Pages

Dec 29, 2013

Egypt’s Minister of Water Resources says Ethiopia”s new dam on Lake Tana won”t affect water influx to Egypt

Arab News
CAIRO, Dec 28 (KUNA) — Egypt’s Minister of Water Resources and Irrigation Mohammed Abdel-Moteleb downplayed the effect of a new dam which Ethiopia plans to establish on Lake Tana.
In statements to the state news agency (MENA), Abdel-Moteleb asserted that the new dam will not impact the influx of water of Nasser Lake in South Egypt.
Egypt’s technical studies have showed that the project will not affect the water flow to Nasser Lake, the minister said.
He pointed that the dam for irrigation and drinking water purposes, adding that the project design was studied thoroughly by a French consultancy firm in 1998. The dam will provide 250 million cubic meter of water per year for an Ethiopian agricultural project to be set up on an area of 336 million square meters. (end) asm.ibi KUNA 282340 Dec 13NNNN
millenniumdam-1024x713
Source:Arab News
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the Authors.

Dec 28, 2013

እባካችሁ የሜንጫ ማንነት ይፋቅልኝ!!!!!!!!!!!! (ያሬድ ኤልያስ)

እባካችሁ የሜንጫ ማንነት ይፋቅልኝ የፖለቲካል ተንታኝ ምናምን ቴዲ ኣፍሮ በደሌ ጥቁር ሰው የኢትዮዽያ ቇንቇ አማርኝ ብቻ አይደለም  በኢትዮዽያ ሙስሊምና በኦሮሞ ህዝብ ትግል መካከል አብረዉ መሄድይችላሉ...........................................
 እንዴ ምን እየተካሄደ ነው ??

ሼም በአገረ ኢትዮዽያ ቀረ እንዴ በሜንጫ ነዉ የምንለዉ ያለውን ዝም ባልን እንደገና ዛሬም

በመጀመሪያ የሜንጫ ማንነት እራሱ ይፋቅ ማን ነው ማንን ነው የሚወክለው ????

ህወሃት ልዩነቶቻችንን አብዝቶና አርብቶ ክብራችንን አዋርዶ ረግጦ ሊገዛን ዘመኑን ሙሉ ሠርቷል። ለብዙ ግዜም አንዱን ህዝብ የአንዱ ጠላት አድርጎ ሲሰብክ ኑሯል። ይህንንም እውነት ለማስመሰል በበደኖ ፤በአርባ ጉጉ፤ በሃረርጌና በሌሎች ሥፍራዎች የብዙ ንጹሃን ዜጎችን ደም አፍስሶ ለርካሽ ፖለቲካ ፍጆታ አውሎታል። በደኖ ላይ አፈር ገፍቶ ይኖር የነበረ አማራ የተባለ ዘር የተጨፈጨፈው በህወሃት ፊታውራሪነት ነው። በአርባ ጉጉ ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ሰቆቃ አዛዥና አስፈጻሚው በመለስ ዜናዊ የሚመራው ህወሃት መሆኑን የምንዘነጋው ጉዳይ አይደለም። ልዩነታችን ውበታችን ሊሆን ሲገባው መጠቂያችን ሁኖ ጎድቶናል። በመለያየታችን ምክንያት ብዙሃኑ ለነጻነታቸው የሚያደርጉት ትግል ተዳከመ እንጂ አልጎለበተም። ጥቂቶች ብዙሃኑን ለመጨቆን አቅም አገኙ እንጂ አደብ አልገዙም። ተራርቀን በመቆማችን መለስ ዜናዊና ቡድኑ በክፍተቱ ተጠቀሙ እንጂ ነጻነት የተነፈገው ብዙሃኑ ያገኘው አንዳች በጎ ነገር የለም።

የመለስ ዜናዊና ቡድኑ ብርቱ ፍላጎት ኢትዮጵያዊያኖች የታሪክ እሰረኛ ሆነን ልዩነታችንን ማጥበብ ተስኖን ተከፋፍለን ተዳክመንና ተስፋ ቆርጠን እንድንኖር ነው።ይህን መፍቀድ ደግሞ ውረደት ነው።

በአገራችን ታሪክ ውስጥ በማወቅም ባለማወቅም ብዙ በጎ ያልሆኑ ነግሮች መፈጸማቸው እውነት ነው።ብዙሃኑ በጥቂቶች ተረግጠውና ተጨቁነው መከራቸው በዝቶ ዘመኑን ማሳለፋቸውም የሚካድ አይደለም።ጥንት ስህተት ተፈጽሟል። በዚህ ልዩነት የለንም። ብዙዎቻችን እንስማማለን።ልዩነታችን የሚሰፋው ያን ክፉ ስህተት መልሰን እንደግመዋለን በሚሉና ከስህተቱ ተምረን አንዲት ጠናካራ አገርን እንመስርት በሚባልበት ግዜ ነው።

ህወሃትን የመሰለ ዘረኛና ዘራፊ ቡድን በራሳችን ላይ ተጭኖ እርሱን በአንድነት ሆነን ከመታገል ፈንታ “እንዲያና እንዲህ” ሁነን ነበር እያሉ ማላዘን ጥቅም የለውም። ጥቅም አለው ከተባለም የሚጠቅመው ህወሃትን እንጂ ነጻነቱን ተነፍጎ የኖረውን ህዝብ አይደለም። ነጻነትን ለመቀዳጀት የፈለገ እርሱ የጠላት ጆሮ እየሰማ አይኑም እያየ እጅ ለእጅ ተያይዞ ጠላትን ለመፋለም መዘጋጀት አለበት። አዎን አማራጫችን አንድ ሆነን ህያው የሆነውን ጠላታችንን መታገል ነው። አንድ ሆነን አንታገለም ማለት ጠላት ህዝባችንን እስከ ልጅ ልጆቻችን እንደጨቆነ ይዝለቅ ከማለት ውጪ ሌላ ትርጉም ሊሰጠው አይችልም።


በአጠቃላይ አነጋገር ሜንጫ ( jawar mohammed) ዘረኛ፤ ውሸታምና ዘራፊ የሆነ ግለሰብ ነው ከህወሃት ከቀደሙት ወያኔ ዘረኛ ወንበዴ የሚሻልበት በጎ ነገር ሳይኖረው ይሻላል ብሎ መደገፍ አሳፋሪ ነው
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

Dec 26, 2013

ሕይወትም የሚጀምረው ራስን ከመሆን ነው – ሰው ራሱን ሲያክል ሌላ ብዙ ነገር ማድረግ ይቻለዋል” ቴዎድሮስ ካሣሁንን

“ሕይወትም የሚጀምረው ራስን ከመሆን ነው – ሰው ራሱን ሲያክል ሌላ ብዙ ነገር ማድረግ ይቻለዋል” ቴዎድሮስ ካሣሁንን


” ቅንነት ከሌለ ጥሩ ነገር ማየት እንደማይቻል አውቆ። ታሪኩንም በቅንነት ስሜት መመርመር ይኖርበታል። የባለታሪክ ሰዎችን ጥሩ ነገር መውሰድና ጥሩ ያልሆነ ነገራቸውን ደግሞ እንዳይደገም ለማረም መትጋት ከኛ ከወጣቱች ይጠበቃል። ትልቁና ቁልፍ ነገር የማንነትን መ...ሠረታዊ ጥያቄ ከመገንዘብ ይመነጫል። ሕይወትም የሚጀምረው ራስን ከመሆን ነው። ሰው ራሱን ሲያክል ሌላ ብዙ ነገር ማድረግ ይቻለዋል።… ስለዚህ የነገር ሁ ምንጭ ፍቅር ስለሆነ ከፍቅር የሚጀምረውን ህይወት በፍቅር ለመጨረስ ቅንነት ያስፈልጋል። አመጣጡን ያዬ አካሄዱን ያዉቃልው ምክኒያቱም ታሪኩን እየዞረ የማያይ ተጋዥ የኋላ መመልከቻ መስታወት የሌለው መኪናን ይመስላልና “
--------------------------------------------------------------------------
(እንቁ መጽሔት) ተወዳጁን ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሣሁንን በዚህ የመጽሔታችን ልዩ ዕትም፤ የዳግማዊ ዐፄ ምኒልክን 100ኛ የሙት ዓመት… በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለመከበሩን ጉዳይ በተመለከተ ጥያቄዎች አቅርበንለታል። ቴዲም በምላሹ “በማንኛውም ሁኔታ ጥሩ የሠራን ሰው ማመስገን፣ ማክበር ጠቃሚ ባህል መሆኑን ተረድተን፤ በዚህ በኩል እስከዛሬ ያለውን ስሕተት ማረም አለብን” ብሏል። ሌሎች መሰል ሐሰብ አስተያቶችንም ሰንዝሯል። ሁሉንም ከቃለ-ምልልሱ ዝርዝር ይዘት ያገኙታል። መልካም ቆይታ!
ዕንቁ፡- የዳግማዊ ዐፄ ምንሊክ 100ኛ የሙት ዓመት በብሔራዊ ደረጃ አለመከበሩን እንዴት አየኸው?
ቴድዎሮስ፡- በቅድሚያ ከአከባበሩ አግባብነት ተነስተን ለይተን ልናስቀምጠው የሚገባ ነጥብ መኖር አለበት። ይከበራል የሚባለው ቀን የሞቱበት ይሁን፤ ሥርዓተ ቀብራቸው የተፈጸመበት ወይስ ምኒሊክ በሠሯቸው አገራዊ ቁም ነገሮች ላይ ያአተኮረ ይሁን የሚለው ሀሳብ እራሱን የቻለ ውይይት የሚፈልግ ነው። እንዲህም ሆኖ ግን በግሌ የምኒልክ ማንነትም ይሁን ለኢትዮጵያ ያበረከቱት አስተዋፅኦ በብሔራዊ ደረጃ አለመከበሩ ያሳስበኛል።
ዕንቁ፡- በአንተ ግንዛቤ ከኢትዮጵያ ባሻገር ባለው ዓለም ብሔራዊ ኩራት የሆኑ ሰዎች ስለምንድነው የሚታሰቡት? አያይዘህም ምኒልክን በማክበር ሊገኝ ይችላል ብለህ የምታምንበትን ብሔራዊ ጥቅም ብትገልጽልን?
ቴድዎሮስ፡- ግለሰቦች እንዲታወሱ የሚደረግበትም ምክንያት፤ መሻሻልና መደገም ያለባቸው ጥሩ ታሪኮች ወደ አዲሱ ትውልድ እንዲሸጋገሩ ስለሚፈለግ ነው። እነዛ ብሔራዊ ኩራት መሆን የቻሉ ሰዎች ሲታሰቡ ወይም የመልካም ስምና ተግባራቸው ማስታወሻ ዝግጅት ተደርጎ ክብራቸው እንዲገለጥ ሲደረግ፤ ሌሎች መልካም የሚሠሩ ሰዎችን ማፍራት የሚያስችል መነሣሣትን ይፈጥራል። በመሆኑም ነው ክብረ በዓሎች በታላላቅ ግለሰቦች ስም እየተሰየሙ፣ የእነሱም መልካምነት እየታሰበ የሚወሱበት አንድ ብሔራዊ ዝግጅት የሚከናወንበት ሥርዓት የሚያስፈልገው።
images (2)
ዕንቁ፡- ዳግማዊ ምኒልክ ስለዛሬይቱ ኢትዮጵያ መፈጠር ሲሉ የገቡበትን ጦርነት እንዴት ነው የምትመለከተው?
ቴዎድሮስ፡- ምንጊዜም ሰዎች የሚበጃቸውን ነገር እስኪገነዘቡት ድረስ ያለመግባባቱ መጠን ይሰፋል። ያም ግጭት ሊፈጥር ይችላል። ይህም ደግሞ በእኛ ሀገር ሁኔታ ብቻ የተከሰተ ሳይሆን በተለያዩ የዓለም ሀገራት የሆነም ነው። እንዲህም ሆኖ ግን ለምሳሌ ምኒልክ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ዘምተው ንጉሥ ጦናን ማረኩ። ከማረኳቸውም በኋላ እግራቸውን እያጠቡ ‹‹የእኛ አንድ አለመሆን፣ ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት አለመመሥረታችን፤ የጋራ ለሚሆነው ጠላታችን ጥቃት አሳልፎ የሚሰጠን አደገኛ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። በዚህ ምክንያት ነው ወደ አንተ ጦር ያዘመትኩት እንጂ ሥልጣንህን ለመቀማትና በአንተ ላይ ለመግነን… ፈልጌ አይደለም። ማእከላዊ መንግሥታችንን ማጠናከሩ ግን ሁላችንንም የሚጠቅመን ነው። አገራችንን፣ በሕላችንን፣ ታሪካችንን፣ ቋንቋችንን ጠብቀንና ድንበራችንን አስከብረን ለመኖር ይረዳናል›› ነበር ያሏቸው።
ለምንጊዜውም ነገሮችን በቀና ማየትና የጎደለውን ሞልቶ፣ ያለውን ጥሩ ነገር እንዳለ ይዞ መሄዱ፤ ለተሻለ ሀገራዊ ርምጃ ጠቃሚ ነው ብዬ አምናለሁ። ይህን የመሰለው አካሄድ ደግሞ በሌሎች አገሮች አልተሠራበትም የሚል ቅንጣት ዕምነትም የለኝም። ወቅቱ በረዳቸው መጠን የነበረውን የአንድነት ክፍተት ሞልተውና አመጣጥነው ማእከላዊ መንግሥቱን ከነበረው የግንዛቤ ማነስ ሁሉ… ቀድመው፤ በተቻለ መጠን በትህትና ዝቅ ብለው እግር በማጠብ ጭምር የነበረውን መጥፎ ሁኔታ መልክ ለማስያዝ ደክመዋል። ዛሬ ያለው ኢትዮጰያዊም ከተለያየ የኢትዮጵያ ብሔሮች ምንጭ ፈልቆ ይኸው በአንድነት ‹‹ኢትዮጵያዊያን ነን›› ለማለት ችሏል። ስለዚህ የምኒልክ ስም ብሔራዊ አክብሮት ማግኘት የሚገባው፣ በሕልውናችንም ላይ ከፍተኛ የሆነ ሚና ያለው፣ የተባበታተነውን ሰብስበው ያቆዩ በመሆናቸው ነው።
ዕንቁ፡- “በዐፄ ምኒልክ ዘመነ-መንግሥት የተጀመሩት ሥልጣኔን የመከተል ጉዞዎች እንደጅምራቸው ቀጥለው ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ያደጉትን ሀገራት ጎራ ለመቀላቀል በቻለች ነበር” በማለት የሚቆጩ ወገኖች አሉ። አንተስ ምን ትላለህ?
ቴዎድሮስ፡- ያንን የሥልጣኔ ጅምር ከነበረው የኋላቀርነት ሁኔታ ጋር ሲመለከቱት ለመቀበል በጣም ከባድ ነበር። ለምሣሌ ‹‹ ስልክ ማነጋገር የሰይጣን ተግባር ነው…›› በማለት የተቃውሞ ሃሳባቸውን የሚሰነዝሩ ሰዎች ነበሩ። እንደዚህ ያለውን አመለካከት እና አስተሳሰብ አሸንፎ ለመሄድ ምኒልክ ብዙ ደክመዋል። ከዚህ ተነስተን የመሄዱ ጉዳይ በእሳቸው ተነሳሽነትና አስተማሪነት የተጀመረ ቢሆንም ቀዳማዊ ሀይለስላሴ በስልጣን ዘመናቸው ትምህርትን በማስፋፋት የተወሰነ ደረጃ ለማስኬድ መሞከራቸው የስልጣኔ ምንጩ ትምህርት መሆኑን ያገናዘበ ቀጣይ እርምጃ ነው ለማለት ያስደፍራል።
images (5)
ዕንቁ፡- አንዳንድ ኢትዮጵያውያን ባለታሪክ የሆኑ አርዓያዎቻቸውን ያለማክበራቸው ችግር ከምን የመነጨ ነው?
ቴዎድሮስ፡- የችግሩን ምንጭ አጠር አድርጎ ለመግለጽ ያስቸግራል። ነገር ግን ምንግዜም ቢሆን ለጥሩም ይሁን ለመጥፎው ድርጊት፤ መንግሥትም በመንግሥትነቱ፣ ሕዝቡም በሕዝብነቱ የየራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል። እንዲያም ሆኖ ለሀገርና ለወገን የሠራን ሰው ማክበር ጠቃሚ ባሕል ነው። ምንግዜም ቢሆን ጥሩ ተምሳሌት በማይኖረው ማኅበረሰብ ውስጥ ጥሩ የሚሰራ ዜጋ ለማፍራት አስቸጋሪ ነው። ስለዚህ በማንኛውም ሁኔታ ጥሩ የሠራን ሰው ማመስገን፣ ማክበር ጠቃሚ ባህል መሆኑን ተረድተን፤ በዚህ በኩል እስከዛሬ ያለውን ስሕተት ማረም አለብን። ጥሩን ነገር ማየትና ማክበር መቻል፤ ጥሩ ነገር በራስ ውስጥ እንዲሰርጽ መፍቀድ ማለት ስለሆነ፤ ከሞቱት ሰዎች ሕይወት ያለው ሥራቸዉን ወስዶ መራመድ የሚገባን ይመስለኛል።
ዕንቁ፡- እስቲ “ምኒልክ ተወልዶ…” ስለሚባልበት ምክንያት የሚሰማህን ግለጽልን?
ቴድዎሮስ፡- አዎ ‹‹ምኒልክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻ፣ ግብሩ ዕንቁላል ነበር ይህን ጊዜ አበሻ›› ተብሏል። ለእኔ ዕንቁላሉ የምዕራባውያንን ባሕልና ቋንቋ፣ በመውሰድ የራስን ባህል እና ማንነት ለማስጣል የተሞከረውን ሀሳብ ይወክላል።ዕንቁላሉ ውስጥ ተደብቆ የመጣው የተገዥነት አስኳል ሌላው ምስጢር ነው። የዚህ ጥቅስ ወርቁ በራሱ ባለብዙ ትርጉም ነው። ምኒልክ በራስ ቋንቋ፣ ባሕል፣ ፍልስፍና… የመመራት አስተሳሰብ እንዳይጠፋ ያደረጉትን አስተዋፆም ደርቦ ይገልፃል።
ዕንቁ፡- “የምኒልክ ታላቅነት መከበር የነበረበት በኢትዮጵያ ብቻ አልነበረም። በአፍሪካም ደረጃም ነው እንጂ” የሚሉ ወገኖች አሉ። ለዚህም አባባላቸው አስረጅ የሚያደረጉት የዓድዋን ድልና የፀረ-ቅኝ አገዛዝ ተጋድሎውን ነው። የአንተ እስተያየትስ?
ቴዎድሮስ፡- በስፋት እንደሚታወቀው የዓደዋ ድል፤ ለመላው አፍሪካውያን ወንድሞቻችን…. ነጻ መውጣት ታላቅ የሞራል ስንቅ መሆን የቻለ ነው። የኢትዮጵያ አርበኞች ትግል ጉልህ አስተዋጽኦ እንደነበረው የመሰከረ ነው። ነገር ግን ይህን ታሪክ አፍሪካዊ በዓል አሳክለን ከማክበራችን በፊት ትርጉሙን ባገናዘበ መልኩ ኢትዮጵያዊ በዓል አክሎስ ይከበራል ወይ የሚለዉን ጥያቄ በቅድሚያ ለራሳችን መመለስ ያለብን ይመስለኛል።
ዕንቁ፡- ከዚሁ ወቅታዊነት ያለው ጉዳይ ጋር ተያያዥነት ይኖረዋል የሚል ግምት አለንና … “ጥቁር ሰው ” የተሰኘውን ዜማ ለመሥራት ምን አነሣሣህ?
ቴዎድሮስ፡- አንድ ሰው ከፍላጎቱ፣ በውስጡ ከሚፈጠረው ስሜትና ከተፈጥሮአዊ ዝንባሌው በመነሳት ሥራዎችን ይሠራል። አንድ ሰው ማንን ይመስላል? ቢባል፤ እናቱንም አባቱንም ከመምሰሉ በላይ አነጋገሩን ይመስላል እንደሚባለው እኔም የምጫወተው ሙዚቃ የምናገረውን ይመስላል ማለት ነው። ከምንምና ከመቼውም ጊዜ በላይ ለእነዚያ ታሪክ የሠሩ ሰዎች አክብሮት መጠስት ተገቢ ነው የሚል ስሜት በውስጤ ይመላለስ ስለነበር፤ ያንን ስሜት ለመግለፅ ስል የሠራሁት ሙዚቃ ነው።
ለምሣሌ የምኒልክ ተግባር ዛሬ ያለንበትን ሀገር መዋቅር የሠራ በመሆኑ፤ የተዘፈነው ዘፈን ለክብራቸው ቢያንስ እንጂ የሚበዛ ሊሆን አይችልም። እንዲህም ሆኖ መቼም የሰው ልጆች አመለከካከት እና ስሜት የተለያየ ስለሆነ ዳግማዊ ሚኒልክ ያበላሹት ተግባር አለ ብለን የምናምን ወገኖች ካለን እንኳ የተበላሸውን ነገር ለማስተካከል በተበላሸ መንገድ መሄድ ተገቢ ነው ብዬ አላምንም። በተበላሸው መንገድ የሚኬድ ከሆነ ምንጊዜም በዚህ ምድር ላይ ዕዳ ተከፍሎ ሊያልቅ አይችልም።ዕዳ ተከፍሎ የሚያልቀው በፍቅር ብቻ ነው። ጥቁር ሰውንም የፈጠረው ‹‹ፍቅር ያሸንፋል›› የሚለው መንፈስ ነው። ። በዳህላክም ላይ የምናየው ይሄንኑ ነው። ስለዚህ ዕዳ የመሰረዝ ጉዳይ ከአበዳሪ አገሮች የሚጠበቅ ብቻ ሳይሆን ከእየራሳችንም ህሊና የሚጠበቅ ተግባር ነዉ።
ዕንቁ፡- የምኒልክ የመሪነት ጥንካሬ ከራሳቸው ብቻም ሳይሆን ከዕተጌ ጣይቱም አጋርነት የሚመነጭ ስለመሆኑ የታሪክ መዛግብት ላይ ሠፍሮ ይነበባል። አንተስ ስለጣይቱ ምን ትላለህ?
ቴዎድሮስ፡- ከእያንዳንዱ ስኬታማ ወንድ ጀርባ አንዲት ሴት አለች እንደሚባለው የምኒልክ ጥንካሬ የጣይቱም ነው። ከዚህም በዘለለ ልናየው ስንሞክር የጣይቱ ሚና ሲመዘን አንደኛ የምኒልክን የልብ ሥፋት የምንረዳበት ነው። በጊዜው እንደማንኛውም ኋላቀር አስተሳሰብ ለሴቶች ከሚሰጠው ግምት አንፃር ምኒልክ ሚስታቸውን በነበሩበት ደረጃ ኃላፊነት የሰጡ፣ ምክራቸውንም ለመቀበል የማያመነቱ ሰው ሆነው እናገኛቸዋለን። ዛሬ ስለሴቶች ጥንካሬ ለማወራት፤ ጣይቱ በጣም ጥሩ ምሣሌ ናቸው። ይሄ የጣይቱ ብልሀት፣ የጣይቱ መንፈሳዊ ጥንካሬ፣ የአመለካከት ሥፋትና ጥልቀት… ምኒልክን ‹‹ዕምዬ›› እስከማሰኘትና አልፎ ተርፎም በዓድዋ ጀግንነታቸው ጎልቶ እንዲዋጣ የወኔ ኃይል እስከመሆን ደረጃ የዘለቀ ነው። የሁለቱ የመቻቻልና የመደማመጥ መጠን በራሱ፤ በተለይ አሁን አሁን… ለሚስተዋለውና ‹‹የሴቶች የበታችነት፣ የወንዶች የበላይነት…›› ለሚባለው አጀንዳ ጥሩ ማጣቀሻ ነው። ከዚህም ባሸገር ጣይቱ በብዙ መመዘኛ ትልቅ ሥራ የሠሩ ሴት ናቸው።
images (3)
ዕንቁ፡- ምኒልክን በተመለከተ እንደ ሙዚቃው ሁሉ ፊልም ሠርቶ ሕያው ሥራዎቻቸውን ማክበር አይቻልም?
ቴድዎሮስ፡- አንተ ያላከበርከውን ሌላው ሊያከብርልህ አይችልም። አፍሪካዊያን ወገኖቻችን የእኛን አባቶችና አያቶች ዋጋ ያውቃሉ። እኛ ግን በዚህ ጉዳይ ላይ ከስምምነት ላይ ለመድረስ ገና ጭቅጭቃችንን አልጨረስንም። ስለዚህ በፊልምም ሆነ በሙዜቃ መደገፎ ጠቃሚነቱ በአያጠያይቅም ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ እኛ በታሪካችን ላይ ያለንን ግንዛቤ የማስፋት ደረጃና ጥልቀቱ በቂ ሆኖ መገኘቱ ላይ ነው።
ዕንቁ፡- የምኒልክ ማንነት በብሔራዊ ደረጃ መከበር ይገበዋል… ከመባሉ አኳያ ለወጣቱ ትውልድ የምታስተላልፈው መልዕክት ይኖርሃል?
ቴዎድሮስ፡- ቅንነት ከሌለ ጥሩ ነገር ማየት እንደማይቻል አውቆ። ታሪኩንም በቅንነት ስሜት መመርመር ይኖርበታል። የባለታሪክ ሰዎችን ጥሩ ነገር መውሰድና ጥሩ ያልሆነ ነገራቸውን ደግሞ እንዳይደገም ለማረም መትጋት ከኛ ከወጣቱች ይጠበቃል። ትልቁና ቁልፍ ነገር የማንነትን መሠረታዊ ጥያቄ ከመገንዘብ ይመነጫል። ሕይወትም የሚጀምረው ራስን ከመሆን ነው። ሰው ራሱን ሲያክል ሌላ ብዙ ነገር ማድረግ ይቻለዋል።… ስለዚህ የነገር ሁሎ ምንጭ ፍቅር ስለሆነ ከፍቅር የሚጀምረውን ህይወት በፍቅር ለመጨረስ ቅንነት ያስፈልጋል። አመጣጡን ያዬ አካሄዱን ያዉቃልው ምክኒያቱም ታሪኩን እየዞረ የማያይ ተጋዥ የኋላ መመልከቻ መስታወት የሌለው መኪናን ይመስላልና።
(እንቁ መጽሔት)

Dec 10, 2013

በብሔር ፖለቲካ ሥር “የተቀበረው ፈንጂ”!

(ከዋለልኝ እስከ ህወሃት/ኢህአዴግ)


article 39ከአስርት አመታት በፊት
የኢትዮጵያ ተማሪዎች በለውጥ አብዮት ናፍቆት እየተናጡ ነው፡፡ እዚህም እዚያም በተፈጠሩ ቡድኖች የማርክሲስት-ሌኒንስት ፍልስፍናን የሚሰብኩ የርዕዮተ ዓለም ጽሁፎች ይነበባሉ፡፡ ተማሪው ይከራከራል፣ የሌኒኒዝም ፍልስፍና ቀለም ቀለም መሽተት ለጀመረው የ1960ዎቹ ትውልድ ልብ የቀረበ ሆኗል፡፡ ፍልስፍናውን በአገራቸው የፖለቲካ ግለት ለመተርጐም የቋመጡት ወጣቶች በሁለት ጠርዝ ተሰልፈው በኢትዮጵያ ያለው “የመደብ ወይስ የብሔር ጭቆና ነው” በሚል በጠረጴዛ ዙሪያ ይፋለማሉ፡፡
የብሔር ጭቆና በአገሪቱ መስፈኑን ለማሳመን ሽንጣቸውን ገትረው ይከራከሩ ከነበሩ ተማሪዎች መካከል የብዙዎችን ቀልብ ለመስረቅ የበቃው ዋለልኝ መኮንን በተማሪዎች መጽሔት “On the Question of Nationalities in Ethiopia” የሚል ጽሑፉን ማስነበብ ጀመረ፡፡ ዋለልኝ በጽሑፉ ኢትዮጵያ አንድ አገር ሳትሆን ብዛት ያላቸው ብሔሮች በአማራ የበላይነት ተጨፍልቀው የሚኖሩበት መሆኗን ሞገተ፡፡ የዋለልኝን መከራከሪያ የተቀበሉ ተማሪዎች የብሔር ጥያቄን ዋነኛ መፈክራቸው አድርገው አረፉት፡፡ በአገሪቱ የሰፈነው ጭቆና የመደብ መሆኑን በመግለጽ “አንዱን ብሔር ጨቋኝና ሌላውን ተጨቋኝ” በማድረግ የተነሱትን እነ ዋለልኝን የተቃወሙ ተማሪዎች የብሔር ጭቆናን በሚያስተጋቡ ተማሪዎች “የነፍጠኛ ልጆች” የሚል ተቀጥላ ተበጀላቸው፡፡
ዋለልኝ ከማርክሲስት – ሌኒኒስት ፍልስፍና በቀጥታ የገለበጠባቸውን ቃላቶች በመጠቀም ኢትዮጵያን “የብሔሮች እስር ቤት” በማለት ሰየማት፡፡ በዋለልኝ እንደተዋወቀ የተነገረለትን የተጨቆነ ብሔርን ነፃ የማውጣት ፍልስፍና የትግራይ ተማሪዎች መሬት ላይ ለማዋል በማቀድ የነጻ አውጪነት ቡራኬን ተቀብለው ደደቢት በረሃ ገቡ፡፡ ወጣቶቹ ትግላቸውን በማስመልከት በእጅ ጽሑፍ ባሰፈሩት የመጀመሪያ ማኒፌስቷቸው ትግራዋይ በአማራ ጨቋኝ ብሔር ሲጨቆን መቆየቱን በመግለጽ ጨቋኙን (አማራን) ብሄር በጠብ መንጃ ትግል በመፋለም ትግራይን ነፃ ለማውጣት መነሣታቸውን አወጁ፡፡ በለስ የቀናቸው የትግራይ ነፃ አውጪዎች መላዋን ኢትዮጵያን በመዳፋቸው ስር ካስገቡ በኋላ በ1987 በጸደቀው ህገ መንግሥት የጆሴፍ ስታሊንን የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች አተረጓጐም ሳይጨምሩና ሳይቀንሱ እንዲሰፍር በማድረግ የስታሊን ደቀ መዛሙርት መሆናቸውን በተግባር አሳዩ፡፡
የአገሪቱ የመንግሥት አወቃቀርም ብሔር ተኮር ፌዴራሊዝም እንዲሆን ተፈረደበት፡፡ ከብዙ አስርት አመታት በኋላ በዋለልኝ መኮንን “የብሄሮች እስር ቤት” ተብላ ከተጠራችው ኢትዮጰያ የተጨቆኑ ብሄሮችን ነፃ ለማውጣት ብሶት አርግዞት እንደወለደው የነገረን ገዥው ፓርቲ ራሱን በነጻ አውጪዎች ሰረገላ ካስቀመጠ 22 ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ የነገው የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓልም በገዥው ፓርቲ እምነት ጥያቄው ምላሽ ለማግኘቱ አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡ ለፓለቲካ ፍጆታ እየዋለ ከሚገኘው ህዳር 29 በስተጀርባ መሬት የረገጡ እውነታዎችን ለመፈተሽ የተነሱ ሰዎች ከ73 የሚልቁ ብሄር ተኮር የፖለቲካ ድርጅቶችን ያገኛሉ፡፡ የእነዚህ ፓርቲዎች ዋነኛ የትግል ማዕቀፍ “ጥያቄው” አለመመለሱን የሚያሳይ ነው፡፡ በአገሪቱ ከመቼውም ግዜ በላይ መንግስትን በትጥቅ ትግል ለማንበርከክ ዱር ቤቴ ያሉ “ብሔር ተኮር” ድርጅቶች ስለመኖራቸውም እየተደመጠ ነው፡፡
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ጭምር ዘውጌ ተኮር ግጭቶች በስፋትና በብዛት እየተደመጡ ነው፡፡ “በኢትዮጵያዊነት” ጥላ ተሰባስበው የትውልድ መንደራቸውን በመልቀቅ በሌሎች ክልሎች ሀብትና ንብረት ያፈሩ ኢትዮጵያዊያን በገዛ አገራቸው እንደ ባይተዋር ተቆጥረው “እየተገደሉ ነው፡፡ በአሩሲ፣ በአርባጉጉ፣ በበደኖ፣ በአፋር፣ በትግራይ፣ በወለጋ፣ በአሰበ ተፈሪ፣ በጋምቤላ፣ ኦጋዴን፣ ጉራፈርዳና በቦረና “ከክልላችን ውጡ” የተባሉ የሌላ ክልል ተወላጆች ተፈናቅለዋል፣ ንብረታቸውን ተዘርፈዋል፣ ከእነ ህይወታቸው ጉድጓድ ውስጥ ተወርውረው ሴቶቻቸው ተደፍረዋል፡፡
በዘመነ ደርግና ከዚያ ቀደም በነበሩ አስተዳደሮች ግጭቶች የሚነሱባቸውና የሰው ህይወት ለከፋ ጉዳት የሚጋለጥባቸው አጋጣሚዎች የነበሩ መሆናቸውን መካድ ባይቻልም እነዚህ ግጭቶች ግን ይነሱ የነበሩት በግጦሽ መሬት ፍለጋ እንደነበር መዘንጋት አይገባም፡፡ በአገሪቱ የጐሳ ፖለቲካ አየሩን ከተቆጣጠረበት ከ22 ዓመታት ወዲህ ግን የግጭቶች ይዘትና መንስኤ ወደ አንድ ጫፍ በማዘንበል ላይ ይገኛል፡፡ “ክልላችንን ለቅቃችሁ ውጡ” የሚለው ድምፅ በሁሉ ልብ ማስተጋባት ሲጀምር “በህዝብ መካከል አለመተማመንን በመዝራት በመጨረሻ የሚያሳጭደው ውጤት አገርን ለመበታተን ይዳርጋል፡፡ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል የሚከበረውም “እኛና እነርሱ” በሚል መንፈስ መሆኑም የተቀበረው ፈንጂ ሰዓቱን እየሞላ እንዲሄድ ከማድረግ ውጪ የሚፈይደው ነገር ስለመኖሩ ብዙዎች ይጠራጠራሉ፡፡
ሁሉም የራሱን መንደር እየፈለገ ወደቀረበው እንዲሄድ የሚያደርግ መድረክ መፈጠሩን የሚተቹት ዶክተር ዘውዱ ውብእንግዳ “የፌደራሊዝም ታሪካዊ አመጣጥ” በሚለው መጽሐፋቸው ትዝብታቸውን እንዲህ ያሰፍራሉ፡፡ “በደርግ ዘመን ቀበሌዎች ስብሰባ ህዝቡን ሲጠሩ በ … ቀበሌ የምትገኙ … አዳራሽ ስብሰባ ስላለ እንዳትቀሩ ይሉ ነበር፡፡ አሁን ግን … ብሔር ተወላጅ የሆናችሁ … አዳራሽ እንድትገኙ ማለት ተጀምሯል፡፡ በፊት በአንድ ቀበሌ መኖር የአብሮነት መለኪያ ተርጐ ይወሰድ ነበር፡፡ አሁን ግን በአንድ ቀበሌ መኖር ብቻ በቂ ሳይሆን የብሔር ማንነት እንደመታወቂያ እየተወሰደ ነው” ይላሉ፡፡ ልዩነቶቻችን ጐልተው እንዲታዩ የሚደረጉባቸው መድረኮች በመንግሥት አታሞ እየተጐሰመላቸው አጀንዳ ሲሆኑ ከማየት የበለጠ ህመም የሚፈጥር ነገር የለም፡፡
በዓሉ የሚከበርባቸው ሥነ ሥርዓቶች ለኢህአዴግ ቱባ ባለስልጣናት አትሮንስ በመሆን ከማገልገል በዘለለ የብሔር ፖለቲካው፣ ፌዴራሊዝሙና የክልል መንግሥታት ነጻነት ለውይይት የሚቀርብባቸው መድረኮች አለመዘጋጀታቸውና እስካሁን ብሔርን/ዘውጌን ተገን በማድረግ በተፈጠሩ ቀውሶች ዙሪያ ውይይት የሚደረጉባቸው መንገዶች አለመፈጠሩ በእኔ እምነት በዓሉን “ከፈንጠዝያ” የዘለለ አያደርገውም፡፡ የአማራው ባህል ለትግሬው፣ የጉራጌው ለኦሮሞው፣ የከምባታው ልጅ ለስልጤው እየተሰጠች ያደግንባት አገር፣ አፋሩ ለሃድያው ዘብ የሚቆምባት ምድር ያፈራችን ሰዎች ለአክሱም ሀውልት ጋምቤላው የሚጨነቅባት የቅኖች ምድር ኢትዮጵያ በብሔር ፖለቲካ በናወዙ ጥቂት ቡድኖች ትልቁን ምስል ጠብቃ እንድትኖር እነዚህ መድረኮች “የእኛና የእነርሱ” የሚሉ ስሜቶች ስር ሳይሰዱ የሚቀርቡባቸው ሊሆኑ ይገባል፡፡ ያን ጊዜም “የተቀበረው ፈንጂ” ይመክናል፡፡
የብሔር ፖለቲካ መዘዝ
በአገሪቱ ከ84 የሚልቁ ብሔረሰቦች እንዳሉ ከመነገሩ ባሻገር የትኛው የማኀበረሰብ ክፍል ብሔር፣ የትኛው ብሔረሰብ ወይም ሕዝቦች የሚሰኙት የትኞቹ እንደሆኑ የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ በአንዳንድ አደባባዮች የጆሴፍ ስታሊንንና የዋለልኝ መኮንን ንግግሮች እንደወረደ በመደስኮር “አንደበተ ርትዕ” ተብለው የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ እንኳን እነዚህን የማኀበረሰብ ክፍሎች ሳይተነትኑ አልፈዋል፡፡ ከስምንት ዓመት ወዲህ መንግሥት የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በተለየዩ ሥነ ሥርቶች እንዲከበር እያደረገ ነው፡፡
በዚህ ቀን ከተለያዩ የማኀበረሰብ ክፍሎች የመጡ ሰዎች በመሰባሰብ እለቱን ይዘክራሉ፡፡ በዚህ ቀን እንኳን የትኛው ብሔር፣ የትኛው ብሔረሰብ፣ የትኞቹ ደግሞ ህዝቦች መሆናቸው አይታወቅም፡፡ ነገር ግን ፍቺ ባልተገኘበት ሁኔታ በዓሉ ይከበራል፡፡ ሌላው አስገራሚ ነገር በህገ መንግሥቱ “ሕዝቦች” ተብለው የተጠቀሱ ክፍሎች ምንም አይነት መገለጫ የሌላቸው መሆኑ ነው፡፡ ለምሣሌ ህገ መንግሥቱ ስለመሬት የሚለውን እንውሰድ፡፡ መሬት የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ስለመሆኑ ተጠቅሷል፡፡ በዚህ መነሻነትም ክልሎች በቋንቋ መነሻነት የየራሣቸውን ወሰን እንዲካለሉ ተደርገዋል፡፡ ህዝቦችስ? ነገሩን ትንሽ ለጠጥ በማድረግ እንውሰደው፡፡
በጉራፈርዳ ሰፍረው የነበሩ አማሮች “እንደ ህገወጥ ሰፋሪ ታይተው በክልሉ መንግሥት ውሣኔ ለአመታት ይዘውት የቆዩትን መሬት ጥለው እንዲሰደዱ ተደርገዋል፡፡ መሬቱን እንዲለቅቁ የተደረጉት “የክልሉ ተወላጅ” ባለመሆናቸው ብቻ ነው፡፡ እነዚህ ወገኖች የክልሉ ተወላጅ ባይሆኑም ሕዝብ በመሆናቸው እንደ ህገ መንግሥቱ የመሬት ባለይዞታነት መብታቸው ሊከበርላቸው ይገባ ነበር፡፡ የፌዴራሊዝሙ ተሳክሮት ዶክተር ዘውዱ በመጽሐፋቸው ለፌዴራል መንግሥት ምስረታ መንስኤ የሚሆን መሠረታዊ ነጥብ “ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ መንግስታት ወይም የየራሣቸውን መንግሥታዊ አስተዳደር ያካበቱ ሕዝቦች በፈቃደኝነት ላይ ተመስርተው የሚያቋቁሙት ሦስተኛ መንግሥት ነው፡፡ ስለሆነም ፌዴራላዊ መንግሥት ከትንሹ ቁጥር ሳንነሳ የሦስት መንግሥት ጥምር ነው” ይላሉ፡፡ በዘውዱ ገለፃ ፌዴራሊዝምን በማስተዋወቅ የመጀመሪያዋ ተጠቃሽ አገር ለመሆን የበቃችው ለ100 ዓመታት ያህል በእንግሊዝ ቅኝ ተገዝታ የነበረችው አሜሪካ ናት፡፡
ቅኝ ገዢዋ እንግሊዝ ሀገሪቱን በ13 የቅኝ ግዛት አስተዳደሮች በመከፋፈል ስታስተዳድር ቆይታለች፡፡ አሜሪካኖች ራሣቸውን ነፃ ካወጡ በኋላ ተከፋፍለው የነበሩት ክልሎች በፌዴራሊዝም አማካኝነት መልሰው አንድነታቸውን አግኝተዋል፡፡ ሌሎች በቅኝ ግዛት ስር የነበሩና የተለያዩ አስተዳደሮችም የአሜሪካውን ፌዴራሊዝም በአርአያነት በመከተል የተበታተኑት አንድ መሆን ችለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ የመንግሥት አወቃቀር ግን የጐሳ በመሆኑ በአለም ከሚታወቀው የፌዴራሊዝም አመሰራረት ጽንሰ ሀሣብ ያፈነገጠ ነው፡፡
በህገ መንግሥቱ ድንጋጌ መሠረት የክልል መንግሥት ለማቋቋም መመዘኛ ሆኖ የቀረበው ብሔር፣ ብሔረሰብና ሕዝቦች በሚል መነሻነት ነው፡፡ አስቀድሜ ለመግለጽ እንደሞከርኩት በአገሪቱ ውስጥ ከ84 የሚልቁ ብሔረሰቦች ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን ክልል እንዲመሰረቱ እውቅና የተሰጣቸው ዘጠኙ ብቻ ናቸው፡፡ ቀሪዎቹስ? ለምን ክልል የመመስረት መብትን ተነፈጉ?
በህገ መንግሥቱ በዘጠነኛ ክልልነት የተቀመጠው “የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል” ተብሎ እንዲቀመጥ ተደርጓል፡፡ የፌዴራሉ መንግሥት ክልሎች የተመሠረቱት ቋንቋን ማዕከል ባደረገ መልኩ ቢሆንም ይህ ወደ ደቡብ ሲያመራጂኦግራፊያዊእንደሆነ የተፈለገበት መንገድ ለማንም ግልጽ አይደለም፡፡ በደቡብ ክልል ከ46 የሚልቁ ብሔረሰቦች ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ብሔረሰቦች በሌሎች ክልሎች የሚገኙ ብሔረሰቦች የራሣቸውን ክልልና መንግሥት የሚመሰርቱበትን መብት ሲጐናጸፉ በደቡብ ያሉት ግን ይህንን መብት ተነፍገዋል፡፡
የፌዴራሊዝሙ አወቃቀር በቋንቋ በአንድ ቦታ ሲሰራ በሌላ ቦታ በጂኦግራፊ መሆኑም የአወቃቀሩን ተሳክሮት ወለል አድርጐ ያሳያል፡፡ በጎሳ ላይ የተንጠለጠለ የመንግሥት አወቃቀር በሩዋንዳ፣ ሶማሊያ፣ ኮሶቮና ሩሲያን በመሳሰሉ አገራት የፈጠረውን ሰብአዊ ቀውስ የተመለከቱ ሰዎች የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግሥት የአወቃቀር ተሳክሮት በአገሪቱ ላይ በጊዜ የማይተነብይ ምስቅልል ሊፈጥር እንደሚችል ይጠቁማሉ፡፡ (ዳዊት ሰለሞን)

Dec 8, 2013

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ ሰራዊት በጋራ ወታደራዊ ጥቃት ፈፀሙ ..

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ ሰራዊት በጋራ ወታደራዊ ጥቃት ፈፀሙ .................

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ ሰራዊት በጋራ ወታደራዊ ጥቃት ፈፀሙ
የጋራ ትግል አስፈላጊ መሆኑን በፅኑ የሚያምኑት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር /ኢሕአግ/
እና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ /ጋሕነን/ በሕዳር 13/2006 ዓ.ም በሁመራ ሉግዲ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1፡00 ለሶስት ሰዓት ያህል በወሰደው ውጊያ የወያኔው 24ኛ ክፍለ ጦር ድባቅ ተመቷል።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በ24ኛው ክፈለ/ ጦር ላይ በተመሳሳይ ሥፍራከፍተኛ ድል መቀዳጀቱ ይታወሳል።
በሕዳር 13/2006 ዓ.ም የኢሕአግና የጋህነን ሰራዊት በወሰዱት ድንገተኛ ወታደራዊ ጥቃት 66 /ስልሳ ስድስት/ ገድለው 113 /አንድ መቶ አስራ ሶስት/ በማቁሰል እንዲሁም ቁጥራቸው የበዛ የጦር መሳሪያዎችን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ማርከዋል።
ሁለቱ ድርጅቶች በጋራ በተለያየ የትግል መስክ ሲተጋገዙና ሲተባበሩ ቆይተዋል የግንኙነታቸውን እድገትና ለውጥ የሚያሳይ ወታደራዊ ጥቃትም ፈፅመዋል።
ይህ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚመኘውና የሚፈልገው የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ስምምነትና አንድነት መገለጫ ሊሆን የሚችል አኩሪ ጥቃት መሆኑ ይታመንበታል ። በጥቃቱ የተካፈሉ የሁለቱ ድርጅቶች ታጋዮች እንዳብራሩት ዛሬ በጋራ የጀመርነው ወታደራዊ ጥቃት በዚሁ የሚያበቃ ሳይሆን የጋራ ዓላማና ራዕይ እስካለን ድረስ ወደኋላ የማይቀለበስ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህም አክለው የዚህ ወታደራዊ ዘመቻ ዓላማ አገር እንደሌለው ሁሉ በሰው አገር ፍዳውን እያየና እየተሰቃየ እንዲሁም ለሞት እየተዳረገ የሚገኙውን በሳውዲ አርቢያ ለተፈፀመው በደል ለመበቀልና ሕዝባዊ ወገንተኝነታችንን ለማሳየት ታስቦ የተወሰደ ወገናዊ እርምጃ ነው በማለት አብራርተዋል።
በውጊያው ከሞት ተርፎ ለከባድ ቁስልና የአካል ጉዳት የተዳረገው የወያኔው ቅጥረኛ የ24ኛ ክፈለ ጦር አባላትን ከሁመራ አንስቶ እስከ ትግራይ የሕክምና ማዕከሎች ማጋጋዝ ዋነኛ ተግባሩ ሆኗል።
ይህንን የጀግና ጥቃትና ድል የተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ሰራዊቱን እንኳን ደህና መጣችሁ ብሎ በመቀበልና ስንቅና ትጥቅ በማቅረብ አጋርነቱን ያስመሰከረ ሲሆን የተጀመረው ወታደራዊ ጥቃት በተለያዩ አካባቢዎች ላይ እንዲደገም ያላቸውን ልባዊ ምኞት ገልፀው በንፁሃን ላይ ያለ አግባብ ሲወሰድ የነበረው የቅጥረኞች እርምጃ አንጀቱ ላረረው ሕዝብ እምባ ያበሰ እንደሆነም ተናግረዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር/ ኢሕአግ/ እና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ /ጋህነን/ ወያኔ ለ22 ዓመት ያህል አገሪቷን ሲበዘብዝና ሕዝቡ የዲሞክራሲያዊ መብቱ ተጠቃሚ እንዳይሆን በሃይል የመግዛቱ ሂደት እንዲያከትም የተቻላቸውን ሁሉ ለማድረግ ቆርጠው መነሳታቸውን አስታውቀዋል።

የጋራ ትግል አስፈላጊ መሆኑን በፅኑ የሚያምኑት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር /ኢሕአግ/
እና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ /ጋሕነን/ በሕዳር 13/2006 ዓ.ም በሁመራ ሉግዲ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1፡00 ለሶስት ሰዓት ያህል በወሰደው ውጊያ የወያኔው 24ኛ ክፍለ ጦር ድባቅ ተመቷል።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በ24ኛው ክፈለ/ ጦር ላይ በተመሳሳይ ሥፍራከፍተኛ ድል መቀዳጀቱ ይታወሳል።
በሕዳር 13/2006 ዓ.ም የኢሕአግና የጋህነን ሰራዊት በወሰዱት ድንገተኛ ወታደራዊ ጥቃት 66 /ስልሳ ስድስት/ ገድለው 113 /አንድ መቶ አስራ ሶስት/ በማቁሰል እንዲሁም ቁጥራቸው የበዛ የጦር መሳሪያዎችን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ማርከዋል።
ሁለቱ ድርጅቶች በጋራ በተለያየ የትግል መስክ ሲተጋገዙና ሲተባበሩ ቆይተዋል የግንኙነታቸውን እድገትና ለውጥ የሚያሳይ ወታደራዊ ጥቃትም ፈፅመዋል።
ይህ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚመኘውና የሚፈልገው የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ስምምነትና አንድነት መገለጫ ሊሆን የሚችል አኩሪ ጥቃት መሆኑ ይታመንበታል ። በጥቃቱ የተካፈሉ የሁለቱ ድርጅቶች ታጋዮች እንዳብራሩት ዛሬ በጋራ የጀመርነው ወታደራዊ ጥቃት በዚሁ የሚያበቃ ሳይሆን የጋራ ዓላማና ራዕይ እስካለን ድረስ ወደኋላ የማይቀለበስ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህም አክለው የዚህ ወታደራዊ ዘመቻ ዓላማ አገር እንደሌለው ሁሉ በሰው አገር ፍዳውን እያየና እየተሰቃየ እንዲሁም ለሞት እየተዳረገ የሚገኙውን በሳውዲ አርቢያ ለተፈፀመው በደል ለመበቀልና ሕዝባዊ ወገንተኝነታችንን ለማሳየት ታስቦ የተወሰደ ወገናዊ እርምጃ ነው በማለት አብራርተዋል።
በውጊያው ከሞት ተርፎ ለከባድ ቁስልና የአካል ጉዳት የተዳረገው የወያኔው ቅጥረኛ የ24ኛ ክፈለ ጦር አባላትን ከሁመራ አንስቶ እስከ ትግራይ የሕክምና ማዕከሎች ማጋጋዝ ዋነኛ ተግባሩ ሆኗል።
ይህንን የጀግና ጥቃትና ድል የተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ሰራዊቱን እንኳን ደህና መጣችሁ ብሎ በመቀበልና ስንቅና ትጥቅ በማቅረብ አጋርነቱን ያስመሰከረ ሲሆን የተጀመረው ወታደራዊ ጥቃት በተለያዩ አካባቢዎች ላይ እንዲደገም ያላቸውን ልባዊ ምኞት ገልፀው በንፁሃን ላይ ያለ አግባብ ሲወሰድ የነበረው የቅጥረኞች እርምጃ አንጀቱ ላረረው ሕዝብ እምባ ያበሰ እንደሆነም ተናግረዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር/ ኢሕአግ/ እና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ /ጋህነን/ ወያኔ ለ22 ዓመት ያህል አገሪቷን ሲበዘብዝና ሕዝቡ የዲሞክራሲያዊ መብቱ ተጠቃሚ እንዳይሆን በሃይል የመግዛቱ ሂደት እንዲያከትም የተቻላቸውን ሁሉ ለማድረግ ቆርጠው መነሳታቸውን አስታውቀዋል።

Dec 1, 2013

Ethiopia most restrictive Sub Saharan Country, Freedom House reports 2013

Ethiopia has one of the lowest rates of internet and mobile telephone penetration in the world, as meager infrastructure, a government monopoly over the telecom sector, and obstructive telecom policies have notably hindered the growth of information and communication technologies (ICTs) in the country. Despite low access, the government maintains a strict system of controls over digital media, making Ethiopia the only country in Sub-Saharan Africa to implement nationwide internet filtering. Such a system is made possible by the state’s monopoly over the country’s only telecom company, Ethio Telecom, which returned to government control after a two-year management contract with France Telecom expired in December 2012. In addition, the government’s implementation of deep-packet inspection technology for censorship was indicated when the Tor network, which helps people communicate anonymously online, was blocked in mid- 2012.
Internet Freedom
Prime Minister Meles Zenawi, who ruled Ethiopia for over 20 years, died in August 2012 while seeking treatment for an undisclosed illness. Before his death was officially confirmed on August 20th, widespread media speculation about Zenawi’s whereabouts and the state of his health prompted the authorities to intensify its censorship of online content. A series of Muslim protests against religious discrimination in July 2012 also sparked increased efforts to control ICTs, with social media pages and news websites disseminating information about the demonstrations targeted for blocking. Moreover, internet and text messaging speeds were reported to be extremely slow, leading to unconfirmed suspicions that the authorities had deliberately obstructed telecom services as part of a wider crackdown on the Ethiopian Muslim press for its coverage of the demonstrations.
In 2012, legal restrictions on the use and provision of ICTs increased with the enactment of the Telecom Fraud Offences law in September,1 which toughened a ban on certain advanced internet applications and worryingly extended the 2009 Anti-Terrorism Proclamation and 2004 CriminalCode to electronic communications.2 Furthermore, the government’s ability to monitor online activity and intercept digital communications became more sophisticated with assistance from the Chinese government, while the commercial spyware toolkit FinFisher was discovered in Ethiopia in August 2012.
Repression against bloggers, internet users and mobile phone users continued during the coverage period of this report, with at least two prosecutions reported. After a long trial and months of international advocacy on behalf of the prominent dissident blogger, Eskinder Nega, who was charged with supporting a terrorist group, Nega was found guilty in July 2012 and sentenced to 18 years in prison.
Read Freedom House reports 2013, Full report about Ethiopia
Read Freedom House reports 2013, Full Report
Source:  http://www.freedomhouse.org/

Total Pageviews

Translate