Pages

Mar 31, 2013

ወ/ሮ አዜብ ተጨንቀዋል!

“ከሁሉም ነገር ጽድት ብለን እንታገል”

azebb mesfin

ሰሞኑንን በተጠናቀቀው የኢህአዴግ ጉባኤ አቶ መለስን አስመልክቶ ወ/ሮዋ የተናገሩት ንግግር በጭንቀት ውስጥ ስለመሆናቸው ማሳያ እንደሆነ የተናገሩት አብረዋቸው ባህር ዳር ስብሰባ የተቀመጡ የድርጅታቸው ኢህአዴግ “ባልደረቦቻቸው” ናቸው።
በጉባኤው ወቅት አቶ መለስ ዜናዊን በማወደስ የተዘጋጀው “ዝክረ – መውደስ” ታሪካዊ ሰነድ እንዲሆን ከመጽደቁ በፊት ወ/ሮ አዜብ በሰጡት አስተያየት “በፔሮል የሚከፈለው ብቸኛ መሪ መለስ ብቻ ነው” በማለት ራሳቸውን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በፔሮል በሚከፈላቸው ገንዘብ ብቻ እንደማይኖሩ የሚያመላክት ንግግር አድርገዋል።
መለስ ደመወዛቸው ስድስት ሺህ ብር እንደሆነ፣ ሁለት ሺህ ብር ሲቆረጥ አራት ሺህ እንደሚቀርና “ይህችኑ ገንዘብ” እየተቀበሉ ላገር ሲሰሩ ያለፉ መሪ መሆናቸውን ያወሱት ባለቤታቸው፣ ለመለስ ዝክረ-መወደስ በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ይህ መካተት ይገባዋል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
“መለስ ጭንቅላቱን ይዞ ወደዚህች ዓለም መጣ፣ ለዚህች ዓለም፣ አገር፣ ምድር፣ የምታገለግል ሃሳብ አመነጨ” ያሉት ወ/ሮ አዜብ፣ ባለቤታቸው ግለኝነት ሳይፈታተናቸው፣ ቤተሰቦቻቸውን በመርሳት፣ ላገራቸው የለፉና ድህነትን ሲዋጉ ኖረው ያለፉ መሪ መሆናቸው ሊረሳ እንደማይገባው አመልክተዋል። አያይዘውም ሊተኩ የሚችሉ መሪ እንዳልሆኑ በማሳሰብ ዝክረ-መወድሱ ከአቶ መለስ የሕይወት ጉዞ ብዙ ቁምነገሮችን የዘለለና ያልተሟላ ነው ብለውታል፡፡ እንዲሁም መለስ የኢትዮጵያ መሪም ብቻ ሳይሆኑ የአዲስ ራዕይ መጽሄት አዘጋጅ መሆናቸው አለመጠቆሙ አግባብ እንዳልሆነ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
በጉባኤው ላይ የተገኙ የድርጅት አባላት እርስ በርሳቸው ሲለዋወጡ የነበረውን የተከታተሉና በግልጽ ከስርዓቱ ባህርይ በመነሳት ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ እንዳሉት ወ/ሮ አዜብ የቀድሞው ስብዕናቸው አብሯቸው የለም። እንዲያውም በጭንቀት ውስጥ ያሉ ይመስላሉ ብለዋል።
በድርጅቱ አባላት ከላይ እስከታች የባለቤታቸውን ስልጣን ተገን በማድረግ በጣልቃ ገብነታቸውና ከፍተኛ የሚባል ንብረት በማካበት የሚታሙት ወ/ሮ አዜብ የባለቤታቸውን ስም በመደጋገም የሚያነሱት የሚታሙበትን ጉዳይ ለማስረሳት እንደሆነ እርስ በርስ በእረፍት ሰዓት ይወራ እንደነበር እነዚሁ ክፍሎች ተናግረዋል።
“ሴትየዋ በግልጽ ስለሚነሳባት ጉዳይ ለምን አትናገርም” በማለት የጠየቁ እንዳሉ፣ ከዚህም በላይ በድርጅቱ ውስጥ ነግሷል የሚባለው ሙስና በግልጽ ለምን አጀንዳ ሆኖ እንደማይቀርብ አባሉ ውስጥ ውስጡን ሲያወራ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። በትክክለኛው መንግድ ለመታደስና ለመጥራት የሙስና ጉዳይ የድርጅቱ ቀዳሚ አጀንዳ መሆን እንዳለበት አስተያየት የሰጡም አሉ።
ወ/ሮ አዜብ ይህ ገብቷቸው ይሁን አይሁን ስለ ባለቤታቸው ድህነት ሲናገሩ “እንደሚባለው ሳይሆን እኛ እንኮራበታለን” ማለታቸው ከሙስና ጋር በተያያዘ ስጋት ስለገባቸው የአባሉን ልብ ለማራራት እንደሆነ አድርገው የወሰዱትም እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል። በግልጽ ባያብራሩትም “እንደሚባለው” ብለው በመጥቀስ በይፋ እስከማስተባበል መድረሳቸው በባለቤታቸው ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት ራሳቸውም የተረዱት አይመስልም፡፡
አቶ መለስ ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ በሚያገኙት መድረክ ስለ ባለቤታቸው ድህነትና ያለ እረፍት ያለፉ መሪ በማድረግ በስፋት የሚናገሩት ወ/ሮ አዜብ፤ ባለቤታቸውን ዴሞክራት መሪ አድርገው ቢስሉም ሪፖርተር በፖለቲካ አምዱ ያስነበበው እውነተኛ ታሪክ የስጋታቸውና የፍርሃታቸው መነሻ እንደሚሆን ከግምት በላይ የሚናገሩ አሉ። ሪፖርተር ወ/ሮ አዜብን በስም ባይጠቅስም፣ “መሐንዲስ አልባው መተካካት” በሚል ርዕስ በጻፈው “(መለስ) በተለያዩ ጊዜያቶች የፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸውን ከፖለቲካ ጨዋታ ውጪ ማድረግ ቢችሉም፣ እስከ 1993 ዓ.ም. ድረስ ሥልጣን የግላቸው አልነበረም፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ ላይ ሆነው የፈለጉትን ማድረግ የሚችሉ ሰውም አልነበሩም፡፡ በወቅቱ የሕወሓት መሰንጠቅን ተከትሎ የድርጅቱ ርዕዮተ ዓለም ቁንጮ (አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም) የወታደራዊ ስትራቴጂ ባለቤት (የቀድሞ የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ስዬ አብርሃ)፣ የፕሮፓጋንዳ ኃላፊው (የቀድሞ የትግራይ ፕሬዚዳንት አቶ ገብሩ አስራት) እና ሌሎች የድርጅቱ ከ10 በላይ ከፍተኛ አመራሮች መወገድን አስከትሏል፡፡ የእነዚህ የድርጅቱ ወሳኝ ሰዎች መወገድን ተከትሎ በመንግሥትም ሆነ በፓርቲ ሥልጣናቸውን የተደላደለና ምንም የፖለቲካ ተቀናቃኝ የሌላቸው ሰው መሆን የቻሉበት ጊዜ ነበር፡፡ የፈለጉትን ሕግ ማውጣት ያልፈለጉትን የመደቆስ ሥልጣኑም ጉልበቱም ነበራቸው” ሲል ሪፖርተር የጻፈላቸው አቶ መለስን ተገን በማድረግ ወ/ሮ አዜብ በሃብት፣ በጣልቃገብነት፣ በተለያዩ ውሳኔዎች፣ ፈላጭ ቆራጭ ሆነው መቆየታቸው በርካታ ወዳጅ ያፈራላቸው ባለመሆኑ የስጋታቸው መጠን ሰፊና ጥልቅ እንደሆነ በስፋት አስተያየት እየተሰጠበት ነው።

የአረብ አገር ተጓዦች ፅንስ በማቋረጥ ለጉዳት እየተጋለጡ ነው!

ሰላም ገረመው
ፒያሳ በሚገኘው ሜሪስቶፕስ ኢንተርናሽናል ክሊኒክ አካባቢ በቋሚነት የሚያንዣብቡት ደላሎች ወደክሊኒኩ የሚያመሩ የመሰሏቸውን ወጣት እንስቶች አያሳልፉም “ክሊኒኩ ተዘግቷል፤ ወዴት ናችሁ?” በማለት በጥያቄ ጣድፋሉ፡፡ ከቀናቸውና የሚያነጋግራቸው ካገኙ የክሊኒኩ ዋና ዶክተር የግሉን ክሊኒክ ስለከፈተ እዛ ልውሠድሽ” በማለት ማግባባት ይጀምራሉ፡፡ አሁንም ከተሳካላቸው (በአብዛኛው ይሳካላቸዋል) አገልግሎት ፈላጊዋን ባህላዊ የፅንስ ማቋረጥ የሚካሄድበት ቦታ (መንደር ውስጥ) ይወስዳሉ፡፡ በዚህ ሰዓት ደላሎቹ የሚያሳዩት ትህትናና ሽቁጥቁጥነት ማንኛዋም ሴት ለክፉ አደጋ ወደሚዳርጋት ሥፍራ ይወስዱኛል ብላ እንዳታስብ ያደርጋታል፡፡ ፅንስ ማቋረጥ የሚፈፀምበት ቦታ ከወሰዳት በኋላም ምናልባት በክፍያ ላትስማማ ትችላለች፡፡ ይኼኔ ደላላው መሀል በመግባት ያደራድራል፡፡ ይሄ ደግሞ የደላላውን የኮሚሽን ክፍያ ይጨምርለታል፡፡ ደላላው ሁሉን ደማምሮ ኮሚሽኑን ተቀበለ በኋላ እብስ ይላል፡፡ ከዚህ በኋላ የሚመጣውን ክፉና ደግ ደግሞ ገባሁ፡፡ ደላላውም ተከትሎኝ ገባ፡፡ የሃኪሙ ጭ ቀለም የተቀባ የሚመስል ጠረጴዛ ለዓይን እንኳን ይዘገንናል፡፡ መሀሉ የተቦረቸፈ ስትሬቸር ግድግዳው ጥግ ይታየኛል፡፡ የእርግዝና ማዳመጫ መሳሪያ ጠረጴዛው ላይ ተቀምጧል፡፡ በቃ እኒሁ ናቸው የህክምና ቁሳቁሶቹ - ሌላ ነገር የለም፡፡ “ስንት ወርሽ ነው?” ሃኪሙ ጠየቀኝ“አራት ወር ገደማ ይሆነኛል” አልኩት- የውሸቴን መሆኑ ንዳይታወቅብኝ በመጠንቀቅ ችግር የለም እስከ ሠባት ወር እንሠራለን ---- ትንሽ ግን ክፍያው ወደድብሻል” አለኝ ሃኪሙ“እኔ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነኝ---- ጓደኛዬ ነው የሚከፍልልኝ፤ዋጋውን ንገረኝና ገንዘቡን ተቀብዬው እመጣለሁ” “እሺ አራት ወር ከሆነሽ ሠባት መቶ ብር ትከፍያለሽ፤በመድሃኒት ወይም በማሽን ይሰራልሻል፤ ብሩ ተወደደብኝ ካልሽ ደግሞ በግሉኮስ ላስቲክ ሊሰራልሽ ይችላል” ሲለኝ የእያንዳንዱን ዋጋ እንዲነግረኝ ጠየቅሁት፡፡ እሱም ማብራራቱን ቀጠለ በመድሃኒት ለሚሠራው ነው ሠባት መቶ ብር ያልኩሽ፤ በማሽን ከሆነ ስድስት መቶ ብር ትከፍያለሽ፤ በግሉኮስ ሶስት መቶ ብር” ከጓደኛዬ ጋር ልምከርበት አልኩትና ሙን አመሥግኜው ወጣሁ፡፡ ከቤቱ እንደወጣን “ቤቱ ደስ አላለኝም” በሚል ሰበብ ወንዱ ሌላ ቦታ እንዲወስደኝ ጠየቅሁት፡ “ችግር የለም” አለኝና መንገዳችንን ቀጠልን - ወደ ሁለተኛው አማራጭ፡፡ ብዙም ሳንደክም ነው የደረስነው፡፡ “በርጌስ ክሊኒክ” የሚል ማስታወቂያ ያለበት የህክምና ተቋም ውስጥ ይዞኝ ገባ - ፈቃዴን ከጠየቀኝ በኋላ፡፡ ክሊኒኩ መጀመሪያ ከገባንበት ቦታ በንፅህና አስር እጅ የተሻለ ነው፡፡ ታካሚዎች ተራ ይጠብቃሉ፡፡ ወንዱ ልክ እንደጓደኛው እጄን ይዞኝ ካርድ ክፍል ሠራተኞች ምልክት ሠጥቷቸው ወደ ሃኪሙ ክፍል ወሰደኝ፡፡ ታዳጊው ደላላ ለክሊኒኩ ቤተኛ መሆኑ ያስታውቃል፡፡ ይሄኛው እንኳን የክሊኒክም ወግ አለው፡፡ የተራቀቁና ዘመን አመጣሽ ባይሆኑም የተለመዱት የህክምና መሳሪያዎች ይታያሉ፡፡ ዶክተሩ ወንዱን ስላየ ነው መሠለኝ በቀጥታ “ስንት ወርሽ ነው?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡ “አራት ወሯ ነው፤ ጓደኛዋ አደራ ብሎኝ ነው” ሲል ወንዱ ፈጠን ብሎ መለሰ “እሺ አሁን ትሠሪያለሽ?” የዶክተሩ ጥያቄ ነበር ጋውን እንዲነግረኝ እና ከጓደኛዬ ጋር ተማክሬ “እዚህ ክሊኒክ ግሉኮስ የሚባል ነገር የለም፤ ዋጋው ደግሞ አንድ ሺህ ሠባት መቶ ብር ነው” አለኝ ፍርጥም ብሎ፡፡ ከሃኪሙ ክፍል እንደወጣን ለወንዱ የፍርሃት ስሜት ውስጥ እንደገባሁና እዚህ ክሊኒክ ውስጥ ያሰራች አንዲት ሴት ባገኝ ሁኔታውን ጠይቄያት እንደምደፋፈር ነገርኩት፡፡ እኔ ግን የፈለግሁት ሊያሰሩ የመጡ ሴቶችን ለማነጋገር ነበር፡፡ ወንዱም ያልኩትን ለመፈፀም ለአፍታ እንኳ ሳያመነታ “ተከተይኝ” ብሎ ይዞኝ ሄደ፡፡ ጥግ ጥጋቸውን ይዘው የሚያቃስቱ ሴቶች ነበሩ፡፡ በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ ባሉ አልጋዎች ላይ በሆዳቸውየተኙም ሴቶች ተመልክቼአለሁ፡፡ ወደ አንዷ ሴት  ጋ አልኩና ጠየቅኋት “ህመሙ ለትንሽ ደቂቃ ነው አትፍሪ” የሚል ማበረታቺያ ሰጠችኝ፡፡ “የስንት ወር ነው ያሰራሽው?” አልኳት፡፡ “እኔ መውለድ ነበር የምፈልገው፤ሆኖም የአረብ አገር ቪዛ መጣልኝና ላስወርድ ፈለግሁኝ፤ ሜሪስቶፕስ ሄጄ ወርሽ ገፍቷል አንሰራም ሲሉኝ ደላላው ወደዚህ አመጣኝ” አለችኝ፡፡ ልጅቱ በነበረችበት ክፍል ውስጥ 18 ሴቶች ነበሩ፡፡ ዘጠኙ ወደ አረብ አገር የሚሔዱ ናቸው፡፡ የዕለቱ ዕለትና በንጋታው የሚበሩ ሴቶችም ነበሩ፡፡ ከክፍሉ ስንወጣ ለደላላው ሀያ ብር ሠጠሁትና ስልኩን ተቀብዬ እንደምደውልለት ነግሬው ተለያየን፡፡ በዚያው ሰሞን በአንድ የዘመድ ለቅሶ ላይ በሜሪስቶፕስ ክሊኒክ ውስጥ የምትሰራ አንዲት ሲስተር አገኘሁና በፅንስ ማቋረጥ ዙሪያ አንዳንድ ነገር ተጨዋወትን፡፡ ሲስተሯ እንደነገረችኝ ወደ ክሊኒኩ ፅንስ ለማቋረጥ ከሚመጡ ሴቶች አብላጫውን ቁጥር የሚይዙት የአረብ አገር ተጓዥ ሴቶች ናቸው፡፡ እሷን የሚያስጨንቃት ታዲያ ሦስት ወር ከሆናቸው በኋላ ወደክሊኒኩ መጥተው የሚመልሷቸው ነፍሰጡር ሴቶች ጉዳይ ነው፡፡ ክሊኒኩ ከፀነሱ ሦስት ወር ለሞላቸው እንስቶች አገልግሎት እንደማይሰጥሲ ግራቸው፤ ወደ ህገወጥ ቦታ መሄዳቸው ክፉኛ  ንደሚያሳስባት ትናገራለች፡፡አንዲት ሴት እስከ ሁለት ወር የሚደርስ ፅንስ በመድሀኒት ማቋረጥ ትችላለች፡፡ አንድ ፍሬ ክኒን በመጀመርያው ቀን ትውጥና በሶስተኛው ቀን ደግሞ አራት ፍሬ እንድትውጥ ይደረጋል፡፡ አብዛኛዎቹ ሴቶች ግን መድሃኒቱን አይመርጡም፡፡” ያለችው ሲስተሯ፤ ምክንያቱን ስንጠይቃቸው አረብ አገር ስለሚሄዱ እንደሆነ ይነግሩናል ትላለች፡፡ አንዳንዶቹ ግን ፅንሱ በመጀመሪያ በዋጡት መድሃኒት ብቻ የሚወርድ ስለሚመስላቸው በዛው ይቀራሉ፤ ይሔ ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል ብላለች፡፡ “አንዳንዶቹ እንደውም የሔዱበት አገር ተመርምረው ነፍሠ ጡር መሆናቸው ሲታወቅ ተመልሠው ይመጣሉ፤ይሔም ሌላ ኪሳራ ነው” የምትለው ባለሙያዋ፤ አረብ አገር እሄዳለሁ ብላ ፅንስ ለማቋረጥ የመጣች አንዲት ሴት የገጠማትን አሳዛኝ አደጋ ታስታውሳለች፡፡ “ልጅቷ ወደ አረብ አገር ልትሄድ ስትል ነው ለማስጠረግ የመጣችው፤ ቀኗ በመግፋቱአንሠራምአልናትና ሌላም ቦታ መሄድ እንደሌለባት መክረን ሸኘናት፤ እሷ ግን ባህላዊ ፅንስ የማቋረጥ አገልግሎት የሚሰጥበት ቦታ በመሄድ በሠጧት የግሉኮስ ላስቲክ ምክንያት ማህፀኗ በመበሳቱ፤ደሟ ወደ ሆዷ ፈስሶ ህይወቷ አለፈ” ብላለች - ሲስተሯ፡፡ ተዘዋውሬ ባየኋቸው የሜሪስቶፕስ ክሊኒኮች አብዛኛዎቹ አገልግሎት ፈላጊዎች ወደአረብ አገር የሚጓዙ ሴቶች መሆናቸውን ለማወቅ ችያለሁ፡፡ በዚህም ምክንያት በቀን ጥቂት ሴቶችን ብቻ ያስተናግዱ የነበሩ የክሊኒኩ ቅርንጫፎች፤ አሁን ከአቅማቸው በላይ እየሆነባቸው ቀጠሮ እስከ መስጠት ደርሠዋል፡፡ ክሊኒኩን ያጨናነቁት በዋናነት የአረብ አገር ተጓዥ ሴቶች ቢሆኑም ክሊኒኩ በፊት ከሚሠጠው በማሽን የመጥረግ አገልግሎት በተጨማሪ በመድሀኒት የመጥረግ አገልግሎት  ጀመሩም የተጠቃሚዎቹን ቁጥር እንደጨመረው ሲስተሯ ትናገራለች፡፡ “በመድሃኒት ፅንስ ማቋረጥን ብዙዎች እንደጨዋታ ነው የሚያዩት፤ ምክንያቱም እምብዛም የህመም ስሜት የለውም” የምትለው ጊዜ “በጣም ነው የምወዳችሁ!” እያሉ በመወሻከት ቁርጥ ቀን ሲመጣ “ልጄ ሁሉም ለራሱ ነው!” ብሎ ነገር የለም፡፡ ፀማይ የእውነት ምድር ነው፡፡ መውደድ ንዳይረክስ በቃል አይጠራም፤ በተግባር ነው የሚገለፀው፡፡ እነዚህን ሁሉ በረከቶች አግኝቷል፡፡ ፀማይ ሰላም ነው! በፀማይ ኮረብቶች፣ በፀማይ ሜዳዎች ላይ ቀን ከምሽት ሳይመርጥ ሲንጐራደድ፣ አፉ ውስጥ የቀረች አንዲት ግጥምን እንደ ብሔራዊ መዝሙር ይደጋግማታል፡፡“ፍላጐት ምኞትህ ወደብ ድንበር አለው?ብለህ አትጠይቀኝ ህልሜ አንተን መሆን ነው!ያለ ስም ቅጥያ ግቤ ሰው መሆን ነው፡፡ሰው መሆን! ሰው መሆን! በቃ ነፃ መሆን!ግጥሟ የአንድ ፋርሳዊ ፀሃፊ ነው ብሎ ጓደኛው ነበር በቃሉ ያስጠናው፡፡ ነፃ ሰው የመሆን ስሜቱን በፀማይ አፈር፣ በፀማይ አየር፣ በፀማይ ሰዎች መካከል አግኝቶታል፡፡ ከሁሉ በላይ ደግሞ ከኦሞ ወንዝ ጋር የማይደበዝዝ ፍቅር አዳብሮ ነበር፡፡ኦሞን እንደሰው እያዋራ፣ በኦሞ የቅዝቃዜ በረከት ሲረሰርስ፣ በኦሞ ፈሳሽ ውሃ ሲዳሰስ ዘላለማዊ መኖሪያው በኦሞ ዳርቻ እንደሚሆን ወስኖ ነበር፡፡ በሰለሞን ውሳኔ ግን ኦሞ የተስማማ አይመስልም፡፡ እጣውን ኦሞ እራሱ ፅፎ ሰጠው፡፡ እጣ ደግሞ የሚመርጡት ሳይሆን የሚወጣ ነው፡፡ በአንድ ወበቃማ ቀን ሰለሞን ወደ ኦሞ ሲወርድ ለሁለት ወራት ያህል ከውሀው ሲገባ ለወትሮ ሚያገኘውን ደስታ በልቡ እያሰበ ነበር፡፡ ወደ ወንዙ የሚያመራውን ጉብታ ቁልቁል እያቋረጠ ሳለ ግን የድረሱልኝ የሚመስል ድምፅ የሰማ መሰለው፡፡ እየሮጠ ወደ ወንዙ ደረሰ፡፡ ብቅ ጥልቅ የሚል ሰው ታየው፡፡ በውሀው ላለመወሰድ የሚታገል፡፡ዘሎ ከውሀው ገባ፡፡ የውሃውን ሃይል እየታገለ ሰው ወዳየበት አቅጣጫ ተምዘገዘገ፡፡ ያየውን ሰው እጅ እንዳገኘ ሽቅብ ገፋው እና ከውሀው በላይ አደረገው፡፡ በአንድ እጁ እየዋኘ ወደ ወንዙ ዳር ተጠጋ፡፡ ኦሞ እንደለማዳ ፈረስ እሺ ብሎ የሚጋልብለት ይመስል በቀላሉ አቋረጠው፡፡ የተሸከመውን ሰው አውጥቶ ከወንዙ ዳር አስተኛው፡፡ በውሀ ሊወሰድ የነበረው ሰው ግዙፍ ወንድ ነበር - ፈረንጅ! ከአለባበሱ ቱሪስት እንደሆነ ገምቷል፡፡ ከነልብሱ ምን ሊያደርግ ኦሞ ውስጥ እንደገባ ለሰለሞን ሊገባው አልቻለም፡፡“እንደኔ የከተማ ቱማታ ናላውን ያዞረው ይሆናል!” ብሎ እያሰበ ሳለ፣ የፈረንጁን ጩኸት የሰሙ ፀማዮች እየተጠራሩ ከቦታው ደረሱ፡፡ የሰውዬውን ደረት እየተጫኑ ከሆዱ የገባውን ውሀ ሲያስወጡለት ቀስ በቀስ ነፍስ ዘራ፡፡ሰለሞን የሰው ነፍስ ማትረፍ መቻሉ ከፍተኛ ደስታ አጐናፅፎት ነበር፡፡ የፀማዮች ተደጋጋሚ የምስጋና ቃል ሲቸረው በሙሉ ልብ ሲቀበል ቆየ፡፡ ያረፈባት ቤት ፈረንጁን ከውሀ ውስጥ መንጥቆ ያወጣውን ጀግና ለማየት ከአቅራቢያ መንደሮች ጭምር በሚመጡ እንግዶች እስከምሽት ድረስ ተጨናነቀች፡፡ የሰለሞን ዝና በአንድ ምሽት ፀማይን አልፎ ጅንካ ደረሰ፡፡ ከጅንካ ምድር አልፎ አዋሳ ለመድረስ አንድ ቀን አልፈጀበትም፡፡ ከአዋሳ አዲስ አበባ በዚያው ቀን ምሽት ዜናው ተሰራጨ፡፡የጋዜጠኞች ቡድን ካሜራ እና ማይኩን ደቅኖ ጀርመናዊውን ቱሪስት ያዳነውን ጀግና ለማየት ወደ ፀማይ አመራ፡፡ሰለሞን ከከተማ የመጡ ሰዎች ሊያናግሩት እንደሚፈልጉ በብሔረሰቡ አባት ሲነገረው፤ ብዙም ደስ ባይለውም እሳቸውን ላለማስቀየም ወጥቶ መጡትን ሰዎች ማነጋገር ነበረበት፡፡“ለመንደራችን ልዩ ሲሳይ ነው ይዘህ የመጣኸው!... አሁንም ከከተማ ትላልቅ ሰዎች አንተን ለማነጋገር መጥተዋል፡፡ እንደምታየው መንደራችን ብዙም አላደገችም፡፡ አንተ የሰራኸው ስራ መንደራችንን ለማስተዋወቅ ጠቃሚ ነው!” የሚለው ንግግራቸው ይበልጥ አሳማኝ ሆነለት፡፡ ጋዜጠኞቹ ሰለሞንን ሲያዩ አይናቸውን ተጠራጥረው ነበር፡፡ ከመካከላቸው አንዱ፤“ዝነኛው አርቲስት ሰለሞን?” አለ ባለማመን ስሜት ተውጦሰለሞን በአዎንታ እራሱን ነቀነቀ፡፡የፎቶ ካሜራዎች ብልጭታ ከየቦታው ሲተኮስበት፣ የካሜራዎች እይታ እሱ ላይ ሲያነጣጥርበት አንድ ነገር ገባው፡፡ ዝነኝነት ምርጫው ባይሆንም እጣው ነበረ፡፡ ቢሸሽ የማያመልጠው! እንደ ጥላ!ዝነኛው ከገፅ 17 የዞረየምትቀበለው እንስቷ ብቻ ናት፡፡በዚህ ዓይነቱ የድለላ ስራ ላይ የተሠማራው የ16 አመቱ ታዳጊ ወንዱ (ጩቤ በሚል ቅፅል ስሙ ይበልጥ ይታወቃል) በቀን ከ8-10 የሚደርሱ ወጣት እንስቶችን ባህላዊ የፅንስ ማቋረጥ ወደሚፈፀምባቸው ሥፍራዎች እንደሚወስድ ይናገራል፡፡ ወንዱ እንደሌሎች ደላሎች “ክሊኒኩ ተዘግቷል” አይልም፡፡ በክሊኒኩ ሲሰሩ የነበሩ ዕውቅ ዶክተሮች የራሳቸውን ክሊኒክ ከፍተው መውጣታቸውንና አሁን ያሉት ተማሪዎች (ተለማማጅ ሃኪሞች) ስለሆኑ “እንዳያበላሿችሁ” በሚል እያስፈራራ ጭምር ነው ሴቶችን ባህላዊ የፅንስ ማቋረጥ አገልግሎት ወደሚሰጡባቸው ሥፍራዎች አግባብቶ የሚወስደው፡፡ይሄ ደላላ አንደበቱን አምነው የተከተሉትን ተላላ ሴቶች፤ እሪ በከንቱ አካባቢ ወደሚገኝ ባህላዊ የፅንስ ማቋረጥ የሚካሄድበት ሥፍራ ይወስዳቸዋል፡፡ እኔ ወደዚህ ሥፍራ ልሄድ የቻልኩት ሜሪስቶፕስ አካባቢ ወንዱን አግኝቼው የአራት ወር ነፍሠጡር መሆኔን ከነገርኩት በኋላ ነው፡፡ እሪበከንቱ አካባቢ ስደርስ ግን አንድም ክሊኒክ የሚመስል ነገር አላገኘሁም፡፡ ሆኖም ደላላው ይሄ ዓይነቱ ጥያቄ ከእንስቶቹ ከመምጣቱ በፊት እያዋከበ በጭቃ የተሠራ ቤት ውስጥ ይዟቸው ዘው ይላል፡፡ ቤቱ ለእንስቶቹ እንጂ ወንዱን ለመሰሉ ደላሎች አዲስ አይደለም፡፡ በዚህ ቤት ውስጥ አንዲት ካርድ የምትሰጥ ሴት፣ አንድ ሃኪምና የፅንስ ማቋረጡን የሚሰራ “ባለሙያ” መኖራቸውን አይቼአለሁ፡፡ ቤቷ አንዲት ክፍል ብትሆንም በአቡጀዲ ጨርቅ ሦስት ቦታ ተከፋፍላለች - ሦስት ክፍሎች ለመፍጠር፡፡ ወደዚህች ቤት እንደገባን በወንዱ መሪነት ለካርድ ሀያ ብር ከፍዬ ከተደረደሩት ወንበሮች በአንደኛው ላይ ተቀመጥን፡፡ ከጎኔ ሁለት የምኒሊክ ት/ቤት ዩኒፎርም የለበሱ ወጣት እንስቶች ተቀምጠው ነበር፡፡ ጠጋ ብዬ ለምን እንደመጡ ጠየቅኋቸው፡፡ ጓደኛቸው አርግዛ ለማስወረድ ይዘዋት እንደመጡና ሃኪሙን ልታነጋግር ወደውስጥ እንደገባች ነገሩኝ፡፡ “አያስፈራም?” ስል ጠየቅኋቸው፡፡ እንደማያስፈራ ከነገሩኝ በኋላ የተለያዩ አማራጮች እንዳሉና አንዱን መምረጥ እንዳለብኝ ምክር ቢጤ ለገሱኝ፡፡ ወዲያው ጓደኛቸው ሃኪሙን አናግራ በመውጣቷ በተራዬ እኔደግሞ ገባሁ፡፡ ደላላውም ተከትሎኝ ገባ፡፡ የሃኪሙ ነጭ ቀለም የተቀባ የሚመስል ጠረጴዛ ለዓይን እንኳን ይዘገንናል፡፡ መሀሉ የተቦረቸፈ ስትሬቸር ግድግዳው ጥግ ይታየኛል፡፡ የእርግዝና ማዳመጫ መሳሪያ ጠረጴዛው ላይ ተቀምጧል፡፡ በቃ እኒሁ ናቸው የህክምና ቁሳቁሶቹ - ሌላ ነገር የለም፡፡ “ስንት ወርሽ ነው?” ሃኪሙ ጠየቀኝ“አራት ወር ገደማ ይሆነኛል” አልኩት- የውሸቴን መሆኑ እንዳይታወቅብኝ በመጠንቀቅ “ችግር የለም እስከ ሠባት ወር እንሠራለን ---- ትንሽ ግን ክፍያው ይወደድብሻል” አለኝ ሃኪሙ “እኔ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነኝ---- ጓደኛዬ ነው የሚከፍልልኝ፤ዋጋውን ንገረኝና ገንዘቡን ተቀብዬው እመጣለሁ” 
“እሺ አራት ወር ከሆነሽ ሠባት መቶ ብር ትከፍያለሽ፤በመድሃኒት ወይም በማሽን ይሰራልሻል፤ ብሩ ተወደደብኝ ካልሽ ደግሞ በግሉኮስ ላስቲክ ሊሰራልሽ ይችላል” ሲለኝ የእያንዳንዱን ዋጋ 
እንዲነግረኝ ጠየቅሁት፡፡ እሱም ማብራራቱን ቀጠለ “በመድሃኒት ለሚሠራው ነው ሠባት መቶ ብር ያልኩሽ፤ በማሽን ከሆነ ስድስት መቶ ብር ትከፍያለሽ፤ በግሉኮስ ሶስት መቶ ብር” ከጓደኛዬ ጋር ልምከርበት አልኩትና ሃኪሙን አመሥግኜው ወጣሁ፡፡ ከቤቱ እንደወጣን “ቤቱ ደስ አላለኝም” በሚል ሰበብ ወንዱ ሌላ ቦታ እንዲወስደኝ ጠየቅሁት፡፡ “ችግር የለም” አለኝና መንገዳችንን ቀጠልን - ወደ ሁለተኛው አማራጭ፡፡ ብዙም ሳንደክም ነው የደረስነው፡፡ “በርጌስ ክሊኒክ” የሚል ማስታወቂያ ያለበት የህክምና ተቋም ውስጥ ይዞኝ ገባ - ፈቃዴን ጠየቀኝ በኋላ፡፡ ክሊኒኩ መጀመሪያ ከገባንበት ቦታ በንፅህና አስር እጅ የተሻለ ነው፡፡ ታካሚዎች ተራ ይጠብቃሉ፡፡ ወንዱ ልክ እንደጓደኛው እጄን ይዞኝ ለካርድ ክፍል ሠራተኞች ምልክት ሠጥቷቸው ወደ ኪሙ ክፍል ወሰደኝ፡፡ ታዳጊው ደላላ ለክሊኒኩ ቤተኛ መሆኑ ያስታውቃል፡፡ ይሄኛው እንኳን የክሊኒክም ወግ አለው፡፡ የተራቀቁና ዘመን አመጣሽ ባይሆኑም የተለመዱት የህክምና መሳሪያዎች ይታያሉ፡፡ ዶክተሩ ወንዱን ስላየ ነው መሠለኝ በቀጥታ “ስንት ወርሽ ነው?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡ “አራት ወሯ ነው፤ ጓደኛዋ አደራ ብሎኝ ነው” ሲል ወንዱ ፈጠን ብሎ መለሰ እሺ አሁን ትሠሪያለሽ?” የዶክተሩ ጥያቄ ነበርዋጋውን እንዲነግረኝ እና ከጓደኛዬ ጋር ተማክሬ እንደምወስን ገለፅኩለት፡፡ “እዚህ ክሊኒክ ግሉኮስ የሚባል ነገር የለም፤ ዋጋው ደግሞ አንድ ሺህ ሠባት መቶ ብር ነው” አለኝ ፍርጥም ብሎ፡፡ ከሃኪሙ ክፍል እንደወጣን ለወንዱ የፍርሃት ስሜት ውስጥ እንደገባሁና እዚህ ክሊኒክ ውስጥ ያሰራች አንዲት ሴት ባገኝ ሁኔታውን ጠይቄያት እንደምደፋፈር ነገርኩት፡፡ እኔ ግን የፈለግሁት ሊያሰሩ የመጡ ሴቶችን ለማነጋገር ነበር፡፡ ወንዱም ያልኩትን ለመፈፀም ለአፍታ እንኳ ሳያመነታ “ተከተይኝ” ብሎ ይዞኝ ሄደ፡፡ ጥግ ጥጋቸውን ይዘው የሚያቃስቱ ሴቶች ነበሩ፡፡ በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ ባሉ አልጋዎች ላይ በሆዳቸው የተኙም ሴቶች ተመልክቼአለሁ፡፡ ወደ አንዷ ሴት ጠጋ አልኩና ጠየቅኋት “ህመሙ ለትንሽ ደቂቃ ነው አትፍሪ” የሚል ማበረታቺያ ሰጠችኝ፡፡ “የስንት ወር ነው ያሰራሽው?” አልኳት፡፡ “እኔ መውለድ ነበር የምፈልገው፤ሆኖም የአረብ አገር ቪዛ መጣልኝና ላስወርድ ፈለግሁኝ፤ ሜሪስቶፕስ  ጄ ወርሽ ገፍቷል አንሰራም ሲሉኝ ደላላው ወደዚህ አመጣኝ” አለችኝ፡፡ ልጅቱ በነበረችበት ክፍል ውስጥ 18 ሴቶች ነበሩ፡፡ ዘጠኙ ወደ አረብ አገር የሚሔዱ ናቸው፡፡ የዕለቱ ዕለትና በንጋታው የሚበሩ ሴቶችም ነበሩ፡፡ ከክፍሉ ስንወጣ ለደላላው ሀያ ብር ሠጠሁትና ስልኩን ተቀብዬ እንደምደውልለት ነግሬው ተለያየን፡፡ በዚያው ሰሞን በአንድ የዘመድ ለቅሶ ላይ በሜሪስቶፕስ ክሊኒክ ውስጥ የምትሰራ አንዲት  ስተር አገኘሁና በፅንስ ማቋረጥ ዙሪያ አንዳንድ ነገር ተጨዋወትን፡፡ ሲስተሯ እንደነገረችኝ ወደ ክሊኒኩ ፅንስ ለማቋረጥ ከሚመጡ ሴቶች አብላጫውን ቁጥር የሚይዙት የአረብ አገር ተጓዥ ሴቶች ናቸው፡፡ እሷን የሚያስጨንቃት ታዲያ ሦስት ወር ከሆናቸው በኋላ ወደክሊኒኩ መጥተው የሚመልሷቸው ነፍሰጡር ሴቶች ጉዳይ ነው፡፡ ክሊኒኩ ከፀነሱ ሦስት ወር ለሞላቸው እንስቶች አገልግሎት እንደማይሰጥ ሲነግራቸው፤ ወደ ህገወጥ ቦታ መሄዳቸው ክፉኛ እንደሚያሳስባት ትናገራለች፡፡ “አንዲት ሴት እስከ ሁለት ወር የሚደርስ ፅንስ በመድሀኒት ማቋረጥ ትችላለች፡፡ አንድ ፍሬ ክኒን በመጀመርያው ቀን ትውጥና በሶስተኛው ቀን ደግሞ አራት ፍሬ እንድትውጥ ይደረጋል፡፡ አብዛኛዎቹ ሴቶች ግን መድሃኒቱን አይመርጡም፡፡” ያለችው ሲስተሯ፤ ምክንያቱን ስንጠይቃቸው አረብ አገር ስለሚሄዱ እንደሆነ ይነግሩናል ትላለች፡፡ አንዳንዶቹ ግን ፅንሱ በመጀመሪያ በዋጡት መድሃኒት ብቻ የሚወርድ ስለሚመስላቸው በዛው ይቀራሉ፤ ይሔ ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል ብላለች፡፡ “አንዳንዶቹ እንደውም የሔዱበት አገር ተመርምረው ነፍሠ ጡር መሆናቸው ሲታወቅ ተመልሠው ይመጣሉ፤ይሔም ሌላ ኪሳራ ነው” የምትለው ባለሙያዋ፤ አረብ አገር እሄዳለሁ ብላ ፅንስ ለማቋረጥ የመጣች አንዲት ሴት የገጠማትን አሳዛኝ አደጋ ታስታውሳለች፡፡ “ልጅቷ ወደ አረብ አገር ልትሄድ ስትል ነው ለማስጠረግ የመጣችው፤ ኗ በመግፋቱ አንሠራም አልናትና ሌላም ቦታ መሄድ እንደሌለባት መክረን ሸኘናት፤ እሷ ግን ባህላዊ ፅንስ የማቋረጥ አገልግሎት የሚሰጥበት ቦታ በመሄድ በሠጧት የግሉኮስ ላስቲክ ምክንያት ማህፀኗ በመበሳቱ፤ደሟ ወደ ሆዷ ፈስሶ ህይወቷ አለፈ” ብላለች - ሲስተሯ፡፡ ተዘዋውሬ ባየኋቸው የሜሪስቶፕስ ክሊኒኮች አብዛኛዎቹ አገልግሎት ፈላጊዎች ወደአረብ አገር የሚጓዙ ሴቶች መሆናቸውን ለማወቅ ችያለሁ፡፡ በዚህም ምክንያት በቀን ጥቂት ሴቶችን ብቻ ያስተናግዱ የነበሩ የክሊኒኩ ቅርንጫፎች፤ አሁን ከአቅማቸው በላይ እየሆነባቸው ቀጠሮ እስከ መስጠት ደርሠዋል፡፡ ክሊኒኩን ያጨናነቁት በዋናነት የአረብ አገር ተጓዥ ሴቶች ቢሆኑም ክሊኒኩ በፊት ከሚሠጠው በማሽን የመጥረግ አገልግሎት በተጨማሪ በመድሀኒት የመጥረግ አገልግሎት መጀመሩም የተጠቃሚዎቹን ቁጥር እንደጨመረው ሲስተሯ ትናገራለች፡፡ “በመድሃኒት ፅንስ ማቋረጥን ብዙዎች እንደጨዋታ ነው የሚያዩት፤ ምክንያቱም እምብዛም የህመም ስሜት የለውም” የምትለውባለሙያዋ፤ ዋናው ነገር ሴቶች ፅንስ ለማቋረጥ ብለው በየመንደሩ በመሄድ ህይወታቸውን ለአደጋ ከማጋለጥ መቆጠባቸው ነው፤ ማናቸውንም ጉዳዮች የህክምና ባለሙያዎች በማማከር ቢፈፅሙት ራሳቸውን ከሞት አደጋና ከጤና እክሎች ሊጠብቁ ይችላሉ ስትል ትመክራለች፡፡ በአሚን ጠቅላላ ሆስፒታል፣ የፅንስና የማህፀን ስፔሻሊስት ዶክተር ገላኔ ሌሊሳ ሲናገሩ፤ ማንኛውም ህክምና በትክክለኛ ባለሙያ መከናወን እንዳለበት ገልፀው፣ የእርግዝናው እድሜ እየገፋ በመ ቁጥር አደጋዎቹም እየከበዱ እንደሚሄዱ ያስረዳሉ፡፡ አንዲት ሴት በመጀመሪያዎቹ አስራ ሁለት ሳምንት የምታደርገው ውርጃዎች ትንሽም ቦሆን ችግር አላቸው ምንኛውም ሴት እስከ ስምንት ሳምንት ያልሞላው ጽንስ አንዳንዴ በተፈጥሮም የሚቋረጥበት አጋጣሚ ይኖራል፤ በህክምናም ሊቋረጥ ይችላል የሚሉት ዶ/ር ገላኔ፤ ይሄ የተለየ ችግር ያመጣል ተብሎ አይታሰብም ብለዋል፡፡ አንዲት ሴት ፅንሷ ከተቋረጠ በኋላ እረፍት ሳታደርግ ለጉዞ ብትነሳ ወይም ወደ ስራ ብትገባ ችግር ያጋጥማታል ማለት አይደለም ያሉት ዶ/ር ገላኔ፣ ነገር ግን ማንኛውም ህክምና ሁሌም ክትትል ያስፈልገዋል፤ ህክምናው ትክክለኛ ውጤት ማስገኘቱን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ለምሳሌ ከህክምና በኋላ፣ እንደተጠበቀው ፅንሱ ሳይቋረጥ ቢቀር በጣም አስጊ ስለሚሆን ክትትል ማድረግ ይኖርባታል ብለዋል ዶ/ር ገላኔ፡፡ የፅንስ ማቋረጥ ህክምና በሁለት መንገድ እንደሚካሄድ ዶ/ር ገላኔ ጠቅሰው፣ አስር ሳምንት ያልሞላው ጽንስ በመድሀኒት ሊቋረጥ ይችላል፤ የፅንሱ እድሜ ከዚህ በላይ ከሆነ ግን የግድ መጠረግ ይኖርበታል ብለዋል፡፡ ከሁለቱ ዘዴዎች መካከል በመድሃኒት ጽንስ የማቋረጥ ዘዴ ተመራጭ ነው፣ ምክንያቱም ከማህፀን ጋር ምንም ንክኪ ስለሌለው የማህፀን መኮማተርን አያስከትልም፡፡ ስለዚህ ያልተፈለገ እርግዝና ሲከሰት ጊዜው ሳያልፍ ወደ ትክክለኛው የህክምና ባለሙያ መሄድ ያስፈልጋል ሲሉ ዶ/ር ገላኔ ይመክራሉ፡፡ 

Mar 29, 2013

ዕውን ኢትዮጵያን የሚመሯት ኢትዮጵያውያን ናቸው?

(ምንጭ፡ ፍኖተ ነጻነት)

ዕውን ኢትዮጵያን የሚመሯት ኢትዮጵያውያን ናቸው?የኢትዮጵያ ክብር ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽ ኮሚቴና ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር በመሆን ያዘጋጁት ሰላማዊ ሰልፍ አላማ ለፋሺስቱና ለጦር ወንጀለኛው ግራዚያኒ በጣሊያን ሀገር የተገነባውን መናፈሻ ስፍራና ሀውልት ለመቃወም ነው፡፡ ይህ ግለሰብ ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመውን ዘግናኝ ጭፍጨፋ ታሪክ አይዘነጋውም፡፡
ግራዚያኒ በመርዝ ጋዝ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ጨፍጭፏል፤ ከየካቲት 12 ጀምሮ ለቀናት በዘለቀው የበቀል ጭፍጨፋም በአካፋ ሳይቀር በአዲስ አበባና በአካባቢዋ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በግፍ ጨፍጭፏል፡፡ ግራዚያኒ በወቅቱ በሰጠው ትዕዛዝ የፋሺስት ወታደሮች ህይወት ያለውን ተንቀሳቃሽ ፍጥረትን ሁሉ ገድለዋል፡፡ ይህ እሩቅ በማይባል ጊዜ የተፈፀመ ድርጊት ነው፡፡
የኢህአዴግ ባለስልጣናት ለእንዲህ አይነቱ ጨፍጫፊ የተገነባን ሀውልት ለመቃወም በወጡ ዜጎች ላይ የወሰዱት የእስር ተግባር እውን ኢትዮጵያን የሚመሯት ኢትዮጵያውያን ናቸው? አስብሎናል፡፡ ኢህአዴግ በስልጣን ዘመኑ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ በተደጋጋሚ ጥፋት ፈፅሟል፡፡ ሀገራችንን የባህር በር ማሳጣትን ጨምሮ ሀገራዊ ስሜትን አንኳሶ ጠባብ የብሔር ስሜት እንዲንሰራፋ አድርጓል፣ ታሪክን ለስልጣኑ መደላድል ሲል በራሱ መንገድ የሚያዘጋጀው የኢህአዴግ መንግስት ኢትዮጵያን ጠፍጥፎ እንደሰራት ሁሉ ደርግን ለመጣል ካደረገው ትግል ውጪ ያለውን የአርበኞች ተጋድሎ እውቅና ሲሰጥ አይታይም፡፡
መንግስት ለፋሽስቱ ሩዶልፍ ግራዚያኒ የተገነባውን ሀውልት በመቃወም የወሰደው እርምጃ አለመኖሩ ሳያንስ ግራዚያኒን ለማውገዝ የወጡ ዜጎችን በመደብደብና በማንገላታት ማሰሩ አሳፍሮናል፡፡ ለዜጎቻቸው እና ለሚመሯት ሀገር ክብር የማይሰጡ ይልቁንም የጦር ወንጀለኛና ፋሺስትን ለመቃወም የወጣን ዜጋ ማሰርራቸው የኢህአዴግ ባለስልጣናት ወገንተኝነታቸው ለዜጎቻቸው ነው ወይስ ለፋሺስት? የሚል ዘግናኝ ጥያቄ እንድንሰነዝር ያስገድደናል፡፡
በሰልፉ ላይ የተገኙት ሀገር ወዳድ ዜጎች በማን አለብኝነት ሲታሰሩ ድባደባ ተፈፅሞባቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የታሳሪዎቹን የኢሜይልና የማህበራዊ ገፅ የይለፍ ቃል (password) በግዳጅ የሚቀበሉ የደህንነት ሀይሎች ተልከውባቸዋል፡፡ ይህን ቅጥ ያጣ አንባገነናዊ ድርጊት የፈፀመው ወይም እንዲፈፀም ትዕዛዝ የሰጠው አካል ማንነት ተጣርቶ የማስተካከያ እርምጃ ሊወሰድ ይገባዋል፡፡ በየምክንያቱ ዜጎችን ማሰር የለመደው አንባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት ምን ያክል ኢትዮጵያዊነትን እየተዋጋ እንዳለም የሚያሳይ ድርጊት ነው፡፡ መሰረቱ ዜጎች በማንኛውም ጉዳይ ላይ የተቃውሞም ሆነ የድጋፍ ሰልፍ ማድረግ እንደሚችሉ ህገመንግስቱ ደንግጓል፡፡ ይህን መብት ዜጎች እንዳይጠቀሙ ያፈነው መንግስት፣ ኢህአዴግን የሚደግፉ አልያም በራሱ ከተጠሩ ሰልፎች ውጪ ዜጎች እንዳይሳተፉ በአሰራር ከልክሏል፡፡ ይህ የመብት ረገጣ ከመሆኑም በላይ በዜጎች መካከል 1ኛ ደረጃና 2ኛ ደረጃ ዜግነትን ያስቀመጠ ነው፡፡
የኢህአዴግን ባናውቅም፣ እኛ ኢትዮጵያውያን በቅኝ ገዢዎች የተዋረደ ስነልቦና የለንም፡፡ ሆኖም የግል ጥቅማቸውን ለማደላደል ሲሉ ለቅኝ ገዢ ጠላቶቻችን ያደሩ ባንዳዎች እንደነበሩ ታሪክ በጥቁር መዝገቡ ሸክፎታል፡፡ ይህን አሳፋሪ ተግባር በጣሊያን ወረራ ወቅት የፈፀሙ ኢትዮጵያውያን ለልጅ ልጆቻቸው የሚያስተላልፉት አንገት ቀና የሚያደርግ ታሪክ አይኖርም፡፡
በዚህም ዘመን ተመሳሳይ ክህደት የሚፈፅሙ አካላት መኖራቸው አይጠረጠርም፡፡
የኢህአዴግ መንግስት በይፋ ለጦር ወንጀለኛውና ለፋሺሽቱ ሩዶልፍ ግራዚያኒ የተሰራውን ሀውልት በይፋ ካለማውገዝ ባለፈ ለተቃውሞ የወጡትን ኢትዮጵያውያን በግፍ የማሰሩን ምክንያት ስንመረምር አንድ መራራ እውነት እንረዳለን፤ ይኸውም ጣሊያን ለኢህአዴግ መንግስት ዋንኛዋ ለጋሽ ሀገር መሆኗ ነው፡፡ ይህ የኢህአዴግ መንግስት ተግባር በስልጣን ዘመኑ በኢትዮጵያዊነት ላይ ከፈፀማቸው ክህደቶች እኩል በታሪክ ጥቁር መዝገብ የሚቀመጥ ይሆናል፡፡

ነገን የተሻለ ቀን ለማድረግ፤ ዛሬ ነው መነሳት፤ ይድረስ ለሀገሬ ወጣቶች

ሉሉ ከበደ
ከዘር ማንነታችን በፊት ሰብአዊ ሰውነታችን፤ ከጎጠኝነታችን በፊት ኢትዮጵያዊነታችን፤ ከሸፍጥ፤ ከተንኮል፤ ከመሰሪነታንችን በፊት ቅንነታችን፤ ከፍርሀታችን በፊት ድፍረታችን፤ እርስEthiopian flag, Green, yellow and red በርስ ከመጠራጠራችን በፊት መተማመናችን፤ ከመፍረክረካችን በፊት በጽናት መቆማችን፤ ከልዩነታችን በፊት አንድነታችን፤ ወያኔ ዛሬ ኢትዮጵያውያንን ከከተተበት መቀመቅ ውስጥ የሚያወጣን ብቸኛ መፍትሄ ከላይ የደረደርኩት ነገር ብቻ የመስለኛል።
ነጻ አውጭ ነን የሚሉ የዘር ፖለቲከኞች፤  ህዝብ መክሮ ዘክሮ ከዚህ ዘር ነጥሉን፤ ከዚያ ዘር ነጥሉን፤ ነጻ አውጡን፤ ብሎ ባይመርጣቸውም፤  በስራቸው ለማሰባሰብ ለፈለጉት ህዝብ ታሪክ እየፈጠሩ መስበካቸው እንዳለ ሆኖ፤  እንዲዋጋላቸው፤ እንዲታገልላቸው ሲያደርጉም የዚያኑ ያህል የውሸት ተስፋ እየመገቡም ነው። ለምሳሌ በትግሉ ዘመን የሻእቢያ ካድሬዎችና ፕሮፓጋንዳ ሰራተኞች ዘወትር ህዝቡን ሲሰብኩ፤ ኤርትራ ነጻነቷን ስታገኝ እያንዳንዱ ኤርትራዊ ዜጋ ምንም ስራ ሳይሰራ ከወደቦች በሚገኝ ገቢ ብቻ በቀን ከሰላሳ እስከ አርባ ብር ገቢ ይኖረዋል እያሉ ይሰብኩ ነበር።  ከነጻነት በኋላ ኤርትራ የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፑር ትሆናለች ይሉ ነበር። እነሆ ነጻነቱ ሀያ ሁለት አመታትን አስቆጠረ፤ የኤርትራ ህዝብ በቀን ሰላሳ ብር በነፍስ ወከፍ እየታደለው ነው? ኦሮሞን ነጻ እናወጣለን የሚሉትን ሰዎች ብትሰሟቸው ወርቁ፤ ቡናው፤ ማእድኑ የብቻቸው እንደሚሆንና ከነጻነት በኋላ እንደሚበለጽጉ ነው የሚቀባዥሩት። ኦጋዴንን ነጻ እናወጣለን የሚሉትን ሶማሌዎች ብትሰሟቸው ጋዙ፤ ነዳጁ የብቻችን ይሆናል ከነጻነት በኋላ እያንዳንዱ ሰው ይበለጽጋል ነው የሚሉት። የብቻ ተጠቃሚነት ቅዥት፤ ስግብግብነት፤ ራስ ወዳድነት፤ በነጻነት ስም የቡድን ጥቅም የስልጣን ምኞት ቅዥት።
አንድ ህዝብ አንድ ቋንቋ ስለተናገረ፤ አንድ ባህል ስለተጋራ፤ ባንድ አካባቢ ስለኖረ፤ ምንጊዜም አብሮ በሰላም ይኖራል ማለት አይደለም። ርእዮተ አለም፤ ሀይማኖት፤ ጥቅም፤ ስልጣን፤ ንኡስ ነገድ፤ የአካባቢ ልዩነት፤ በሰው ልጆች መካከል ግጭትና አለመግባባትን፤ ብሎም ጦርነትና ፍጅትን ለመፍጠርም ሆነ ለማስነሳት በቂ ሀይል አላቸው። ሶማሌዎች አንድ ቋንቋ፤ አንድ ባህል፤ አንድ መልካምድር የሚጋሩ ናቸው።ለምንድነው አብረው መኖር ተስኖአቸው መንግስት አልባ ሆነው የቀሩት?
ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማሪያም “አቡሸማኔው ትውልድ” በሚለው የእንግሊዝኛ ጽሁፋቸው ውስጥ እንዳስቀመጡት “…ከኢትዮጵያ ህዝብ አርባ አንድ ሚሊዮን የሚሆነው እድሜው ከአስራ ስምንት አመት  በታች እንደሚሆን ይገመታል። ካጠቃላዩ ህዝብ ከግማሽ በላይ ማለት ነው። ዩኒሴፍ የተባለው የህጻናት መርጃ ድርጅት እንደሚገምተው ከአምስት አመት በታች ያሉ ህጻናቶቻችንን ከግማሽ በላይ የሚገላቸው የምግብ እጦት ነው። ኢትዮጵያ አምስት ሚሊዮን የሚገመቱ ወላጅ አልባ ህጻናት አሏት። 800 000 ያክሉ ወላጆቻቸውን ያጡት በኤድስ በሽታ ምክንያት እንደሚሆን ይገመታል። በከተሞች አካባቢ የስራ አጥ ወጣቶች ቁጥር 70 በመቶ በላይ መድረሱ ይገመታል። በ2011 የወጣ የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት ሪፖርት እንደሚያመለክተው 77.8 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ወጣት ኑሮን የሚገፋው በቀን ከሁለት የአሜሪካን ዶላር ባነሰ የገንዘብ አቅም ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች ስራ ለማግኘት፤ ለመኖር ሲሉ፤ ራሳቸውን ለመሸጥ ይገደዳሉ። በ 2010 የወጣ የአሜሪካ መንግስት የሰባዊ መብት ሪፖርት እንዳመለከተው የኢህአደግ ድርጅት አባል ያልሆነ ወጣት ስራ ለማግኘት ከቀበሌ የድጋፍ ደብዳቤ አያገኝም። ትምህርት ለመማር፤ ስራ ለመቀጠር፤ በግል ስራ ለመሰማራት የፓርቲ አባልነት መስፈርት ሆኖ ተቀምጧል።…..”
ታዲያ ለዚህ ትውልድ እየመሸ ነው እየነጋ? ለዚህች አገር እየመሸ ነው እየነጋ ? የጥቂት ህውሀት መሪዎችና ቅጥረኞቻቸው ህይወትና እድል እየለመለመና እያማረ ሲሄድ፤ የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ህይወት እየጨለመና እያሽቆለቆለ ሲሄድ፤ የመላው ኢትዮጵያ ወጣቶች የነገ ህይወት ጸሊም ተስፋ ተጋርዶበት፤ አስፈሪውን መጪ ጊዜ ሁላችንም እያየነው ተነስተን አንድ ነገር ማድረግ የተሳነን ለምን ይሆን?
በሚሊዮኖች ለሚቆጠረው ወጣት ትውልድ በዚህ ዘረኛ ገዢ ቡድን ምክንያት ህይወት ጭለማ ከሆነችበት፤ የተፈጥሮ መብቱን፤ የዜግነት መብቱን በጥቂት ማፊያ ቡድን ካስነጠቀ፤ የወደፊት ህይወቱን፤ እድሉን፤ የጋራ ሀገሩን ለዚህ አጥፍቶ ጠፊ የዘረኞች ቡድን መቆመሪያ አሳልፎ ከሰጠ፤ ይህ ወጣት እንዴት ለሀገሩና ለወገኑ መድህን ሊሆን ይችላል? ወጣትነት ለውጥ ፈላጊነት ነው። ወጣትነት አዲስ ነገር ናፋቂነት ነው። ወጣትነት የሀገር ተረካቢ ባላደራነት ነው።
በ1998 እኤአ ናይሮቢ ኬንያ ውስጥ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመንግስታቸው ጋር ከፍተኛ ግጭት የፈጠሩበትና ከፖሊስ ጋር አደባባይ የተፋለሙበትን አንድ አጋጣሚ ላንሳ፤ በዚያን ጊዜ የነበረው የሞይ መንግስት የሆነ መሬት ለኢንቨስተሮች በሊዝ ሊሸጥ ይስማማል። ወዲያው ጉዳዩ ለህዝብ ውይይት ይፋ እንደተደረገ፤ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከየተቋሙ በቁጣ ተፈንቅለው ድርጊቱን ለመቃወም ያልተፈቀደ ሰልፍ ይወጣሉ። የተማሪዎቹ ቁጣ ሊሸጥ የታሰበው መሬት በደን የተሸፈነና ለአራዊትም መኖሪያ ለተፈጥሮውም ጥበቃ ሀገሪቱን የሚጠቅማት በመሆኑ፤ “ሀገራችንን ነገ የምንረከብ እኛ ስለሆን፤ ይህ መንግስት ሀላፊነት የጎደለው ስራ እንዲሰራ አንፈቅድም፤ ለም መሬታችን ለማይረባ የባእድ ኢንቨስትመንት አይሸጥም” በማለት አደባባይ ወተው ከመንግስታቸው ጋር ግብግብ ገጠሙ። ህዝቡም ከያቅጣው ደገፋቸው። መንግስት አቋሙን ቀይሮ ሌላ አማራጭ ለመፈለግ ተገደደ።
ድፍን ኢትዮጵያ እለት በእለት ሲቸበቸብ የኛ ተማሪዎች በዘር ተቧድነው በድንጋይ ይደባደባሉ። ወያኔ መላውን የሀገራችንን ምድር ከየትም አለም እየጠራ፤ ስለአጭር ጊዜም ሆነ ስለረጅም ጊዜ ጉዳቱ ምንም አይነት ጥናትና የህዝብ ውይይት ሳያደርግ በርካሽ ምድራችንን መሸጡን ቀጥሏል። ከሰላሳ አምስት በላይ ከሚሆኑ አገሮች ለሚመጡ ወይም ለመጡ 8000 በላይ ባለሀብቶች የንግድ እርሻ ፍቃድ አድሏል። መሬቱ ለባለሀብቶቹ ሲሰጣቸው፤ ዜጎች ከቀያቸው በሀይል እንዲወጡ፤ መኖሪያቸው እየፈረሰና ልጆቻቸው ደጅ እየተበተኑ፤ እንዲፈናቀሉ እየተደረገ፤ እንቢ ካሉ እየታሰሩ፤ እየተገረፉና እየተገደሉ ነው። በቅርቡ 150 የሚሆኑ የሰሬ ብሄረሰብ ወገኖቻችን በወያኔ ሚሊሺያ ተጨፍጭፈው መሬቱ ለባእዳን ባለሀብቶች ጸድቶላቸዋል።  በሚቀጥሉት አስርና አስራአምስት አመታት ውስጥ ወያኔ ስልጣን ላይ ከቆየ ለራሳችን ፍጥነቱን የማንቆጣጠረው የህዝብ ብዛታችን ሲፈነዳ፤ መሬታችን ሁሉ በባእዳን እጅ ገብቶ የምናርሳት ኩርማን መሬት ቀርቶ፤ መቆሚያ መቀምጫ እንደምናጣ ለመተንበይ ነብይ መሆን አያስፈልግም። ለመኖር ስንል ሀገራችንን ከወረራት አለም ጋር ጦርነት መግጠማችን የማይቀር ነገር ነው። ወያኔ በመርዝ እንዲያልቁ ካላደረጋቸው የህዝባችን ብቻ ሳይሆን የቤት እንስሳቶቻችንም ቁጥር ያድጋል፤ ወደፊት የሚሰማሩበትም ቦታ ይጠፋል። ዛሬ ወያኔ ብቻ ነው ዋናው ገዳያችን። ያኔ ግን እርሻቸውንና ሀብታቸውን ንብረታቸውን የሚጠብቁት የአለም ሀብታሞች ወታደሮቻቸውን ልከው ያግዙታል። በደንብ እንገደላለን።
ያሁሉ ከመምጣቱ በፊት፤ ኢትዮጵያዊው ወጣት ትውልድ ዛሬ ላይ ቆሞ እየተጓዘበት እየቀረበው የመጣውን ጨለማ ጊዜ መመልከት ከቻለ፤ ፈጥኖ መነሳትና ህብረተሰቡን አስከትሎ የወያኔን መንግስት ማስወገድና ሀገሪቱን ማዳን መጪውን የጨለመ ተስፋ ወደ  ብርሀን መለወጥ አለበት። በዘር ተከፋፍሎ መናቆሩን ከቀጠለ፤ እርስ በርሱ ሲባላ ወያኔና የባእድ ሽርካዎቹ ቅርጥፍ አድርገው በልተውት ምድሪቷን ያለስጋት ይኖሩባታል።
አቶ አስገደ ገብረስላሴ “መለስ ከደደቢት እስከ ህልፈት” በሚለው የጽሁፍ ስራቸው ውስጥ እንዳስቀመጡት፤  “….የሀገራችን መሪዎች ልጆችና ዘርማንዘራቸው በመንግስት ባጀት ያለ አንዳች የትምህርት ውድድር በቻይና፤ በአሜሪካ፤ በአውሮፓ፤ በደቡብ ኮርያ፤ ከፍተኛ ትምህርት በሚማሩበት፤ ፍትሀዊ የሆነ የሀገር ሀብት ክፍፍል በሌለበት፤ የሀገራችን ሀብት በህውሀትና ግብረአብሮቻቸው በባለቤትነት በተያዘበት፤ ህዝብ መጠለያ የማግኘት መብት ባጣበት፡ህብረተሰብ በሙሉ በግድ የህውሀት ኢህአደግ አባል ካልሆነ የማይኖርበት ሀገር ሆና እያለች፤ የትምህርት ነጻነት በሌለበት፤ የትምህርት ተቋማት ሁሉ የህውሀት ኢህአደግ አባላት መመልመያና ማደራጃ  በሆነበት፤ የሴፍቲ ኔት፤ የድርቅ፤ ማናቸውም እርዳታ ሁሉ ለህውሀት አባላትና ደጋፊዎች ብቻ የሚሰጥበት፤…ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሁለተኛ ዜጋ የሆኑበት ሁኔታ እያለ መለስ እንዴት ዲሞክራሲያዊና ተራማጅ ሊባል ይችላል?….”
ዛሬ ስልጣን ላይ ተጣብቀው ሞት ነው የሚያስለቅቀን የሚሉት የትግራይ ናዚዎች ስልጣኑን ላለመልቀቅ ሲሉ የኢትዮጵያን ህዝብ እየገፉ የሚወስዱበት መቀመቅ አሁን ካለንበት ከደረስንበት ቦታ ላይ ቆመን የነገውን ስንመለከተው ወለል ብሎ የሚታይና የተለያዩ መድረሻዎችም ያለው ነው።
አንድ ሁለት እውነታ ላንሳ። ሩዋንዳ ውስጥ ሶስት ዘሮች አሉ። ሁቱ፤ ቱትሲና ቱዋይ ። እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር በ1919 አም ጀርምኖችን ተክተው የበልጅየም ቅኝ ገዢዎች ሩዋንዳን ተቆጣጠሩ። ከሌሎች የአውሮፓ ቅኝ ገዢዎች ጋር ሲነጻጸሩ ቤልጅየሞች እጅግ ጨካኝና ግፈኛ ቅኝ ገዢዎች መሆናቸው ይነገራል። ስለተቆጣጠሩት አገር ህዝብ ምንም አይነት ደግነት የላቸውም። ላገሩ የተፈጥሮ ሀብት፤ ለህዝቡ ባህል፤ ለመሬቱ … ወዘተ። ዋናው እስትራቴጂያቸው ከህዝቡም ከመሬቱም ማናቸውንም ጠቃሚ ነው ብለው ያመኑትን አገራቸው ቤልጅየምን የሚገነቡበትን ሀብት መቦጥቦጥና ወደሀገራቸው ማሻገር ብቻ ነበር። ልክ  ያለፈ ሀያ ሁለት አመታት ጀምሮ ወያኔ  እያደረገ እንዳለው ሁሉንም ነገር ለትግራይና ወደትግራይ ክልል ማለት ነው። ቤልጂየሞች እንደመጡ ጀምሮ የነዋሪዎቹን የዘር ግንድ ልዩነት ሲያጠኑ ቆይተው በ1933 ላይ ሁቱ የትኛው ቱትሲ፤ ትዋይ አውቀው ሲጨርሱ፤ ሁሉም በየብሄረሰቡ መታወቂያ እንዲሰራለት፤ ሩዋንዳዊ ነኝ ሳይሆን የተለጠፈለትን የዘር አይነት እንዲጠራ ተደረገ። አሁን የኛ ቅኝ ገዥዎች ጀግኖቹ የትግራይ ፍልፈሎች እንዳደርጉን ማለት ነው። ሁቱዎች ብዙሀን ናቸው። ቱትሲዎች ሀዳጣን ናቸው 15%። የኛ ትግሬዎች እንዲያውም ከዚያ ያነሱ ናቸው 5%።  አምስት እጅ የምለው አጠቃላዩን የትግራይ ህዝብ እንጂ በጦር ሀይል አገሪቱን ተቆጣጥረው በመግዛት ላይ ያሉትን ጥቂቱን የህውሀት መሪዎች አይደለም። በማናቸውም ጽሁፌ ውስጥ እማወራው የትግራይን አርሶ አደርና ሰራተኛ ህዝብ አይመለከትም። ህዝቡ ለራሱ ከማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ  በከፋ መልኩ ታፍኖ ተረግጦ የሚኖር ነው።  ቤልጂየሞች የከፋፍሎ መግዛቱን ሂደት ሲያስተካክሉ ቱትሲዎችን ቀድሞውንም የሀገር ባላባት ሆነው ራሳቸውን ከፍ አድርገው ይኖሩ የነበሩትን አቀፉና ብዙሀኑን ሁቱዎችን ገሸሽ አደረጉጓቸው። የወያኔ ገዢዎቻችን ትግሬን አቀፉ፤ የቀረውን የኢትዮጵያ ህዝብ አርባ ክንድ አራቁት።  የመንደር፤ የጎሳ፤ የአካባቢ መሪ ተብለው ህዝቡ የሚያውቃቸውን የሚቀበላቸውን በሙሉ ቤልጂየሞች እያባረሩ በምትካቸው በታማኝነት የሚመለምሏቸውን ሀዳጣን ቱትሲዎችን አስቀመጡ። ወያኔ በሀገራችን እያደረገ እንዳለው ማለት ነው።
የትምህርት እድሉን፤ የመንግስቱን ስራ ሀላፊነትና ተቆጣጣሪነት፤ በማናቸውም መስክ በጥቅማጥቅሙም “በዝምበለው ይውሰድ” ንቅዘቱም የበላይነቱን ለቱትሲዎቹ ሰጧቸው። የወያኔ ገዢ ቡድን ከትግራይ የሚመለምላቸውን ሁሉ በማናቸውም የኢትዮጵያ ክፍል የበላይ እንዳደረገው፤ ቤልጅየሞችም ቱትሲዎችን አጠናከሩ። ቤልጂየሞች ከሌላው ወገን ለሆዱ የተገዛውንና ከተጠቀመ  ለጥፋት ስራቸው ሁሉ ፍጹም ተባባሪ ለመሆን የቆረጠውን ትንሽ ትንሽ እያላሱ፤ የገዛ ወገኑን መቀጥቀጥ የሚችል መዶሻና ድንጋይ አደረጉት። አሁን በየክልሉ ወያኔ በአምሳሉ የፈጠራቸው የአማራ፤ የኦሮሞ፤ የሀረሪ፤ የሶማሌ፤….ወዘተ አይነት ደደቦችና ጅቦች።
ታዲያ ብዙሀኑን የሩዋንዳ ህዝብ ሁቱዎችንና ቱዋዮችን ያስከፋቸውና ለበቀል ያነሳሳቸው ነገር፤ ህዳጣኑ ቱትሲዎች የቅኝ ገዚዎችን ከለላና ድጋፍ በማግኘታቸው ብቻ ከሌሎች ወገኖቻቸው ተለይተው ተጠቃሚ በመሆናቸው ብቻ፤ ከቅኝ ገዢዎቹ ብሰው ወገኖቻቸውን የሚረግጡ፤ የሚገፉ፤ የሚጨቁኑ ሆኑ። አሁን በሀገራችን ህውሀት ስር ተለጥፈው የሚጥሉላቸው ቅንጥብጣቢ ብሶባቸው፤ ሆዳቸው ስለሞላ ብቻ ህሊናቸው ታውሮ፤ በወያኔ ትእዛዝ የገዛ ወገናቸውን የሚገሉ፤ የሚያፈናቅሉ ኢትዮጵያውያንን አይነት ማለት ነው።
በ1950 ዎቹ ቱትሰዎችንና ቅኝ ገዢዎቹን የሚያጣላ ሁነት ተከሰተ። በመላው አፍሪካ የተነሳው የነጻነት እንቅስቃሴና፤ አንዳንድ ተደማጭ የሀይማኖት አባቶች ስለነጻነት ህዝቡን ማነሳሳታቸው፤ ቱትሲዎች በቤልጂየሞች ላይ የእንቢታና የመነሳሳት፤ የነጻነት ጥያቄም አነሱ። በዚህን ጊዜ ለሩዋንዳ ነጻነት የሚንቀሳቀስ የሁቱዎች ፓርቲ ነበር። ቤልጂየሞች ገልበጥ አሉና እሳትን በሳት እንዲሉ ቀድሞ  በእንክብካቤ ይዘው ከፍከፍ ያደረጓቸውን ቱትሲዎች ማግለልና የሁቱዎቹን ንቅናቄ መደገፍ ጀመሩ።
በሁቱና ቱትሲ ወንድማማቾች መካከል ይህ መጨካከን ይህ መገፋት፤  በተለያየ ጊዚ ብዙ ደም ያፋሰሰ ግጭት አስነስቶ በብዙ ሺዎች ለሚቆጠሩ የሀገሪቱ ተወላጆች እልቂት መክንያት ሆነ። 1961 ከነጻነት በሁዋላ ሁቱዎች እንደገና በቤልጂየሞች ድጋፍ ስልጣኑን ተቆጣጠሩ። የበቀል አዙሪቱ ቀጠለ። በጋራ ሀገራቸው ስልጣኑን ተጋርተው በሰላም ሀገራቸውን ማስተዳደሩ ተስኗቸው በስልጣንና በጥቅም ህሊናቸው ታውሮ እንደሰው ማሰብ ተስኗቸው እንደ አውሬ ሁነው እንደገና ሁቱዎች ደሞ በተራቸው ቱትሲዎችን ያሳድዱ ይጨቁኑ ጀመር። ቱትሲዎች ሽሽት ወደየጎረቤት አገራት መበተን ጀመሩ። ከ1961 እስከ 1964 ብቻ ቱትሲዎች አስር ጊዜ ከጎረቤት አገር እየተንደረደሩ ሁቱዎችን ለማጠጥቃትና ወደ ስልጣን ለመመለስ ሞክረዋል። ይህ ሙከራ ደግሞ በሀገር ውስጥ የቀሩ ቱትሲዎች በበቀል እንዲጨፈጨፉ ምክንያት ሆነ። እንዲህ እንዲህ እያለ ቅኝ ገዢዎች ስራ ላይ ያዋሉት እየከፋፍሉ እያጋጩ መግዛት የህብረተሰቡ ቋሚ በሽታ ሆኖ አረፈው።
እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር በ1994 በሁቱዎች የበላይነት የሚመራው የሩዋንዳ መንግስት በቱትሲ አማጽያን መሪው ሲገደል፤ በቱትሲዎች ላይ ያንቀሳቀሰው የዘር ማጽዳት ዘመቻ ቀድሞውንም የታለመ የታቀደ ነበር። ለረጅም ጊዜ በሀገሪቱ ሬዲዮና ጋዜጦች ሁቱዎችን ኢላማ ያደረገ የዘር ጥላቻ ፕሮፓጋንዳ በይፋ ይነዛ ነበር። “ሁቱዎች ከዚች ምድር ተጠራርገው ካልጠፉ ሩዋንዳ ሰላም አይኖራትም” ይሉ ነበር። ህውሀት በአማራው ህዝብ ላይ አሁንም በተለይ በትግራይ ክልል የማያቋርጥ የሬዲዮና የህትመት ፕሮፓጋንዳ፤ የዘር ጥላቻ ትምህርት ይሰጣል። እርግጥ ኢትዮጵያ በሽፍቶች የተያዘች ሀገር በመሆኗ ህግ የለምና ነው እንጂ ይህ የህውሀት ቀንደኛ መሪዎች በህዝቡ ውስጥ የሚረጩት መርዝ እድሜልክ ወህኒ መቀመቅ እንዲያርፉ የሚያደርጋቸው ነበር። ደጉ ነገር የኢትዮጵያ ህዝብ ከነሱ የቀደመ በመሆኑ የሚፈልጉትን የሚያስቡትን ነገር አያደርግላቸውም።
ወያኔ በህብረተሰቡ ውስጥ እያበረታታና እያስፋፋ ያለው እስከዛሬም ያከናወነው ዘርን ከዘር ሀይማኖትን ከሀይማኖት የማጋጨት ስራና እስትራቴጂ ባይዝለትም ተስፋ ይቆርጣል ማለት አይደለም። ተስፋውንና እስትንፋሱን የሚቆርጠው የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድነት ተነስቶ ጉሮሮውን ያነቀ እለት ብቻ ነው። በሰላማዊ አመጽም በሉት እሱ በሚያውቀውና በሚገባው አይነት። ለዚህም ተግባር ፊት አውራሪ መሆን ያለበት የኢትዮጵያ ወጣት ዛሬ ነገ ሳይል ሁሉም ወደተመቸው የትግል ስልት ተካቶ ህብረተሰቡን በመምራት ለውጥ ማምጣት ግድ ይለዋል።
የደቡብ አፍሪካውን አፓርታይድ ታሪክ ላንሳ። በአስራሰባተኛው ክፍለ ዘመን በደቾችና በእንግሊዞች የቅኝ አገዛዝ ስር  በነበሩበት ወቅት፤ በደቡብ አፍሪካ የተጀመረው ከፋፍሎ የመግዛት ስልት፤ እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር ከ1948 ጀምሮ አፓርታይድ የመንግስቱ ይፋ ፖሊሲ ሆኖ በህግ ተደነገገ። ህዝቡ አንገዛም በማለቱ ህዳጣኑ ነጮች (ከእንግሊዞችና ደቾች ተዳቅለው እዚያው የተራቡ)፤ የደቡብ አፍሪካ ህዝብ በዘሩ እየተለየ የሚሰባሰብበት ክልል አዘጋጁ። የሀገሪቱን ዜጎች በአራት መደቧቸው። ነጮች፤ ጥቁሮች፤ ክልሶች፤ አና እስያውያን። ባንቱስታን በሚል የሚታወቁ አስር ትንንሽ አካባቢዎችን ከፋፍለው 75% ለሚሆነው ጥቁር ህዝብ፤ ከሀገሪቱ አጠቃላይ ስፋት 13% በሚሆን ክልል ውስጥ አጎሩት። ሀይል በተቀላቀለበት ሁኔታ ወደየ ክልላቸው እንዲሰባሰቡ ተደረገ። አሁን ወያኔ በአማራው ህዝብ ላይ እያንቀሳቀሰ ያለው ንብረት እያስቀማ ወደ ክልላቸው እንዲባረሩ የማሳደድ እርምጃ፤ አፓርታይድ ያደርገው የነበረ፤ ሁሉንም ወደከለለት አካባቢ የማካተት ስራ አይነት ነው።  ከህዳጣኑ ነጮች በስተቀር ማናቸው ወገን የፖለቲካ ውክልናም ሆነ ተሳትፎ በኢኮኖሚ በህግ እኩልነት እንደማይኖረው ደነገጉ። ባንቱስታንስ በሚል ለጥቁሮቹ የተከፋፈሉ የጎሳ አካባቢዎችን ከከለሉላቸው በኋላ የደቡብ አፍሪካ ዜጋ መሆናቸው ተሰርዞ፤ የየንኡስ ነገዳቸው አባልና ክልል ዜጋ የመሆን መብት ብቻ ሰጧቸው። ነጮቹ ይህንንም ያደረጉት ጥቁሮች፤ ራሳቸውን የደቡብ አፍሪካ፤ የገዛ አገራቸው ዜጋ አድርገው  መቁጠር እንዲያቆሙ፤ ብሎም የፖለቲካ ተሳትፎና እኩልነት እንዳይኖራቸው ለማድረግ ነበር። የህዳጣኑን ነጮች የበላይነት የበለጠ ዘላቂና አስተማማኝ ለማድረግ ነበር።
ወያኔ ስልጣኑን ከተቆጣጠረበት ጊዜ ጀምሮ  “ዜግነት” የሚለውን ቃል “ብሄረሰብ” በሚለው የጥፋት ቋንቋው የለወጠበት ዋና ምክንያት፤ የኢትዮጵያዊነት እምነትና አስትሳሰብ በሂደት ከህዝቡ ውስጥ ይጠፋል በሚል ከንቱ ምኞት ነው። የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ እንዳደረገው፤ ኢትዮጵያውያንም ኢትዮጵያዊነታቸው ተሰርዞ ማንነታቸው በየጎጣቸው ተወስኖ ይቀራል የሚል መለስ ስብሀት የፈጠሩት ከንቱ ራእይ አለ። ይሁንና እነሱ ይጠፋሉ እንጂ የኢትዮጵያዊነት ኩራትና ክብር ከእውነተኛ ኢትዮጵያውያን ደምና ስጋ ውስጥ አይጠፋም። የሚኒሊክን ሀውልትም ቢያፈርሱት፤ የአቡነጴጥሮስንም ሀውልት ቢያፈርሱት፤ የአሉላ አባነጋንም ሀውልት፤ ቢንዱት፤ ስድስት ኪሎ የቆመውን የሰማእታት ሀውልት አፍርሰው ጣሊያንንም ቢያስደስቱት፤ ለሺዎች ዘመናት በኢትዮጵያ ህዝብ ልብ ውስጥ የተገነባችውን ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን ከቶም ከቶ ከዜጎች ልብ ውስጥ ሊያፈርሱት አውጥተው ሊጥሉት አይችሉም። ቀን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል እንደተባለው ዛሬ ክፉ ቀን ለወያኔ መሪዎች አድልቷልና እስከምናጠፋቸው ታሪካችንን መለያ ቅርሶቻችንን ማጥፋታቸውን ሊቀጥሉ ይችላሉ። በህውሀት ማቃብር ላይ መልሰን ብንገነባቸውም።
የደቡብ አፍሪካ ህዳጣን ነጭ ገዢዎች ያኔ ነጮችና ጥቁር ልጆች አብረው ትምህርት ገበታ ላይ እንዳይቀመጡ አደረጉ። አገልግሎት መስጫ ተቋማት፤ ህክምናና የመዝናኛ ስፍራዎች ሳይቀር ዝቅ ባለ ደረጃ ለብቻቸው ሰሩላቸው።  የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች የነሱ ወዳልሆ ክልል ለመጓዝ የይለፍ ወረቀትና የዘር መለያ መታወቂያ የግድ አስፈላጊ ሆነ….  ለጥቁሮቹ ብቻ።ያ ከሌለ ከክልሉ ወደሌሎች ክልል ለመዝለቅ የሞከረ ጥቁር እስርና ቅጣት የሚጠብቀው ሆነ።
አሁን ኢትዮጵያውያን እዚህ ደረጃ ላይ ደርሰናል። በተለይ አማራና ኦሮሞ የሚተኮርባቸው ሲሆን፤ የሌላ ክልል ዜጎችም ቢሆኑ ወደ አፋር ክልል ወደ ሶማሌ ክልል ወደ ትግራይ ክልል ሄዶ እንደልቡ በነጻ መንቀሳቀስ አይችልም። የአካባቢው ፖሊሶች በስነስራት እንግዳ የሆነባቸውን ሰው አስቁመው ዘሩን፤ አድራሻውን፤ ከየት እንደመጣ ለምን እንደመጣ ይጠይቃሉ። የሚነጠቅ ነገር እንዳለው ካረጋገጡም ያለምንም ምክንያት አስረው ገርፈው፤ አሰቃይተው፤ የያዘውን ነገር ነጥቀው፤ ቢፈልጉ ይለቁታል፤ ወያኔን ማስደሰት ከፈለጉም አንድ አሸባሪ ሊያፈነዳ ሲል ያዝን ብለው ንጹሁን ዜጋ አሳልፈው ይሰጡታል። ያ መከረኛ ወያኔ እጅ ከገባ  በኋላ ደግሞ እንደሁኔታው ታይቶ የሆነ ትያትር ይሰራበትና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ይውላል። የአማራ ክልል ታርጋ ያለው መኪና ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከተገኘ፤ ፖሊሶች አስቁመው ወዴት እንደሚሄድ ምን እንደሚፈልግ ይጠይቃሉ። ታዲያ አፓርታይድ ከዚህ የተለየ ምን አደረገ?
የደቡብ አፍሪካው የዘረኞች መንግስት፤ ያን ሁሉ ሽንሸናና አፈና፤ ያን ሁሉ ግድያና እስራት ሰብአዊ መብት ረገጣ፤ ያን ሁሉ የመከፋፈል ስልት እየተጠቀመ፤ የደቡብ አፍሪካን ወጣቶች አንድ ሆነው አምርረው አፓርታይድን ታግለው ከማሸነፍና መሪያቸው ማንዴላን ከማስፈታትና ነጻነታቸውን ከመቀዳጀት አልገታቸውም። ልዩነታችን የኛ ዘረኞች አገር በቀል መሆናቸው፤ እነዛኛዎቹ መጤ መሆናቸው፤ የነዛ ወጣቶች በእንድነት ጸንተው እስከመጨረሻው መታገላቸውና የኛ ወጣቶች ደሞ ለራሳቸው የዘረኞቹ ፕሮፓጋንዳ ሰለባ ሆነው፤ እርስ በራሳቸው በድንጋይ መደባደባቸው ነው…… የጋራ ጠላታቸውን ትተው።
የሆነው ሆኖ ኒልሰን ማንዴላ ከተናገራቸውና ለደቡብ አፍሪካ ወጣቶች ጽናትና ብርታት ከሆናቸው ቁም ነገዎች ጥቂቱን ለወጣቶቻችን ልጥቀስና ዛሬ ነገ ሳትሉ አንድ ሁናችሁ አሁኑኑ ተነቃነቁ ልበል…
“ድፍረት ማለት ፍርሀት በሰው ልብ ውስጥ የለም ማለት አለመሆኑን ተምሬአለሁ፤ የራስን ፍርሀት ማሸነፍ እንጂ፤ ጀግና ማለት የማይፈራ ማለት አይደለም፤ ፍርሀቱን አሸንፎ ያሰበውን የሚያደርግ እንጂ!!!””
“በየትኛውም አቅጣጫ ቢሄዱ ወደ ነጻነት የሚደረግ ጉዞ ቀላል አይደለም። ወደምንመኘው ተራራ አናት ላይ ከመድረሳችን በፊት፤ ብዙዎቻችን ደግመን ደጋግመን ሞት ጥላውን በሚያጠላበት ሸለቆ ውስጥ ማለፍ አለብን”
ኢትዮጵያ ለዘለአለም ትኑር!
ሞት ለወያኔ!
lkebede10@gmail.com

Freedom For Ethiopian Women & Childern: Tamagn With ESAT Europe Journalists

Freedom For Ethiopian Women & Childern: Tamagn With ESAT Europe Journalists

Mar 28, 2013

ከ3 ሺ በላይ ተፈናቃዮች ያለምንም መጠለያ ሜዳ ላይ ወድቀዋል


 መጋቢት ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  

ኢሳት ዜና:- ከ3 እስከ 4 ሺ የሚሆኑ ከቤንሻcccጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉ የአማራ ተወላጆች በምእራብ ጎጃም ዞን በፍኖተሰላም ከተማ ከመስተዳድሩ ፊት ለፊት ባለ ሜዳ ላይ ያለምንም መጠለያ እንዲሰፍሩ ተደርጓል። ከከተማው ነዋሪዎች ያገኘነው መረጃ እንደሚያስረዳው ተፈናቃዮቹ ቀን በጸሀይ፣  ሌሊት በብርድ እየተሰቃዩ ነው። እጅግ በርካታ ህጻናትና ሴቶች ከተፈናቀሉት መካከል ይገኙበታል። ተፈናቃዮች ከአካባቢያቸው ይዘውት የመጡትን ዱቄት እየጋገሩ በበመገብ ላይ መሆናቸውም ታውቋል። እስካሁን ድረስ ተፈናቃዮችን ቀርቦ ያነጋገራቸው ባለስልጣን አለመኖሩንም ለማወቅ ተችሎአል። ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉ 60 የአማራ ተወላጆችን  ይዞ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ መኪና ተገልብጦ 59 ሰዎች መሞታቸውን እንዲሁም ትናንት ሁለት ህጻናት በአይሲዙ መኪና ተጭነው ሲጓዙ ታፍነው መሞታቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

መንግስት ለአባይ ግድብ ግንባታ ከህዝብ ለመሰብሰብ ያወጣውን እቅድ ሳይተወው አይቀርም ተባለ

 መጋቢት ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 

ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ መንግስት የአባይ ግድብን በሕዝብ ተሳትፎ ለመገንባት ባቀደው መሰረት ከመንግስት ሰራተኞች፣ባለሃብቶች፣አርሶአደሮችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች እያካሄደ ያለውን የገንዘብ ማሰባሰብ ሒደት ዘንድሮም ለመቀጠልም አቅዶ ቢንቀሳቀስም ከህዝቡ የታሰበውን ያህል ምላሽ ባለመገኘቱ ለማቋረጥ ሳይገደድ እንደማይቀር ምንጮቻችን ገለጡ። የአባይ ግድብ ከተጀመረ በኋላ በተለይ ባለፈው ዓመት የመንግስት ሰራተኞች ሳይወዱ በግድ የአንድ ወር እና ከዚያ በላይ ደመወዛቸውን በአንድ ዓመት ከፍለው ለመጨረስ ቃል እንዲገቡ በማድረግ ገንዘብ ለማሰባሰብ መሞከሩ የሚታወስ ሲሆን፣  መዋጮው ስጦታ መሆኑ ቀርቶ በቦንድ ግዥ እንደሚያዝ፣ይህም የቁጠባ ባህልን ለማበረታታት ጥሩ አጋጣሚ መሆኑን በመጥቀስ መንግስት ዘንድሮም መዋጮ ለማሰባሰብ ሙከራ ያደረገ ቢሆንም ምላ ሹ ጥሩ ባለመሆኑ ምክንያት ለማቋረጥ ሳይገደድ አይቀርም። ለዚህ አንዱና ዋንኛው ምክንያት ከዋጋ ንረት ጋር ተያይዞ ደመወዝተኛው በገቢው ለመተዳደር ያለመቻል ሲሆን በተጨማሪም ለፕሮጀክቱ ከሕዝብ በመዋጮ መልክ የሚሰበሰበው ገንዘብ በምን መልኩ ስራ ላይ እየዋለ እንደሆነ፣ከሙስናና ብልሹ አሰራር የጸዳ ስለመሆኑ ምንም ዓይነት ግልጽ መረጃ አለመኖሩ በሕዝብ ውስጥ ጥርጣሬን ፈጥሯል፡፡  ሌላው ቀርቶ ስንት ብር እንደተዋጣ እንኳን መንግስት ተከታታይነት ያለው በቂ መረጃ እየሰጠ አለመሆኑ የበርካታ ወገኖችን ቅሬታ አስከትሏል፡፡ ለግድቡ ገንዘብ ለመስጠት ቃል የገቡ ሼህ አላሙዲንን ጨምሮ በርካታ ባለሃብቶችም ገንዘቡን በወቅቱ ገቢ አለማድረጋቸው በእነአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝና አቶ በረከት ስምኦን የሚመራውን የአባይ ግድብ ብሔራዊ ም/ቤትና አንዳንድ የመንግስት ባለስልጣናትን ማበሳጨቱ ታውቋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከመጋቢት 18 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ግድቡ የመሰረት ድንጋይ የተጣለበት ሁለተኛ ዓመት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በመከበር ላይ ነው፡፡ ከነዚህ ዝግጅቶች መካክል የስነጹሑፍ ፣የስዕል፣የሙዚቃ ዝግጅቶች፣ልዩ ልዩ የአትሌቲክ ውድድሮች፣በተዋናዮችና በድምጻዊያን መካከል መጋቢት 21 በሚካሄድ የእግር ኳስ ውድድር እንዲሁም ግንባታው በሚካሄድበት ቦታ መጋቢት 24 ቀን በሚካሄድ በዓል እንደሚከበር የወጣው መርሃግብር ያሳያል፡፡ ግድቡ በአሁኑ ወቅት 18 በመቶ ስራው መጠናቀቁ በመገለጽ ላይ የሚገኝ ሲሆን በስራው ላይ በህወሃት የቀድሞ ታጋዮች የሚመራውና ከተመሰረተ የሁለት ዓመት ዕድሜ ብቻ ያለው የብረታብረት ኮርፖሬሽንን ጨምሮ የኢህአዴግ ኢንዶውመንት ድርጅት የሆነው መስፍን ኢንዱስትሪያል በልዩ ድጋፍ በቢሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ያለው ስራ እንዲያንቀሳቅሱ እየተደረገ ነው፡፡፡ የወ/ሮ አዜብ የእህት ልጅ በሆኑት በወ/ሮ አቲኮ ስዩም አምባየ የሚመራው ኦርቺድ ድርጅትም በግድቡ ስራ ከሳሊኒ በመቀጠል ከፍተኛ ገንዘብ በማግበስበስ ላይ የሚገኝ ድርጅት ነው።ግድቡ በተፋሰሰ አገራት በተለይም በግብጽና ሱዳን ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የማያስከትል መሆኑን ለማረጋገጥ የተቋቋመውና በስራ ላይ የሚገኘው የዓለምአቀፍ የኤክስፐርቶች ቡድን በግንቦት ወር 2005 የመጀመሪያ የጥናት ሪፖርቱን ይፋ ያደርጋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ምናልባት የጥናቱ ግኝት እነ ግብጽን የማይጠቅም ከሆነ የግድቡ ግንባታ የመቀጠሉ ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ የሚወድቅ እንደሚሆን ተገምቷል፡፡የኢትዮጵያ መንግስት ግን ጥናቱ ግድቡ በተለይ የኢንቫይሮመንት ተጽዕኖ እንደማያስከትል ማረጋገጫ ይሰጥልኛል ብሎ ተስፋ ያደረገ ሲሆን ይህ ባይሆንም እንኳን ግድቡን ከመገንባት የሚያግደኝ የለም እያለ ነው፡፡

እስር ቤቶቻችን በሕገ-መንግሥት ወይንስ በ‹‹ሕገ-አራዊት››?




ምንጭ፣ ዞን ዘጠኝ ጦማር
በጌታቸው ሺፈራው
 የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትን እንዲጸድቅ በበላይነት የመሩት አቶ መለስና አቶ ሌንጮ ለታ መሆናቸው ይነገርላቸዋል፡፡ ይህ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳይ ቀጥተኛ ተሳታፊ ባልሆኑት የተገንጣይ መሪዎች ጠንሳሽነት የጸደቀው ሕገ መንግሥት ለአገር ሉኣላዊነት፣ አንድነትና ታሪክ ክብር የሌለው ቢሆንም ዓለማቀፋዊ የሰብኣዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን አጠቃልሏል፡፡ ሆኖም እነዚህ ሰብኣዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ለእርዳታ ማሰባሰቢያ የተቀመጡ እንጂ ወደመሬት ወርደው ተግባራዊ መሆና ባለመቻላቸው የይስሙላህ ሕግ ሆኗል፡፡ ከሕገ መንግሥቱ ይልቅ የገዥዎች ጊዜያዊ ሥልጣን ጥቅም ለማስጠበቅ በየጊዜው ትርጉሙ የሚቀያየረው የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ‹‹መርሕ›› ሕዝብ ላይ የተጫነ ገዥ ሕግ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ይህን ስርዓት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ‹‹ሕገ አራዊት›› ሲሉ ይገልጹታል፡፡ በዚህ ስርዓት ሕዝብ በሕግ ስም እንጂ በሕግ የሚዳኝበት አጋጣሚ አይታይም፡፡ ብዙዎቹ በዚህ ስርዓት ያለውን የኢትዮጵያን ሕዝብም የታሰረ፣ ታስሮ የተፈታና ለወደፊት የሚታሰር እያሉ በቀልድ መልክ በሦስት የእስራት ምድብ ያስቀምጡታል፡፡ እንደ እኔ ሌላ አራተኛ ምድብም ሊካተት ይገባዋል፡፡ ይኸኛው እንደ ሦስቱ ምድቦች የአካል ጉዳትና ሰብኣዊ መብት ጥሰት የማይደርስበት ሕገመንግሥቱን አጽድቆ ራሱ የሚጥሰው አሳሪው ክፍል ነው፡፡ ይህ አሳሪው የኅብረተሰብ ክፍል በአካል ያልታሰረና ስርዓቱ እስካለ ድረስ በአካል ሊታሰርበት የሚችለው አጋጣሚ ጠባብ ቢሆንም የአዕምሮ እስረኛ ነው፡፡
ኢሕአዴግ እየዘመረለት የሚገኘው አቶ መለስና በእኩል ደረጃ የሚያወግዘው ‹‹አሸባሪው›› አቶ ሌንጮ ያጸደቁት ሕገ-መንግሥት ኢትዮጵያውያን ታሳሪዎች ምቹ ሁኔታ እንዲመቻችላቸው በርካታ አንቀጾችን አስቀምጧል፡፡ ለአብነት ያህል አንቀጽ 19 (2) የተያዙ ሰዎች ላለመናገር መብት እንዳላቸው ይደነግጋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (5) ‹‹የተያዙ ሰዎች በራሳቸው ላይ በማስረጃነት ሊቀርብ የሚችል የእምነት ቃል እንዲሰጡ ወይንም ማንኛውንም ማስረጃ እንዲያምኑ አይገደዱም፡፡ በማስገደድ የተገኘ ማስረጃ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡›› ቢልም በተለያዩ ጊዜያት የተሰሩ የፕሮፖጋንዳ ፊልሞች ላይ ‹‹እማኝነታቸውን›› የሰጡ ታሳሪዎች የሚሰጡት ቃል በኃይል የተደረገ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡
መጋቢት 8/2005
ይህን እውነታ እሁድ መጋቢት 8/2005 ‹‹ለማርሻል ግራዚያኒ ክብር መሰጠት የአባቶቻችንን መስዋዕትነት ማራከስ ነው›› በሚል የተደረገ ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ እኔና ጉዋደኞቼ በታሰርንበት ወቅት ለማረጋገጥ ችያለሁ፡፡ አንድ ታሳሪ ከአንድ ጊዜ በላይ ቃል መስጠት እንዳለበት የሚገልጽ የሕግ አሠራር ባይኖርም ከሶስት እስከ አራት ጊዜ ቃል እንድንሰጥ ተደርገናል፡፡
በመጀመሪያው ዙር ሁሉም ሕገ መንግሥቱ ‹‹ሰጥቶኛል›› ያለውን መብት ተጠቅሞ ‹‹ቃል አልሰጥም›› ብሎ ፊርማውን አስቀምጦ ወጣ፡፡ በዚህ የተደናገጡት መርማሪዎች አንዳንዶቹን ቃል እንዲሰጡ ቢያባብሉም ሊሳካላቸው አልቻለም፡፡ በታጎርንበት ጣቢያም ሆነ በሌሎቹ ጣቢያዎች የፖሊስ አባል መሆናቸው ያልታወቀውና ከመጀመሪያው ጀምሮ ሰልፉን የበጠበጡት ‹‹ኮማንደር›› ግን ‹‹ይህ ፒቲሽን በመሆኑ ጥንቃቄ ሊደረግበት ይገባል›› በሚል መርማሪዎች የቻሉትን ሁሉ ተጠቅመው ቃል እንዲቀበሉን ትዕዛዝ አስተላልፈዋል፡፡ ሆኖም ሁሉም ታሳሪዎች ቃል ሳይሰጡ ቀሩ፡፡ ይህን ተከትሎም የይስሙላህ ሕገ መንግሥቱ ተግባር ላይ የዋለው ለተወሰኑ ደቂቃዎች ብቻ ሆነ፡፡
ቃል አንሰጥም ካልንበት ወቅት በኋላ ለጥቂት ጊዜ ጠፍተው የቆዩት ‹‹ኮማንደር›› ታሳሪዎች በእየተራ ፎቶ ግራፍና ቪዲዮ እየተቀረጹ ሌላ ተጨማሪ ቃል እንዲሰጡ አደረጉ፡፡ ይህን ምርመራ የሚያከናውኑት ፖሊሶች ሳይሆኑ ደህንነቶች በመሆናቸው ቃል አልሰጥም የሚለው መብት አይሰራም፡፡ ተመርማሪው ገና ከመግባቱ ስድብና ዘለፋ ይገጥመዋል፡፡ ከእነኮማንደር በሚደርስ ቅድሚያ ፍረጃ አንዳንዶቹ ለቃል ከመግባታቸው ዱላ ጠብቋቸዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ወጣቶች ብሄራቸውን ሲጠየቁ ‹‹ኢትዮጵያዊ›› በማለታቸው ዱላና ዱላ ቀረሽ ስድብና ዘለፋ ገጥሟቸዋል፡፡ አንዲት የሰማያዊ ፓርቲ አመራር ወጣት ከደህንነቶቹ በደረሰባት ድብደባና አስጸያፊ ዘለፋ እራት መብላት አልቻለችም፡፡የባሰው ደሞ ቅዳሜ መጋቢት 7 ቅስቀሳ ላይ እያሉ የታሰሩ ወጣቶች የደረሰባቸው ከፍተኛ ድብደባ ነው፡፡ ተክለሀይማኖት አካባቢ ታስረው የነበሩት መካከል አንደኛው ብሔሩን ‹‹ኢትዮጵያዊ›› በማለቱ ይመረምረው የነበረው ደኅንነት ከመደብደብ አልፎ በሽጉጥ አስፈራርቶ መረጃ እንደጠየቀው አውግቶኛል፡፡
ቃል ስንሰጥ ከተጠየቅናቸው ጥያቄዎች በተጨማሪ የኢሜልና የፌስ ቡክ አድራሻና የይለፍ ቃል በግድ ተቀብለውናል፡፡ ‹‹በምርመራው›› በ1997 ዓ/ም ማንን እንደመረጥን ተጠይቀናል፡፡ መልሱን ከመመለሳችን በፊት ደኅንነቶቹ ራሳቸው ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ መምረጣችንን ያለ ጥርጥር እየነገሩ ‹‹አፍራሽነታችን›› የቆየ መሆኑን ለማስገንዘብ ሞክረዋል፡፡ ይህ ሁሉ የሚደረገው ለሕዝብ ይቆማል በሚባለው ፖሊስ ተቋም ግቢ ውስጥ ሲሆን ፖሊስ በደኅንነቶች የሚሰጠው ክብር ለታሳሪዎች ከሚሰጠው የሚለይ አይደለም፡፡
የተያዙ ሰዎች አያያዝ በፓሊስ ጣቢያዎች
ተግባር ላይ መዋል ያልቻለው ሕገ መንግሥት አንቀጽ አንቀጽ 17(1) ‹‹ማንኛውም ሰው ጭካኔ ከተሞላበት፣ ኢሰብኣዊ ከሆነ ወይንም ክብሩን ከሚያዋርድ አያያዝ ወይንም ቅጣት የመጠበቅ መብት አለው›› ቢልም የሚፈጸመው ግን በተቃራኒው ነው፡፡ ስርዓቱ ለይስሙላህ ከሚጠቀምበት ሕገ-መንግሥት በተቃራኒ ‹‹በሕገ አራዊቱ›› እንደሚመራ በደንብ የተረዳሁት ለማሰላቸት ተብሎም ይሁን ለሌላ ዓላማ ከፖሊስ ጣቢያ ፖሊስ ጣቢያ ሲያዟዙሩን ካመሹ በኋላ ከለሌቱ አምስት ሰዓት ገደማ ቀጨኔ አካባቢ በሚገኘው ወረዳ 9 ፖሊስ ጣቢያ ከገባን በኋላ ነው፡፡ ከታሰርነንበት ጊዜ ጀምሮ በሆነ ባልሆነው በዚህ የወረዳ 9 ጣቢያ በተደጋጋሚ የታሰሩ የባለራዕይ ወጣት አመራሮች እንደተለመደው ለመቀጣጫ ወደዚሁ ጣቢያ ሊወስዱን እንደሚችሉ በእርግጠኝነት ይናገሩ ነበር፡፡ ማታ ላይ ሁላችንም ወደጣቢያው እንድንሄድ ተፈልጎ የነበረ ቢሆንም ቀድሞ በመሙላቱ የተወሰኑት ጃን ሜዳ አካባቢ ባለው የማዘዣ ጣቢያ እንዲያድሩ ተደርገዋል፡፡
በወረዳ 9 ሦስት በአራት የሆነች ጠባብ ክፍል ውስጥ እድሜያቸው 15 አመት የማይበልጥ ህጻናትን ጨምሮ 37 ሰው እንዲይዝ ተደርጓል፡፡ በእርግጥ ይህ ክፍል እስከ 50 ሰው የሚይዝበት አጋጣሚ እንዳለ ታሳሪዎቹ ነግረውኛል፡፡ በክፍሉ ወስጥ በተነጠፈው ቆሻሻ የወለል ምንጣፍ ላይ ሰው በሰው ላይ ተኝቷል፡፡ ሙቀቱ ከፍተኛ በመሆኑ ብዙዎቹ ራቁታቸውን ናቸው፡፡ አስተባባሪዎቹ ከፖሊስ ቦታ እንዲፈልጉልን በተላለፈላቸው ትዕዛዝ መሠረት በዚህ መተላለፊያ በሌለው ቤት ውስጥ ለመቀመጫ ያህል ቦታ ሰጡን፡፡ ታሳሪ ወጣቶቹም የያዝነውን ገንዘብ እንድናስረክባቸው ጠየቁን፡፡ ተከትሎም ሳንቲም ሳይቀር ያለንን ገንዘብ በሙሉ ተቀብለውናል፡፡ይህ ታዲያ እኛ ወጣቶቹ ላይ ብቻ ሳይሆን ከእድሜ የገፉትም ላይ ተግባራዊ የሆነ ውስጣዊ የታሳሪዎች ህግ መሆኑን ሰምተናል፡፡እንዳስተዋልኩት ከሆነ ይህ ቤት ሰው እንደሰው የማይቆጠርበት ዘግናኝ ቤት ነው፡፡ በዚህ ሰዎች እንደሰው በማይቆጠሩበት ቤት ውስጥ ሰው ሊማር የሚችለው ጭካኔን ብቻ ነው፡፡
እንደገባንም የገጠመኝ ይህ ነው፡፡ በግድግዳው ላይ የተጻፉት ጽሑፎችም የሚያሳዩት ጨካኝ በሆኑት ታሳሪዎች ላይ የሚደርስባቸውን በደል ነው፡፡ አብዛኛዎቹ ግድግዳው ላይ የተጻፉ ጽሑፎች እስረኞቹ ያለምንም ጥፋት መታሰራቸውን የሚገልጹ ናቸው፡፡ በተለይ ‹‹አገሬ ሆይ ወንድ አይወለድብሽ››፣ ‹‹በደልን ለማን ይነግሩታል››፣ ‹‹አይ ስቃይ››፣ ‹‹ገሃነብ ከመግባት በምን ይለያል››፣‹‹ሰው እንዴለለኝ›› የሚሉት ግድግዳው ላይ የተጻፉ ጽሑፎች የእስረኞችን ምሬት ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ፡፡ በዚህ በደል የተሞላበት እስር ቤት የሚገኙት አብዛኛዎቹ ታሳሪዎች ከጨካኝነታቸው ባሻገር የአእምሮ ችግርና ተስፋ መቁረጥ የሚስተዋልባቸው ናቸው፡፡ በቀጨኔውና በሌሎቹ በተዘዋወርንባቸው ለሰው የማይመቹ እስር ቤቶች ውስጥ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በተደጋጋሚ እንደሚታሰሩ በየግድግዳው የተጻፉት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ስም ዝርዝር ምስክር ነው፡፡
በእነዚህ ጨካኝ ቤቶች የሚገኙ እስረኞች ከስርዓቱ እንደሚሻሉ ግን እየቆዩም ቢሆን አሳይተውናል፡፡ በምን እንደታሰርን በነገርናቸው ወቅት ለእኛ የነበራቸው አመለካከት ተቀየረ፡፡ ቀደም ብለው ተደራርበው ተኝተው የነበሩትን በማስነሳት ሰፋ ብሎ ለማስቀመጥ የሚያስችል ቦታን እንድንተኛበት አመቻቹልን፡፡ እስረኞች ጫማና ልብሳቸውን ጨብጠው ነው የሚተኙት፡፡ አልፎ አልፎ ዘመድ ያመጣላቸውን ምግብም ከልብስና ጫማቸው ጋር መደበቅ የግድ ይላቸዋል፡፡ አንድ እስረኛ ሊቀርብለት የሚገባውን ምግብ ባይቀርብልንም የታሰርንበትን ምክንያት ዘግይተው ያወቁት ያች ጠባብ ቤት ውስጥ የሚገኙ እስረኞች በርህራሄ ከጓደኞቻቸው የደበቁትንና ለራሳቸው የቆጠቡትን ቆሎና ጁስ ለእኛ አቅርበውልናል፡፡ በተለይ እነ ዶክተር ያቆብ በእስረኞች ዘንድ ይታወቁ ስለነበር በሌላኛው ክፍል ውስጥ መታሰራቸውን ስንነግራቸው በስርዓቱ ላይ ያማረሩት ብዙዎቹ ናቸው፡፡
ከአንገቱ በላይ ካለው የሰውነት ክፍሉ ውጭ ቀሪው ሰውነቱ ላይ ጓደኞቹ የተኙበት አንድ ወታደር ዶክተር ያቆብና ኢ/ር ይልቃል በቀጣዩ ክፍል መታሰራቸውን ሲሳማ ‹‹ይች ግፈኛ አገር!›› ብሎ እንደገና ተኛ፡፡ ሌላኛው አዛውንት ‹‹ምሁሮቿን ሞባይል ሰርቀው ከተያዙ ሕጻናት ጋር ወለል ላይ እንደዚህ የምታስር አገር የት ትገኛለች?›› ለሚል ጥያቄያቸው መልስ ሳይጠብቁ ‹‹የኢትዮጵያ ምሁራን ክብር ቦታና ፓስፖርት እንደልባቸው ከሚሰጣቸው የሶማሊያ ስደተኞች ያነሰ ሆነ፡፡ አገራችን የጠላት እንጂ የዜጎቿ መኖሪያ አልሆነችም፡፡›› ብለው ተናገሩ፡፡
በዚህ ክፍል ውስጥ የተሻለ ጥንቃቄ ሲደረግለት ያየሁት ሽንት የሚሸናበት የጀሪካን ቅዳጅ ብቻ ነው፡፡ ይህ ጀሪካን ማንም እንዳይጫነው ጥንቃቄ የሚደረግለት ብቸኛው ታሳሪ ነው፡፡ ይህንም የሚያደርጉት ተደራርበው የተኙት እስረኞች የሽንት ማጠራቀሚያውን በሀይል ሲገፉት አሊያም በእንቅልፍ ልባቸው ሲወጡበት በተደጋጋሚ እየተደፋ ቤቱ ስለሚበላሽ ነው፡፡ የሰው ትንፋሽ እና በየቦታው የሚጨሰው ሲጋራ የክፍሉ ሌላኛው አስከፊ ገጽታ ነው፡፡ አብዛኛው እስረኛ ቀን የተወሰነች ሰዓት ተኝቶ ለሌቱን ሌሎች እስረኞች እንዳይጫኑት እየተከላከለ ቁጭ ብሎ ያድራል፡፡ አንዱ በአንዱ ላይ ተደራርቦ ያደረው አብዛኛው እስረኛ በጠባቧ ግቢ ውስጥ ‹‹ሊዝናና›› ሲወጣ ቁጭ ብለው ያደሩት መተኛት ይጀምራሉ፡፡ ሆኖም በየደቂቃው በቆጠራና በሌላ ምክንያት እስረኞች ወደክፍል እንዲመለሱ ስለሚደረግ ሌሊት ከሚደርስባቸው ያልተለየ ችግር ያጋጥማቸዋል፡፡ አንድ ሰው ከፍ ያለ ድምጽ በማሰማቱ አሊያም የመውጫ ሰዓት ደርሶ ፖሊስ ውጣ ሳይለው ሊወጣ በመሞከሩ ክፍሉ እንደገና በቅጣት ተቆልፎ ቤቱ ወስጥ ያለው ሁሉም ሰው አብሮ ይቀጣል፡፡
ዝቅተኛ ካድሬዎች ከመቶ በላይ እስረኛ ከሚታጨቅበት የቀጨኔው እስር ቤት የተሻለ ስፋት ያለው የቀበሌ ቤት፣ ኮምዶሚኒየምና ቪላ ባለቤቶች ናቸው፡፡ ከፍ ያለ ስልጣን ያላቸው ፖለቲከኞች፣ ዘመዶቻቸው፣ የደኅንነት ኃላፊዎች፣ ወታደራዊ አመራሮችና የመሳሰሉት ደግሞ ከሚኖሩባቸው ዘመናዊ ቤቶች በተጨማሪ በሽዎች ብር የሚያከራዩትን ቤት በሕዝብ ገንዘብ ገንብተዋል፡፡ ለሥልጣኑ ሲል ሰዎችን ማሰቃየት አንዱ ስልት ነውና በህግ ጥፋተኝነታቸው ያልተረጋገጠ ታሳሪዎች ወለል ላይ እግራቸውን ዘርግተው የሚተኙበት እስር ቤት ለመገንባት ፍላጎት ያለው አይመስልም፡፡ልንቃወመው ወጥተን በስርዓቱ ድጋፍ ያገኘው የፋሽስት ስርዓት እንኳ በሞቃዲሾና ሮም ቁም ስቅል ያሳዩትን ወገኖቻችንን ያጉርበት የነበረው እስር ቤት አሁን አዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኙት በተለየ ሰው በቅጡ ሊያስተኛ የሚችል እንደነበር ታሪክ ያስረዳል፡፡
እንዳያውቅ የተደረገው የሕዝብ ፖሊስ
ፖሊሶች ሕግ እንዲያውቁ አይደረግም፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ ከመበተኑ ጀምሮ እስከተፈታንበት ጊዜ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ የመውጣት መብት በሕገመንግሥቱ መደንገጉን የሚያውቁ ፖሊሶች አላጋጠሙኝም፡፡ ሁሉም ይህ መብት ከፓርቲው የሚለገስ አድርገው የሚቆጥሩ ናቸው፡፡ ሕግ እንዳያውቁ ተደርገው እንጂ ለአገራቸው ሕዝብ የተለየ ጥላቻ ኖሯቸው እንዳልሆነ ግን ዓላማውና ሕጉ ሲገባቸው ከእኛ ጎን ቆመው አበረታትተውናል፡፡ በተለይ አመራሮቻቸው ከነገሯቸው በተቃራኒ በፖሊሶች ላይ ግርታ የተፈጠረው በአንድ የፖሊስ መኪና እንደ ሽንኩርት ከሰው ላይ ሰው ጭነው ወደ ጣቢያ ሲወስዱን በመደብደባቸው ይሸማቀቃሉ ተብለው የተገመቱት ወጣቶች፡-
‹‹ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም፣ በአባቶቻችን ደም፣
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም፣ ያስደፈረሽ ይውደም!››
እያሉ ሲጨፍሩ ነው፡፡ ሰባራ ባቡር አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ባረፍንበት ወቅት ሁሉም ሰው እስረኛ ሳይሆን ለሌላ ዓላማ የተገናኘ ያህል ልዩ ስሜት ውስጥ ነበር፡፡ ፖሊሶችንና ‹‹ኮማንደሩን›› ስለሕግ ያስረዳል፡፡ ስለአገሩ ድምፁን ከፍ አድርጎ ይዘምራል፡፡ ኢሕአዴግን ይተቻል፡፡ ፕሮፌሰር መስፍን የታሰርነውን ለማየት ወደጣቢያው ለመግባት ሙከራ ሲያደርጉ ፖሊስ ሲያስመልሳቸው ሁሉም ለእርሳቸው ክብር ከመቆም በጭብጨባ ክብራቸውን ገለጸላቸው፡፡ በወጣቶቹ ላይ መሸማቀቅና የጥፋተኝነት መንፈስ መመልከት ያልቻሉት ፖሊሶች ይበልጡት ተደናገጡ፡፡ ‹‹ኮማንደሩ›› እና አንዳንድ አመራሮች ደግሞ በመናደዳቸው ጩኸታችንን እንድንቀንስ በተደጋጋሚ ወቀሳ ያደርሱብን ነበር፡፡ ይህን ባለመሳካቱም በቪዲዮ ቀረጻ ተጀመረ፡፡ በወቅቱ ግን ለማሸማቀቅ በሞከሩት አካላት ላይ ይበልጥ ያናደደና ፖሊሶቹ ከእኛው ጋር እንዲሆኑ ያደረገ ሁኔታ ተፈጠረ፡፡ በወቅቱ ከወጣቱ ተለይተው ተቀምጠው የነበሩት እነ ዶ/ር ያቆብ፣ ኢ/ር ይልቃል፣ አቶ ታዲዮስና ሌሎችም በመጨመራቸው ድምፃችን ከፍ ብሎ መሰማት ጀምሯል፡፡ ለማሸማቀቂያነት የታሰበው ቪዲዮ መቅረጽ ሲጀመርም፡፡
‹‹ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም፣ በአባቶቻችን ደም፣
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም፣ ያስደፈረሽ ይውደም!›› እንደገና ተዘመረ፡፡
እኛን ለመጠበቅና ለማስቀረጽ ፊት ለፊታችን መሳሪያና ዱላ ይዘው የተኮለኮሉት ፖሊሶች ከመገረም አልፈው በስሜት አብረውን ዘምረዋል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ፖሊሶቹ የጠየቅናቸውን ነገር ለማቅረብ ቀናኢ ከመሆናቸውም በተጨማሪ ከተነገራቸው ባሻገር ሌላ አዎንታዊ ዓላማ ይዘን መነሳታችንን ማረጋገጥ የሚያስችላቸውን ጥያቄ በጓደኝነት መንፈስ ይጠይቁን ነበር፡፡ በኮማንደሩ ትዕዛዝ ከፖሊስ ጣቢያ ፖሊስ ጣቢያ ሲያንከራትቱንም ጠባቂ ፖሊሶች ያጅቡን የነበረው ያለ መሳሪያ ነበር፡፡ ስልኮቻችን በመያዛቸው ከቤተሰብ ጋር መገናኘት እንደምንችል በማወቃቸውም ባለ አንስተኛ ደሞዝተኞቹ ፖሊሶች በራሳቸው ጥያቄ ብዙ ሰው ወደቤተሰብ እንዲደውል ተባብረዋል፡፡ እንደኛ ጾማቸውን ውለው የእረፍት ጊዜያቸው ሲደርስ የተለዩን በጓደኛና ዘመድ ስሜት ነው፡፡

Mar 27, 2013

ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉ 60 የአማራ ተወላጆችን ይዞ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ መኪና ተገልብጦ 59 ሰዎች ሞቱ

መጋቢት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 
ኢሳት ዜና:-ከአካባቢው ተፈናቃይ አርሶ አደሮች ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው አደጋው የተፈጠረው፣ ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረው መኪና ትክሻ በምትባል ቀበሌ ውስጥ ጀዴሳ በሚባል ወንዝ ውስጥ ገብቶ ነው።
ከትናንት ወዲያ በተፈጠረው አሰቃቂ አደጋ ለሞቱት ሰዎች የደረሰላቸው ሰው አለመኖሩን ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይገልጽ የፈለጉ ተፈናቃይ አርሶደሮች ተናግረዋል።
ከሞቱት መካከል ህጻናትና ሴቶችም ይገኙበታል። በአደጋው ዙሪያ የክልሉን ባለስልጣናት ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።
በተመሳሳይ ዜናም በዛሬው እለት በርካታ አርሶ አደሮች በክልሉ ልዩ ሚሊሺያ ጥቃት እንደደረሰባቸው ተናግረዋል።
የክልሉ ባለስልጣናት የሚፈናቀሉት ሰዎች በህገወጥ መንገድ ወደ ክልሉ የገቡ ናቸው ሲሉ ለአዲስ አድማስ መናገራቸው ይታወሳል።
የዜጐች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብትን በተለከተ አስተያየታቸውን የሰቱት የሕግ ባለሞያ አቶ ግዛው ለገሠ የሕገ-መንግሥቱ አንቀፅ 32 “የመዘዋወር ነፃነት” በሚል ርእስ ስር ‹‹ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወይም በሕጋዊ መንገድ አገሪቱ ውስጥ የሚገኝ የውጭ ዜጋ፤ በመረጠው የአገሪቱ አካባቢ የመኖርና የመኖሪያ ቦታ የመመስረት እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከአገር የመውጣት መብት እንዳለው መደንገጉን ለጋዜጣው ገልጸዋል።

Mar 26, 2013

“አሁን በስልጣን ላይ ያሉ ሰዎች ባመዛኙ ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ የባንዳ ልጆች ነበሩ”

ፍኖተ ነጻነት መጋቢት 15 ቀን 2005 ዓ.ም.

የዛሬው እንግዳችን አቶ ታዲዎስ ታንቱ ይባላሉ፡፡ አቶ ታዲዎስ የታሪክ ምሁርና በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ነፃ ፕሬስ ውስጥ ትልቅ ሚና ያላቸው ሲሆን በአሁን ወቅት “ለኢትዮጵያ ህዝብ ክብር ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽነት ኮሚቴ” ዋና ሰብሳቢ ናቸው ፡፡ በተለይ ለፋሺስቱ ግራዚያኒ ከተሰራው ሐውልት ጋር በተያያዘ አጭር ቆይታ አድርገናል ተከታተሉን፡፡
በጣሊያን የሩዶልፍ ግራዚያኒንን የሐውልት ለመቃወም የሐሳቡ ጠንሳሽ ማን ነው?
አቶ ታዲዎስ፡- የፋሽቱ ጣሊያን የኢትዮጵያውያን ዋና ጨፍጫፊ የነበረውን ሩዶልፍ ግራዚያኒ ሐውልት መሰራት ለመጀመሪያ ጊዜ ተቃውሞው የተጀመረው በውጭ ሀገር ባሉ
Interview with Ato Tadiwos Tantu
አቶ ታዲዎስ ታንቱ
ለኢትዮጵያ ህዝብ ክብር ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽነት
ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ
ኢትዮጵያውያን ነው፡፡ በሀገር ውስጥ ግን የሐሳቡ ጠንሳሽ “ለኢትዮጵያ ህዝብ ክብር ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽነት ኮሚቴ” ነው፡፡ ከዛ በኋላ የባለዕራዕይ ወጣቶች ማኀበር ሰልፉን ለማስተባበር ፈቃደኛ መሆኑን ገለፀልን፤ በዚህም ላይ ሰማያዊ ፓርቲ እንደሚተባበረን ከገለፀ በኋላ መጋቢት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. ሰልፉን ለማካሄድmወሰንን፡፡
ተቃወቅሞውን ለማቅረብ ያነሳሳችሁ ዋነኛ ምክንያት ምን ነበር?
አቶ ታዲዎስ፡- ብዙውን ጊዜ እኔ በጋዜጦች ስለ አርበኞች ታሪክ ያነበብኩትንና ያወቅሁትን እፅፋለሁ፣ እመረምራለሁ፡፡ የጣሊያኑ ፋሽስት ግራዚያኒ ሀገራችንን በመውረር በአባቶቻችንና እናቶቻችን አርበኞች ላይ የፈፀሙት የግፍ ግድያ አሰቃቂ እንደነበር ስለተረዳሁ፤ ያ ሲቆጨኝ ደግሞ አሁን በጣሊያን ሀገር ለእሱ ሙዚየምና ሐውልት የመሰራቱን ወሬ ከኢንተርኔት ምንጮች ስላየሁ በጣም ተናድጄ እንደውም ተቃውሞ ማሰማት አለብን ብዬ ተነሳሁ፡፡ በኋላ ደግሞ እኛም የአንተ ዓይነት ሐሳብ ነበረን ብለው የባለ ዕራዕይ ወጣቶች ማኀበር አነጋገሩን፡፡ ከዛ በመቀጠል ሰማያዊ ፓርቲ በጋራ እንስራ የሚል ጥያቄ አቀረበ፡፡ በዚህ ምክንያት ሶስቱ አካላት በጋራ ሰልፉን ለማድረግ ዝግጅት ማድረግ ጀመርን፡፡ ስለዚህ ለኢትዮጵያ ጠላት አይደለም ጣሊያን ሀገር ጨረቃም ላይ ቢሆን ሀውልት እንዲሰራ አንፈቅደም፡፡
በጊዜው ሩዶልፍ ግራዚያኒ ወንጀለኛ በመሆኑ የነበረው ፊልድ ማርሻል ማዕረግ ተገፎ ከወታደርነቱ ተባሮ በጦር ወንጀል ተከሶ 19 ዓመት ተፈርዶበት ቅጣቱን ሳይጨርስ ከእስር ቢለቀቅም እ.አ.አ. በ1955 ዓ.ም. ሞቷል፡፡ ታዲያ ይህ በጊዜው ወንጀለኛ ለተባለው ሰው ሐውልትም ሆነ የመታሰቢያ ሙዚየም ማሰራት ኢትዮጵየውያንን መናቅና የአባቶቻችንን ክብር የሚነካ በመሆኑ ሊሰራለት አይገባም፤ እንደውም ለፈፀመው እልቂት ጣሊያን በቂ ካሳ ስላልከፈለች ካሳ መክፈልና በይፋ ይቅርታ መጠየቅ ይገባታል የሚል አቋም ይዘን ነው የወጣነው፡፡ ስለዚህ ግራዚያኒ ከነ አዳፋ ታሪኩ ሌላው እንዳይደግም ሲወሳ መኖር አለበት እንጂ እንደ ጀግና ሐውልት ሊሰራለት፣ሊወደስና ሊመሰገን አይገባም እንላለን፡፡
በወቅቱ የደረስው ጉዳት ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ ይቻላል?
አቶ ታዲዎስ፡- በወቅቱ ግራዚያኒ በፊርማው በግፍ ኢትዮጵያውያንን ያስጨፈጨፋቸው ሰዎች ስም ዝርዝር ከነደብዳቤው አለ፤ የዚህ ቅጂ እኔም ጋር አለ ይታወቃል፡፡ በተለይ የካቲት 12-14 ቀን 1929 ዓ.ም. ከ30 ሺህ በላይ ዜጎቻችንን በግፍ አዲስ አበባ ላይ እራሱ ግራዚያኒ አስጨፍጨፏል፡፡ ከ250 በላይ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስን ጨምሮ መነኮሳትን አስጨፍጭፏል፡፡ ነገር ግን የኢትዮጵያ መንግስት በ1938 ዓ.ም. እ.ኤ.አ. በፈረንሳይ ፓሪስ በተካሄደው አለም አቀፍ ጉባኤ ያቀረበው ሰነድ እንደሚያስረዳው 760,300 ሺህ ዜጎች ወዲያው ሲገደሉ 525,000 ደግሞ ከነቤት ንብረታቸው እንዲቃጠሉ ተደርጎ ህይወታቸው አልፏል፡፡ ከሁለት ሺህ በላይ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለው መነኮሳት ተገድለዋል፣ በርካታ ቅርሶች ተዘርፈው ተወስደዋል፡፡ በርግጥ ከተዘረፉ ቅርሶቻችን መካከል እስካሁን የተመለሰው የአክሱም ሐውልት ብቻ ነው፤ ሌሎቹ ግን አሁንም እዛው ናቸው፤ ሊመለሱልንም ይገባል፡፡ ከዛ ውጭ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የቀንድ ከብቶች በወቅቱ ተዘርፈው ተወስደዋል፤ 7 ሺህ ግመሎችም ተገድለውብናል፡፡ ይህም በሰነድ በተደገፈ ማስረጃ ለዓለም አቀፉ የሰላም ጉባዔ የቀረበ ነው፡፡ በወቅቱ ሰነድ ያልቀረበባቸውና ሰፊ ጥናቶች ሊደረግባቸው የሚገቡ በርካታ ጥፋቶች ተፈፅመዋል፡፡
ይህንን ተቃውሞ በዋነኝነት ማቅረብ የነበረበት መንግስት ነበር የሚሉ ወገኖች አሉ፤ እርስዎስ ምን ይላሉ?
አቶ ታዲዎስ፡- እኔም እስማማለሁ፤ ነገር ግን መንግስት ማዘጋጀት ካልቻለ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ማዘጋጀት ይችላል፡፡ እኔ እንደሚገባኝ መንግስት ተቃውሞ ያላቀረበው ከጣሊያን የሚያገኘው ዕርዳታ ይቀርብኛል በሚል ይመስለኛል፡፡ እኔ እስከማውቀው ይሄ መንግስት ዕለታዊና የፖለቲካ ገበያ ጥቅምን መሰረት ያደረገ እንጂ ወደፊት ትውልድ የሚኮራበትን ስራ የመስራት ዓላማ የለውም፡፡ ከዚህ በፊት የቀደሙ አባቶቻችን የሰሩትን በጎ ታሪኮች ሲያንቋሽሽ የኖረ መንግስት ስለሆነ እንዲህ ዓይነት የአባቶቻችንና እናቶቻችን አርበኞች ታሪክና ክብር የሚያስጠብቅ ስራ ይሰራል ብዬ አላስብም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያዊ ስሜት ያለው፣ ብሔራዊ ስሜትን የጠበቀ ህዝባዊ መንግስት ቢሆን ኖሮ ህዝቡን አስተባብሮ ይሄንን ስራ በቀዳሚነት መስራት የነበረበት እሱ ነበር፡፡ ስለዚህ መንግስት ባያደርግም ዜጎች ይህንን ሰልፍ የማድረግ መብት ስላላቸው እኛም ሰልፉን አድርገናል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የሀውልት ግንባታውን አለመቃወሙ ምን ያስረዳናል?
አቶ ታዲዎስ፡- ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ በእጅ አዙር ለሀውልት ግንባታው እውቅና እንደሰጠ ይቆጠራል፤ ይህንን እኔም አምናለሁ፡፡ ከዚህም በላይ አሁን በስልጣን ላይ ያሉ ሰዎች ባመዛኙ ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ የባንዳ ልጆች የነበሩ ናቸው፡፡ እንደውም ነፃነታችንን ባወጅንበት ሁለት ዓመት ሳይሞላ በአርበኞች ላይ ጦርነት የከፈቱ ናቸው፡፡ ስለዚህ ለግራዚያኒ የጀግና ሐውልት መሰራቱን ባይቃወሙ አይገርመኝም፤ ምክንያቱም እነሱ የማን ልጆች ናቸው? እስኪ በስልጣን ላይ ካሉት (ከኢህአዴግ) መካከል ለሀገሩ እና ለወገኑ ብሔራዊ ስሜት፣ ነፃነትና ክብር የተዋጋ የአርበኛ ልጅ አንድ ሰው ካለ ንገረኝ? አንድም ሰው የለም፡፡ ስለዚህ የባንዳ ልጅ ለጨፍጫፊው ግራዚያኒ በእጅ አዙርም ሆነ በቀጥታ እውቅና በመስጠት ድጋፍ ቢያደርጉ አያስደንቀኝም፡፡
እናንተ ሰላማዊ ሰልፉን ከማድረጋችሁ አንድ ቀን በፊት መጋቢት 7 ቀን 2005 ዓ.ም ስምንት ሰዎች መታሰራቸው ይታወቃል፡፡ ይህ ክስተት በሰልፉ ወቅት እስር እንደሚኖር አልጠቆማችሁም?
አቶ ታዲዎስ፡- እሱን አውቀንም ነው ሰልፍ የወጣነው፡፡ አንድ ቀን አስቀድሞ ሌሎች ቢታሰሩም መውጣት አለብን ብለን ነው የወጣነው፤ እኛም ብንታሰር ሌሎችም እንደሚወጡ እናውቃለን፡፡ ችግር ይፈጠራል ብለን አልተውንም ፤መተውም የለብንም፡፡ ምክንያቱም ይሄ የሀገርና የወገን ጉዳይ ነውና፡፡ በዚህ አጋጣሚ ሰልፉ ላይ የተገኙትን ላመሰግን እወዳለሁ፡፡
የታሰራችሁት ምን ወንጀል ሰርታችኋል ተብላችሁ ነው?
አቶ ታዲዎስ፡- ፍቃድ አልጠየቃችሁም ፣ አላስፈቀዳችሁም በሚል ነው፡፡ ነገር ግን በኢትዮጵያ በነበሩ የአጼ ኃይለስላሴ፣ በደርግ ዘመንም ሆነ አሁንም በወያኔ አገዛዝ ሰላማዊ ሰልፍ ለመውጣት ፈቃድ ይጠየቃል የሚል የተፃፈ ህገመንግስትም ሆነ አዋጅ አልነበረም፤የለምም፡፡ ዋናው ከእኛ የሚጠበቀው ሰላማዊ ሰልፍ እንደምናደርግ ማሳወቅና አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግ ማድረግ እንጂ ፈቃድ መጠየቅ አይደለም፡፡ ይህንንም ለእኛ ጥቅም እንጂ እነሱን ለማስደሰት አይደልም፡፡ እኛ ደግሞ የሀገሪቱን የተፃፈ ህግ ተከትለን ሰልፉን ከማድረጋችን 10 ቀናት አስቀድመን አሳውቀናል፡፡
ኢትዮጵያውያንን በግፍ ለጨፈጨፈው ግራዚያኒ የተሰራለትን ሐውልት በመቃወማችሁ በኢትዮጵያ መንግስት መታሰራችሁ ምን ስሜት ፈጠረባችሁ? ለእኛ የበለጠ የተነሳሽነት ስሜት ሰጥቶናል፡፡ ጉዳዩንም አጠናክረን እንድንሄድ ትልቅ የሞራል ድጋፍ ሆኖናል፡፡
ከእስር ሲለቋችሁ ምን ብለው ነው?
አቶ ታዲዎስ፡- ምንም ሳይሉን ለሁለት ሰው አንዳንድ ዋስ በማስጠራት ለቀውናል፡፡ ምክንያቱን ግን አልነገሩንም፤አላወቅንም፡፡ ከዛ ስትፈለጉ ትመጣላችሁ ብለው በዋስ ለቀውናል፡፡
በታሰራችሁበት ወቅትስ የገጠማችሁ ችግር አለ?
አቶ ታዲዎስ፡- በርግጥ እኔ ላይ ድብደባ አልፈፀሙም እንጂ ተመትተው ፊታቸው በተለይም አፋቸው አካባቢ የደማ ወጣት አይቻለሁ፡፡ ፊታቸው ያባበጠ ወጣቶችንም አይቻለሁ፡፡ ሌሎችንም ወጣቶች እንደደበደቧቸውም ሰምቻለሁ፡፡ በተለይ ደህንነቶች ማታ መጥተው በግል እያስጠሩ በቢሮ ያናግሩ ነበር፡፡ ስራው ግን የፖሊሶች እንጂ የደህንነቶች አልነበረም፡፡ በታሰርንበት ዕለት ያለምግብና ውሃ ቀን ሙሉ እንድንውል ተደርገናል፡፡ በተለይ እስር ቤቱን ስቃይ አራዳ ፖሊስ መምሪያና ጃንሜዳ ፖሊስ ጣቢያ ያለውን ስታይ ዕቃ ለማስቀመጥ ሆነ ለሌሎች እንሰሳቶች ለአንዲት ደቂቃ እንኳን እንዲቆዩበት አይመችም፡፡ እስር ቤቱን ስታይ በጣም ያሳዝናል፤ እዛ የገቡ እኮ ጤነኛ ሆነው የመውጣታቸው ዕድል እራሱ አነስተኛ ነው፤ለበሽታ የሚያጋልጡ ብዙ ነገሮች አሉ፤ ብቻ በጣም ያሳዝናል፡፡ ይሄ ደግሞ የወንበዴ ስራ ነው፤ ይሄንን መንግስት ማረም አለበት፡፡ ሌላው መርማሪ ፖሊሶችና ደህንነቶች ያልተገቡና ከእስሩ ጋር የማይገናኙ የግል ህይወትን የሚመለከቱ ጥያቄዎችን ይጠይቃሉ፣ የኢ-ሜይል የይለፍ ቃል ይጠይቃሉ፣… ብቻ ብዙ ነው፡፡ በግል እኔን ደግሞ ፊታቸውን በኮፊያ የሸፈኑና ጥቁር መነፅር ያደረጉ ደህንነቶች ዋስ ጠርቼ ከወጣሁ በኋላ አንተ የአርበኞችን ታሪክ እያነሳሳህ ወጣቶችን እያነሳሳህ ስለሆነ ብታርፍ ይሻልሃል፤ በግል ልናናግርህ እንፈልጋለን እያሉ ለማስፈራራት ሞክረዋል፡፡ እኔ ግን በህጋዊ ደብዳቤ ያውም ያመንኩበት ካልሆነ ብትጠሩኝ አልመጣም፤ አላናግርም ብያለሁ፡፡
ከዚህ በኋለስ ይህን ተቃውሞ ለመቀጠልስ እቅዱ አላችሁ?
አቶ ታዲዎስ፡- አዎ አለን፡፡ ይህ ተቃውሞ ምላሽ አግኝቶ ያሰብነው እስኪሳካ እንቀጥላለን፡፡ ነገር ግን ዝርዝር ሁኔታውን በተመለከተ እያጠናን ስለሆነ ወደፊት ሀገር ውስጥ ያለነው ውጭ ካሉ ወገኖቻችን ጋር በመመካከር ምን መልክ መያዝ እንዳለበት ስንወስን ይፋ እናደርጋለን፡፡
በመጨረሻም የሚሉት ነገር ካለ ዕድሉን ልስጥዎት
አቶ ታዲዎስ፡- ህዝቡ ዓላማችን ከግብ እንዲደርስ የተለመደ ድጋፉን ከመስጠት ወደ ኋላ እንዳይል አደራ እላለሁ፡፡

ኢህአዴግ ብቻውን እየተወዳደረም አልመረጥም ብሎ ሰግቷል

ላይተቀምጠው ያሉ ካድሬዎችና ደህንነቶች ሠራተኞችንና ነዋሪዎችን በየቀበሌው እንዲሁም በተለያዩ አዳራሾች እየሰበሰቡ ኢህአዴግን መምረጥ ግዴታ እንደሆነ ከዛቻና ከማስፈሪያ ጋር መመሪያ እየሠጡ
መሆናቸውን ምንጮቻችን ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡
የገዢው ፓርቲ ካድሬዎችና ደህንነቶች በተለያዩ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ነዋሪዎች እንዲሰበሰቡ ካስደረጉ በኋላ ስብሰባው
የተጠራበትን አጀንዳ በመተው “ኢህአዴግን መምረጥ ግዴታ ነው፤ ኢህአዴግን አለመምረጥ ፀረ ህዝብነት ነው፡፡”
የሚሉና ሌሎች ማስፈራሪያዎችን እየሰጡ ነው ሲሉ ማንነታቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ መምህራንና የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
ቅሬታቸውን ገልፀዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ከፍለ ከተማ ወረዳ 9 አስተዳደር መጋቢት 11 ቀን 2005 ዓ/ም ነዋሪዎችን ስብሰባ ጠርቶ
እንደነበር የሚናገሩት ምንጮቹ “ስብሰባ የተጠራነው ስለአካባቢያችን ልማትና መልካም አስተዳደር ላይ ለመወያየት
ተብለን ነው፡፡ ስብሰባውን የመሩት የወረዳው ህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ አሰግድ (የወረዳው ኢህአዴግ ኃላፊ
ናቸው፡፡) በስብሰባው ላይ ኢህአዴግን መምረጥ ግዴታ ነው፡፡ በሚል መንፈስ ዛቻና ማስፈራሪያ ሲናገሩ ውለዋል፡፡”
ብለዋል፡፡
ምንጮቻችን አክለውም “ተሰብሳቢው በበኩሉ በየሠፈሩ ያሉትን ችግሮች እያነሳ ተናግሮአል፤ አንዳንዶቻችን እኛ
ጥያቄአችን ምርጫ ሳይሆን የእለት ዳቦ ነው ብንልም ሰብሳቢው ተገቢ ያልሆነ መልስ ሰጥተውናል” በማለት
ቅሬታቸውን ገልጸዋል፡፡
መጋቢት 13 ቀን 2005 ዓ/ም የመዝናኛ ክበባት ሠራተኞች በክፍለ ከተማ ደረጃ ስብሰባ ተጠርተው ነበር፡፡
ከስብሰባው በኃላ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት “የተጠራነው አገልግሎት አሰጣጥ ጉዳይ ለመወያየት ተብሎ ነው፡፡
ነገር ግን ኢህአዴግን መምረጥ ግዴታ እንደሆነ መመሪያ ተስቶናል፡፡ የፈለግነውን መምረጥ እንደምንችል ወይም ማንንም
አለመምረጥ ህገ መንግስታዊ መብታችን መሆኑን ሊረዱልን አልቻሉም፡፡” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በዘንድሮ ምርጫ ነዋሪነታቸው ያልተረጋገጠና የቀበሌ መታወቂያ የሌላቸው ሰዎች ሁሉ በግዳጅ እንዲመዘገቡና ካርድ
እንዲያወጡ ተደርጓል፡፡ የሚል ቅሬታዎች ሲናገሩ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡ በመንግስት ደመወዝ እየተከፈላቸው ሙሉ
ጊዜያቸውን የፓርቲውን ሥራ የሚሠሩና በመንግስት የሥራ ሰዓት ሠራተኛቸውን ለፓርቲው ሥራ የሚያውሉ
የመንግስት ባለሥልጣናት በሙስና ወንጀል ሊጠየቁ ይገባል የሚሉ አስተያየቶችም እየተሰጡ ናቸው፡፡
በመጪው የአካባቢና የአዲስ አበባ መስተዳድር ምርጫ ብቻውን የሚወዳደረው ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ አዲስ አበባ
ላይ ላልመረጥ እችላለሁ በሚል ስጋት ነዋሪዎችንና ሰራተኞችን በስብበሳ ማዋከቡ ብዙዎችን እያስገረመ ነው፡፡
ምንጭ፦ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

Mar 22, 2013

freedom more than food !!!: የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በአብዛኛው ነባር አመራሮቻቸው በስራ አስፈጻሚነት ቀጠሉ

freedom more than food !!!: የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በአብዛኛው ነባር አመራሮቻቸው በስራ አስፈጻሚነት ቀጠሉ

የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በአብዛኛው ነባር አመራሮቻቸው በስራ አስፈጻሚነት ቀጠሉ

ኢሳት ዜና:-የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ሰሞኑን በተከታታይ ባካሄዱዋቸውና በመተካካት ረገድ እምብዛም ለውጥ ያልታየባቸውጉባዔዎች በአብዛኛው ነባር አመራሩን ይዘው ሲያስቀጥሉ መጠነኛ የሆነ እርምጃም ወስደዋል፡፡በዚሁ መሰረት ኦህዴድ አቶ አባዱላ ገመዳን፣ ግርማ ብሩን እና ኩማ ደመቅሳን ከስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት ሲያሰናብት፤ ብአዴን በበኩሉ የፍትህ ሚኒስትር የሆኑትን አቶ ብርሃን ኃይሉን፣ደኢህዴን ደግሞ አቶ ተሾመ ቶጋን አሰናብቷል፡፡ብአዴን በጤና ችግር መደበኛ ስራቸውን ማከናወን የተሳናቸውና ነባር ታጋይ የሆኑትን አቶ ህላዊዮሴፍን፣ኦህዴድ ወ/ሮ አስቴር ማሞን በኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚነት እንዲመረጡ አድርጓል፡፡በተጨማሪም ኦህዴድ የፌዴራል ፖሊስ ኮምሽነሩን አቶ ወርቅነህ ገበየሁን የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ አባል እንዲሆኑ መርጧቸዋል፡፡ በሟቹ ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዕቅድ መሰረት በመተካካት ሒደቱ እስከ 2007 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ቦታ ይለቃሉ ተብለው ይገመቱ የነበሩት ነባር ታጋዮች ለቀጣይ ሁለት ዓመት ተኩል ጊዜያት እንዲቀጥሉ መደረጉ በተለይ ከፍተኛ አመራሩ የመለስን ራዕይ ለማሳካት በተደጋጋሚ የገባውን ቃል ማጠፉን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ተናግረዋል፡፡ በ2003 ዓ.ም በመተካካት ስም የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊነታቸው የለቀቁት አቶ አዲሱ ለገሰን ጨምሮ አቶ በረከት ስምኦን፣አቶ ህላዊ ዮሴፍ፣አቶ አባይ ወልዱ እና የመሳሰሉት ስልጣናቸውን ወደማጠናከር ፊታቸውን ማዞራቸው የመተካካት ዕቅዱ ውሃ እንደበላው ማሳያ ሆኗል፡፡ አቶ አዲሱ ከድርጅቱ በአቶ መለስ አማካኝነት ከተሰናበቱ በሁዋላ ተመልሰው መምጣታቸው አስገራሚ ሆኗል። አቶ አዲሱ ከስልጣን እንዲነሱ የተደረገው እርሳቸው ባልጠበቁበት መንገድ እንደነበር መግለጻቸው ይታወሳል። በመተካካት ስም በ2003 የመንግስት እና ከፓርቲ ኃላፊነታቸው የለቀቁትን እነ አቶ ስዩም መስፍን ጨምሮ ሌሎች 9 የህወሃት አባላት በራሳቸው ፈቃድ በአብዛኛው ከጤና ጋር በተያያዘ ድርጅቱን ለመልቀቅ ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት የተሰናበቱ ሲሆን የእነዚህ ሰዎች መልቀቅ እንደመተካካት ለማየት እየተደረገ ያለው የማደናገሪያ ፕሮፖጋንዳ አሳዛኝ መሆኑን ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡በራሳቸው ፈቃድ ከለቀቁት መካከል አቶ ስዩም መስፍን ፣ አቶ ብርሃነ ገብረክርስቶስ ፣ አቶ አርከበ ዕቁባይና አቶ ዘርዓይ አስገዶም ይገኙበታል፡፡ የዘጠኝ የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በአንድ ጊዜ መልቀቂያ ማቅረባቸው አጋጣሚ ሳይሆን ከአቶ መለስ ህልፈት በሓላ በህወሃት ውስጥ ከተፈጠረው ልዩነት ጋር በተያያዘ ሳይሆን እንደማይቀር ምንጫችን ቢጠቅስም ይህን በተመለከተ ለማረጋገጥ ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም፡፡ ብዙዎች እንደሚገምቱት ከአቶ አርከበ እቁባይ ጋር ጤነኛ ግንኙነት ያልነበራቸው ወ/ሮ አዜብ መስፍን በዚህ ጉባኤ በድል አድራጊነት ወጥተዋል። ህወሀት የአቶ አባይ ወልዱን  ባለቤት ወ/ሮ  ትረፉ ኪዳነማርያምንም በስራ አስፈጻሚነት መርጧቸዋል። ድርጅቶቹ ባካሄዱት ምርጫ መሰረት ከህወሃት፡- አቶ አባይ ወልዱ፣ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል፣ወ/ሮ አዜብ መስፍን፣አቶ አባይ ጸሐዬ፣ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/እግዚአብሔር፣አቶ በየነ ምክሩ፣አቶ ኪሮስ ቢተው፣አቶ አስመላሽ ወ/ስላሴ፤ከብአዴን፡-አቶ አዲሱ ለገሰ፣አቶ በረከት ስምኦን፣አቶ አያሌው ጎበዜ፣አቶ ገዱአንዳርጋቸው፣አቶ ደመቀ መኮንን፣አቶ አለምነው መኮንን፣አቶ ካሳ ተ/ብርሃን፣አቶ ህላዊ ዮሴፍ፣አቶ ተፈራ ደርበው፤ከኦህዴድ፡-አቶ አለማየሁ አቶምሳ፣አቶ ሙክታር ከድር፣ወ/ሮ አስቴር ማሞ፣አቶ ወርቅነህ ገበየሁ፣አቶ ሶፊያን አህመድ፣አቶ ድሪባ ኩማ፣አቶ አድልቃድር ሁሴን፣አቶ ኡመር ሁሴን፣አቶ አበራ ኃይሉ፤ ከደኢህዴን፡-አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣አቶ ሽፈራው ሽጉጤ፣አቶ ሬድዋን ሁሴን፣አቶ መኩሪያ ኃይሌ፣አቶ ሲራጅ ፈጌሳ፣ዶ/ር ሽፈራው ተ/ማርያም፣አቶ አለማየሁ አሰፋ አቶ ደሴ ዳልቼ፣አቶ ተስፋዬ ቢነግዴ የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ሆነው እንዲሰሩ በየድርጅቶቻቸው ተመርጠዋል፡፡ ከፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን እስከ 17 ቀን 2005 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ የሚካሄደው የኢህአዴግ ጉባዔ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝን በሊቀመንበርነት፣አቶ ደመቀ መኮንን በምክትል ሊቀመንበርነት በድጋሚ ይመርጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮቻን ጠቁመዋል፡፡ የኢህአዴግ ድርጅቶች ያደረጉትን ሹም ሽር በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸው አንድ የቀድሞ የሀወሀት ነባር ታጋይ ፡ ምርጫውን “ውሀ ቢወቅጡት ነው” ብለውታል። “ከእነዚህ ሰዎች ምንም የሚጠበቅ ነገር የለም፣ ምን አዲስ ነገር እንደማይፈጥሩም ይታወቃል። የአፈና ስርአቱ እንደሚቀጥል ጥሩ ማሳያ ነው” ብለዋል ታጋዩ።

በአፋር ህጻነት በርሀብ እየረገፉ ነው

ኢሳት ዜና:-በክልሉ ካለፉት አራት ወራት ጀምሮ የተከሰተው ከፍተኛ ረሀብና የውሀ እጥረት የበርካታ ህጻናትን ህይወት መቅጠፉን ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል።ምንም እንኳ 60 በመቶ በሚሆነው የአፋር አካባቢ ከፍተኛ የሆነ የምግብና የውሀ እጥረት ቢከሰተም ፣ ችግሩ ከሁሉም ወረዳዎች አስከፊ ሆኖ በቀጠለበት የእዳ ወረዳ 6 ህጻናት በአንድ ወር ውስጥ ሞተዋል። ይህ አሀዝ በአንድ ሰፈር ብቻ የተጠናከረ እንጅ በአጠቃላይ በወረዳው በተከሰተው ረሀብና የውሀ እጥረት የሟቾች ቁጥር በብዙ መቶዎች ሊደርስ እንደሚችል የአካባቢው ተወላጆች ገልጸዋል።አንድ ጀሪካን ውሀ በ60 ብር ለመግዛት መገደዳቸውን የገለጹት አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የእዳ   ወረዳ ነዋሪ፣ የአካባቢው ነዋሪ ፍየሎቹና ግመሎቹ አልቀውበት ወደ አሳይታ ስደት መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡ አሳይታ በሰላም የደረሱት በህይወት ሲትረፉ ሌሎች ደግሞ በመንገድ ላይ አልቀዋል ።የመንግስት እርዳታ እንዳልመጣላቸው የተነጋሩት ነዋሪዎቹ ፣ አስቸኳይ እርዳታ ካልደረሰ አስከፊ እልቂት ይፈጠራል ብለዋል።በአካባቢው የትጥቅ ትግል በማድረግ ላይ የሚገኘው የአፋር ጋድሌ ሊ/መንበር ኮሎኔል ሙሀመድ አህመድ ለኢሳት እንደገለጡት ከፍተኛ ረሀብ በአካባቢው መግባቱን ድርጅታቸው እንደሚያውቅ ገልጸዋል።በዚህ አመት ከአፋር ሌላ በሶማሊና በተለያዩ የአማራ፣ የደቡብና ኦሮሚያ ክልሎች ድርቅ መግባቱን መረጃዎች ያመለክታሉ።በአዲስ አበባ ህጻናት በምግብ እጦት ትምህርታቸውን መከታተል እንዳልቻሉ ሸገር ኤፍ ኤምን በመጥቀስ ኢሳት ትናንት መዘገቡ ይታወሳል።በግብርናው መስክ ከፍተኛ እመርታ እንዳገኘ ከመናገር ተቆጠቦ የማያውቀው የኢህአዴግ አገዛዝ ፣ ላለፉት 21 አመታት ኢትዮጵያን በምግብ ራሱዋን እንደሚያስችል ቢናገርም እስካሁን ድረስ የታየ ለውጥ የለም። በቅርቡ ይፋ ሆነ አንድ ጥናት እንዳለመከተው ከ7 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በምግብ ለስራ ታቅፈው ከአለም ባንክና ከአውሮፓ ህብረት በሚለገስ ስንዴ እየተደጎሙ ነው። በዚህ አመት የአስቸኳይ ምግብ እርዳታ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከፍ ሊል እንደሚችል ባለሙያዎች ይናገራሉ።በመላው አገሪቱ ከፍተኛ የሆነ የውሀ እና የምግብ እጥረት ቢከሰተም ገዢው ሀይል በቅርቡ 200 ሚሊዮን ብር በማውጣት የብሄር ብሄረሰቦችን በአል አክብሮአል። ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት ደግሞ የመከላከያ ቀንን አክብሮአል።

Total Pageviews

Translate