በዹኔ ሰው ገብሬና በህዝቡ ዘንድ ዋካ መሆን ይገባታል ዹሚል ዹነበሹ ሲሆን ዹዞኑ ዹዮህዮን አመራር አባላት ዋካ መጀ ነዋሪ ዚመጣባት ኹተማ በመሆኖ አይቻልም ሲሉ መቆዚታ቞ው ተገልጩል::
ዛሬ በሎሜ ወሚዳ ዹዞኑ ዚካቢኔ አባላት ሰራተኞቜን ሰብስበው በቅርቡ በሚደሹገው ዚወሚዳ ምርጫ ደኢህዎን ኢህአዎግን ምሚጡን ለመስበክ ሰራተኞቜን ሰብስበው ዹነበሹ ቢሆንም ዚዋካ ዋና ኚተማነት ካልጞደቀ ኹናንተ ጋር አንወያይም ሲል ነው 1500 ሰራተኛ ስብሰባውን ሹግጠው ዚወጡት::
ምንጮቻቜን ኹሎሜ ወሚዳ ባደሚሱን ዘገባ መሰሚት ዹዞኑ ዚካቢኔ አባላት መኹፋፈላቾውንም ለማወቅ ተቜሎል::

ESAT New Frequency advert

በኩዌት፣ በሳዑዲ ዓሚቢያና ጅዳ ዚኢትዮጵያ ኀምባሲ ዹሰው ኃይልን በርካሜ ዋጋ ሊያቀርብ እንደሚቜል በአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ማስታወቂያው እያስነገሚ ነው



ኹሔለን ዘውዱ
ሰው በፈለገበት ቊታና አገር ዹመዘዋወር መብቱ በሕገ መንግሥቱ ተሚጋግጊለታል፡፡ በኮንትራት በቀት ሠራተኝነት ወደ
አሚብ አገሮቜ ዚሚሄዱ ኢትዮጵያዉያን ዚሚደርስባ቞ዉ በደል ኹጊዜ ወደ ጊዜ መባባሱ ይሰማል። ኢትዮጵያውያኑ
ላይ ኹፍተኛ ዹሆነ አካላዊና ሥነ ልቩናዊ ጉዳት እዚደሚሰ ነው። ለዚህም በዋነኛነት ማሳያ ዹሚሆነው በተለያዩ ዚዓሚብ
አገሮቜ በቀት ሠራተኛነት በሚሄዱት እህቶቻቜን ላይ ዚሚታዚው ዚሞት፣ ዚአካል መጉደል፣ ዹመደፈርና ያለደመወዝ
ማባሚር ጥቂቶቜ ናቾው፡፡ በዚህ ዓመት እንኳን ኹዓለም ደቻሳ ጀምሮ በድብደባ ህይወታ቞ውን ያጡትን ለኹፍተኛ
ዚአካል ጉዳት ዚተዳሚጉትን ዚተደፈሩትን ኹፎቅ ዚተወሚወሩትን ለአእምሮ መቃወስ ዚተዳሚጉት ዚትዚለሌ ናቾው
ኢትዮጵያዉያን ዚኮንትራት ሰራተኞቜ በአሰሪወቻ቞ው ዚሚደርስባ቞ውን ጥቃት ታዋቂ ዚሳዉዲ ጋዜጊቜ ሳይቀሩ
በዝርዝር እዚዘገቡት ነው፡፡
ዚወገኖቻቜን እንግልት ዹሚጀምሹው አገራ቞ው ላይ ነው፡፡ ዚሳዑዲ ዓሚቢያ ዜግነት ያላ቞ው ኢትዮጵያውያንም
በዜጎቻቜን ላይ ክብራ቞ውን ጭምር ዚሚነካ ተግባር ዚሚፈጜሙ አሉ፡፡ በተለያዩ ዚአገሪቱ ክልሎቜ በደላላዎቜ
እዚተደለሉ ኚዚቀያ቞ው እዚተፈናቀሉ ዜጎቻቜን ለጉዳት እዚተዳሚጉ ነው፡፡ ሁሉም ነገር አልጋ ባልጋ እንደሆነና ወርቅ
ተነጥፎ እንደሚጠብቃ቞ው በመስበክ ወጎኖቻቜንን እያስጚሚሱ ነው፡፡ ኚእነዚህ ደላሎቜ በስተጀርባ ዚመንግስት እጅ
አለበት መንግሥት ዜጎቜን ኹመጠበቅና ካለበት ኃላፊነት አንጻር እሱም ተጠያቂ ነው፡፡ ዕድሜያ቞ው እንዳልሞላ
እዚታወቀ ኹ13-15 ዓመትን ልጅን 23-26 ዓመት በማለት በማጣራትና አይቶም መገመት ሲቻል ፓስፖርት
ይሰጧቾዋል ዚሚያስደነግጥ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ወደ ሳዑዲና ኩዌት ለመሄድ ዚሚመጡት መጻፍ፣ ማንበብ ዚማይቜሉና
መታወቂያና ፓስፖርት መሆኑን መለዚት ዚማይቜሉ ናቾው፡፡ ፓስፖርት እስኚሚያወጡና ዹሕክምና ምርመራ
እስኚሚደሚግላ቞ው ድሚስ ብዙ ቜግሮቜን ያሳልፋሉ ሁሉም ነገር ተሳክቶላ቞ው እስኚሚሄዱ ድሚስ ዚደላሎቹ ዚወሲብ
መፈጞሚያ ይሆናሉ፡፡ ዚጀና ምርመራ ሲደሚግላ቞ውም ዹHIV ተጠቂ ሆነው ይገኛሉ ውጀታ቞ው ሲነገራ቞ው እንደ
ውርደት ስለሚቆጥሩት ተመልሰው ወደቀያ቞ው መግባትን ይተዉና ራሳ቞ውን በመሞጥ ለመተዳደር ይሞክራሉ፡፡
በሜታውንም ያስተላልፋሉ ላልተፈለገ እርግዝና ለ አደንዛዥ ዕፆቜ ተጋላጭ እዚሆኑ ነው፡፡
ዚጀና ምርመራ ውጀቱን አግኝተው ኹተጓዙ በኋላ በተቀባይ አገሮቜም ቜግር ይደርስባ቞ዋል፡፡ እዚያ ሲመሚመሩ ብቁ
አይደላቜሁም ተብለው እንዲመለሱ ይገደዳሉ ወይም ዚት እንዳሉና ማን እንደቀጠራ቞ው፣ ስንት ቀተሰብ ያለበት ቀት
እንደሚገቡ በስንት እንደተቀጠሩ፣ ቀጣሪዎቜ ለሕገወጊቜ ኹፍለናል ዚሚሉት ገንዘብ ስንት እንደሆነና ኚሄዱ ኚስንት
ጊዜ በኋላ ደመወዛቾውን እንደሚያገኙ አያውቁትም፡፡ ዱባይ ኚደሚሱ በኋላ ወደ አፍጋኒስታንና ኢራን ሳይቀር ለቀት
ሠራተኝነት ያግዟ቞ዋል፡፡ ወይም ዱባይ አዹር መንገድ ደርሰው ዹሚቀበላቾው ሰው ባለማግኘት አዹር ማሚፊያው አካባቢ
ሜዳ ላይ ለመዋልና ለማደር፣ ለምኖ ለመብላትም ዚተገደዱ በርካቶቜ ናቾው፡፡ እነዚህ ልጆቜ ወዎት እንደሚሄዱና
ለምን እንደሚሄዱ እነሱ ብቻ ሳይሆኑ መንግሥት ራሱ ማወቅ ነበሚበት፡፡ ዚዜጎቹን መብት ዚሚያስኚብር መንግስት
ዹለንም በዚህ ዚተነሳ ዜጎቜ በተለያዩ መንገዶቜ በሕገወጥ መንገድ እዚወጡ ነው፡፡ ዚሚደርስባ቞ውን አደጋ መንግሥት
ጠንቅቆ ያውቀዋል፡
ዹዚህ ምክንያት ብዙ ነው፡፡ አንዱና ዋነኛው ቁጥጥሩና ክትትሉ በአግባቡ አለመቃኘቱ ነው፡፡ ዜጎቜ በዚትኛውም ቊታ
ዹመዘዋወር ሕገመንግሥታዊ መብት አላቾው፡፡ ነገር ግን በተለይ ወደ መካኚለኛው ምሥራቅ ዹሚደሹገው ጉዞ ለሥራ
መሆኑን መንግሥት ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ጉዞው በህጋዊ መንገድ መሆን ሲገባው፣ በተለያዚ መንገድ ዚሚመጣላ቞ውን
ቪዛ ሕጋዊ ሳያስደርጉና ሳይመዘገቡ ዝም ብለው ነው ዚሚሄዱት፡፡ ይኜ ደግሞ በውጭ አገር ያሉ ሕገወጊቜ ቪዛዎቜን
እያወጡ ወደ ኢትዮጵያ ሲልኩ እዚህ ያሉት ሕገወጊቜ ተቀብለውና በሕገወጥ መንገድ ለመለመሏቾው ዜጎቜ

ይሰጣሉ፡፡ በዚህ መካኚል ሕገወጊቹ እዚተጠቀሙባ቞ው ይገኛሉ፡፡
በኢትዮጵያ ዚኩዌት ኀምባሲ ኚሚሠሩ ዚበታቜ ሠራተኞቜ ጋር በሚደሹግ ዚምስጢር ግንኙነት ሕጋዊ ሥርዓቱን
በሚቃሹን መልኩ እዚተሠራ ነው፡፡ በመሆኑም ሕጋዊዎቹ ኀጀንሲዎቜ ሥራ቞ው እዚተዳኚመ ነው፡፡ መንግስት ባለበት
አገር ሕግ እዚተጣሰ በሕጋዊ መንገድ በሚላኹው ቪዛ ዜጎቜ በሕገወጥ መንገድ እዚሄዱ ነው፡፡
በሳዑዲ ዓሚቢያ ያሉ ዚኢትዮጵያ ቆንስላዎቜ ወደ ሳዑዲ ዚሚላኩ ሠራተኞቜ ስለሚያገኙት ደመወዝ መወሰን
ዚሚቜሉት እነሱ እንደሆኑና እጅግ በወሹደ ደመወዝ እንደሚያስቀጥሩ መሹጃ አለ፡፡ በኩዌትና በሳዑዲ ዓሚቢያ በተለይ
ጅዳ ላይ ኀምባሲው ዹሰው ኃይልን በርካሜ ዋጋ ሊያቀርብ እንደሚቜል በአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን እያስነገሚና በጋዜጣ
ላይ ማስታወቂያው እዚወጣ ነው፡፡ ተልዕኮአ቞ውና ኃላፊነታ቞ው አይደለም፡፡ በዚህ ጉዳይ ዚሚሳተፉ ዚኀምባሲ
ሠራተኞቜ አሉ፡፡ በኩዌት አካባቢም ኚአሠሪዎቻ቞ው ሞሜተው ኹለላ ለማግኝት ወደ ኀምባሲ ለመጠለል ስሄዱ
ኀምባሲው ውስጥ ባሉ ሰራተኞቜ አማካይነት ለሌላ አሠሪ አሳልፈው እንደሚሞጧ቞ው ነው መሚጃዎቜ
ዚሚያመለክቱት፡፡ ይህንን ጉዳይ ለማስቆም ዚተንቀሳቀሱትን ወገን ወዳድ ዜጎቜ በመንግስት ባለስልጣናት ታፍነዋል፡፡
በአሁኑም ጊዜ ወደ ሳዑዲ ዓሚቢያ በቀን ኚአንድ ሺሕ እስኚ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ይሄዳሉ፡፡ ተቀባይ አገሮቜ
ኚሌሎቜ ሠራተኛ አቅራቢ አገሮቜ ጋር ያላ቞ው ግንኙነት ጥሩ ስላልሆነ ፊታ቞ውን መሪና መንግስት ወደ ሌላት
ኢትዮጵያ አዙሹዋል ምክንያቱም ሌሎቜ አገሮቜ ዚዜጎቻ቞ውን መብት እያስኚበሩ ሰለሚልኩ በአሁኑ ጊዜ ብዙ አገሮቜ
ወደ መንግስት አልባዋ ኢትዮጵያ ትኩሚት እያደሚጉ ነው፡፡
ለምሳሌ ፊሊፒንን ብንወስድ በዱባይ ዹሚገኘው ኀምባሲያ቞ው ጉዟቾውን ሳያፀድቅ አገራ቞ውን ለቀው አይወጡም፡፡
ዚአገራ቞ው መንግሥትም ማንኛውም ዚቀት ሠራተኛ ሆኖ ዚሚሄድ ዜጋው ኹ450 ዶላር በታቜ ተኹፋይ ሆኖ
እንዳይጓዝ በሕግ ደንግጓል፡፡ ቜሎታና ዚትምህርት ደሹጃቾውን በሚመለኚት ዚሚሞሉት ዚቅጥር ፎርም ትክክለኛና
እውነተኛ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ለሚያጋጥሟ቞ው አስኚፊ ቜግሮቜ፣ ለሚደርስባ቞ው ኹፍተኛ ዚሰብዓዊ መብት
ሚገጣና ዚጉልበት ብዝበዛ መነሻ ዚሎቶቹ ዚአገሩን ባህልና አኗኗር ዘይቀ አለማወቅና ለሥራ቞ው ዚሚያስፈልጋ቞ውን
ሥልጠና አለማግኘት ነው፡፡ እንደ ልብስ ማጠቢያ ወይም ምግብ ማብሰያ ባሉ ማሜኖቜ ግራ ይጋባሉ፡፡
ስለሚቀጠሩበት ቀት ሁኔታ፣ ዚቀተሰብ ብዛት ሌላም ሌላም አንድም ዚሚያውቁት ነገር ሳይኖር ኹአገር ይወጣሉ፡፡
በተለይም ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ እንደሚታዚው ወደ አሚብ አገሮቜ በመሔድ ላይ ያሉት ለአዲስ አበባ እንኳ እንግዳ ዹሆኑ
ኹገጠር አካባቢ ዚሚመጡ ልጆቜ ናቾው፡፡
በሌላ በኩል ዚሚቀጥራ቞ው እንዲገኝ ሲባል ዚኢትዮጵያውያኑ ዚቅጥር ፎርም ቜሎታ቞ው ምንም ይሁን ምን ሁሉንም
ዘመናዊ ዚቀት ውስጥ መገልገያ ማሜን መጠቀም እንደሚቜሉ፤ ማንኛውንም ሥራ ለመሥራትም ብቃት እንዳላ቞ው
ተደርጎ ይሞላል፡፡ ይህን ኹፍተኛ ቁጥር ዚተመለኚቱ ዱባይ ውስጥ ዹሚገኙ ህንድና ፓኪስታናዊ ደላሎቜ አማርኛ
ለምደው ሥራ቞ውን እያቀላጠፉ ኢትዮጵያውያኑ በወር ዹሚኹፈላቾው 135 ዶላር ሲሆን፣ ኀጀንሲዎቜ አንዲት
ኢትዮጵያዊትን በማስቀጠር ዚሚያገኙት 500 አልያም 550 ዶላር ነው፡፡ በተቃራኒው አንዲት ፈሊፒን ዚቀት
ሠራተኛን በማስቀጠር ኀጀንሲዎቜ ኹ2700 ዶላር በላይ ያገኛሉ፡፡ ‹‹áŠ áŠ•á‹²á‰µ ፊሊፒን ለሚቀጥር ኢትዮጵያዊ
ይመሚቅለታል›› ዹሚሉ ማስታወቂያዎቜ በተለያዩ ዚሥራ ማስታወቂያ ጋዜጊቜና ድሚ ገጟቜ ላይ መመልኚትም
ዹተለመደ ሆኖአል፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ
ኹዚህ በፊት በዘ-ሐበሻ ላይ ተለጥፎ ዹነበሹና አሚቊቜ ኢትዮጵያዊቷን ሲያሰቃዩ ዚሚያሳዚውን ቪድዮ በድጋሚ






ኢትዮጵያ ምዕመን በዘማሪት ዘርፌ ኹበደ “አለው ነገር” መዝሙር ስሜቱን እዚገለጞ ነው


ሐበሻ) ዘማሪ ዲ/ን ትዝታው ሳሙኀል፣ ዘማሪት ምርትነሜ ጥላሁን እና ዘማሪት ዘርፌ ኹበደ ኚወራት በፊት
ያወጡት አዲስ ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር ሲዲና ካሎት በመላው ኢትዮጵያ እዚተደመጠ ሲሆን በተለይ ዚዘማሪት
ዘርፌ ኹበደ “አለው ነገር እግዚአብሄር እንዲህ አብዝቶ ዝም ካለ” ዹሚለው መዝሙርን ኚወቅታዊ ዚቀ/ክ ሁኔታ ጋር
ይያያዛል በሚል በርኚት ያሉ ሰዎቜ ስሜታ቞ውን በዚህ መዝሙር እዚገለጹ እንደሚገኙ ዹዘ-ሐበሻ ዚኢትዮጵያ ዘጋቢዎቜ
አስታወቁ። እንደ ዘጋቢዎቻቜን ገለጻ ኹሆነ በሕዝብ ማመላለሻ ታክሲዎቜና በዚቊታው ሕዝቡ ይህን መዝሙር
እዚደጋገመ እንደሚኚፍትና ኚወቅታዊው ሁኔታ ጋር በማያያዝ ይነጋገርበታል። አነጋጋሪው ዚዘማሪት ዘርፌ ኹበደ
መዝሙር ኚነግጥሙ ይኾው፦

Dec 26, 2012

“ዚኊርቶዶክ ቀ/ክርስቲያን አመራር ለሃይማኖቱም ሆነ ለአጠቃላይ ሥርዓቱ አደጋ ወደመሆን ተቃርቧል” – ስብሃት ነጋ (ቃለምልልስ)



• በግለሰብ ላይ ዹተቀመጠ ራዕይ ሳይሆን ዚሁላቜንም እሎት ዹሆነ ዚጋራ ራዕይ ነው
ያለን፣
• ዚኊርቶዶክ ቀ/ክርስቲያን አመራር ለሃይማኖቱም ሆነ ለአጠቃላይ ሥርዓቱ አደጋ
ወደመሆን ተቃርቧል፣
• ኢህአዎግ በታሪክ እያላዘነ፣ ታሪክ እዚሚገመ፣ ታሪክ እያደነቀ አይኖርም፣
• ሥርዓት ኚጣስኩ ኚግንቊት ሰባት፣ ኚኊብነግ እና ኹኩነግ በምን እሻላለሁ፣
• ለኢህአዎግ ብቁ ያልሆኑ ሰዎቜ በልካ቞ው አዲስ “ድርጅት ይፈጥራሉ”
Read full story in PDF  http://www.zehabesha.com/wp-content/uploads/2012/12/sibehat-nega.pdf

ተወካዮቜ ምክርቀት አባላት በአዲስ አበባ ለኢህአዎግ ዚምርጫ ቅስቀሳ ዚሚመስል ጉብኝት አደሹጉ


ዚተኚበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ አልተጋበዙም
ዛሬ ኚማለዳው ጀምሮ በአዲስ አበባ ዚተወካዮቜ ም/ቀት አባላት በአራት ተኹፍለው ዚአዲስ አበባ መስተዳድር
ሰራሁዋ቞ው ያላ቞ውን ተለያዩ ስራዎቜ እንደጎበኙ ዹደሹሰን መሹጃ አመለኹተ፡፡ ዚአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና
ዚህዝብ ተወካዮቜ ም/ቀት ብ቞ኛ ዹተቃዋሚ አባል ዚሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ሳይጋበዙ እንቀሩ መሹጃው ይጠቁማል፡፡
ኚጉብኝቱ በሁዋላ በሂልተን ሆቮል ኹፍተኛ ዚምሳ ግብዣና ፌሜታ ያደሚጉት ዹምክር ቀት አባላቱ ለጉብኝታ቞ው
ምክንያት ዹሆነው ሚያዚያ ውስጥ ዚሚካሄደው ዚአዲስ አበባና ዚወሚዳ ምርጫ ሳይሆን እንዳልቀሚ እዚተነገሚ ነው፡፡
አሁንም ያለተወዳዳሪ በሜፍንፍን ምርጫ አሾናፊ ሆኖ መውጣት ዹሚፈልገው ኢህአዎግ ዹምክር ቀት አባላቱ
ሰራሁዋ቞ው ለሚለው ልማት ዕውቅናና አድናቆት እንዲሰጡ በማድሚግ ኹፍተኛ ፕሮፓጋንዳ በማካሄድ ዚምርጫ
ቅስቀሳው አካል እንዳደሚጋ቞ው አስተያዚት ዹጠዹቅናቾው ውስጥ አዋቂ ምንጮቻቜን ነግሹውና፡፡

ESAT Daily News Amsterdam 25 December 2012 Ethiopia

አፋሮቜ በብዛት እዚታሰሩ ሎቶቻ቞ውም እዚተደፈሩ ነው ተባለ


ኢሳት ዜና:-ኚስኳር ልማት ጋር በተያያዘ በአፋር አካባቢ ዹሚደርሰው ዚሰብአዊ መብቶቜ ጥሰት መጚመሩን ዚአካባቢው ተወላጆቜ ተናግሹዋል።
ህዳር 20 ቀን 2005 ዓም በዱብቲ ወሚዳ ቀይ አፈር እዚተባለ በሚጠራው አካባቢ ፋጡማ ኡህመድ ገዶ ዚተባለቜ ዹ11 አመት ልጅ ተደፍራ መሞቷን ዚልጂቱ አጎት ለኢሳት ገልጾዋል። ልጂቷን ዚደፈሩት ሰዎቜ መንግስት ለስኳር ልማት ስራ ብሎ ያመጣ቞ው ሰራተኞ ቜ ይሁኑ ዚመኚላኚያ ሰራዊት አባላት  áˆˆáˆ›á‹ˆá‰… እንዳልቻሉ ዚልጂቷ አጎት ገልጾው፣ ይሁን እንጅ ዹአፋር ተወላጆቜ እንዲህ አይነት ድርጊት እንዳልፈጞሙ በእርግጠኝነት ተናግሹዋል።  á‹šáŠ áŠ«á‰£á‰¢á‹ ባለስልጣናት ጉዳዩን ይፋ ቢያወጡ እርምጃ እንደሚወስዱባ቞ው እንደዛቱባ቞ው ዚልጂቷ አጎት ገልጾው፣ በድርጊቱ ዚተበሳጩ ዚጎሳው አባላት ተቃውሞ እንዳያሰሙ  á‹šáˆ˜áŠšáˆ‹áŠšá‹« ሰራዊት በአካባቢው እንዲሰፍር መደሹጉን ተናግሹዋል።
በአካባቢው ምንም ሰላም እንደሌለ ዚተናገሩት ነዋሪዎቜ ፣ ለስኳር ልማቱ ቀታ቞ውን እንዲያፈርሱ ተጠይቀው ፈቃደኛ ያልሆኑ በርካታ ሰዎቜ ወደ እስር ቀት መጓዛቾውንም ገልጾዋል።
በቅርቡ ደግሞ ሩቢ ኢብራሂም አሊ ዚተባለቜ ዹ8 አመት ህጻን በአሰቃቂ ሁኔታ ተደፍራ ወደ አዲስ አበባ ጩር ሀይሎቜ ሆስፒታል መላኩዋን እስካሁን ድሚስ ሊሻላት እንዳልቻለ አንድ በአፋር ሰብአዊ መብቶቜ ጉዳይ ላይ ዚሚሰሩ እናት ተናግሹዋል። ግለሰቡዋ ኢሳት ቜግራ቞ውን ለመዘገብ ስለደሚሰላ቞ውም ምስጋና አቅርበዋል
በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርና቞ው ዹአፋር ሰብአዊ መብቶቜ ድርጅት ሃለፊ ዚሆኑት አቶ ገአስ አህመድ ለኢሳት እንደተናገሩት ኚስኳር ልማት ጋር በተያያዘ በአካባቢው ያለው ቜግር እዚተባባሰ መምጣቱን ገልጾዋል።
በክልሉ ያለውን ቜግር ለአለማቀፍ ማህበሚሰብ ለማሳወቅ ድርጅታ቞ው እዚሰራ መሆኑንም አቶ ገአስ ገልጾዋል።
በሌላ ዜና ደግሞ ዹአፋር ገድሌ እዚተባለ ዚሚጠራው ታጣቂ ሀይል በአፋር አካባቢ መንቀሳቀሱ መሰማቱን ተኚትሎ ዞን 1 እዳር ወሚዳ አካባቢ ያለው ሰራዊት ተንቀሳቅሶ ህዝቡ ኚቊታ ቊታ እንዳይንቀሳቀስ እና ታጣቂው ሀይሉን እንዳይቀላቀል ኬላዎቜ መዘርጋታ቞ውን ዹአፋር ጋድሌ ወታደራዊ ጉዳይ ዋና አዛዥ ዚሆኑት ኮሎኔል  መሀመድ አህመድ ተናግሹዋል

ሁለት ዹአሹና አባላት ዚድርጅቱን ልሳን ሲበትኑ ተያዙ


ኢሳት ዜና:-አሹና ፓርቲ በዚሶስት ወሩ ማሳተም ዹጀመሹውን ዚድርጅቱን ልሳን ሲያሰራጩ ዹተገኙ 2 ዚድርጅቱ አባላት በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቾውን ያገኘነው መሹጃ ያመለክታል።
ዹመቀሌ ዹአሹና  ጜህፈት ቀት ተጠሪ ዚሆኑት አቶ ሱልጣን ህህሾ ለኢሳት እንደተናገሩት አቶ አያሌው በዹነና አቶ ተካልኝ  ታደሰ ዚተባሉት ድርጅቱ አባላት ዚተሳሩበት ምክንያት ዚፓርቲውን መታወቂያ አልያዛቜሁም ተብለው ነው። ይሁን እንጅ ፓርቲው እስሚኞቹ ዚድርጅቱ አባላት መሆናቾውን ለአካባቢው ፖሊስ መግለጹን አቶ ሱልጣን ተናግሹዋል።
ትናንት ሰኞ እለትም በሁመራ አደላይ ቀበሌ ሌላው አባላ቞ው ወሚቀት ሲበትኑ መያዛ቞ውን ፣ ዚጜህፈት ቀታ቞ው ሰንደቅ አላማ ዚሚውለበለብበት ምሰሶ መሰሹቁንም ገልጾዋል።
በአሹና ትግራይ አባላት ላይ ዹሚፈጾመው እንግልት እዚጚመሚ መምጣቱን ድርጅቱ በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል።
በጉዳዩ ዙሪያ ዚሜራሮ ፖሊስ አመራሮቜን ለማግኘት ሙኚራ ብናደርግም አልተሳካልንም።

ዹ40 በ60 ዹ”ቀት ልማት ፕሮግራም ትግበራ ዚመንግስት አካላትን ግራ አጋብቷል


ኢሳት ዜና:-በአዲስአበባ ኹተማ ተጀምሮ ወደ ክልሎቜ ይስፋፋል በሚል ትልቅ ተስፋ እዚተሰጠበት ያለውና በቁጠባ ላይ ዹተመሰተሹው
ዹ40 በ60 ቀቶቜ ፕሮግራም አጀማመር ባለቀቱን አዲስአበባ አስተዳደርን ግራ በማጋባቱ እስካሁን ምዝገባ መጀመር
ባለመቻሉ በተለያዩ ዚተምታቱ መግለጫዎቜ ሕዝቡን ግራ እያጋቡት መሆናቾው ተሰማ፡፡
በአቶ መኩሪያ ኃይሌ ዚሚመራው ዹኹተማ ልማትና ኮንስትራክሜን ሚኒስ቎ር አጠናሁት ባለው መሰሚት አንድ ቀት ፈላጊ
በስቱዲዮ፣ባለአንድ መኝታ ወይም ባለሁለት መኝታ መርጩ ውል ኹፈጾመ በኃላ ለአምስት ዓመታት ዚቀቱን ግምት 40
በመቶ ቆጥቊ ቀሪው 60 በመቶ ኚባንክ በሚገኝ ብድር ተሾፍኖ ዚቀት ባለቀት ዚሚሆንበት ዕቅድ ነበር፡፡
ዕቅዱ በተለይ መካኚለኛ ገቢ ያለውን ዚመንግስት ሰራተኖቜን ጚምሮ ሌሎቜ ዚኀብሚተሰብ ክፍሎቜን ተጠቃሚ ያደርጋል በሚል
ብዙ ዚተወራለት ቢሆንም በቀላሉ ሥራ ላይ ማዋል ግን አልተቻለም፡፡
ዕቅዱን አስመልክቶ ዹኹተማ ልማትና ኮንስትራክሜን፣ዚአዲስአበባ ኹተማ አስተዳደር እና ብድር ያቀርባል ዚተባለው
ዚኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዚሥራ ኃላፊዎቜ እርስበርስ ዚሚጣሚሱ መሚጃዎቜን ለሕዝብ ኹመልቀቅ ጀምሮ ምዝገባ በዚህ
ቀን ይጀመራል በሚል ኹፍተኛ ሁካታና ሰልፍ ያስኚተለ መግለጫዎቜን ሲሰጡ ቢኚርሙም ምዝገባውን ግን መጀመር
አልቻሉም፡፡
ስለዚህ ጉዳይ በመንግስት መገናኛ ብዙሃን በቅርቡ አስተያዚት ዚተጠዚቁት ዹኹተማ ልማትና ኮንስትራክሜን
ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ኃይሌ ዚተሳሳተ መሹጃ ዚሚሰጡ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ እስኚመግለጜ ዚደሚሱበት
ሁኔታ መኖሩንም ምንጫቜን አስታውሶአል፡፡
ይህም ሆኖ አቶ መኩሪያ ራሳ቞ው በጥቅምት ወር 2005 ዓ.ም ለፓርላማው በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ዚቀት ፕሮግራሙ ምዝገባ ይጀመራል በማለት ቃላቾውን ቢሰጡም ሁለት ወራት አልፎም ምዝገባው ሊጀመር አለመቻሉም ውዥንብር ኚሚነዙት ውስጥ አንዱ አድርጓ቞ዋል፡፡
ዹ40 በ60 ዚቀት ልማት ፕሮግራም ምዝገባ ለመጀመር አስ቞ጋሪ ያደሚገው በርካታ ያልተመለሱ ጥያቄዎቜ በመኖራ቞ው
መሆኑን ምንጫቜን ጠቅሷል፡፡ኹነዚህም መካኚል “መዝጋቢው አካል ማንነው?አንድ ሰው ቀት እንደሌለው በምን ተሹጋግጩ
ይመዘገባል?አንድ ሰው ለአምስት ዓመታት ቆጥቊ በቀጥታ ቀቱን ማግኘት ይቜላል ወይ?ዚተገነቡት ቀቶቜ ኚቆጣቢዎቹ
ቁጥር በላይ ኹሆነ ምን ይደሹጋል?በዕጣ ዹሚለይ ኹሆነ አንድ ሰው አምስት ዓመት ሙሉ ተ቞ግሮ ዚመቆጠቡን ፋይዳ
ዋጋ አያሳጣውም ወይ? በዹጊዜው በዕጣ ዹሚለይ ኹሆነ ሰውዹው ዚቀት ባለቀት ዹሚሆነው መቌ ነው?እስኚዚያስ ገንዘቡ
በባንክ ታስሮ መቆዚቱ ምን ያህል ተገቢ ነው?ዚቀቱን ሙሉ ክፍያ በአንዮ መፈጾም ዚሚቜሉ ቀት ፈላጊዎቜ እንዎት
ይስተናገዳሉ?አንድ ሰው ቁጠባ ጀምሮ ቢያቋርጥ ገንዘቡን እንዎት ማግኘት ይቜላል?ቁጠባውን ያቋሚጠው ሰው
ዹጀመሹውን መሞጥ ወይም ለሌላ ማስተላለፍ መብት ይኖሹዋል ወይ?” እና ዚመሳሰሉ ጥያቄዎቜ ሚኒስ቎ሩም ሆነ ዹኹተማ
አስተዳደሩ በመመሪያ መመለስ አልቻሉም፡፡
በዚህ ምክንያት አሁንም ሕዝቡን ኹነገ ፣ዛሬ ምዝገባው ይጀመራል ፣ዚቀት ቜግራቜሁም ይቀሹፋል በሚል ተስፋ ኚመመገብ ባለፈ በትክክለ ምዝገባው ዚሚጀመርበት ጊዜ አለመታወቁ እንቆቅልሜ ሆኗል፡፡
ኹዚሁ ጋርም ተያይዞ አነስተኛ ገቢ ላላቾው ዚኀብሚተሰብ ክፍሎቜ ዚገነባል ዚተባለው ዹ10 በ90 ዚቀቶቜ ግንባታም
ተመሳሳይ ቜግር ውስጥ በመሆኑ እንዳልተጀመሚ ታውቋል፡፡

ዚህወሀት አባላት ዹሆኑ ኹፍተኛ ዚመንግስት ባለስልጣናት አሜሪካ በመምጣት ኚትግራይ ተወላጆቜ ጋር ብቻ ሊመክሩ ነው


ኢሳት ዜና:-ምክትል ዚውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር  ደብሚ-ጜዮን ገብሚሚካኀል፣ ዚውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቎ዎድሮስ አድሀኖም እና አቶ አባይ ወልዱ በመጪው ጥር ወር አሜሪካ በመምጣት  ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ኚትግራይ ተወላጆቜ ጋር ብቻ እንደሚመክሩ ተመለኹተ።
ዚመንግስት ኹፍተኛ ባለስልጣናቱ በ ኢትዮጵያ  ፖለቲካዊ ጉዳይ ኚትግራይ ተወላጆቜ ጋር እንዲመካኚሩ መድሚኩን ያመቻ቞ው ዚትግራይ ልማት ማህበር ነው።
ደ-ብሚብርሀን ብሎግ እንደዘገበው ዚትግራይ ልማት ማህበር በዲያስፓራ  ራሱን ዚቻለ ዚትግራይ መንግስት እዚፈጠሚ ያለ  ድርጅት ነው።
አንድ ዚትግራይ ተወላጅ ወደ ውጪ አገር በሚመጣበት ጊዜ ወዲያው በመመዝገብ ታክስ እንደሚሰበስብ ዹጠቀሰው ብሎጉ፤ ማህበሩ  ኚሚዥም ጊዜ አንስቶ በዲያስፖራ ዹሚገኙ ዚትግራይ ተወላጆቜን ኚሌሎቜ ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻ቞ው ለመለዚት እዚደኚመ ዹሚገኝ ጜንፈኛ ማህበር መሆኑን ጠቁሟል።
ይህ ጜንፈኛ ማህበር ኚኢትዮጵያዊነት ይልቅ ዚትግራይ ብሄርተኝነትን ለማስፋፋት  እዚተንቀሳቀሰ መሆኑን በማውሳትም፤ በመጪው ጥር ወር ወደ አሜሪካ ዚሚመጡት ኹፍተኛ ዚመንግስት ባለስልጣናት በ አገር ጉዳይ ኚትግራይ ተወላጆቜ ጋር ብቻ እንዲሰበሰቡ ዚግብዣ ጥሪ ያቀሚበውና ፕሮግራሙን ያዘጋጀውም ይኾው ዚትግራይ ልማት ማህበር መሆኑን አመልክቷል።
በሚኒሶታና አካባቢው ዚሚኒሩ ዚትግራይ ተወላጆቜ በተደጋጋሚ ባወጧ቞ው መግለጫዎቜ ፦ዚመንግስት ባለስልጣናት  ወደ ወጪ አገር ሲመጡ ዚትግራይ ተወላጆቜ ጋር ብቻ ስብሰባ ማድሚጋ቞ውን በማውገዝ፤ ዚህወሀት መሪዎቜ  ዚትግራይን ህዝብ ኹሌላው ዚኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ለመለያዬት ኚሚኚተሉት ጠባብ  ዚጎሰኝነት መንገድ እንዲታሚሙ ማሻሰባ቞ው ይታወሳል።

ኢትዮጵያውያን ሎቶቜ ወደ ዱባይ ለሥራ እንዳይሄዱ በህግ ታገዱ


ኢሳት ዜና:-ዚኢትዮጵያ መንግስት  ሎቶቜ ወደተባበሩት አሚብ ኢምሬት(ዱባይ) ለሥራ  እንዳይሄዱ በህግ ማገዱን አስታወቀ።ህገ-ወጥ ጉዞው ግን እንደቀጠለ ነው አለ።
በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ዚህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሜን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ሞለመ ፥ በጉብኘትና በግል ቪዛ በቀት ሰራተኛነት ለመቀጠር ወደ ዱባይ ዚሚያደሚገው ጉዞ እንዲቆም ዹተደሹገው ራስን ለኹፋ ቜግር ዚሚዳርግ በመሆኑ ነው ብለዋል።
ዜጎቜ ህጋዊ ጥቅሞቻ቞ውና መብቶቻ቞ው ተጠብቀውላ቞ው እንዲሰሩ ዚኢትዮጵያ መንግስት ኚተለያዩ ሀገራት ጋር ዚንግድ ዚሰራተኛ ቅጥርና ዚተለያዩ ውሎቜ  ስምምነት አለው  ያሉት ዳይሬክተሩ፤ኢትዮጵያ በዚህ መልኩ ስምምነት ዚተፈራሚመቜው ኚሳውዲ አሚቢያና ኚኩዌት ጋር ሲሆን ፥ ኚተባበሩት አሚብ ኀምሬትስ ጋርም ተመሳሳይ ስምምነት ላይ ለመድሚስ  ገና በሂደት ላይ  ትገኛለቜ ብለዋል።
<<ወደ ዱባይ   ዹሚደሹግ ጉዞ ለዜጎቜ ደህነነት ሲባል ቢኚለኚልም፤ በህገ ወጥ መንገድ ዹሚደሹገው  ጉዞ ግን  አሁንም አልቀሹም።>>ብለዋል-አቶ ግርማ።
መንግስት ወደ ዱባይ ለቀት ሰራተኝነት ዹሚደሹገው ጉዞ እንዲቆም ያደሚገው ፥ በዚህ ጉዞ ውስጥ ያሉ ዜጎቜን ለኹፋ እንግልት ዚሚዳርጉ ውስብስብ ቜግሮቜን ኚተባበሩት አሚብ ኢምሬትስ መንግስት ጋር በመመካኚር ለመፍታት ነው ሲሉም አክለዋል።
ዜጎቜ ኹሁሉም በላይ በሀገራ቞ው ባለው ዚስራ አማራጭ ለመጠቀም መጣር አለባ቞ው ያሉት አቶ ግርማ ፥ ጉዞ ካስፈለገም ህጋዊ መንገድን ተኚትሎ ብቻ በመሄድ መስራት እንደሚገባ መናገራ቞ውን ዹፋና ዘገባ ያመለክታል።
ይሁንና ዳይሬክተሩ ዚኢትዮጵያ መንግስት ስምምነት ያለው  ኚሳዑዲ አሚቢያና ኚኩዌት መንግስታት ጋር ነው ቢሉም፤  አለ ዚሚሉት ውልና ስምምነት  በተጠቀሱት አገሮቜ  ያሉትን ኢትዮጵያውያን ኚመኚራ ሊታደጋ቞ው አልቻለም።
በሳዑዲና በኩዌት  በሚገኙ  በርካታ ኢትዮጵያውያን ላይም  ኚዱባይ ባልተናነሰ መልኩ በተደጋጋሚ ዘግናኝ በደልና ግፍ እዚተፈጞመባ቞ው እንደሚገኝ በተደጋጋሚ መዘገባቜን ይታወሳል።

ወይ “መዓልቲ” አለ ያገሬ ሰው!

ኢትዮጵያ ዚተባበሩት መንግስታት ሰብአዊ መብት ኮሚሜን አባል ሀገር ሆና ተመሚጠቜ።
ዚትኛዋ ኢትዮጵያ!? ዚትኛው ሰብአዊ መብት!? ዚትኛው ዚተባበሩት መንግስታት ዚሰብአዊ መብት ኮሚሜን!?

እኔ ዹምለው ኢትዮጵያዊው ዚዩልኝታ ባህላቜን ያለው ህብሚተሰቡ ዘንድ ብቻ መሆኑ በጣም አሳሳቢ ቜግር አይመስላቜሁም? እንዎ መንግስት እኮ ይሉኝታ ቢኖሚው ኖሮ “ተመድ ዚሰባዊ መብት ኮሚሜን አባል አድርጌ መርጹሀለሁ!” ሲለው… “አሹ በህግ አምላክ እኔ አልሆናቜሁም ሀገር ተሳስታቜሁ ነው! ወይ ደግሞ ባታውቁኝ ነው ዚመሚጣቜሁኝ…!” ማለት ነበሚበት። ነገር ግን መንግስ቎ “ምን ይሉኝ” ያልፈጠሚበት ነውና አሜን ብሎ መቀበሉ ሲገርመን፤ ጭራሜ በአደባባይ “እንዲህ ነን እኛ ሰብአዊ መብት ጠባቂዎቜ” ተብሎ ተነገሹን!ኢቲቪ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታማሚ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን አማካይነት፤ “ድሮውንም እኛ ለሰብአዊ መብት ጥበቃ ዘብ ዹቆምን ሰዎቜ ነን!” ብሎናል።
አቶ ዲና በሚወዱት ይማሉልኝ ዚሚናገሩት ዚምርዎትን ነው!? ኹማሉልኝ ዛሬ ነገ ሳልል ሀገሬ እመጣለሁ። እኔ ብቻ ሳልሆን ሁሉም ዚሰብአዊ መብት ጥሰቱን ፈርቶ ዚወጣው ኢትዮጵያዊ ሁሉ “ምን አለኝ ሀገሬ” (“ለ“ን አጥብቆ) ዘፍኖ እንደወጣው ሁሉ፤ “ምን አለኝ ሀገሬ” በሚል “ለ”ን አላልቶ ዘፍኖ ይመለሳል። ግን እርግጠኛ ነኝ በሚወዱት አይምልሉንም! ለመሆኑ ዚሚወዱትስ አለ…!? ወይስ ነፍስ ይማር እንበልልዎ!?
ዹምር ግን ሰብአዊ መብት ማለት ምን ማለት ነበሹ!?

“ወይ መዓልቲ” አለ ያገሬ ሰው!
ዚኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ ዚተሳካ እና ውጀታማ ለማድሚግ በ አንድነት ተነስተናል

ሰላም ወገኖቜ
እኛ በኖርዎይ ዹምንገኝ ዚኢትዮጵያ ስደተኞቜ ሃገራቜን ዹሚገኘውን ዘሹኛ ፣ አፋኝ እና አምባገነን መንግስት በመቃዎም ሁለንተናዊ እንቅስቃሎዎቜ እያደሚግን እንገኛለን ። ኹነዚህ እንቅስቃሎዎቜ መካኚል አንዱ ዚኢትዮጵያን ህዝብ እውነተኛ ዹሆነ መሹጃ እንዲያገኝ ፤ በሃገር ወዳድ ዚኢትዮጵያ ዜጎቜ ዹተቋቋመውን ኢትዮጵያ ሳተላይት ቎ሌቪዥንን(ኢሳት) መርዳት ነው ።


እንደምናውቀው ተራራውን አንቀጠቀጠን ዚሚሉትን ዚማፊያ ቡድን ወያኔን ፤ ኢሳት እውነት ለኢትዮጵያን ህዝብ በማቀበል ብቻ እያንቀጠቀጣ቞ው ይገኛል ። ኢሳት ዚኢትዮጵያን ብ቞ኛ ህዝብ አይን እና ጆሮ ብ቞ኛ ሳይሆን በተግባርም አንደበት ስለሆነ Feb 10-2013 በ ኖርዎይ ዋና ኹተማ በኊስሎ ይካሄዳል ። በዚህ ቀን ሃገር ወዳድ ወንድማቜን ታማኙ አርቲስት ታማኝ በዹነ ተጋባዥ እንግዳቜን ነው ። ለኢሳት ፣ ለአርቲስት ታማኝ በዹነ እንዲሁም ለኢትዮጵያን ህዝብ ክብር ስንል በስደት ዚምንኖርበት ሃገር ዹሚደሹገውን ዚገቢ ማሰባሰቢያ ዚተሳካ እና ውጀታማ ለማድሚግ በ አንድነት ተነስተናል ።

በዚህ አጋጣሚ በኖርዎይ ዚምትገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያ ወዳጆቜ በዚህ ዝግጅት በመገኘት ኢትዮጵያ ሳተላይት ቎ሌቪዥንን (ኢሳት) ለሚደሹገው ዚገቢ ማሰባሰቢያ ዚራስዎን አስተዋጜኊ እንዲያደርጉ በክብር ጋብዘንዎታል ።


ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!
ሞት ለውያኔ እና ሆድ አደሮቜ !!!

HISTORIC SPEECH BY ABEBE GELAW

እውነትን ሞሜተን ዚቀተ ክርስቲያንን አንድነት ልናመጣ አንቜልም






ዘመነ ካሣ ኹጀርመን
ለሁለት አሥር ዓመታት ቀ ተ ክርስቲያንን ለሁለትና ብሎም ለሊስት እንድትኚፈል አንድነታ ተናግቶ ካሕናትና
ምዕመናን ተለያይተው አሁን ለደሚስንበት ጊዜ ዹቆዹው በሕገ ቀተ ክርስቲያን ዚተሟሙት ፓትርያርክ ብጹእ ወቅዱስ
አቡነ መርቆሬዎስ ኚጜርሐ መንበሹ ፓትርያርክ ወንበራ቞ው ያለአገባብ በሕመም ምክንያት አሳበው በዘሹኛውና
በጎጠኛው ወያኔ መንግሥት አማኚይነት እንዲለቁ ዹተደሹገ መሆኑ ሁሉም ዚሚያውቀው አውነት ነው::
ይሁን እንጂ ይህነ ግዙፍ እውነት በመካድ አዲስ አበባ ያሉት ዚሲኖዶሰ አባላት በሕመም ምክንያት መሥራት አልቜልም
ብለው ነው ዚለቀቁት በማለት መሠሹተ ቢስ ዹሆነ ዚሀሰት ቃል ሲናገሩ መሰማት ኚመነኮሳት አባቶቜ ያውም ለእውነትና
ለቀተክርስቲያን ቆመናል ኹሚሉ ሰዎቜ ሲሰማ እጅግ ዹሚዘገንን ነው ማን ነው ታዲያ እውነት ሊናገር ዚሚቜል ??
አባሕዝቅኀል ተብለው ዚሚጠሩት ጳጳስ ዓይናቾውን በጹው አጥበው ዓለም ዚሚያውቀው እውነት በመካድ ሀሰት
ሲናገሩ ትንሜ እንኳን ዚማይኚብዳ቞ው ሰው ናቾው

ሰሞኑን በፕሬዝዳንት ግርማ ዚተጻፈውና ወዲያው ዚተሻሚው ደብዳቀ መልካም ዚሚያሰኝ ነገር እንዳለ አመላክቶ ነበር፡፡
ሆኖም ዋናው ቜግር በማን በኩል እንዳለ ዚፕሬዝዳንቱን ደብዳቀ ተኚትሎ ዚተወሰዱ እርምጃዎቜ ትልቅ ማሳያ
ሆነዋል፡፡ ቀተክህነቱ በፕሬዝዳንቱ ደብዳቀ ስላልተደሰተ መንግስትን በሃይማኖት ጣልቃ እንደገባ በመቁጠር
ፕሬዝዳንቱን መውቀሱና ፕሬዝዳንቱም ዚጞፉትን ደብዳቀ ለማጠፍ እንደተገደዱ መሚዳት ተቜሏል፡፡ ቀተክህነቱ
ዚፕሬዝዳንት ግርማን ደብዳቀ ተቃውሞ ሲነሳ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ ገቡ በሚል ቢሆንም በዋናነት ግን አቡነ
መርቆሬዎስን ላለመቀበል ትልቅ ሜፋን ዹነበሹውና «áŠ¥áŠ› ይመለሱ ብንልም መንግስት አይደግፋቾውም» ዹሚለው ሰበብ
በፕሬዝዳንት ግርማ ደብዳቀ በጥቂቱም ቢሆን መሞርሞሩ ደስ ስላላሰኛ቞ውና ኹዚህ ውጪ ዚሚያቀርቡት ምክንያት ብዙ
ዚሚያራምዳ቞ው ሆኖ ባለመገኘቱ እንደሆነ ተገምቷል፡፡

አቡነ ጳውሎስ
በሕይወት
እያሉ በውጭ
ካለው
ሲኖዶስ ጋር
ለሚካሄደው
ዚእርቁ ሂደት
ትልቅ
እንቅፋት
እንደሆኑ
ተደርጎ
አብሚዋ቞ው
ባሉትና ያኔ
ሲቃወሟ቞ው
በነበሩትና ዛሬ
ዚሚሉትላለመታሚቅ á‹ˆáˆµáŠá‹ እርቁ 

ጳጳሳት ጭምር ብዙ ሲባል እንደነበር ዚሚታወቅ ነው፡፡ ኚእርሳ቞ው ዕሚፍት በኋላ ነገሮቜ ይለወጣሉ ተብሎ ቢጠበቅም
እንዲያውም ብሰው ነው ዚተገኙት፡፡ ቀድሞስ አቡነ ጳውሎስ ናቾው እንቢ ያሉት እንበል፤ አሁን ግን አቡነ መርቆሬዎስ
ወደመንበራ቞ው ሊመለሱ አይገባም ዚሚሉት ጳጳሳት አላማቾው ምንድነው? ዹሚለው አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ በተለይም
«5ኛ ብለን ወደ4ኛ አንመለስም፤ 6ኛ ነው ዹምንለው» ዹሚለው ምላሜ ለአቡነ ጳውሎስ ክብር ኹመጹነቅ ዹሚመነጭ
እንዳልሆነ ታውቋል፡፡ ይህን መግለጫ ዚሰጡት አቡነ ህዝቅኀልን ጚምሮ ሲኖዶሱን እያናወጡ ያሉት ጥቂት አስ቞ጋሪ
ጳጳሳት አቡነ ጳውሎስ ዚሟሟ቞ውና ዚአቡነ ጳውሎስ ተቃዋሚ ሆነው ዹዘለቁ ናቾው፡፡ ታዲያ ኚእርሳ቞ው ህልፈት በኋላ
ለምን እንዲህ አሉ? ይህን አቋምስ ለምን ያዙ ቢባል አንዱ ምክንያት ቀጣዩ ፓትርያርክ ለመሆን እዚተሻኮቱ ስለሆነና
ዚአቡነ መርቆሬዎስ ወደመንበራ቞ው መመለስ ነገሮቜን ሊቀይርባ቞ው ስለሚቜል ነው። እነዚህ ጳጳሳት ዹግል
ጥቅማ቞ው እንጂ ዚቀተክርስቲያን አንድነት እንደማያሳስባ቞ው ግልጜ እያደሚጉ ነው፡፡
ቀተ ክርስቲያናቜን ለ 20ዓመታት በ ሁለት ሲኖዶስ ስተመራ ዚቆዚቜው እኮ ዚቀድሞው ፓትርያርክ በህይወት እያሉ
ለምን ሌላ ፓትርያርክ ተሟመ በሚል ዹቀኖና ቀተ ክርስቲያን ጥያቄ ነበር። እግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ አንደኛው ኹዚህ
ዓለም በሞት ተለዩ። ቀተ ክርስቲያንን ወደ አንድነት ለመመለስ ግልጜና ትክክል ዹሆነው እርምጃ በይህወት ያሉትን
ፓትርያርክ ለመላዋ ቀተ ክርስቲያን መሪ ማድሚግ ነው። ይሄ ለምን ድርድር እንደሚያስፈልገውና ኚባድ እንደሆነ
ለህዝብ ግልጜ አይደለም።
ዚዚህቜ ቀተ ክርስቲያን አንድ መሆን ለሀገርና ለቀተ ክርስቲያን ኹፍተኛ ድርሻ ነበሹው ይሁንና ዹቀኖና ቀተክርስቲያንን
መጣስ ወደ ጎን በመተው ላለመታሚቅ ሰንካላ ምክንያት በመደርደር ዚቀተ ክርስቲያን መኚራ እንዲራዘም ዚሚሮጡ
ትንሜ ናቾው ማለት አይቻልም ኚአንዳድ ዚሥልጣን ጥመኞቜ ጳጳሳት በግለሰብና በማሕበር ዚተደራጁ ቡድኖቜ
በስውርና በግልጜ ዚሚሞርቡት ተንኮል እጅግ አስገራሚነው ዹማሕበሹ ቅዱሳን አባላት ነን ዚሚሉት እነ ዲያቆን ዳንኀል
ክብሚት ዚሚሰጡት አስተያዚት ስድስተኛ ፐትርያርክ ለማስመሚጥ ሕግ በማርቀቅ ዚሚሮጡት አነ ቄስ ሰሙ ምትኩ
በፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚ቎ነት ላይ ታቜ ኚሚሉት እነ አአቶ ባያብል ሙላቮ ዚሚሞርቡት ተንኮል እጅግ አሳፋሪ
ነው ታዲያ ቀደም ሲል በፓትርያርክ ምርጫና ቅስቀሳ ተጠምዶ ዹነበሹው ደጀሰላም አሁን ላይ ስለ እርቅ መስበኩ ሹፈደ
ባይባልም ስለ ቀኖና ቀተክርስቲያን መጣስ ዚቀተ ክርስቲያን አንድነት እንዎት ሊፈርስ እነደቻለ እውነቱን ኚመጻፍ
ይልቅ ” አቡነ መርቆሬዎስ ዚት ነው ያሉት ” በማለት ዹፍለጋ ማስታወቂያ ሲሠራና ዚምርጫ ደንብ ሲያሚቅ እንደሰነበተ
ሊካድ ዚማይቜል እውነት ነው

ስለዚህ ዛሬ ቀተ ክርስቲያናቜን መስቀለኛ መንገድ ላይ ትገኛለቜ መፈትሔው አጭርና ግልጜ ነው ቜግሩ ዹቀኖና ቀተ
ክርስቲያን መጣስ እስኚሆነ ድሚስ መፍትሔው በሕይወት ያሉትን ፓትርያርክ ወደ መንበራ቞ው እንዲመለሱ ማድሚግ
ነው ሐቁንም መኹተል ሕገ ቀተ ክርስተያንንንም ማክበር ነው
እውነትን በማድበስበስ መግለጫ በመደርደር አንድነት ሊመጣ አይቜልም

ESAT Meade Esat Ethiopia Dec 24 2012

Dec 25, 2012

ዚግንቊት7 ህዝባዊ ሐይል ኚሌሎቜ ድርጅቶቜ ጋር በጋራ እዚሰራ መሆኑን አስታወቀ


ኢሳት ዜና:-ዚድርጅቱ ቃል አቀባይ ታጋይ ዜና ጉታ ለኢሳት እንደገለጠው ኚትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ወይም ደሚት፣ ኚኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞቜ ግንባር፣ ኚኢትዮጵያ ህዝብ ፍትህና እኩልነት ግንባር፣ ኚጋምቀላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ፣ ኚቀንሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ እንዲሁም ዚአማራ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ኚተባሉት ድርጅቶቜ ጋር በጥምሚት ለመስራት አስፈላጊው ዝግጅት አጠናቋል።
ታጋይ ዜና ጉታ ህዝባዊ ሀይሉ በዶ/ር ብርሀኑ ነጋ ኚሚመራው ዚግንቊት7 ዚፍትህ ዚነጻነትና ዚዲሞክራሲ ንቅናቄ ጋር ግንኙነት እንዳለው ጥያቄ ቢቀርብለትም አስተያዚት ኚመስጠት ተቆጥቧል።

ኚቀጣዩ ዚኢህአዎግ ጉባዔ ምርጫ አዳዲስ አመራሮቜ አይጠበቁም ተባለ


ኢሳት ዜና:-ዚኢህአዎግ ጉባዔ በዚካቲት ወር በመቀሌ ኹተማ ዚግንባሩን አመራር ይመርጣል ተብሎ ዹሚጠበቅ ቢሆንም ምርጫው ግን
ብዙም አዳዲሰ ለውጊቜ እንደማይኖሩት ለድርጅቱ ቅርበት ያላ቞ው ሰዎቜ ገለጡ
በግንባሩ ሕገደንብ መሰሚት ኚሁለት እስኚ ሁለት ዓመት ተኩል ባለው ጊዜ ውስጥ ዚሚካሄደው ይኾው ጉባዔ በዚካቲት
ወር 2005 ሲካሄድ ግንባሩን ለቀጣይ ሁለት ዓመት ዚሚያገለግሉ አመራሮቜን ይመርጣል፡፡
በዚሁ መሰሚት ዚግንባሩ አባል ድርጅቶቜ እስኚቀጣዩ ወር ዚራሳ቞ውን ጉባዔ በማካሄድ ለኢህአዎግ ሥራ አስፈጻሚነት ዚሚያገለግሉ
እያንዳንዳ቞ው ዘጠኝ አባላትን ዚሚመርጡ ሲሆን እነዚህ በጠቅላላው 36 አባላት ዚግንባሩ ሥራ አስፈጻሚ በመሆን
ኚመካኚላ቞ው ዚግንባሩን ሊቀመንበር፣ምክትል ሊቀመንበር ምርጫ በጉባዔው ላይ ያኚናወናሉ፡፡
ይህ ጉባዔ ኚአቶ መለስ ሞት በኃላ በቅርቡ ዚተሟሙትን ዚግንባሩን ሊቀመንበር አቶ ኃይለማርም ደሳለኝ እና ምክትላ቞ውን አቶ ደመቀ መኮንን ያነሳል ተብሎ እንደማይገመት ታውቋል፡፡
በሕመም ምክንያት ሚዥም ዹሕክምና ክትትል ላይ ዚሚገኙት ዚአህዎድ ሊቀመንበር አቶ አለማዹሁ አቶምሳ በምክትላ቞ው
አቶ ሙክታር ኚድር ይተካሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
አቶ አለማዹሁ ቀደም ሲልም መልቀቂያ ኚማቅሚባ቞ው ጋር ተያይዞ በቅርቡ በተካሄደው ዚሶስት ምክትል ጠ/ሚኒስትሮቜ ሹመት ውስጥ ኊህዎድን መወኹል ዚሚገባ቞ው እሳ቞ው ዚነበሩ ቢሆንም ምክትላ቞ው አቶ ሙክታር እንዲሟሙ ኊህዎድ በወኹላቾው መሰሚት አቶ ኃይለማርያም ካቢኔ ውስጥ መካተታ቞ው ይታወሳል፡፡
በተያያዘ ዜና በቅርቡ ዚተካሄደው ሹመት ብዙም ያላስደሰታ቞ው ዚህወሃት አባላት ዚቀድሞ ዚጀና ጥበቃ ሚኒስትር
ዚነበሩትን አቶ ቎ዎድሮስ አድሃኖምን ወደ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነት እንዲዛወሩ ያደሚጉት ኚሁለት ዓመት በኃላ
ዹጠ/ሚኒስትርነትን ቊታ እንዲይዙ ታቅዶ ሊሆን ይቜላል ዹሚሉ አስተያዚቶቜ አሉ።
ዚአቶ መለስ ሞት ኹማንም በላይ ህወሃቶቜን ያደናገጠና ሁኔታውንም ተኚትሎ ዚተሰጡ ሹመቶቜ ነባር ዚሚባሉ ኹፍተኛ
ዚህወሃት አመራሮቜን ጭምር እንዳላሚካ ዚሚጠቅሱት ዚቅርብ ሰዎቜ፣  á‰µáˆá‰ ዚህወሃቶቜ ስጋት ኚእጃ቞ው ዚወጣውን ስልጣን መቌ
መልሰው እንደሚያገኙት እርግጠኛ መሆን አለመቻላ቞ውና ብዙዎቹ አመራሮቜ ኹፍተኛ ሃብት ኚማፍራታ቞ው ጋር ተያይዞ
ስጋት ላይ በመውደቃቾው ነው ተብሎአል፡፡
ይህ ጉዳይ በህወሃቶቜ በሚስጢር ተመክሮበት አቶ ቎ዎድሮስ ኹጠ/ሚኒስትር ኃይለማርም ጋር በቅርበት መስራት በሚያስቜላ቞ው ቊታ በማስጠጋት በ2007 ዓ.ም አገራዊ ምርጫን ተኚትሎ በሚደሹገው ዹጠ/ሚኒስትር ሹመት ብቁ ማድሚግ ዹሚለው ዕቅዳ቞ው በፓርቲያ቞ው ተቀባይነት አግኝቶ መተግበሩን አስሚድተዋል፡፡
እንደ ህወሃቶቜ ዕቅድ ኹሆነ አቶ ኃይለማርያም ኚሁለት ዓመት ስልጣን በኃላ መሰናበታ቞ው ግድ ይሆናል፡፡ ይሁን እንጅ  á‹­áˆ… ዚተባለው ዕቅድ መኖርና አለመኖሩን ኹገለልተኛ ወገን ማሚጋገጥ አልተቻለም።
ኢህአዎግ ባስቀመጠው ዚመተካካት ዕቅድ መሰሚት ዚብአዎን ጎምቱ ዚተባሉ አመራሮቜ በአዲስ መተካት ሚኖርባ቞ው á‰¢áˆ†áŠ•áˆ እስካሁን ባለው መሹጃ መሰሚት እንደ እነአቶ በሚኚት ስምኊን ዚመሳሰሉ ነባር አመራሮቜ ኚፓርቲው ስራ áŠ áˆµáˆáŒ»áˆš ስለመነሳታ቞ው ጉዳይ ምንም ዓይነት ፍንጭ አለመኖሩን ጠቁሟል።

መንግስት ዹኩጋዮን ነጻ አውጭ ግንባር አንድ አንጃ ኚመንግስት ጋር ለመደራደር አዲስ አበባ ገባ በማለት ዹገለጾውን ግንባሩ አስተባባለ


ኢሳት ዜና:-ኚኢትዮጵያ መንግስት ጋር መደራደር እፈልጋለሁ ህገመንግስቱንም ተቀብያለሁ ሲል በኢትዮጵያ ቎ሌቭዥን መግለጫ ዹሰጠው ግለሰብ ኚድርጅቱ ዚተባሚሚ ተራ አባል መሆኑን ዹኩጋዮን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር አስታወቀ::
ዚኢትዮጵያ መንግስት ኚኊብነግ አንድ አንጃ ጋር መደራደሩን ቢያስታውቅም ኊብነግ ሀሰት ነው ሲል አስተባብሎል: በኊብነግ ውስጥም ዹተፈጠሹ  አንዳቜ አንጃ አለመኖሩን ገልጧል::
ዹኩጋዮን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር ኹፍተኛ አመራር አቶ ሀሰን አብዱላሂ ለኢሳት በሰጡት  መግለጫ አብዲኑር አብድላሂ ፋራህ በኬኒያ ዚድርጅቱ ዹውጭ ግንኙነት ተራ አባል ሆነው ሲሰሩ እንደነበር አመልክተው ዚድርጅቱ ዚስለላ ቡድን ኚኢትዮጵያ መንግስት ጋር ግንኙነት እንዳላ቞ው ስለደሚሰበት በዚ ተገምግመው ኊክቶበር 14 ኚድርጅቱ ዚተባሚሩ መሆናቾውን ገልጠዋል::
ይሄ ዚኢትዮጵያ መንግስት ድርጊት ለኛ አዲስ አይደለም ያሉት አቶ ሀሰን ኹዚ በፊት ኚኊብነግ ጋር በሞራተን ሆቮል ፊርማ መፈራሚማ቞ውን በማስታወስ ኚግለሰብ ጋር ዚተፈራሚሙት ፊርማ ያመጣው ለውጥም ውጀትም እንደሌለ ተናግሹዋል::
ዹኩጋዮን ነጾ አውጪ ግንባር በ 64 አገሮቜ ዚሚንቀሳቀስ ትልቅ ድርጅት ነው ያሉት አቶ ሀሰን በአሁኑ ሰአት በፖለቲካ አንጻር በኹፍተኛ ሁኔታ ዚተጠናኚሚበት ፡ በውጊያ አውደ ግንባርም በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ዚመንግስት ወታደሮቜ በዹጊዜው እጃ቞ውን እዚሰጡ ያሉበት ደሹጃ ላይ እንደሚገኙ ገልጾዋል::
አንጃና መኹፋፈል ዚሚባለው ዚኢትዮጵያ መንግስት ምኞትና ው቞ት ነው ብለዋል አቶ ሀሰን አብዱልላሂ

በህውሀት ዚብ቞ኝነት እዝ ዚሚመራው ዚኢትዮጵያ ሰራዊት ለዎሞክራሲና ለፍትህ ኹሚደሹጉ ህዝባዊ ትግሎቜ ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ ቀሹበ


ኢሳት ዜና:-ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዚጋራ ትግል ሾንጎ ዚትግል አቅጣጫውንና ዚኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ባወጣው መግለጫ እንዳመለኚተው ዚኢትዮጵያ መኚላኚያ ሰራዊትና ዚደህንነት ሀይሎቜ ለመንግስት ህዝብን ዹመጹቆኛ መሳሪያ መሆናቾውን አቁመው ኚህዝብ ጎን እንዲቆሙ ጥሪውን አስተላልፎል::
ህውሀት ኢህአዎግ በህዝባቜን ላይ ዚሚያደርሰው በደልና ግፍ ሊያበቃ ይገባል ያለው ዹሾንጎ መግለጫ በእስር ላይ ያሉት ዚፖለቲካና ዹህሊና እስሚኞቜ ባስ቞ኮይ እንዲፈቱም መንግስትን አሳስቊል::
አፋኝ ዹሆኑ ዚሚዲያና ዚሜብርተኝነት ህጎቜ በሙሉ እንዲሰሚዙ ያሳሰበው ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዚጋራ ትግል ሾንጎ ዚመንግስት ሚዲያዎቜ ለምርጫ ግዜ ብቻ ለፕሮፓጋንዳ ሲባል ዚሚሰጥ ሜርፍራፊ ሰአት ቆሞ በመደበኛነት ዹተቃዋሚ ፓርቲዎቜ ዚሚሳተፉበት እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል\::
ዚዲፕሎማቲክ ዚበላይነት በአንድ ወይም በሁለት ድርጅት ትግል እንደማይገኝ ያመለኚተው ዹሾንጎ መግለጫ ለዘለቄታ ዲፕሎማሲያዊ ዚበላይነት ለመብቃት ጠቃሚ ስትራ቎ጂዎቜን በመቀዚስ ኚሌሎቜ ሀይሎቜ ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አመልክቶል::

አዲስ ራዕይ ዹተሰኘ መጜሄት በሁሉም ዚመንግስት መ/ቀት ሰራተኞቜ ዘንድ በግዳጅ እዚተሞጠ ነው


ኢሳት ዜና:-በሞቹ ዚቀድሞ ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ዚስራ ታሪክ ዙሪያ ዚሚያጠነጥን አዲስ ራዕይ ዹተሰኘ መጜሄት በሁሉም ዚመንግስት መ/ቀት ሰራተኞቜ ዘንድ በግዳጅ በ 100 ብር እዚተሞጠ መሆኑ ተገለጾ::
ኹሀገር ቀት ዚኢሳት ምንጮቜ እንደገለጡት በጠ/ሚሩ ህይወት ዙሪያ ዚሚያጠነጥነውን አዲስ ራዕይ ዹተሰኘ መጜሄት ኹ 2000 ብር በላይ ደሞዝተኛ ዹሆነ በአንድ ክፍያ 100 ብር ለመግዛት ይገደዳል ኹ2000 ብር በታቜ ደመወዝ ያለው እንደደሞዙ ልክ በዚወሩ ይቆሚጥበታል::
ዚተለያዩ ዚመንግስት መስሪያ ቀት ሰራተኞቜ በስብሰባ ተነግሮ቞ውና ሳያቁ እንዲፈርሙ ተደርጎ ኹደመወዛቾው ለአዲስ ራዕይ መጜሄት 100 ብር መወሰዱን ቢቃወሙም ሰሚ እንዳላገኙ አስታውቀዋል::
ዚቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በህይወት ዘመናቾው ዚሰሩትን ስራ አጉልቶና አኩርቶ ይተርካል በተባለው መጜሄት ዚግዢ  ድርድር ዚሚባል ነገር ዹለም ሁሉም ሰራተኛ በአንድ መቶ ብር ዚመግዛት ግዎታ እንዳለበት በግልጜ ተነግሮል እንደ ምንጮቻቜን ዘገባ::

አቶ በሚኚት ስምአን ተጜእኖ቞ው አዹቀነሰ ዚህዋሃት ጡንቻ አዹፈሹጠመ መምጣቱ ተገለፀ


ኢሳት ዜና:-ዚቀድሞው ጠቅላይ ሚንስተር መለሰ  ዜናዊ ማለፋቾውን ተኚትሎ በኢትዮጵያ ፖለትካ መድሚኚ ውስጥ  ሚናቾው ጎልቶ ዹነበሹው አቶ በሚኚት ስምአን ተጜእኖ቞ው አዹቀነሰ ዚህዋሃት ጡንቻ አዹፈሹጠመ መምጣቱ ተገለጾ::
ዹአሹና ትግራይ አመራር አባል ዚሆኑት አቶ አስራት አብርሃም ዚውስጥ ምንጮቜን ጠቅሰው ባሰራጩት ጹሁፍ አንዳመለኚቱት አቶ በሚኚት ስለ ኀርትራ ዚስጡት መግለጫ  ህዋሃትን አሰተባብሮባ቞ዋል::
አቶ በሚኚት ስምኊን ዚኀርትራ ተቃዋሚዎቜ ፖልቶክ መድሚክ ላይ ባድሜ ዚኀርትራ ነው በማለት መናገራ቞ው  እና ኀርትራዊያን ኹሃገር አንዲባሚሩ ያደሚጉት አቶ ስዚ አብርሃም ናቾው ሲሉ መደመጣ቞ው ዚህዋሃት ሰዎቜ በአቶ በሚኚት ላይ አንዲነሱ ምክናዚት መሆኑም ተመልክቷል::
አቶ በሚኚት ኀርትራዊያን ኹሃገር አንዳይባሚሩ እርሳ቞ውና አቶ መለስ መሞኚራ቞ውን ሆኖም አቶ ተወልደ ወ/ማሚያም : አቶ ስዚአብርሃና  አቶ ገብሩ አስራት ዚማባሚሩ ሂደት ዋነኞቹ ተዋናዮቜ መሆናቾውን መስክሚዋል::
አቶ በሚኚት በዚህ ሚገድ ዚሰጡት መግለጫ ዚህዋሃትን ሰዎቜ በማስቆጣቱ ሚናቾው እዚተገደበ ፡ተጜኑዋ቞ው እዚቀነሰ መምጣቱን በዚህም ዚአቶ ሰብሃት ነጋ ቡድን እንዲያንሰራራ እድል መፍጠሩን ኚጹሁፉ መሚዳት ተቜሏል::

Dec 24, 2012

Ethiopia 2012: Human Rights and Government Wrongs By Alemayehu G Mariam

Groundhog Year
In December 2008, I wrote a weekly commentary lamenting the fact that 2008 was "Groundhog Year” in Ethiopia:
It was a repetition of 2007, 2006, 2005, 2004... Everyday millions of Ethiopians woke up only to find themselves trapped in a time loop where their lives replayed like a broken record. Each "new" day is the same as the one before it: Repression, intimidation, corruption, incarceration, deception, brutalization and human rights violation… They have no idea how to get out of this awful cycle of misery, agony, despair and tribulation.
So, they pray and pray and pray and pray... for deliverance from Evil!
It is December 2012. Are Ethiopians better off today than they were in 2008, 2009, 2010, 2011? 
Does bread (teff) cost more today than it did in 2008…, a year ago? Cooking oil, produce, basic staples, beef, poultry, housing, water, electricity, household fuel, gasoline...?
Are there more poor people in Ethiopia today than there were in 2008? More hunger, homelessness, unemployment, less health care, fewer educational opportunities for young people?
Is there more corruption and secrecy and less transparency and accountability in December 2012 than in December 2008?
Are elections more free and fair in 2012 than in 2008?
Are there more political prisoners today than in 2008?
Is there less press freedom and are more journalists in prison today than in 2008?  
Is Ethiopia more dependent on international handouts for its daily bread today than it was in 2008?
Is there more environmental pollution, habitat destruction, forced human displacement and land grabbing in Ethiopia today than 2008?
Is Ethiopia today still at the very bottom of the U.N. Human Development Index?
The Evidence on Government Wrongs in Ethiopia in 2012
Human rights violations in Ethiopia continue to draw sharp and sustained condemnation from all of the major international human rights organizations and other legal bodies. In 2012, the ruling regime in that country has become intensely repressive and arrogantly intolerant of all dissent and opposition. The regime continues to trash its own Constitution, sneer at its international legal obligations and thumb its nose at its critics. Though some incorrigible optimists hoped a post-Meles regime would open up the political space, reach out to opposition elements and at least engage in human rights window dressing, the nauseating litany of those who are falling head over heels to fit into Meles’ shoes has been “there will be no change. We will (blindly) follow Meles’ vision…” In other words, 2013, 2014, 2015… will be no better than 2012 or 2008.
The evidence of sustained and massive official human rights violations in Ethiopia is overwhelming and irrefutable. Let the evidence speak for itself. 
The U.S. State Department Country Reports on Human Rights Practices in Ethiopia (May 2012) concluded:
The most significant human rights problems [in Ethiopia] included the government’s arrest of more than 100 opposition political figures, activists, journalists, and bloggers… The government restricted freedom of the press, and fear of harassment and arrest led journalists to practice self-censorship. The Charities and Societies Proclamation (CSO law) continued to impose severe restrictions on civil society and nongovernmental organization (NGO) activities… Other human rights problems included torture, beating, abuse, and mistreatment of detainees by security forces; harsh and at times life-threatening prison conditions; arbitrary arrest and detention; detention without charge and lengthy pretrial detention; infringement on citizens’ privacy rights, including illegal searches; allegations of abuses in connection with the continued low-level conflict in parts of the Somali region; restrictions on freedom of assembly, association, and movement; police, administrative, and judicial corruption…
Ethiopian authorities continued to severely restrict basic rights of freedom of expression, association, and assembly. Hundreds of Ethiopians in 2011 were arbitrarily arrested and detained and remain at risk of torture and ill-treatment. Attacks on political opposition and dissent persisted throughout 2011, with mass arrests of ethnic Oromo, including members of the Oromo political opposition in March, and a wider crackdown with arrests of journalists and opposition politicians from June to September 2011. The restrictive Anti-Terrorism Proclamation (adopted in 2009) has been used to justify arrests of both journalists and members of the political opposition…
Freedom House concluded:
Ethiopia is ranked Not Free in Freedom in the World 2012, with a score of 6 for both political rights and civil liberties.  Political life in Ethiopia is dominated by the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), which was led by Prime Minister Meles Zenawi from 1995 until his death in August 2012. May 2011 federal and regional elections were tightly controlled by the EPRDF; voters were threatened if they did not support the ruling party, and opposition meetings were broken up while leaders were threatened or detained.  The EPRDF routinely utilizes the country’s anti-terrorism laws to target opposition leaders and the media.  Parliament has declared much of the opposition to be terrorist groups and has targeted journalists who cover any opposition activity.  Media is dominated by state-owned broadcasters and government-oriented newspapers.  A 2009 law greatly restricts NGO activity in the country by prohibiting work in the area of human and political rights and limiting the amount of international funding any organization may receive.  This law has neutered the NGO sector in the country.  The judiciary is independent in name only, with judgments that rarely deviate from government policy.
Amnesty International urged that the “government of Ethiopia should see the succession of Meles as an opportunity to break with the past and end the practice of arresting anyone and everyone who criticizes the government.”
A group of U.N. Special Rapporteurs (an independent group of investigating experts authorized by the United Nations Human Rights Council) in 2012 issued public statements condemning the ruling regime for its indiscriminate use of the so-called anti-terrorism law to suppress a broad range of freedoms and for flagrantly perpetuating and sanctioning human rights violations.  
Maina Kiai, the U.N. Special Rapporteur on the rights to freedom of peaceful assembly and of association, concluded, “The resort to anti-terrorism legislation is one of the many obstacles faced by associations today in Ethiopia. The Government must ensure protection across all areas involving the work of associations, especially in relation to human rights issues.”
Ben Emmerson, the U.N. Special Rapporteur on counter-terrorism and human rights warned that “the anti-terrorism provisions should not be abused and need to be clearly defined in Ethiopian criminal law to ensure that they do not go counter to internationally guaranteed human rights.”
Frank La Rue, the U.N. Special Rapporteur on freedom of expression stated that “Journalists play a crucial role in promoting accountability of public officials by investigating and informing the public about human rights violations. They should not face criminal proceedings for carrying out their legitimate work, let alone be severely punished.”
Margaret Sekaggya, the U.N. Special Rapporteur on human rights defenders criticized that “journalists, bloggers and others advocating for increased respect for human rights should not be subject to pressure for the mere fact that their views are not in alignment with those of the Government [of Ethiopia].”
Gabriela Knaul, the U.N. Special Rapporteur on the independence of judges and lawyers argued that  “Defendants in a criminal process should be considered as innocent until proven guilty as enshrined in the Constitution of Ethiopia… And it is crucial that defendants have access to a lawyer during the pre-trial stage to safeguard their right to prepare their legal defence.”
On December 18, 2012, 16 members of the European Parliament issued a public letter to Prime Minister Hailemariam Desalegn “expressing grave concern over the continued detention of journalist and blogger Eskinder Nega”. In the letter, the members reminded Desalegn to comply with his “government’s obligation to respect the right to freedom of expression as established under customary international law and codified in Article 19 of the International Covenant on Civil and Political Rights, to which Ethiopia is a party.”
The Regime Must Cease and Desist All Unlawful Interference in the Exercise of Religious Freedom
Article 11 of the Ethiopian Constitution  mandates “separation of state and religion” to ensure that the “Ethiopian State is a secular state” and that “no state religion” is established. Article 27 prohibits “coercion by force or any other means, which would impair his freedom to have or to adopt a religion or belief of his choice.”
Despite clear legal obligations to respect the religious liberties of citizens, the ruling regime in Ethiopia has played fast and loose with the rights of Muslim citizens to select their own religious and spiritual leaders. According to the U.S. Commission on International Religious Freedom, an independent body constituted by the Congress and the President of the United States to monitor religious freedom worldwide:
Since July 2011, the Ethiopian government has sought to impose the al-Ahbash Islamic sect on the country’s Muslim community, a community that traditionally has practiced the Sufi form of Islam.   The government also has manipulated the election of the new leaders of the Ethiopia Islamic Affairs Supreme Council (EIASC).  Previously viewed as an independent body, EIASC is now viewed as a government-controlled institution.  The arrests, terrorism charges and takeover of EIASC signify a troubling escalation in the government’s attempts to control Ethiopia’s Muslim community and provide further evidence of a decline in religious freedom in Ethiopia. Muslims throughout Ethiopia have been arrested during peaceful protests: On October 29, the Ethiopia government charged 29 protestors with terrorism and attempting to establish an Islamic state.
The regime must conform its conduct to the requirements of its Constitution and international legal obligations and cease and desist interference in the free exercise of religion of Muslim citizens. All citizens unlawfully arrested and detained in connection with the peaceful protest of unlawful deprivation of religious liberty must be released forthwith.
All Political Prisoners Must be Released
The number of political prisoners has yet to be fully documented in Ethiopia today. While human rights organizations have focused on multiple dozens of high profile political prisoners, there are in fact tens of thousands of ordinary Ethiopians who are held in detention because of their beliefs, open opposition or refusal to support the ruling regime. All political prisoners must be released immediately.
In a broader sense, there are two types of political prisoners in Ethiopia today. There are prisoners of conscience  and prisoners-of-their-own-consciences. The prisoners of conscience are imprisoned because they are dissidents, opposition party leaders and journalists. They have done no legal or moral wrong. In fact, they have done what is morally and legally right. They have told the truth. They have spoken truth to power. They have stood up to injustice. They have defended freedom, democracy and human rights by paying the ultimate price with their lives and liberties. They can be set free by the stroke of the pen.
The prisoners-of-their-own-consciences became prisoners by committing crimes against humanity in the first degree with the lesser included offenses of the crimes of ignorance, arrogance and  petulance. These prisoners are numbed by the opiate of power. They live in fear and anxiety of being held accountable any given day. They dread the day the wrath of the people will be visited upon them. They know with certainty that they will one day be judged by the very scales they have used to judge others. 
The prisoners-in-their-own-conscience can free the prisoners of conscience and thereby free themselves. That is their only salvation. In the alternative, let them heed Gandhi’s dire warning: “There have been tyrants and murderers, and for a time they seem invincible, but in the end they always fall—think of it always.” 
Stop Repressing the Press
Napoleon Bonaparte said, “Four hostile newspapers are more to be feared than a thousand bayonets.” That rings true for the ruling regime in Ethiopia. Last week three imprisoned and one exiled Ethiopian journalists received the prestigious Hellman/Hammett Award for 2012 “in recognition of their efforts to promote free expression in Ethiopia, one of the world’s most restricted media environments”. The recipients included Eskinder Nega, an independent journalist and blogger and recipient of the 2012 PEN International freedom to Write Award;  Reeyot Alemu, one of the few Ethiopian female journalists associated with the officially shuttered weekly newspaper Feteh and recipient of the 2012 International Women’s Media Courage in Journalism Award; Woubshet Taye, editor of the officially shuttered weekly newspaper Awramba Times and Mesfin Negash of Addis Neger Online, another weekly officially shuttered before going online. The four were among a diverse group of 41 writers and journalists from 19 countries to receive the Hellman/Hammett Award.According to Human Rights Watch: 
The four jailed and exiled journalists exemplify the courage and dire situation of independent journalism in Ethiopia today. Their ordeals illustrate the price of speaking freely in a country where free speech is no longer tolerated.  The journalistic work and liberty of the four Ethiopian award-winners has been suppressed by the Ethiopian government in its efforts to restrict free speech and peaceful dissent, clamp down on independent media, and limit access to and use of the internet. They represent a much larger group of journalists in Ethiopia forced to self-censor, face prosecution, or flee the country.  
All dictators and tyrants in history have feared the enlightening powers of the independent press. Total control of the media remains the wicked obsession of all modern day dictators who believe that by controlling the flow of information, they can control the hearts and minds of their citizens.  But that is only wishful thinking. As Napoleon realized, “a journalist is a grumbler, a censurer, a giver of advice, a regent of sovereigns and a tutor of nations.” Like Napoleon, the greatest fear of the dictators in Ethiopia is the “tutoring” aspect of the press -- teaching, informing, enlightening and empowering the people with knowledge. They understand the power of the independent press to effectively countercheck their tyrannical rule and hold him accountable before the people. Like Napoleon, they have spared no effort to harass, jail, censor and muzzle journalists for criticizing and exposing their criminality, use of a vast network of spies to terrorize Ethiopian society, shining the light of truth on their military and policy failures, condemning their indiscriminate massacres of unarmed citizen protesters in the streets and for killing, jailing and persecuting their  political opponents. 
All imprisoned journalists must be released immediately.
“Those who make peaceful change impossible will make violent revolution inevitable.” JFK
Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino and is a practicing defense lawyer.

“ቅድሚያ ለእርቀ ሰላም!” (ዚሰንበት ትምህርት ቀቶቜ አንድነት ጉባኀ)




ለኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጜ/ቀት
አዲስ አበባ

ዚተኚበራቜሁ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አባቶቻቜን፣ በቅድሚያ ቡራኬያቜሁ ይድሚሰን። ቀተ ክርስቲያናቜን ለሁለት
አሥርት ዓመታት በፈተና ውስጥ እንድትቆይ ያደሚገውን ዚልዩነት ግድግዳ አፍርሶ አንድ ሲኖዶስ፣ አንድ
ፓትርያርክ፣ አንድ አስተዳደር እንዲኖራት ለማድሚግ ዹተጀመሹውን ዚእርቀ ሰላም ዓላማ በመደገፍ ልዑካንን
በመሰዹም ዚጀመራቜሁት ሂደት አስደስቶናል። ነገር ግን ዚእርቀ ሰላሙ ሂደት ሳይጠናቀቅ ወደ ፓትርያርክ ምርጫ
ጉዞ መጀመሩ በእጅጉ እንድናዝን አድርጎናል።
እንደሚታወቀው በአሁኑ ወቅት በሰንበት ት/ቀት ውስጥ ዹምንገኝ ወጣቶቜ አብዛኛው ዘመናቜንን ያሳለፍነው
ቀተክርስቲያናቜን በሁለት ሲኖዶስ ተኹፍላ ዚልዩነት፣ ዚውግዘት እና ዚመራራቅ ባዕድ ሥርዓቶቜን ስናስተናግድ
ነው። ይህም በሰንበት ት/ቀት ተሳትፎ ለቀተክርስቲያናቜን ዚሚገባውን አገልግሎት እንዳንሰጥ ትልቅ መሰናክል
ሆኖ ቆይቷል። ቢሆንም ጊዜው ደርሶ ዹተጀመሹው ዚእርቀ ሰላም ሂደት ትልቅ ተስፋ ሰጥቶን ነበር። ነገር ግን
በተቃራኒው እዚተኚናወነ ያለው ዚፓትርያርክ ምርጫ ጉዞ ዹተቀሹ ዘመናቜንን በተስፋ እና በበለጠ መነሳሳት
እንዳንጓዝ እያደሚገን ይገኛል።
በተለይም እኛ በሰሜን አሜሪካ ዹምንገኝ ዚሰንበት ት/ቀት ወጣቶቜ ዹምንገኘው ዚቀተክርስቲያን ልዩነት በእጅጉ
ገዝፎ በሚታይበት አኅጉር በመሆኑ ዚእርቀ ሰላሙ ሂደት መደናቀፍ ዚቀተክርስቲያናቜንን ቜግር ወደ ባሰ አዘቅት
ውስጥ እንደሚጚምሚው ለመገመት አያዳግተንም። በእርቀ ሰላም ጉባኀያቱ ምክንያትም ዹተጀመሹውን ወደ
አንድነት ዚመምጣቱን ዚተስፋ ጭላንጭልን አክስሞ ለሚቀጥሉት ዚማይታወቁ አያሌ ዘመናት ዚምእመናንን
አንገት ዚሚያስደፉ ሁኔታዎቜን ሊፈጥር እንደሚቜልም ግልጜ ነው።
ዚቀተ ክርስቲያን አንድነት ወደ ተሻለ ዚአገልግሎት ምዕራፍ አሞጋግሮን በልዩነት ምክንያት ያልተነኩ ዘርፈ ብዙ
ተልዕኮዎቜን ለመፈጾም እዚተሰናዳን ባለንበት ወቅት ኚእኛ አልፎ ለልጆቻቜን ዹምናወርሰው ዹመኹፋፈል እና
ዚመለያዚት ሥርዓትን በድጋሚ ዚምናስተናግድበት አቅም ለማግኘትም እን቞ገራለን።
ስለዚህ ፍጹም በሆነ ዚልጅነት መንፈስ ዹሚኹተለውን መልእክት ለማስተላለፍ እንወዳለን፦
1) ዹተጀመሹው ዚእርቀ ሰላም ሂደት ሳይጠናቀቅ ወደ ፓትርያርክ ምርጫ ጉዞ በመጀመሩ በእጅጉ አዝነናል።
ዚቀጣይ ዚአገልግሎት ዘመናቜንንም በተስፋ እንዳንጓዝ እንቅፋት ሆኖብናል። ስለዚህ ለተተኪ ልጆቻቜሁ ስትሉ
ዚእርቀ ሰላሙ ሂደት እንዲጠናቀቅ እንድታደርጉ በቅድስት ቀተክርስቲያን ስም እንጠይቃለን።
2) እንደ ቀደሙት አባቶቻቜን ለቀተክርስቲያን እና ለመንጋቜሁ ስትሉ ኚቀተ ክርስቲያን ውጭ ኹሆነ ተፅዕኖ
በጞዳ ሁኔታ መክራቜሁ ዚእርቀ ሰላሙን ሂደት ለውሳኔ እንድታበቁ እንማጞናለን።
3) ዹተፈጠሹው ዚአስተዳደር ልዩነት ተወግዶ ቀተ ክርስቲያንን ወደ አንድነት ሊያመጣ ዚሚቜል ጥንቃቄ
ዚተሞላበት ዚመፍትሄ ውሳኔ እንድትወስኑም አደራ እንላለን።
አምላካቜን እግዚአብሔር ዹተፈጠሹውን መለያዚት አስወግዶ እና ዚቀተ ክርስቲያን አንድነትን ወደ ቀድሞ ቊታው
መልሶ በአንድነት እንድናመሰግነው ያበቃን ዘንድ መልካም ፈቃዱ ይሁንልን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር።
ህዳር 13/2005 ዓ. ም
በሰሜን አሜሪካ አኅጉሹ ስብኚት ዚሰንበት ትምህርት ቀቶቜ አንድነት ጉባኀ
ሰሜን አሜሪካ
ግልባጭ:
ለመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜ/ቀት
ለሰሜን አሜሪካ አኅጉሹ ስብኚት
ለሁሉም ሊቃነ ጳጳሳት በያሉበት ፣
ለኢትዮጵያ ዚሰንበት ት/ቀቶቜ ኅብሚት ፣
ለአዲስ አበባ ሀገሹ ስብኚት ዚሰንበት ት/ቀቶቜ ኅብሚት ፣
በካናዳ፣ በአፍሪካና አና በአውሮፓ ለሚገኙ ሰንበት ት/ቀቶቜ ፣
ለሰላም እና አንድነት ጉባኀ፣
ለመገናኛ ብዙኃን በሙሉ።

Total Pageviews

Translate