Pages

Jan 6, 2013

የተቃዋሚ ፖለቲካ ኃይሎች በድረ-መለስ ኢትዮጵያ፣ አይዲዮሎጂካል እና ስትራተጂካዊ ሁኔታዎች በጋሻው አለሙ

የተቃዋሚ ፖለቲካ ኃይሎች በድረ-መለስ ኢትዮጵያ፣ አይዲዮሎጂካል እና ስትራተጂካዊ ሁኔታዎች
1. መግቢያ
የጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊን ህልፈተ-ህይወት ተከትሎ በኢህአዴግ እና በተቃዋሚ
ኃይሎች የሚታየው የመረበሽና ትርምስምስ በመሰረታዊነት ምንጮቹ ፖለቲካዊ፣
ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ቢሮክራሲያዊ ስልጣኖችን በአጠቃለለ ሁኔታ ጠ/ሚ መለስ
በእጃቸው ማስገባታቸውና በእሳቸው ህልፈተ-ህይወት ምክንያት የተከፈተውን የስልጣን
ክፈተት የሚሞላ ተቋማዊ አቅም አለመገንባቱና ሁለተኛ ግለሰብ በስርአቱ ውስጥ አለመኖር
ናቸው:: ስለዚህም በእርሳቸው ህልፈተ-ህይወት የተፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት በሚደረግ
ሂደት ውስጥ በሁለተኛው የኢትዮጵያ ሪፐብሊክ ውስጥ የነበረውን የሃይል አሰላለፍ
የሚያፋልስና፤ ይህም የስልጣን ሽግግር አይዲዮሎጂካልና ስትራተጂካዊ አመክንዮችን
የሚላበስ ነው::  ለመልካምም ይሁን ለመጥፎ ምክንያት፣ ጠ/ሚ መለስ የሁለተኛው
የኢትዮጵያ ሪፐብሊክ መስረታ ሂደትን በበላይነት የመሩ፣ የስርአቱን አይዲዮሎጂካዊና
ስትራተጂካዊ ንድፈ-ሃሳቦች በመቅረጹ ሂደት ላይ ወሳኝ ድርሻ የተጫወቱ ናቸው:: ስለዚህም
የእርሳቸው አለመኖር በገዢው ሃይል ውስጥ የሚከፍተው ክፍተት በአጭር ጊዜ ውስጥ
ሊሞላ የሚችልና ውስጣዊ የስልጣን ሽግግሩ በቀላሉ ሊካሄድ የሚችል አይደለም::
በሌላ በኩል ጠ/ሚ መለስ የተቀዋሚ ሃይሎችን የቀን-ተቀን ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን
በአግባቡ በመከታተል የተቃዋሚ ሃይሎችን አይዲዮሎጂካዊና ስትራተጂካዊ አጀንዳዎች
አስቀድሞ በመቀየስ እንዲሁም የተቃዋሚ ሃይሎች ህዝባዊ ይሁንታ ያገኙባቸውን ፖለቲካዊ
አጀንዳዎችን በመውሰድና ኢህአዴጋዊነትን እያላበሱ በመተግበር የተቃዋሚ ሃይሎችን
አይዲዮሎጂካዊና ስትራተጂካዊ መሰረቶች ለማጥበብ ችለው ነበር::  ይህም ከተቃዋሚ
ሃይሎች ቁመናና አሰላለፍ ጋር ተዳምሮ የተቃውሞ ፖለቲካው በሀገር አቀፍ እንዲሁም
በዲስፖራው ውስጥ ተቋማዊ ገጽታው በትናንሽ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሞላ እንዲሆን
አድርጎታል:: ብዙዎች የገዢው ሃይል ሁሉን አቀፍ ተጽእኖ ለትናንሽ ፖለቲካ ፓርቲዎች
መመስረት እንደምክንያትነት ይጠቅሳሉ:: ነገር ግን፣ ፈረንጆቹ እንደሚሉት ወረራ በራሱ

የድክመት ማሳያ ሲሆን በወረራ ተሸናፊነት ምንጩ ደግሞ ውስጣዊ ድክመት ነው:: የገዢው
ኃይል ተጽእኖ ውጤታማነት ምንጩ የተቃማዊ ኃይሎች ውስጣዊ ድክመት ነውና::
የተቃማዊ ኃይሎች ውስጣዊ ድክመት ሁሉን አቀፍ ድክመት ነው:: በአሁኑ ጊዜ ተቃማዊ
ኃይሎች አይዲዮሎጂካዊ፣ ስትራተጂካዊ፣ ተቋማዊ እና ዕቅዶችን ገቢራዊ የማድረግ
ድክመቶች አለባቸው::  እነዚህም ድክመቶች ከ1997ቱ ምርጫ በኋላ    በስፋት የተቃማዊ
ኃይሎች መሰረታዊ የህዝብ ድጋፍ እያሳጣቸው እንደሆነ እየታየ ነው:: የተቃማዊ ኃይሎች
ልሂቃን ለምሳሌ ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም፣ ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ፣ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ አሁን
ያለውን ስርአት ለመታገል የአሁኑ ትውልድ ሃገራዊ ፍቅርም ሆነ ወኔ ያንሰዋል የሚል
የመከራከሪያ ሃሳብ እያቀረቡ ናቸው:: የአሁኑ ወይስ የትላንቱ ትውልድ ይበልጥ ሀገራዊ
ፍቅር አለው የሚለውን ክርክር ወደ ጎን እንተወውና፣ መሰረታዊ በሆኑ የተቃውሞን
እንቅስቃሴ    እየጎዱ ባሉና አሁን ካለው ሀገራዊ ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ሊስተካከሉና
እንደገና ሊታዩ የሚገቡ አይዲዮሎጂካዊና ስትራተጂካዊ ጉዳዮች ላይ ማተኮር ተገቢ ነው::
የዚህ ጽሁፍ ዋና አላማው በተቃማዊ ሃይሎች ውስጥ ያለውን አይዲዮሎጂካዊና
ስትራተጂካዊ ጉዳዮች በድረ-መለስ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር
ለመዳሰስ ነው:: ምንም እንኳን የድረ-መለስ ኢትዮጵያን በተመለከተ ሁሉን አቀፍ ትንተና
ለማድረግና የወደፊቱን ለመተንበይ ጊዜው ገና ቢሆንም፣ ከተቃማዊ ኃይሎች የሃይል
አሰላለፍ፣ ተቋማዊ ገጽታና ከገዢው ኃይል ተቋማዊ ባህል አንጻር መመልከት የሚቻልበት
ዕድል ሰፊ ነው:: የታላቁ እስክንድሪያ አባባል በመዋስ፣ ኢህአዴጎች የሚፈሩት በበግ የሚመራ
የአንበሶች ተቃውሞ ሳይሆን በአንበሳ የሚመራ የበጎችን ተቃውሞ ነው:: ስለዚህም ይህ
ጹሁፍ ተቃዋሚ ኃይሎች ላይ ትኩረት የሚያደርግና ተቃማዊ ኃይሎች የተጋፈጡባቸውን
አይዲዮሎጂካዊና ስትራተጂካዊ ጉዳዮች ከሀገራዊና አለም አቀፋዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች
አንጻር እንደሚከተለው ለመዳሰስ ሞክሯል::
2. አይዲዮሎጂካዊና ስትራተጂያዊ ጉዳዮች
2.1 አጠቃላይ የትግሉን አላማና ስልት ስለመወስን
አሁን በተቃዋሚ ኃይሎች መካከል ያለው ልዩነት አሁን ያለውን ስርአት ለመቀየር በሚደረግ
ትግል    አስፈላጊ መሆኑ ወይም አለመሆኑ ላይ አይደለም:: በአጠቃላይ በትግሉ አላማና
ስልት ላይ እንጂ:: በአንድ ወቅት ዶ/ር ብርሃኑ የአሁኑን ትግል ከ 1970ዎቹ ትግል ያለው
ልዩነት የገለጸው፤ያለፈው ትግል ሲካሄድ የነበረው የመጨረሻ እውነትን ለማግኘትና
እውነተኛ ህዝባዊና ሶሻሊስታዊ ስርአት ለመገንባት ነበር:: የአሁኑ ትግል በባህሪ ደረጃ ግን

በሂደት ላይ የተመሰረተ የመጨረሻ እውነትን ሳይሆን ሁሉንም የፖለቲካ ኃይሎች
የሚያስማማ አማካይ ቦታ የመፈለግና ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን የመገንባት ነው:: ነገር
ግን ዶ/ር ብርሃኑ እንደሚያስበው ሳይሆን በሁለቱም ትግሎች በመሰረታዊ አስተሳሰብ ደረጃ
በተቃዋሚ ኃይሎች መካከል ያለው ልዩነት እምብዛም ነው:: ሁሉም ተቃዋሚ ኃይሎች
የሚያነጣጥሩት ስርአት ስለመቀየር እንጂ በምንመልኩ መሬት ላይ ያለውን ፖለቲካዊ
ስርአትና ባህል በመሰረታዊነት ስለመለወጥ አይደለም::
ሁሉም የፖለቲካ ስርአቶች ሊሻሻሉ የሚችሉ አይደሉም:: ለምሳሌ የአጼውም ሆነ የደርግ
ስርአት በባህሪያቸው ሊሻሻሉ የሚችሉ አልነበሩም:: በጥገናዊ ለውጥ ሳይሆን እንዚህ
ስርአቶች መወገድ ያለባቸው በመሰረታዊ ለውጦች ነበር:: የሆነውም እንደዛ ነበር:: ነገር ግን፣
ደርግ የአጼውን ቢሮክራሲያዊ፣ ወታደራዊና የደህንነት መዋቅሮች በመውረስ የህልውናው
መሰረቶች እንዲሆኑ ይበልጥ አጠናክሯቸው ነበር:: እንዚህ ተቋሞችና መዋቅሮች በባህሪቸው
ህዝባዊ ሳይሆኑ የህዝቡን የዕለት-ተዕለት ተግባሮች መንግስት የሚቆጣጠርባቸው የጭቆና
ቀንበሮች ነበሩ:: ኢህአዴግም የደርግን ቢሮክራሲያዊ፣ ደህንነት እና ኢኮኖሚያዊ መዋቅሮችን
ከሞላ ጎደለ ከተወሰነ ቅርጻዊ መሻሻሎች ጋር ሲያስቀጥላቸው የደርግን ወታደራዊ ኃይል
በራሱ ኃይል ተክቷል:: ስለዚህም በኢህአዴግ ዘመንም መንግስታዊና ቢሮክራሲያዊ
መዋቅሮች ህዝባዊነት የተላበሱ፣ የሀገሪቷንና የህዝቦቿን ፍላጎትና አንድነት የሚያስጠብቁ
ሳይሆን የገዢውን ቡድን ስልጣን የሚያስጠብቁ ናቸው::
ተቃዋሚ ሃይሎች በአሁኑም ወቅት በዚህ የትግል ልማዳዊ አስተሳሰብ ውስጥ ነው
የሚገኙት:: ተቃማዊ ኃይሎች ከዚህ የትግል አስተሳሰብ ውስጥ መውጣት አለባቸው:: የዚህ
ዝግ አስተሳሰብ ዋነኛ ምንጩ የ1960ዎቹ እና 70ዎቹ ግራ ዘመም እና የዜሮ ድምር
የፖለቲካ ስትራተጂ ናቸው:: ስለዚህም ካለፈው የፖለቲካ ትግል ልምድ ብቻ ሳይሆን
ያለፈውን ትግል በአግባቡ ገምግመው ጠንካራ ጎኖችን ይበልጥ አጠናክረው ደካማ ጎኖችን
ለመቅረፍና ለማሻሻል መትጋት አለባቸው:: ትግል ሂደት ቢሆንም ሂደቱን መረዳትና
የሂደቱን አቅጣጫ መተለም ግን ቁልፍ ጉዳይ ነው ለአንድ ትግል ውጤታማነት::
የቀድሞ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ የተቃዋሚዎችን አይዲዮሎጂካዊና ስትራተጂያዊ ጉዳዮች ላይ
የበላይነት ብቻ ሳይሆን ይዘው የነበሩት፣ ተቋማዊና ውስጣዊ ድክመቶቻቸውን አብጠርጥረው
ለይተው በአስፈላጊው ቦታ ተስማሚውን የፖለቲካ ካርድ እያወጡ አንድም ተቃዋሚዎች
የሃሳብ የበላይነት እንዳይዙ ሁለትም ተቃዋሚዎች ሲጠንክሩ እጅ በመዘርጋት ማለትም
በጥቅማ ጥቅሞች በመደለል እንዲሁም እጅ በመጠምዘዝ ይቆጣጠሯቸው ነበር:: ስለዚህም
የተቃዋሚዎች ውስጣዊ ድክመቶችና የገዢው ቡድን ሁለንተናዊ የበላይነት ጋር ተዳምሮ

ተቃዋሚዎች በመርህ ላይ የተመሰረተ የጋራ አጀንዳና ትብብር መፍጠር እንዳይችሉ
አድርጓቸዋል:: በመሆኑም የተቃውሞ ትግሉ ወደፊት መራመድ እንዳይችልና እስካሁን
ከተከፈለበት መስዋእትነት አንጣር ውጤታማነት እንዳይኖረው ሆኗል::
ስለዚህም አጠቃላይ የትግሉ አላማ መሆን የሚገባው አንዱን ስርአት ጥሎ በሌላ ስርአት
መተካት ሳይሆን፤ ስርአት የመተካቱ ሂደት በባህሪው ዴሞክራሲያዊና ሁሉን አቀፍ
መሰረታዊ ለውጥን ሊላበስ ይገባዋል::  ለዚህም፣ ግለሰቦች ላይ የተንጠለጠለ፣ በትላንት
ቅራኔዎች የተተበተበ፣ በበቀል የተሞላ፣ በጭፍን አስተሳሰብ የተደገፈ የተቃውሞ እንቅስቃሴ
ውጤት እንደማያመጣ መገንዘብና የውጩን መልካም ዕድልና ፈተናዎች በአግባቡ
ለመጠቀም ውስጣዊ ብቃት ወሳኝ መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸዋል::
መሰረታዊ የትግል ስልት ሊመራ የሚገባው በሰላማዊና ህጋዊ ማዕቀፍ ሊሆን ይገባል::
ብዙዎች ወታደራዊ አመጽን እንደ ዋነኛ የትግል ስልት የሚወስዱ አሉ:: ነገር ግን በጠመንጃ
አፈሙዝ አንድትን፣ ሰላምን፣ ዴሞክራሲያዊነትንና ነጻነትን ማግኘት የሚቻልበት መንገድ
በጣም ጠባብና እጅግ አደገኛ ነው:: ትሬር ካረቭር የተባለው ፖለቲካ ሳይንቲስት “Dictatorship in History and Theory: Bonapartism, Caesarism, and Totalitarianism”
ብሎ በሰየመው መጽሃፉ እንደሚሟገተው ምንኛውም ትግል የሃይል እንቅስቃሴን በይበልጥ
የሚጠቀም ከሆን ዴሞክራሲያዊ የመሆን እድሉ በዛው ልክ በጣም አናሳ ነው::  በእርሱ
ቃሎች እንደሚከተለው ይገልጸዋል::
“There has been a good deal of violence, terrorism, armed struggle,
civil war, and worse in the history of the foundation and defense of
democratic regimes. By definition, none of them emerged through democratic process, and the close any struggle comes to force of arms, the
less democratic it is bound to become (Terrell Carver 2004: 107)”
የአጠቃላይ የትግል አላማውም ሆነ ግቡ ለሁሉም እኩል የሆነች፣ ነጻነትና እኩልነት
የሰፈነባት፣ ማህበራዊ ፍትህና የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት፣ መሰረታዊ የብሔር
ብሔረሰቦች ጥያቄዎች የተመለሰባት ዴሞክራሲዊያት ኢትዮጵያን መፍጠር እስከሆነ ድረስ
የትግል ስልቱም እነዚህን ጉዳዮች ይበልጥ ሊያሳካ በሚችልበት አኳኋን መሆን አለበት::
ለዚህም፣ የመጨረሻ ውጤቱ የውጤቱን መንስኤ ይገልጸዋል፤ ወይም ደግሞ የውጤቱ
መንስኤ የመጨረሻ ውጤቱን ይገልጸዋል የሚለው ከሁለት አንዱ አስተሳሰብ ሳይሆን
ለአጠቃላይ የትግሉ አላማ ስኬት የሚስፈልገው ሁለቱንም አስተሳሰቦች ያማከለ መሆን
ይገባዋል::  የትግል ስልቱም የመጨረሻ ውጤቱን ታሳቢ ያደረገ፣ የውጤቱን መንስኤዎች

ከጠቃላይ የትግሉ አላማ ጋር እያዛመዱና መንስኤዎችን ወደውጤት የመቀየር ሂደቱን
ሁሉን አሳታፊና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆን ማስቻልን የሚጠይቅ ነው::
2.2  የብሔር ብሔረሰቦችን ጥያቄ በተመለከተ
የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ የያ ትውልድ እንዲሁም የአሁኑንም ትግል ማዕከላዊ አጀንዳ
ነው::  ይህ ጥያቄ በሶሻሊስታዊ በተለይ ደግሞ በሌኒኒስታዊ-ስታሊኒናዊ ዕይታ እንዲታይ
ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተውና ፈረ-ቀዳጅ የሆነው የዋለልኝ ጹሁፍ ነው::  ይህን ጥያቄ
ከራሱ ታሪካዊ ዳራና ትርጉም መታየት ያለበት ጉዳይ ነው::  የገዢው ቡድን ይህን ጥያቄ
ከአማራ ገዢ መደብ በተለይ ከሸዋ-አማራ የበላይነት አንጻር ሲያዩት፣ የተወሰኑ ምሁራን
የዋለልኝን ጹሁፍ ጨምሮ ይህን ጥያቄ ከአማራ-ትግራይ የበላይነት አንጻር ሲመለከቱት፣
እንደ ጆህን ማርካኪስ “Ethiopia: The Last Two Frontiers” የመሳሰሉ ሙሁራን ደግሞ
የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ ከመሃል ሃገር-ዳር አካባቢ ባሉ የህዝቦች ግንኙነት አንጻር
ይመለከቱታል::  እንደ ዶ/ር መራራ ያሉ ደግሞ ይህንኑ ጥያቄ ከአማራ፣ትግራይና ኦሮሞ
ልሂቃን መካከል በሚደረግ የስልጣን ሹኩቻ አንጻር ያዩታል::  በሌላ በኩል ደግሞ እንደ
ሮደሪገር ኮርፍ የመሳሰሉ የፖለቲካል ሶሾዮሎጂ ሳይንስ ሙሁራን የብሔረሰብ ጉዳይን
ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሚታ አንጻር ሲመለከቱት በዚህም ላይ የሚመሰረት ግንኙነትን
በመሰረታዊነት አንድን ቡድን ያገለለ የጥቅም ግንኙነት እንደሆነ ይገልጹታል:: ይህም ማለት
የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ በጣም ውስብስብና በአመክንዮ ላይ የተመሰረተ መልስ
የሚያስፈልገው ነው::
ይህ ጥያቄ ለተቃዋሚ ኃይሎች የበለጠ ውስብስብ የሚሆነው ከኢህአዴግ አቋም አንጻር ነው::
በአሁኑ ጊዜ ያሉ ተቃዋሚ ኃይሎች የተወሰኑት የበለጠ ስልጣንና መብት ለብሔር
ብሔረሰቦች መሰጠት አለበት የሚል አቋም ሲያራምዱ፤ የተቀሩት ደግሞ አሁን ከተሰጠው
ለብሔር ብሔረሰቦች ስልጣንና መብት ተቀንሶ ለማዕከላዊ መንግስት ይሁን የሚሉ ናቸው::
በዚህም ምክንያት ገዢው ግንባር በዚህ ጥያቄ ላይ ያለው መልስ አማካይ የሆነ የሚመስል
ነው::  በሌላ በኩል ደግሞ አሁን ያለው የፌደራል አወቃቀር የበለጠ የተቃማዊ ኃይሎችን
በብሔረ ፖለቲካ የተጠመዱ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል::  እንደ አብነትም ያህል በአሁኑ ጊዜ
ተመዝግበው ከሚንቀሳቀሱት የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ አብዛኞቹ በብሔር ላይ የተመሰረቱ
የፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸው::  እንደዚሁም በብሔር ላይ የተመሰረቱ ፓርቲዎችና ህብረ-
ብሔራዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያደረጉት የጥምረትና ቅንጅት እንቅስቃሴዎች በአጠቃላይ
ሊባል በሚችል መልኩ ፍሬ አልባ ነበሩ:: ወይም ደግሞ ፍሬ አልባ ናቸው::

በንድፈ-ሃሳባዊ የፖለቲካ ውይይት ዕይታ የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ የሚወድቀው
በግለሰብና የቡድን መብቶች ቅድም ተከተል ላይ የቱ ቅድሚያ መውሰድ አለበት በሚል ነው::
በፖለቲካ ፍልስፍና ታሪክ እንደሚታወቀው በግለሰብ መብቶች ላይ ያተኮረ የፖለቲካ ዕይታ
በደንብ ተጠናክሮ የወጣው በሶሻል ኮንትራስቸዋሊስት (social contractualists)  ተብለው
በሚታወቁት ሆብስ፣ ሩሶው፣ ሞንተስኪውና ሎኬ ስራዎች ነው::  ሆኖም ግን በነዚህ
ፈላስፋዎች ስራዎች እንደተመለከተው የግለሰብ መብቶች ራሳቸውን ችለው የሚቆሙ
ሳይሆን ከሌሎች ግለሰቦች መብቶች፣ ግዴታዎችና ፍላጎቶች ጋር በተያያዘ መልኩ
ማህበረሰባዊ ስምምነቶች ሲኖሩ ብቻ ነው::
ከላይ የተጠቀሰውን በአውሮፓ ተጨባጭ የህይወት አውድ ላይ የተመሰረተውን ንደፈ-ሃሳባዊ
ዕይታ በበለጠ መልኩ ወደ አፍሪካ አምጥቶ መመልከቱ ተገቢ ነው::  በአውሮፓውያን
ፍላስፍና አድማስ እኔ ማለት እኔ ነኝ (I am because I am)  ሲሆን፣ በአፍሪካውን
ፍልስፍና ደግሞ እኔ ማለት እኛ (I am becasue we are)  ማለት ነው::  ይህ ልዩነት
መሰረታዊ የሚሆነው የአውሮፓውያንን የማህበረሰብ አወቃቀርና እዚያ ላይ የተመሰረተውን
ፍልስፍናቸውን ለመረዳት በሚደረግ ጥረት ውስጥና እንዲሁም የአፍሪካውያንን የማህበረሰብ
አወቃቀር ጋር ለማስተያየት በሚሞከርበት ጊዜ ነው::  በተጨባጭ በአገራችን ኢትዮጵያ
የተለያዩ የየራሳቸው ቋንቋ፣ ማንነት፣ ባህልና ትውፊት ያላቸው የብሔር ብሔረሰቦች፣
ሃይማኖቶች፣ ልምዶችና ባህሎች የሚገኙባት ናት::  ከዚህም በላይ፣ በዘመናዊት ኢትዮጵያ
የግንባታ ሂደት ውስጥ የተደረጉ የብሔር ብሔረሰቦችን መብትና ባህሎች የሚጋፉና
በተወሰኑ የሀገሪቱ ክፍሎችም ህልውናቸውን በሚፈታተን መልኩ የተደረገ ነበር::
ስለዚህም የብሔር ብሔረሰቦች መብቶችን ከግለሰቦች መብት ጋር አጣምሮ ማክበር
የሚቻልበት ዕድል ዝግ አይደለም::  መሆን የሚገባውም የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሀገራዊና
ታሪካው ሁኔታዎች ያገናዘበ፤ የተዛነፍን የህዝቦች ግንኙነት በሚያድስና የነገን አብሮነትና
አንድነት በሚያጠናክር መልኩ አይዲዮሎጂካዊና ስትራተጂካዊ ቅርጽ መያዝ አለበት::
ተቃዋሚ ኃይሎችና ልሂቃን ኢትዮጵያዊነትንና የብሔር ብሔርተኝነትን እንደ ሁለት
የተለያዩ ማንነቶች ሳይሆን ተያይዘው በአንድነት ሊከበሩና ሊገለጹ የሚችሉ የአብሮነታችን
ሁለትም አንድም፣ አንድም ሁለትም የሆኑ መብቶች ማድረግ በሚቻልበት መንገድ ላይ
መስራት አለባቸው:: ይህም የገዢው ግንባር በቋንቋ ላይ የተመሰረተ ፌደራሊዝም ስርአትን
እንደ ቋንቋ፣ ኢኮኖሚዊ ትስስር፣ ለአስተዳደር አመቺነትና የመሳሰሉ መስፈርቶች ላይ
የተመሰረተና የህዝቦች በግባባት ላይ የቆመ የፌደራል ስርአት መዘርጋትን እንደ ግብ
መያዝን የሚጠይቅ ነው::

2.3  የእርቅና የመታደስ አስፈላጊነት
የዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ከሞላ ጎደል የውስጥና የውጭ ጦርነቶች የበዛበት ታሪክ
ነው::የውጩን ጦርነቶች እንኳን ብንተው፣ የውስጥ ጦርነቶች የሚፈጥሩት ኢኮኖሚያዊ ፣
ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጫናዎችን ወደ ጎን ብንተው፣ በህዝቦች ላይ ያደረሰውን ስነ-ልቦናዊ
ችግሮችን ወደ ጎን የማያስደርገን ደረጃ ለይ ደርሰናል::ይህ የጦርነት ታሪክ ይበልጥ ውስብስብ
የሚሆነው የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ አስተዳደር ማለትም ፊዊዳላዊ፣ ወታደራዊና አምባገነናዊ
አገዛዝ የስልጣን መደላድሎችንና ስልጣናቸውን የሚያስጠብቁበት መንገድ በህዝብ ውስጥ
ፍርሃትን የሚያነግስ በመሆኑ ጭምር ነው::  በጦርነቶች የመጨረሻ ውጤት የአንድ ወገን
አሸናፊነትና የሌላ ወገን ተሸናፊነት ሲሆን ይህም አሸናፊው በአሸናፊነት ሊቀጥል የሚችለው
ተሸናፊው እንደገና እንዳያንሰራራ በሚያደረግ መልኩ ሲጫነው ሲሆን ተሸናፊውም
ተሸናፊነቱን አምኖ የሚቀበለው እራሱን እንደገና እስኪያንሰራራ ድረስ ነው:: ይህም ሁኔታ
የጦርነት አዙሪትን ይፈጥራል:: በኢትዮጵያም ያለው ሁኔታ በእርግጥም ይሄው ነው::
ይህንን የጦርነት አዙሪት ለመስበር፣ አሸናፊው ሁሉንም ይወስዳል አስተሳሰብ ለመላቀቅና
ሁሉም ወገን አሸናፊ ሊሆን የሚችልበትን ስርአት ለመገንባት ሁሉም ኃይል የዕርቅና
የመታደስ ሂደት ውስጥ ማለፍ ይገባቸዋል::  አለም አቀፉ የዴሞክራሲና የምርጫ ድጋፍ
ተቋም የዕርቅና የመታደስ ሂደትን እንደሚከተለው ይፈታዋል:: [It is] a process through
which society moves from a divided past to shared future (IDEA Handbook
2003: 12).  በዚህ ፍቺ መሰረት የዕርቅና የመታደስ ሂደት ዋና አላማም አንዱ ይቅርታ
ሰጪ ሌላው ተቀባይ አሊያም ደግሞ በባለፈው ጥፋቶች ላይ ለመወቃቀስ ሳይሆን፤ ዋናው
አላማው አንድን ማህበረሰብ ከተከፋፈለ ግንኙነት ወደ የጋራ አንድነትና ብልጽግና መውሰድ
ነው::
የኛም ማህበረሰብ በፖለቲካ ቅራኔ የተወጠረ ማህበረሰብ ነው::  ለምሳሌ፣ በሁለት የተለያዩ
የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በመርህ ላይ የተመሰረተ ግንኙነት ኖሮን አያቅም:: በኢህአፓና
መኤሶን መካከል የነበረው የጥላቻ ፖለቲካ መሰረቱ ግለሰባዊ ፉክክር ቢሆንም፣ የጥላቻ
ፖለቲካውን ወደ ግልጽ የመጠፋፋት ግንኙነት የቀየረው ግን ፖለቲካዊ ልዩነቶች ሳይሆኑ
ማህበራዊ ቁርሾዎች ናቸው::  በነዚህ አንጋፋ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የነበረው
ግንኙነት ከነሱ በኋላ ለተፈጠሩትን የፖለቲካ ፓርቲዎች የእርስ በእርስ የጥላቻ  ግንኙነቶች
መንገድ ከፋች ሆኖ ነው የቀረው::  ይህ የጥላቻ ፖለቲካ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ብቻ
ሳይሆን በአንጋፋ የፖለቲካ ልሂቃንና መሪዎች መካከል ያለ ጭምር ነው:: በፖለቲካ

ፓርቲዎች መካከል ብቻ ሳይሆን ዛሬ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በውስጥ ቅራኔዎችና
የስልጣን ሽኩቻዎች እየታመሱ ናቸው::
በጥላቻ ፖለቲካ በሚመራ የፓለቲካ ስርአት ውስጥ ሁሉንም ሊያስማሙ የሚችሉ ተቋማትና
ተቋማቱ ሊመሩባቸው የሚችሉ የህግ ማዕቀፎች ሊኖር አይችልም:: ለዚህም ሁሉም ኃይሎች
መጀመሪያ ራሳቸውን ማደስና ውስጣዊ ዴሞክራሲያዊ ስርአት መዘርጋት አለባቸው::
የተቀዋሚ ኃይሎች ውስጣዊ ጥንካሬ ከሌላቸው ምንም ያህል ውጫዊ አጋጣሚዎች
ቢኖራቸው በውጤታማነት ሊጠቀሙበት አይችሉም:: ለዚህም እንደምሳሌ እንዴት ደርግ
ስልጣን እንደያዘ ማስታወስ ተገቢ ነው:: ውስጣዊ መታደስ በፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ
መጀመሪያ መካሄድ ያለበት አንገብጋቢ ጉዳይ ነው:: እራሱን ያላደሰ፣ እራሱን ከውስጣዊ
የስልጣን ሹኩቻ ያላወጣ፣ በጥላቻ ፖለቲካ ጽንፍ የያዘ በምንም ታምር ሁሉን አቀፍ
የይቅርታ መድረክ ላይ በውጤታማ ሁኔታ ሊሳተፍ አይችልም::
የፖለቲካ መሪዎች በተማሪነት ዘመናቸው አሊያም ደግሞ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል
በነበረ ግንኙነት ያዳበሩትን ጽንፍ የወጣ በጥላቻ የታፈነ የእርስ በእርስ ግንኑነት ማስወገድ
ያለባቸው በስልጣን ላይ ያለውን ስርአት ለመቀየር ለሚደረገው ትግል ብቻ ሳይሆን ለቀጣይ
ለሚመሰረተው ሁሉን-አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ስርአት መሰረትም ስለሆነ ጭምር ነው::
ውስጣዊ መታደስ እንግዲህ ግቡ ስልጣን ላይ ለመውጣት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን
የፖለቲካ ባህል በመሰረታዊነት ለመቀየር ጭምር ነው::  ባልተቀየረ ፖለቲካዊ ባህል ላይ
ሊተካ የሚችልው ቀድሞ የነበረውን ስርአት ከተወሰነ ኮስሞቲክስና ግለሰቦች ለውጥ ነው::
ባልተቀየረ ፖለቲካዊ ባህል ላይ ተመስርቶ መሰረታዊ መንግስታዊና ብሮክራሲያዊ
የአወቃቀር ለውጥ ሊመጣ አይችልም:: ብሔራዊ እርቅ ያስፈልጋል በማለት ብቻ ብሔራዊ
እርቅ ሊኖር አይችልም:: ላለፉት 20  ዓመታት ብዙ ሙሁራኖችና የፖለቲካ ኃይሎች
ብሔራዊ ዕርቅ እያሉ ቢለፉም አንድም ጠብ ያለ ነገር የለም:: ይህም ውስጣዊ መታደስን
ሳያስቀድሙ በመቅረታቸው ነው:: ለዚህም ካለፈው በመማር መጀመሪያ ውስጣዊ መታደስን
በማምጣት ተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች ውስጣዊ አንድነታቸውን በማጠናከር ለጋራ አላማ
መሳካት በአንድነት ሊቆሙ የሚችሉት::
2.4 ውስጣዊ አቅምን በተመለከተ
የተቃማዊ ኃይሎች ካለባቸው ሁለንተናዊ ድክመቶች ውስጥ አንዱ ውስጣዊ አቅም አለመኖር
ነው:: ውስጣዊ አቅም ሲባል ተቃዋሚ ኃይሎች ድርጅታዊ አደረጃጀት፣ ድርጅታዊ ስርአትና
የሰው ኃይልን የሚመለከት ነው:: አደረጃጀት ከስርአት መቅደም አለበት አሊያም ስርአት
ከአደረጃጀት ይቀድማል የሚለው የስትረተጂክ ማኔጅመንት ንደፈ-ሃሳባዊ ክርክር በራሱ ብዙ

የሚያስብል ቢሆንም፣ ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይሎችና ልሂቃኖች ልምድ ስንነሳ ግን
በአብዛኛው የመናገኘው አስተሳሰብ ማደራጀት፣ ማስታጠቅና ማታገል የሚለውን ንድፈ-ሃሳባዊ
ሃዲድ ነው:: በመሰረቱ ይሄ የአስተሳሰብ ሂደት የሚመነጨው ከማርክስ፣ ሌኒንና ማኦ
ፍልስፍናዎች ናቸው::
ትናንሽ የተቃማዊ ኃይሎች አደረጃጀት የተበጣጠሰ አሰራርና የተወሰነ የሰው ኃይል
ስለሚይዝ የህዝብ ተደራሽነትን የማያጎናጽፍ፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ፍላጎት
አቻችሎና አጣጥም ወደ ሁሉን-አቀፍ አላማ (common objective)  የማያሸጋግርና
ለተቋማዊ ልህቀት ማለትም የፖለሲ ጥራት፣ የነጠረ ራዕይና የፖሊሲና ዕቅድ አፈጻጸም
አቅም ውስኑነት የሚዳርግ ነው:: በሌላ በኩልም የኢትዮጵያን ፖለቲካ በገዢው ግንባር
ውስጥም ሆነ በተቃማዊ ጎራ ሆነው የሚመሩት በተመሳሳይ መልኩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን
ተቋማዊ አቅም የሚለኩባቸውም ሆነ የሚመኩባቸው መስፈርቶች በአመዛኙ የሌኒዚምና
ስታሊኒዝም አሰተሳሰቦች ላይ የተመሰረቱና የአሁኑን ተጨባጭ ሁኔታዎች ያላገናዘቡ
ናቸው:: የገዢው ግንባር የተቋማዊ አቅም አስተሳሰብ የሚንጠለጠልባቸው ነገሮች በዋናነት
የፋይናስና የማቴሪያል አቅርቦቶች፣ ሁሉን አቀፍ ቁጥጥርና የህዝብ አደረጃጀቶች ናቸው::
በተመሳሳይ መልኩ የተቃዋሚ ኃይሎች ጊው ግንባር ጋር የመገዳደር አቅማቸውን
የሚለኩባቸው መስፈርቶች ሃሳባዊ የህዝብ ተቀባይነት፣ የገዢው ኃይል አምባገነንነትና
የነርሱ ዴሞክራሲያዊነትና ኢትዮጵያዊነት ናቸው::
ከላይ የተመለከቱት ተቋማዊ መስፈርቶች አንድም ተቋማዊ ኃይሎች አንድነታቸውንና
መስተጋብራቸውን እንዳያጠናክሩ የትኛው ኃይል ይበልጥ በገዢው መደብ ተበድሏል፣
ተጨቁኗል በሚል የተሸናፊነት ስነ-ልቦና ጋር በመዳበሉ ምክንያት በኢትዮጵያ ፖለቲካ
የሚሳተፉ የፖለቲካ ሊህቃኖች ከፊታቸው የተደቀነውን ትግልና የሃይል መዛለፍ ካለመረዳት
ጋር ተዳምሮ በአሁኑ ሰአት የተቃዋሚ ኃይሎች በህብረተሰቡ ውስጥ ያላቸው የተቀባይነት
ደረጃ ከምርጫ 1997  ጋር ሲወዳደር አነስተኛ ነው:: ደካማ ተቋማዊ ብቃት ህብረተሰባዊ
ተቀባይነትን ብቻ ሳይሆን ፖለቲካ ኃይሎች የሚከተሉንትን የፖለቲካ ስልት ጭምር
ይወስነዋል:: ለምስሌ፣ በምርጫ 1997  ይብዛም ይነስም የተቃማዊ ኃይሎች የነበራቸው
አቀራረብ ከዜሮ-ድምርና እንካ-ሰላንቲያ ፖለቲካ ወጣ ያለና ገዢውን ኃይል በወሳኝ ሀገራዊ
ጉዳዮች ላይ የሞገቱበትና አማራጭ ሃሳቦች ያቀረቡበት ነበር:: ይህ ሁኔታ በኢትዮጵያ
ፖለቲካ አንዴ ብቻ ፈንጥቆ የጠፋ ጉዳይ ነው::
ውስጣዊ አቅሙን የገነባ የተቃዋሚ ኃይል ለመቃወም ብቻ የሚቃወም የፖለቲካ ኃይል
ሳይሆን የሚሆነው የገዢው መደብን ድክመቶችና ጥፋቶች እያመላከተ አማራጭ ሃሳብ

የሚያቀርብ፤ተቋማዊ ቅርጹ ከግለሰቦች ስብእና የላቀና የሌሎችን የፖለቲካ ኃይሎች አማራጭ
የሚረዳና ሁሉን አቀፍ አጀንዳዎች ላይ በሚያስማሙ ጉዳዮች ላይ እየተስማማና የሃሳብ
ልዩነትን እንደተፈጥሮአዊ ህግ የሚቀበል ነው የሚሆነው:: በሀገራችና በሁሉም የፖለቲካ
ኃይሎች ላይ የሚስተዋለው ዋናው ችግር ግለሰባዊ ስብዕና ከፓርቲዎች ህብረተሰባዊ
ተቀባይነት በላይ የሆነና፣ በዚህም ምክንያት የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደግለሰባዊ ንብረትነት
የሚታይበት አስተሳሰብ እያየለ ነው:: ይህም በፖለቲካ ኃይሎች ውስጥ የሃሳብ ልዩነት
ሳይሆን የግለሰቦች ግላዊ ጥላቻዎች በልጠው እንዲታዩ አድርጓል:: በዚህም ሳቢያ የተበታተነ
የተቃውሞ ኃይሎች እንዲፈጠሩና በተመሳሳይ መልኩ እርስ በርሳቸው በጠላትነት
መተያየታቸው በትንሹ እንኳን የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው በሚለው መርህ እንኳን ላይ
የተመሰረተ ጊዜያዊና ታክቲካዊ ትብብር መመስረት ተስኗቸዋል::
ይህ የተቀውሞ ተቃዋሚነትን ያለመረዳት ችግር በመሰረታዊነት የፖለቲካ ኃይሎችን
ህብረተሰባዊ ተቀባይነትንና መሰረትን እያሳጣቸው ይገኛል:: ይህም የፖለቲካ ኃይሎች ወደ
ህብረተሰቡ ውስጥ በመግባትና ህብረተሰቡን በማንቃት የተጠናና በደንብ የተመራ መሰረታዊ
ስርነቀል   ለውጥ ለማምጣት የሚችሉበትን እድል ከመዝጋቱም በላይ እራሳቸው የተቃማዊ
ኃይል ልሂቃኖች የተጣለባቸውን ሃላፊነት በወጉ የተረዱ አይመስሉም:: ለምሳሌ ያህል
በቅርቡ ዶ/ር ነጋሶ በጻፉት ጹሁፍ ላይ “ህብረተሰባችን ብሶተኛና የሚያጉረመርም እንጂ ይህ
ስሜቱ ወደ ህበረተሰባዊ ንዴት አልተለወጠም” ብለዋል:: ይህ አባባል በመሰረታዊነት
የሚነሳው ህዝቡ በመጀመሪያ ደረጃ በሥልጣን ላይ ያለውን ሃይል ለማውረድ አደባባይ
መውጣት አለበት ከዚያ የፖለቲካ ልሂቃኖቹ ወደስልጣን እንምጣ ከሚለው አስተሳሰብ ነው::
ለፖለቲካ ፓርቲዎች ወሳኝ ከሆነው ፖለቲካዊ ስራዎች ወሳኙ ህብረተሰቡን የማንቃትና
የማደራጀት ስራ ነው:: ይህን የቤት ስራ ሳይሰሩ የህበረተሰቡን የንቃት ደረጃ
እንደምክንያትነት ማቅረብ ተገቢ አለመሆን ሳይሆን ለፖለቲካ ፓርቲዎች ውድቀት ጭምር
ነው::
3. እንደማጠቃለያ
የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ባህልና የተቃውሞ አደረጃጀት ታሪክ እንደሚያሳየው ከሆነ በወዳጅና
ጠላት ክፍፍል ላይ የተመሰረተ ነው:: ይህ ክፍፍል በፓለቲካ ተዋናዮች መካከል
በመተማመን ላይ የተመሰረተ ግንኙነት እንዳይፈጥሩ ብቻ ሳይሆን ያደረጋቸው፣ በተቃማዊ
ኃይሎች መካከልም ጭምር አንድነት እንዳይኖሯቸው አድርጓል:: ይህ የጥላቻ ፖለቲካዊ
ባህል ስር የሰደደና ተቋማዊ ቅርጽ የተላበሰ ሆኗል:: በሌላ በኩልም፣ የገዢው ኃይል
ልሂቃኖች እውቀት ላይም ሆነ ጉልበት ላይ የተመሰረተ በተቃዋሚዎቻቸው ላይ የበላይነት

ነበራቸው በጊዜ የተወሰነም ቢሆን:: አጼ ኃይለስላሴ፣ ጓድ መንግስቱና ጠ/ሚ
በተቃዋሚዎቻቸው ላይ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የበላይነት ነበራቸው:: ለዚህም አንዱ
ምክንያት የኢትዮጵያ መሪዎች ተቃዋሚዎቻቸውን ለማጥፋት መንግስታዊ ተቋማትን
ጭምር መጠቀማቸው ነው:: በሌላ በኩል ግን፣ ተቃዋሚዎች እራሳቸው አንድነት መፍጠር
አለመቻላቸው ነው::
ይህ ከላይ የተመለከተው የፖለቲካ ድህነት አዙሪት አሁንም በኢትዮጰያ ፖለቲካ ውስጥ
ጉልህ ሥፍራ መያዙ ነው:: ይህ አዙሪት ሳይወገድና በመሰረታዊነት የኢትዮጵያ ፖለቲካ
ባህል ሳይለወጥ፣ ዴሞክራሲያዊት    ኢትዮጵያን ለመፍጠር የሚደረገው ትግል የመጨረሻ
ውጤቱ አሁን ያለውን አገዛዝ በባሰ አገዛዝ መተካት ይሆናል:: ይህ እንዳይሆን የፖለቲካ
ሃይሎች ተቋማዊ አቅም በመገንባት፣ ውስጣዊ ዴሞክራሲያዊ ባህል በማስፈን እራሳቸውን
መዳስ ይገባቸዋል:: በዚህም በገዢው ሃይል ተይዞባቸው የነበረውን አይዲዮሎጂካዊና
ስትራተጂካዊ የበላይነት በመቀልበስ የሃይል አሰላለፉን መቀየር ይችላሉ::

በሃይማኖት ጉዳዮች ውስጥ የሚደረገው ጣልቃ ገብነት ይቁም! ኢሕአፓ (ዴሞክራሲያዊ)


ህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥት በሃይማኖቶች የውሰጥ አስተዳደር የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት አሁንም በፊት ከነበረው በበለጠ አጠናክሮ ቀጥሎበታል። የውስጥ አሰተዳደራችን ይከበርልን ብለው በሰላማዊ መንገድ በጠየቁ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃ ዘግናኝና አሳፋሪ ከመሆን አልፎ ፍጹም ኢ-ዴሞክራሲያዊ መሆኑ ያሳሰበው ኢሕአፓ (ዴሞክራሲያዊ) ከዚህ በፊት ድርጊቱን በማውገዝ ባወጣው ድርጅታዊ መግለጫው አቋሙን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ አድርጓል። በትዕቢት የተወጠረው ህወሓት/ኢህአዴግ ግን አሁንም በማናለብኝነት የእስልምና እምነት ተከታይ ማኅብረሰብ ተወካዮችን በአሸባሪነት አስሮ እያንገላታቸው፤ እያሰቃያቸውና እየገደላቸው መሆኑ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰወረ አይደለም። ይህ አጉራ ዘለል የመብት ረገጣ በተቃዋሚው ጎራ ብቻ ሳይሆን በውጭ መንግሥታትም ጭምር ተቃውሞ እየቀረበበት ያለ ቢሆንም ህወሓት/እህአዴግ ግን ከዚህ እኩይ ተግባሩ ሊታቀብ አልቻለም።
ህወሓት/እህአዴግ ወደ ሥልጣን እንደመጣ ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቀኖና ሕግና ደንብ ውጭ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያሪክ ወብፁዕ አቡነ መርቆሪዮስን በመሣሪያ አስገድዶ ከመንበራቸው አውርዶ በማባረር የራሱ አባልና ደጋፊ የሆኑትን ሟቹን አቡነ ጳውሎስን መሾሙ ይታወሳል። በዚህም ምክንያት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በሁለት ጎራ ተከፍላ ስትታመስ ከርማለች፤ አሁንም ከዚህ አሳዛኝ ሁኔታ አልተላቀቀችም።
ህወሓት/ኢህአዴግ እራሱ ያወጣው ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 27 “ማንኛውም ሰው በግልም ሆነ በስብስብ የፈለገውን ዕምነት የመከተልና ዕምነቱን የማዳበር፤ የማስተማር ሙሉ መብት አለው፤ መንግሥትም ጣልቃ አይገባም” ይላል። ይሁን እንጂ ህወሓት/ኢህአዴግ ይህን ሕገ-መንግሥት ተብዬው ለዜጎች የሰጠውን መብት እንኳን እየጣሰ በሃይማኖት ተቋሞች የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ገብነቱን ቀጥሎበታል። ይህ ሁኔታ እጅግ ያሳሰባቸው በሁለቱም በኩል ያሉ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ሰላም እንዲወርድና ወብፁዕ አቡነ መርቆሪዮስ ወደ መንበራቸው እንዲመለሱ የውጣ ውረድ ውይይት በማካሄድ ላይ ናቸው። ይሁን እንጂ በለመዱት አምባገነናዊ አሠራር እነ አቶ አባይ ፀሐዬና አቶ ስብሃት ነጋ ጣልቃ በመግባት ሌላ ፓትርያርክ ለማስመረጥ አስመራጭ ኮሚቴ እንዲቋቋም ባስተላለፉት ቀጭን ትዕዛዝ መሠረት አገር ቤት ውስጥ አስመራጭ ኮሚቴ ተቋቋሟል። ከአዲስ አባባ በኩል ለእርቁ መጥተው ከነበሩት አባቶች ውስጥ አንዱ እርቁ ሳይቋጭ ለምን ምርጫ እናደርጋለን ብለው ተቃውሞ በማሰማታቸው ከአገር እንዲባረሩ ተደርጓል። ይህንንም ጅብደኛው በረከት ስሞን ያለምንም ሃፍረት አባረነዋል ሲል ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አረጋግጧል። በሃይማኖት ተቋም ውስጥ በገሃድ ጣልቃ ገብነት ይሏል ይሄ ነው!
የኢትዮጵያው ፕሬዘዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ወብፁዕ አቡነ መርቆሪዮስ ወደ መንበራቸው እንዲመለሱ የሚገልጽ ደብደቤ ጽፈው እንደነበረም ይታወሳል። ይሁን እንጂ ደብዳቤው የተፈረመበት ቀለም እንኳን ሳይደርቅ የተሰረዘ መሆኑን ሰምተናል። ይህ ሊሆን የቻለው በሌላ ምክንያት ሳይሆን አሁንም የነስብሃት ነጋ ጣልቃ ገብነት ለመሆኑ ማስረጃ የሚያስፈልገው አይደለም። አቶ ስብሃት ነጋ አሁን በቅርብ ቀን በመገናኛ ብዙሃን “ህወሓት የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንንና የአማራውን የጀርባ አጥንት ስብሮታል” ብሎ ያለ ሃፍረት መናገሩ ምን ያህል በማናለብኝነት ትዕቢት መወጠሩን የሚያመለክት ነው።
ፀረ-ሰላምና ፀረ-ዴሞክራሲ የሆነው የነስብሃት ነጋ ቡድን ህወሓት/ኢህአዴግ አፀደቅሁት ያለውን ሕገ-መንግሥት ለነሱ በሚያመች መንገድ እየተረጎሙ ሕዝብንና ሀገርን በሚያጠፋ ሜዳ እየጋለቡ ቁልቁለቱንም እየተንደረደሩ ነው። ይህ የመብት ረገጣና አፈና ሊወገድ የሚችለው የተቃዋሚው ኃይል ጠንካራ ኅብረት ፈጥሮ የተረገጠውንና የተበደለውን ሕዝብ አስተባብሮ በመምራት ሲታገል ብቻ ነው። በተነናጠል የሚደረግ ትግል ከኅብረት ትግል የሚገኘውን የፈረጠመ የትግል ውጤት ከመንፈጉም ሌላ ህወሓት/ኢህአዴግ በማናለብኝነት በሕዝባችን ላይ ለሚያደርገው መረን የለቀቀ የአፈና አገዛዝ አስተዋጽዖ እያደረገ መሆኑ በፍጹም አጠያያቂ ሊሆን አይገባም።
ኢሕአፓ (ዴሞክራሲያዊ) ህወሓት/ኢህአዴግ በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነትና ፀረ-ዴሞክራሲያዊ እርምጃዎች ሁሉ አምርሮ ይቃወማል። በኢትዮጵያዊነታቸው ፀንተው በመቆማቸውና በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን የግፍና የአፈና አገዛዝ በማጋለጥና በመቃወም የሕዝብ ድምፅ በመሆናቸው ብቻ እንደ ወንጀለኛ ተቆጥረው በእንበለ ፍርድ (ፍርድ አልባነት) የታሰሩት ንፁህ ኢትዮጵያውያን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ ይፈቱ ይላል ኢሕአፓ (ዴሞክራሲያዊ)።
ሰፊው ሕዝብ ምን ጊዜም አቸናፊ ነው!

በአፈናና ግድያ የህዝቡን የነጻነትና የመብት ጥያቄ ትግል ማቆም አይቻልም! ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ም/ቤት የተሰጠ መግለጫ


ኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግር ም/ቤት በዛሬው እለት ሙስሊም ወገኖቻችን ባካሄዱት ድምፃችን ይሰማ ተቃዉሞ የተጀመረበትን 1ኛ አመት ለማክበር ባከናወኑት እጅግ ታላቅ ሀገር አቀፍEthiopian National Transitional Council የተቃዎሞ ሰላማዊ ስልፍ ላይ እጅግ በሚያሳዝንና በሚሰቀጥጥ ሁኔታ አንድ እድሜዉ ከአስር አመት በታች የሆነ የሀረር ከተማ ህጻን በጨካኞቹና ጨፍጫፊዎቹ ፌደራል ፖሊሶች ተገድሏል። ምክር ቤቱም የህፃን ልጅ ግድያዉ እጅግ ሰብአዊነት የጎደለዉና የስርአቱን አረመኔነት ደግሞ የሚያረጋግጥ ተግባር መሆኑን በመግለጽ ግድያዉን በምሬት አጥብቆ ያወግዛል። የሽግግር ም/ቤቱም ጉዳዮ ባስቸኳይ ተጣርቶ ግድያዉን የፈፀሙት በህግ ፊት በሃላፊነት እንዲጠየቁ አጥብቆ ይጠይቃል። ግድያዉንም ሁሉም የሀገራችንና የአለማቀፉ ማህበረሰብ እንዲያወግዘዉና በሃገር ዉስጥ ያሉ የፖለቲካና ሲቪክ ድርጅቶችም ግድያዉ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ ግፊት እንዲያደርጉና ወንጀለኞቹ ለህግ የሚቀርቡበት ሁኔታ ላይ ተባብረዉ እንዲሰሩ ጥሪዉን ያቀርባል። በዛሬዉ እለት ሰማእት የሆነዉ ህፃን በሁላችንም ለዲሞክራሲ፤ ለፍትህ፤ ለህዝቦች ነፃነትና፤ እኩልነት በምንታገለዉ ወገኖች ዘንድ ዘላለም በሰማእትነት ሲዘከር ይኖራል። የህፃኑም ሰማእትነት ሁላችንም ለትግሉ ያለንን ቅርጠኝነትና አንድነት ይበልጥ እንደሚያጠናክርና የድሉንም ሂደት እንደሚያፋጥን ጨቋኞቻችን እንዲረዱ በድጋሚ እያረጋገጥን ለሰማእቱ ልጃችን ቤተሰቦች አምላክ ጽናቱን እንዲሰጥ እንለምናለን።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!
ሽግግር ም/ቤቱ ስራ አመራር

Reframing the Post Meles Political Discourse (Ali Belew)


By Ali Belew
A couple of months ago, a group of longtime friends spent a three day weekend at Raytown, Pennsylvania, a picturesque resort town whose landscape reminds us of our Ethiopian homeland. One night, while we were all gathered by the fire place in this wooded area, one person took it on himself to solicit our reaction to the death of Meles. The parameter for the discussion was fairly limited: we would limit our opinion to a few minutes; there will not be questions and exchanges.
We took turns expressing our reaction. Many people applauded the Prime Minister’s leadership skill citing Ethiopia’s success in maintaining uninterrupted and sustained economic growth. Many others also condemned his dictatorial rule citing the lack of democratic space and the state’s infringement on human rights and free elections. Almost all of us lamented his death and expressed sadness at a promising life cut short, and sympathy for his family. No one rejoiced his death; no one gloated; no one said that Ethiopia would be better for it.
I was surprised both by the diversity of opinion regarding Prime Minster Meles’ rule and the tone of the language used to express our feelings for his death. When my turn came, I said, I understand both the negative and the positive statements made and added, on balance, the Prime Minster has done more good than bad to the country and history would be a lot kinder to him for this. In my view, Meles would be one of the greatest leaders Ethiopia ever had, which generated some applause from a few of my friends. I know this judgment is better left to posterity. I am comparing him to Mengistu, Haile Selassie, Lej Eyasu, Zewditu, Menelik, Yohannes and Theodros, etc.
I can’t claim our group is representative of Ethiopia or the diaspora for that matter although we are quite a mix of people with varying background and interest. In the current political lexicon, we can be considered mostly Amharas although many would find this term un acceptable and would prefer to be called Ethiopians. However the sentiment expressed that night can be generalized to be reflective of the mood of the Country and the diaspora.
This is the first time in over 80 years that a ruler of Ethiopia had died while still holding the reign of power. Haile Selassie died in prison having been forced out of his throne and strangled to death by Mengistu’s henchmen. The country, gripped in a frenzy of revolutionary fervor, did not mourn a leader who had introduced a degree of modernity to an ancient empire. Mengistu was overthrown, but is now living in a foreign land rewriting history and spreading falsehood.
The death of Meles is thus a new experience to Ethiopia. That is probably why both his illness and death were shrouded in mystery, an understandable confusion considering the lack of collective historical experience in this respect.
Now Meles has passed away leaving a legacy the like of which the county has never known, both the ruling party and the opposition groups seem to have no clue as to how to handle the vacuum created by his death.
First EPRDF
The EPRDF or TPLF, its political epicenter remains a formidable organization that no opposition can challenge. Despite its remarkable success in the battlefields and running a state, its experience in managing a transition of this magnitude is limited. True it has managed the rifts in its ranks in its formative years much more intelligently than EPRP did for example. It has also survived the more recent serious rift within its ranks with Meles consolidating power. The 1998 split is said to have seriously weakened the narrow Tigrai nationalism. As easy as it seems from outside, political transition is both tricky and dangerous notwithstanding the seeming lack of concern by Sebhat Nega and Berket Simeon and other officials. Had it been easy, this shrewd organization would not have made a fool of itself in its handling of the Prime Minister’s absence from power for two months prior to his death. The transition to the next Prime Minster is fraught with all sorts of dangers that could destabilize the system.
In the short run, Hailemariam Desalegne will hold the office without the actual power since it takes time and skill to yield effective authority. Without prejudicing the ability of the new prime minster, he has a long way to go to align his authority with the power centers of the country, the political parties, the military and security apparatus. By all accounts the Prime Minister is a descent fellow of faith un-accustomed to the byzantine leftist politics and intrigues.
The Opposition:
Much of the domestic opposition in Ethiopia is decimated by EPRP’s repressive measures and by its own scandal ridden coalitions. The 2005 elections showed the promise of competitive elections in Ethiopia. Although the opposition scored impressive victories, it also showed that that it lacked coherent strategy and unified post-election posture. The forged unity was more for winning parliamentary seats than forming a governing coalition. When the opposition faced a real crisis after the election, with the government annulling some of its hard-won seats, the opposition failed to respond in a way that showed that it grasped the problem it faced and its impact for its political future. It ignited an urban rebellion that proved disastrous and resulted in the current disarray.
The government learning from its mistake tried to address the public discontent with policies that foster more economic growth in areas which were previously neglected. This was combined with a systematic repression of the opposition groups that left them crippled and un-able to compete in any meaningful way with the omniscient EPRDF parties.

Growth at the cost of human rights (Graphics: Awramba Times)
The opposition, divided as it is, has not really responded in a meaningful way to the death of Meles. Individuals such as Seye Abraham and Birtukan have spoken with empathy and thoughtfulness mourning the death of a worthy adversary, but expressing hope for a more inclusive political environment. A group of political opposition groups has also put out a statement that calls for a national convention to bring about political reconciliation. National Convention and National Reconciliation appear as slogans all the time when there is a political impasse, but they can’t be road maps to the future. One may recall there was a similar slogan when EPRDF triumphantly marched into Addis 20 years ago. The rest of the opposition of course consists of individuals who write in the opposition media. These range from the most strident who express jubilation to those who are enormously conflicted about death. These individuals express their sorrow at the death of a fellow human being regardless of his attributes while castigating his rule and legacy.
Many others see some opportunities and may want to take the high road in exploiting it. This is a developing event, but we don’t know the direction it will follow. Of course what happens next depends much on what the ruling party does than on the opposition. But the opposition can also play a more positive role that can encourage changes conducive to more ordered political debate in Ethiopia.
Clash of Narrative – Suggestion for a revision
Much of the conflict that animates Ethiopians is not a more recent phenomenon. It started when EPRDF took power.
The Opposition’s Narrative: TPLF, which is the power behind the EPRDF coalition is an organization dedicated to transforming Ethiopia in a way that we will never recognize it. It wants to weaken central power by divulging it into ethnic states. Each ethnic entity has the right to secede from the Union leaving Ethiopia in a permanent state of conflict. This allows TPLF to rule the country indefinitely exploiting the resource rich south and developing its Tigrai state through direct resource transfer. If this ethnic federation arrangement does not work, says this narrative, the goal of TPLF is to maintain independent Tigrai separate from the rest of Ethiopia, using the intervening period to build its infrastructure and industry.
This narrative claims the TPLF’s leadership, especially Meles does not have emotional affinity to Ethiopia. The more strident view expressed by well educated people in and outside the country even goes as far to say Meles hates Ethiopia. They claim Ethiopia is the only country in the World ruled by a man who hates it. There is similar narrative about Obama that the right wing opinion makers in this country also push. Example for this is given citing Meles statement on the national flag, his praise of the people of Trigrai as indestructible, etc. The fallacy of this argument lies in the fact that if one loves Tigrai, one would have to love Ethiopia less or loving Ethiopia means loving other ethnic groups less. We know the world does not work that way.
If you follow the premise of the narrative to its logical end, then everything that happened in Ethiopia ever since TPLF came to Ethiopia has only contributed to the weakening of the country. TPLF is conveniently blamed for the breakaway of Eritrean and Ethiopia’s land locked status. Ethiopia is now at war within itself, economic progress has not happened, but if it did, it is only to benefit TPLF or EPRDF cadres and Tigrai. The Diaspoa opposition even postulates EPRF did not win power in an armed struggle, but was handed power by Herman Cohn and the U.S Government . Even the Renaissance Dam that is being built to harness the Nile River is to swindle the people of their hard earned money and expand the regime’s political legitimacy. In effect, this narrative does not allow you to acknowledge the impressive victory the country has scored in the past two decades. It does not acknowledge the period of peace and stability (marred briefly by the bloody war with Eritrea) that has brought far reaching changes; there is no room even for a grudging respect to the country’s regional and international standing.
EPRDF’s Narrative
EPRDF also has its own ideological blinders. It is blind to the emotional toll that ethnic political arrangement has created to many urbanized intellectuals who see themselves as Ethiopians first and Amhara, Oromo, etc., second. It sees its opposition mainly as Amhara chauvinists who are raging mad that the Ethiopia they ruled with iron fist lording it over other ethnic groups is replaced with a country that celebrates everyone as equal and provides them with the opportunity to grow their culture and economy. If EPRDF was to follow this logic, the situation in Ethiopia would lead to the political and economic ascendancy of Oromo, with which the regime seems uncomfortable for now. But here, EPRDF’s narrative and ideological world comes in conflict with itself and it has not found a way out of it. While the Amhara “chauvinism” was, for better or worse, dealt a serious blow in the last 40 years, one wonders now if it is not being replaced by Tirgrai chauvinism. That is to show that EPRDF’s narrative is as much in crisis as the Opposition’s narrative.
It is time to rethink these clashing narratives because conditions have changed on the ground. The reality is much more complex than these world views can explain. The TPLF leadership that once entertained the idea of separate Tigrai has now allowed it to be much more integrated with the rest of the country and sees its success in the success of the rest of the country. Individuals who were considered hardened Tigrai nationalists like Seye have broken off from the party and joined opposition groups. Intellectuals like Berhanu Nega who warned against alienating TPLF leadership are now associated with a group that advocates communal boycott of Tigrai owned business and the only Ethiopian flag carrier, the Ethiopian Air Lines.
The Facts on the Ground:
1. Economics:
I was in Ethiopia recently and saw a county that has made strides on different fronts. The changes are astonishing. I saw a country on the move, a hectic, chaotic place, and restless young people who are building a foundation for a country to take off. In my view, the foundations of Ethiopia’s economic progress are the following.
1.A sustained period of political stability and the regime’s intelligence in the economic sphere. Maybe Dr. Stieglitz is right – Meles had an unusual aptitude for economics. He also had the vision and the leadership qualities to make it work.
2.Generous international assistance and the country’s capacity to utilize it
3.Single-minded focus on building the country’s infrastructure (roads, power plants, airports)
4.Remittances – the 2 + million plus Ethiopians living outside the country seem to contribute to the building boom and are a source of livelihood for millions of Ethiopians
5.Sheik Alamoud’s investments.
6.Tremendous improvement in the healthcare of the people.
This we can’t deny. Whether we like the government or not, we have to acknowledge the fact that the country has made enormous progress in education, healthcare, reversing the deforestation of the country. In fact we should celebrate our roads, hydroelectric dams, massive building projects in Addis and everywhere as are our national treasure that no one would take away. They are here to stay and they are good for the future of the country.
Critics say that there is unacceptable level of wealth transfer from the center to Tigrai. There is also the valid criticism that business linked to the ruling parties and mostly TPLF have an unfair advantage in the market place. The TPLF affiliated endowment groups have become huge conglomerates that no one can compete with. Access to bank capital also favors the endowment groups and the politically connected individuals, mostly Tigraways, but Amharas, Gurage, and Oromos. Corruption is rife. All of these can distort the functioning of the market and slow economic growth. It also has bred enormous animosity within many people which could destroy the very fabric of the unity of the people. I think these are valid criticisms that a responsible opposition could raise and struggle to change.
2 The Constitution:
Ethiopia has now experimented with constitutional government for many years. The constitution, despite its shortcomings has served the country very well. Even the opposition, before it fractured accepted the main tenets of the constitution when it participated in the elections. Many serious intellectuals and opposition members have issue with article 39 of the constitution which enshrines “Every Nation, Nationality and People in Ethiopia has an unconditional right to Self-determination, including the right to secession.” Although no one has so far attempted to exercise this right, the very existence of this clause in the constitution is seen as subversive to the country’s unity and strength and many patriotic individuals are vehemently opposed to it. This will remain a point of contention for a long time to come.
The question is then how do people who are opposed to Article 39 struggle against. Do they oppose the Ethiopian constitution altogether and attempt to change it? How does one struggle against a government when one has fundamental opposition to the constitution?
It is imperative on the opposition to have an honest and consistent opinion vis-à-vis the Ethiopian constitution. Do they accept this and try to make amendments to the constitution? Does this mean that they struggle to come to power through elections? Alternatively do they reject the constitution which means reject the very legitimacy of the government and try to overthrow it by other means which includes armed struggle?
The constitution is a fact on the ground. This means, a responsible opposition which strives for peaceful transfer of power, no matter how hard it is and how long it takes, has to work within the current constitutional arrangement. Any other alternative, when there are so many desperate political groups, who are superficially united by their opposition to the regime, but are by no means unified in their vision and governance of the Country after the current regime, would lead to political instability from which no one would benefit.
3.Ethnic Federalism:
Whether one likes it or not, this is the most transformative change that has taken place in Ethiopia. Ethnic Federalism has now deep roots in Ethiopia. It has its discontents and in some cases, has led to violent clashes between communities. We may argue that it has taken the lead off simmering communal conflicts that were suppressed under the previous governments. That is why we see so many conflicts. For many Oromos, this arrangement falls far short of their maximalist goal of separation from rest of Ethiopia, but it offers them a chance to have their legitimate share of resources and power in the country. At this time, many Oromos in the opposition don’t see it that way. They have formed tactical alliance with the opposition, but I am not sure the maximalist ideology is weakend. It would raise its head again if EPRDF is seen to be weak. There is no threat more dangerous to the stability of Ethiopia than the Oromo question. The question is then would the Ethnic Federalism arrangement be able to blunt the maximalist tendencies of the Oromo movements? Is the Oromo dissatisfaction more because EPRDF is not implementing the policy seriously allowing the Oromos to have their share of political power? Whether or not Ethnic Federalism will stay the reality on the ground will be determined by the
4.Freedom of the Press, Speech, etc.
No one would argue Freedom of the Press and Speech exists in Ethiopia as we have come to understand these rights. For a country not used to these rights, there was a tremendous opening by the government, but a demonstrated lack of professionalism on the part of the media early on. There was abuse of these rights initially. One can’t forget the sensational and malicious stories printed on many newspapers and magazines in the early periods of EPRDF rule. I recently heard an interview in Sheger Radio that was really revealing. Dr. Kifle Wodajo, who apparently struggled more than any other person to enshrine these rights in the Constitution, was also the person who fell victim to it. Talk of an irony.
Governments are generally afraid of the damage that a free press can do to their stability. EPRDF was no exception. It saw the potential damage to national unity and economic progress this could create and reacted harshly. I understand this reaction. I see governments everywhere, even the ones that have longer history of press freedom, do it. The question now is has EPRDF gone too far in suppressing press freedom snuffing out even responsible publication. I believe it has. This is especially true in the post 2005 period. Just to mention a few, Addis Neger, Awramba, etc in recent times. This opposition papers have to also be responsible and play a positive role to the expansion of a democratic space. It is not enough to say the government is the only one responsible for it. The opposition media has responsibility to it. The arrest of Eskender Nega is also an act of intimidation designed to stifle political opposition.
5.The Terrorism Law:
EPRDF emerged from the most recent election as the strongest organization in the country with a higher degree of legitimacy. Right when it became the strongest organization in its history, it also became the most repressive. Now, I think EPRDF believes that the only way to achieve sustained economic growth is through a strong one party rule unencumbered by a political opposition. The imperative for growth has trumped the need for democracy, political freedom and the right to organize, and sustain political parties. The public disgust with the political opposition in the aftermath of the 2005 election seemed to have reinforced EPRDF’s conviction that if Ethiopia is to become a modern country with strong industrial and agricultural base, a visionary one party state just like China is an imperative. Given EPRDF’s ideological predilection, this swing to the left should come as no surprise.
One can see the terrorism law in this light. EPRDF is determined not to allow political opposition in the short run until Ethiopia’s economic growth achieves a level that can propel the country to a middle-income nation status.
As long as the economic growth continues and the Ethiopian people benefit from an expanding economy, the public may tolerate the lack of political freedom for a while. However, this is not easy to sustain. For one thing, EPRDF is not the Chinese Communist Party. While a corruption is rampant in CCP, in Ethiopia there is the wide-spread perception that equates the corruption to the ruling Ethnic group. Increase in prosperity raises relative expectations. When people feel that the economic growth brings disproportionate benefit to the other people, their resentment increases. In Ethiopia this feeling is easy to manipulate.
This is to say, achieving Economic growth through a one party state may not be so feasible in Ethiopia. The current inflation rate by itself has a destabilizing effect. The fact that there is no opposition group in the country to exploit this situation, is not a justification to continue with the repressive measure and draconian terrorism laws that forestall the growth of a viable opposition. As enticing as it is, to say we will bring economic growth through a one party-rule, but will not be obliged to open up the political space, will not work for the ruling party. EPRDF will need to bring the political opposition to have a stake in the economic progress and for that to happen, and the opposition must have political to room to organize.
This is to say the terrorism law must be rescinded or applied only in cases of real threat to the country’s stability. The danger of relying on its limited applications only however is that uncertainty it engenders. No one will feel safe enough to oppose the government and escape the wide reach of the law.
How do we discuss these issues?
Ethiopia faces a transition period that is fraught with dangers. The ruling party has no experience with political transition of this magnitude.
The Government:
1.The government must understand that it is incumbent on it to lead the transition in orderly fashion
2.In the short-term, the regime may feel the need to show there is a continuity of policy
3.In the long-run, the departure of a leader who had assumed so much power within government and in the party creates conditions for change and EPRDF must embrace it
4.It is incumbent on the regime to examine the closing of the political space and open it up for the sake of the political stability of the Country. Political liberalization does not necessarily result in political destabilization. The regime is powerful enough to engineer the smooth transition of the country where political competition exists. Meles’ personality may have made the current political reality workable, but there is no guarantee the next leader has all the attributes to make the system work as it is.
5.The regime must understand it is better to be proactive and bring out political changes, than to be forced to do so. The time to do the political reform is when you are at your strongest. No one benefits from a crisis resolution mode that is now unfolding in Syria, one of the strongest and most powerful states in the Middle East.
The Opposition:
Here, I am referring to the broad opposition within the country and diaspora including influential writers and intellectuals.
1.Many of the opposition figures especially the diaspora based, is hell bent on the fall of the regime without any consideration to the consequences of it. There is no political opposition now or in the foreseeable future that could take over the country and create a stable regime. The formation of a ruling coalition consisting of the opposition elements is not in the horizon yet.
2.Stop demonizing the regime as an evil entity. This is true of elements of the diaspora. Malicious publications designed to create communal strife and incite against the regime won’t do anyone any good.
3.Acknowledge that Ethiopia has enjoyed an unprecedented period of political stability and economic growth, which has lifted millions of Ethiopians out of poverty and given them a life of dignity.
4.Ethiopia’s transition to multi-party country takes a long time. It is not to be expected in the span of a couple of elections. It is through a long, arduous struggle that it can become a truly democratic country. We can’t use the yardstick of an ideal democracy to measure Ethiopia’s political progress.
5.Economic progress is good. It creates a class of people that will struggle for its rights and political empowerment. There is nothing wrong in praising the government’s success while criticizing the short coming. For example, the land-lease policy is an area the opposition could engage the country’s leadership positively.
6.The opposition must acknowledge that it has some responsibility in moderating its language and reframing and elevating the political discourse. Should Ethiopia descend into political chaos, the opposition can’t escape the blame.
This article is intended to stem the political polarization that has now reached a dangerous level. I am sure there are voices like mine that have chosen to remain quiet and feel alienated by the current political discourse. Our voices should be heard.

Jan 5, 2013

የክርስትና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የኢህአዴግ አባላት ወገኖቻችን!




By Nasrudin Ousman 
ላለፉት 12 ወራት ስናካሂድ የቆየነውን ሰላማዊ የመብት ጥያቄ እጅግ በቅርበት እንደተከታተላችሁት እናውቃለን፡፡ የህዝበ
ሙስሊሙን ጥያቄዎች ምንነት እና ህገ መንግሥታዊ መብታችንን ለማስከበር እስካሁን የተጓዝንበትን ፍፁም ሰላማዊ


አካሄድም ከእናንተ በላይ የሚያውቅ የለም፡፡ በወርኃ መስከረም “ለመጅሊስ ምርጫ ተመዝገቡ” ልትሉን በራፋችንን
ባንኳኳችሁበት ጊዜ “እስኪ አረፍ በሉ” ብለን በሰከነ መንፈስ ያዋራናችሁ የኢህአዴግ አባላት ይህንን ሐቅ አሳምራችሁ
እንደምታውቁ በአንደበታችሁ ነግራችሁናል፡፡
በጥሩ መንፈስ ስላነጋገራችሁን በምርጫው የማንሳተፍበትን ምክንያት በዝርዝር ካስረዳናችሁ በኋላ፣ ያኔ የጠየቅናችሁን
አንድ  ጥያቄ ዛሬም እናስታውሳችሁ፡ እኛ ሙስሊሞች የእያንዳንዳችሁን በር ቀብቅበን ‘በሲኖዶስ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ
ተመዝገቡ’  ብንላችሁ፣ ምን ይሰማችኋል?”  ብለናችሁ ነበር፡፡ ህዝበ ክርስቲያኑና ሙስሊሙ እጅተሰባጥ  
ተከባብሮ በሚኖርባት አገራችን፣ ይበልጡንም ይህ አብሮ መኖር ጎልቶ በሚታይባት ዋና ከተማችን፣ ለዘመናት የቆየው
የመከባበር ባህል ይህንን እንድናደርግ አይፈቅድልንምና እኛ አናደርገውም፡፡ አባል የሆናችሁበት ድርጅት ኢህአዴግ ግን
የክርስትና እምነት ተከታይ የሆናችሁትን እናንተን ይህንን እንድታደርጉ አዘዛችሁ፡፡ ይህንንም በማድረግ ድርጅታችሁ
ኢህአዴግ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች መካከል በክፉም ሆነ በደግ ጊዜ ለፈተናዎች ሳይበገር ፀንቶ የቆየውን
በመከባበር አብሮ የመኖር ታላቅ ኢትዮጵያዊ እሴት ገሠሠው፡፡ አዎ፣ ድርጅታችሁ ኢህአዴግ ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ኢትዮጵያ
የተለያዩ ሃይማኖት ተከታዮች ተሳስበውና ተከባብረው በሰላምና በፍቅር አብረው የሚኖሩባት አገር ስለመሆኗ
እየለፈፈ፣ መሬት ላይ ግን ይህንን የመከባበርና የመተሳሰብ ታላቅ እሴት በአደባባይ ረገጠው፤ ጨፈለቀውም፡፡
ድርጅታችሁ ነገ በታሪክ ፊት በአስነዋሪነት ለሚወሳው ለዚህ ዕኩይ ተግባር ሲያሰማራችሁ፣ እናንት ወገኖቻችን የዘመንን
አጥር ለተሻገረው  ተከባብሮና ተሳስቦ የመኖር ታላቅ ኢትዮጵያዊ እሴት ጥብቅና ከመቆም ይልቅ ጊዜውን ጠብቆ ማለፉ
ለማይቀረው ኢህአዴግ ታማኝ መሆናችሁ አሳዝኖናል፡፡ ምንም እንኳ የድርጅታችሁ ኢህአዴግ ርዕዮት እንደ ግለሰብ
የምታስቡትን፣ ኅሊናችሁ የሚነግራችሁንና የምታምኑበትን እንድትሠሩ ባይፈቅድላችሁም፣ መቼም ሰው ናችሁና አንዳንድ
ጊዜ “ምን እየሠራሁ ነው?” ብላችሁ ከኅሊናችሁ ጋር መነጋገር እንዳለባችሁ እኛ ልናስታውሳችሁ አይገባም፡፡ … ስለዚህ
ጉዳይ በስፋት እና በጥልቀት ብንወያይ ምንኛ በወደድን! … ነገር ግን ያንን ለማድረግ በቂ ጊዜ የለንም፡፡ ስለዚህ፣ ከፊት
ለፊታችን ስለተደቀነውና በእኛ እምነት ለአገራችን ሰላምና መረጋጋትም ሆነ ለህዝባችን ተሳስቦና ተከባብሮ የመኖር እሴት
አደጋ ስለሆነው የነገው ድርጅታዊ ተልዕኳችሁ ብንነጋገር ይሻላል፡፡
… ዘግይተን እንደሰማነው፣ ከፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር በመጣ ትዕዛዝ በአዲስ አበባ የምትገኙ በርካታ የክፍለ ከተማና
የወረዳ ኢህአዴግ፣ እንዲሁም የ“ደኅንነት”  አባላት በነገው ዕለት የሚካሄደውን የህዝበ-ሙስሊሙ ሰላማዊ ተቃውሞ
በመስጊድ ውስጥና በዙርያው በሰጋጁ ህዝበ-ሙስሊም ውስጥ ሰርጋችሁ በመግባት እንድታስተጓጉሉ የቤት ስራ
ተሰጥቷችኋል፡፡ …
በዚህ ዙርያ አንዳንድ መሠረታዊ ሐቆችን ብንነግራችሁ መልካም መስሎ ታይቶናል፡፡ … በመጀመርያ እንደከዚህ ቀደሞቹ
ሁሉ ይህኛውም የቤት ስራችሁ እጅግ አስነዋሪና በታሪክ ፊት አንገትን በሚያስደፋ መልኩ እንድትታወሱ የሚያደርጋችሁ
ነው፡፡ ሁለተኛ፣ በከፍተኛ ቁጥር ወደ መስጂዶቻችን እንድትመጡ ኃላፊነት ከማይሰማቸው የመንግስት ባለሥልጣናት
የተሰጣችሁ ተልዕኮ ለአገራችን  ሰላምም ሆነ ለተለያዩ ሃይማኖት ተከታዮች ተከባብሮ መኖር ምን ያህል አደጋ እንደሆነ ልብ

እንድትሉት እንፈልጋለን፡፡ ከእነዚህም በላይ ግን በዋነኝነት ይህን ትዕዛዝ ለመፈፀም የምትሰማሩ ወገኖቻችን በሙሉ
ከእምነታችን ጋር በጥብቅ የተቆራኘና በሀቅ ላይ የተመሠረተ ህጋዊ የነፃነት፣ የመብትና የፍትኅ ጥያቄ ያነሳነው
ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለእንዲህ ዓይነት ዕኩይ ሤራዎች ፈጽሞ የማንንበረከክ መሆኑን እንድታውቁ እንፈልጋለን፡፡
...  እኛ ሁከትና ብጥብጥ ፈፅሞ አንፈልግም፡፡ ይህንን ባለፈው አንድ ዓመት በተግባር አሳይተናችኋል፡፡ በትንኮሳ
ወጥመዶች ውስጥ ላለመውደቅም እጅግ እንጠነቀቃለን፡፡ ነገር ግን ሁከት ይቀሰቀሳል በሚል ፍራቻ ስለመብታችን ከመጮህ
መቼም ቢሆን ወደኋላ ላንል ተማምለናል፡፡ ይህ ለእኛ የሃይማኖት፣ የእምነት ብሎም የሰብአዊ ክብራችን ጉዳይ ነው፡፡
ባለፈው
የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በድርጅታችሁ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ትዕዛዝ በሃይማኖታችንና በመስጂዶቻችን፣
በወንድሞቻችንና በእህቶቻችን ላይ በርካታ ነውሮችና ድፍረቶች ሲፈፀሙ እያየንና እየሰማን ለአገራችን ሰላም ስንል
ነገሮችን በከፍተኛ ትዕግስት አሳልፈናል፡፡ ይህንን ያደረግነው ግዴለም እኛ እየታሠርንም፣ እየተገደልንም፣ እኛ ግለሰቦቹ
እየተዋረድንም፣ እንደ ባዕድ እየተደበደብንም፣ እኛው በኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችን አስፀያፊ ስድቦች እየተሰደብንም፣
የአገራችን ሰላም ሳይናጋ ለጋራ  ሃይማኖታዊ ጥያቄያችን በሰላማዊ መንገድ እንታገል ብለን ስለወሰንን ነው፡፡ ይህ የሰላም
ፈላጊነት አቋማችን በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ያለፈ ሲኾን፣ እነሆ ዛሬም አጥብቀን እንደያዝነው አለን፡፡
…  እያንዳንዳችን የምንጮኸው ከራሳችን በላይ ለሆነ ታላቅ ዓላማ ነው፡፡ በእርግጥም የሃይማኖታችን ክብር ከእኛ
ከግለሰቦቹ በላይ ነው፡፡ አባቶቻችንና አያቶቻችን ይህንን ሃይማኖት  በከፍተኛ መስዋዕትነት በክብር አቆይተውልናል፡፡
…  ታዲያ እኛ የሃይማኖት፣ የእምነትና የአስተሳሰብ ነፃነት በህገ መንግስት ተረጋግጧል በሚባልበት በዚህ ዘመን
የሃይማኖታችን፣  የእምነታችንና የመስጂዶቻችን ክብር ሲደፈር ዝም እንድንል ትጠብቃላችሁን?! … በፍፁም ይህንን ከእኛ
አትጠብቁ!
… የተከበራችህ የክርስትና እምነት ተከታይ የኢህአዴግ አባላት ወገኖቻችን ሆይ፣ ኃላፊነት በጎደለውና ከእብሪት በመነጨ
ስሜት ለነገ የተሰጣችሁን “መስጊዳቸው ውስጥ ዘልቃችሁ በመግባትና በመካከላቸው በመሰግሰግ የተቃውሞ
ትዕይንታቸውን አስተጓጉሉ”  የሚል ትዕዛዝም ሆነ፣ በሌላ ጊዜ የሚሰጧችሁን መሰል ትዕዛዛት ለመፈፀም ስትሰማሩ
ስለድርጅታዊ
ታማኝነት ብቻ ሳይሆን፣ ስለአገራችን ሰላምም፣ በየዘመናቱ አያሌ ፈተናዎችን አልፎ ዛሬ ላይ ስለደረሰው አብሮነታችንም፣
እንደኢህአዴግ ሳይሆን፣ እንደዜጋ አስቡ፡፡ እውነቱን ማወቅ ከፈለጋችሁ አንድ በግልጽ የሚታወቅ ሐቅ እንንገራችሁ፤ ከእኛ
መካከል ብዙዎች ትናንት የኢህአዴግ ደጋፊ ነበሩ፡፡ ብዙዎቻችን “ፍፁም ባይሆንም፣ ኢህአዴግ ጥሩ ድርጅት ነው” ብለን
እናምን ነበር፡፡ … የአህባሽ አጀንዳን ይፋ ባደረገበት በሐምሌ 2003  ግን “ኢህአዴግ ምን ነካው?!”  ብለን መጠየቅ
ጀመርን፡፡ የአህባሽ አጀንዳውን በመቃወማችን “ጥቂት አክራሪዎች” ሲለን ግን፣ … በሃይማኖታችን ጣልቃ ገብቶ እያቦካ
በፕሮፖጋንዳ ህዝባችንን ለማሳሳት መወሰኑን ስናውቅ ግን፣ … “ጥቂት አክራሪዎች በኢትዮጵያ እስላማዊ መንግሥት
ለመመስረት ያልማሉ” በሚል ቅጥፈት ክርስቲያኑ ወገናችን እኛን በጥርጣሬ እንዲያየን አልሞ መንቀሳቀሱን በዉል ስንረዳ
ግን … በቃ የእውነትን መንገድ ይዘን ሐሰትን በሰላማዊ መንገድ ልንታገላት ተማማልን፡፡ …
…. ውድ የክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ሆይ! እናንተስ ስለምን ከሐሰት ጎን ትሰለፋላችሁ?! መጽሐፍ ቅዱስ
“እውነትም አርነት ያወጣችኋል!”  ይል የለምን?! …  ከኢህአዴግ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ዲስኩር ይልቅ፣ ይህ ታላቅ
እውነት አይደለምን?! … ለምን ነገሮችን  ሁሉ በኢህአዴግኛ ብቻ ታያላችሁ?! እናንተ ሰብአዊ ፍጡራን አይደላችሁምን?!
…  አንዳንድ የማይካዱ እውነቶችን እንደሰው፣ እንደ ጥሩ ክርስቲያን ብታስቡ መልካም አይደለምን?! … እባካችሁ፣
ኢህአዴግ ከመሆናችሁም ጋር …  ሰው ሁኑ፡፡ ለዘመናት በጉርብትና አብረን ስንኖር በቅርበት የምታውቁንን እኛን፣
ኢህአዴግ ‹‹ጥቂት አክራሪዎች››  የሚል ስያሜ የሰጣቸው ጭራቅ አድርጎ ስለሳለባችሁ ብቻ ያልሆንነውን ሁነን

አንታያችሁ፡፡ ይህ ለእናንተም፣ ለእኛም ለአገራችንም አይበጅም፡፡ … የሰማያትና የምድር፣ በመካከላቸው ያለውም ሁሉ
ፈጣሪ የሆነው ኃያል ጌታችን አላህ (ሱ.ወ.)  ቸር ያሳስበን፡፡ …  ኢትዮጵያንና መላ ህዝቧንም ኃያሉ    ፈጣሪያችን
ከተንኮለኞች ተንኮል ይጠብቃት፡፡
አሚን፡፡
ከነስረዲን ዑማን

አዲሱ የሃይማኖት ህግና የሃገሪቱ ህገመንግስት


አዲሱ የሃይማኖት ህግና የሃገሪቱ ህገመንግስት

constitution and religionአዲሱ የሃይማኖት ህግና የሃገሪቱ ህገመንግስት (በሰለሞን)
መንግሥት ሕገ-መንግስቱን ሊያከበር ይገባል! (ከእምነት ቤቶች)
በጉዳዩ ላይ እንድንወያይ ስንጠየቅ ይህ  የሃገረቱን ህገመንግስት ይቃረናል እኛም እዚህ ተወክለን የመጣነው ለሌላ ጉዳይ እንጂ በህግ ላይ ህግ ለማውጣት አይደለም ብለን አጀንዳው እንዲመለስ አድርገናል ፡፡(ከተስብሳቢዎች አንዱ)
በስራ ላይ የዋለውን እንደ አዲስ ለማጸደቅ በተዘጋጀው ረቂቅ ላይ ውይይት እንዲደረግ የእምነት ተቌማት የጋራ ጉባኤ ላይ ቀርቦ ነበር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አይመለከተኝም ብላ ወጥታ ነበር ቀጥሎም የኢትዮጵያ እስልምና ጽህፈት ቤትም አይመለከተኝም ብሎ ነበር፡፡ በመጨረሻምወንጌላዊያን ይህ ህግ እነርሱ ላይ ተፈጻሚ ሆኖ የቆየ ቢሆንም በህግ መልክ እንደገና ሲቀርብ ግን ተገርመውበታል፡፡
“ኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መርጠው በላኳቸው ተወካዮቻቸው አማካይነት ሕዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስትን በአዋጅ ቁጥር 1/1987 ያጸደቁት” ሕገ መንግሥትን መንግሥት በተለያዩ ጊዜያት እየጣሰ መሆኑን የሀገሪቱ የተለያዩ ህብረተሰቦችና ተቋማት መናገር ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡
በቅርቡ ደግሞ “በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የተዘጋጀ የሃይማኖት ድርጅቶች እና ማኅበራትን” አስመልክቶ የወጣው “መመሪያ” የተጠቃሻቹ የሃይማኖት ድርጅቶች እና ማኅበራትን በበቂ ሁኔታ ሃሳባቸው ሳይሰማና በማያውቁት ሁኔታ ሥራ ላይ በማዋሉ ምክንያት የሃይማኖት ድርጅቶችና ተቋማትን  በተለይም ደግሞ የክርስትና እምነት ተከታዩ ኅብረተሰቡን በእጅጉ የማጉረምረሚያ ሃሳብ ከመሆን አልፎ መንግሥት መመሪያውን በድጋሚ እንዲያስብበት በመጠየቅ ላይ ይገኛሉ፡፡
ኢትዮጵያና ሃይማኖት የአምስት ሳንቲም ግልባጮችና ፈጽሞ ሊለያዩ የማይችሉ መሆኑን መንግሥት በ1997 ዓ.ም ያወጣው እስታስቲክስ 62.8 ከመቶ ክርስቲያን፣ 33.9 ከመቶ ሙስሊም ፣ 2.7 ከመቶ ባህላዊ እምነት ተከታይ ፣ 3.3 ከመቶ ሌሎች  እና ስለ እምነታቸው መልስ ያልሰጡ ደግሞ 0.6 ከመቶ መሆኑን ባሳየው እስታስቲካዊ መረጃ አረጋግጣአል፡፡ ይህ እስታስቲካዊ አሃዝ እንደሚያሳየው በሀገሪቱ ውስጥ ያለእምነት የሚኖር ከቁጥር የማይገባና መሆኑንና በአጠቃላይ በሃገሪቱ የሚኖሩ ዜጎች 100 ፐርሰንት ሃይማኖተኛ እንደሆኑ ያሳያል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያን ማለት ሃይማኖተኛ የበዛባት ሃገር ማለት ሳትሆን ራሷ ሃይማኖት ማለት ናት ብንል የምንሳሳት አንሆንም፡፡ ስለዚህ መንግሥት ሃይማኖትን አስመልክቶ የሚያወጣቸው መመሪያዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ የታከለበትና ከሕገመንግሥቱ ሃሳብ ጋር የማይቃረን ማድረግና በሕገ መንግስቱ ውስጥ የተገለጡትን ሃይማኖታዊ መብቶች የማክበርና የማስከበር ኃላፊኑን ካልተወጣ ሀገሪቱን ወዳልታሰበ ቀውስ ውስጥ ሊከታት ይችላል ብለው ያሳሰባቸው ጥቂቶች አይደሉም፡፡
ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 27 በግልጽ ለሕዝቡ ያረጋገጠለትን ተፈጥሯዊ የሃይማኖት ነጻነቱን ወንጀል እስካልፈጸሙ ድረስ ሊያከብርለትና ሊያስከብርለት ይገባል እንጂ ሊሸራርፍ የሚችል ሕግ ወይም መመሪያ ሊያወጣ በምንም መልኩ ሕገመንግስታዊ መሠረት የለውም፡፡
በአሁኑ ጊዜ ከረቂቂነት አልፎ የሃገሪቱ መመሪያ በመሆን ሥራ ላይ የዋለው የሃይማኖት ድርጅቶችንና ማኅበራትን አስመልክቶ የወጣው መመሪያ በሚኒስቴሩ መስራቤት የተዘጋጀ መሆኑንና መጠቀሻውም “የሃይማኖት ድርጅቶችን እና ማኅበራትን ለመመዝገብና ተዛማጅ አገልግሎቶችን ለመስጠት የወጣ መመሪያ ቁጥር 1/2005 ተብሎ ሊጠቀስ” እንደሚችል “ክፍል አንድ ጠቅላላ” ከሚለው አንቀጽ ሥር በንዕስ አንቀጽ ሁለት ላይ ይናገራል፡፡ ይሄው መመሪያ በዘጠኝ ክፍል ተከፋፍሎ 45 አንቀጾች ያሉት ሲሆን በእያንዳንዱ አንቀጽ ሥር ከ 2-15 ንዑስ አንቀጾችን ያቀፈ ነው፡፡
ወደዚህ መመሪያ ዝርዝር ይዘቱ ከመምጣታችን በፊት በሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 11 “የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት” በሚለው አንቀጽ ሥር ንዑስ አንቀጽ 1-3 የተቀመጠውን ብንመለከት “መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው፡፡ መንግሥታዊ ሃይማኖት አይኖርም፡፡ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፡፡ ሃይማኖትም በመንግሥት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፡፡” በሚል በግልጽ መንግስትና ሃይማኖትን የማይገናኙ በሀገሬ አባባል “አራንባና ቆቦ” እንደሆኑ ይናገራል፡፡
እንደገናም ይሄው ሕገ መንግሥት በአንቀጽ 27 “የሃይማኖት፣ የእምነትና የአመለካከት ነጻነት” በሚለው አንቀጽ ሥር ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2 የተቀመጠው ብንመለከት “ማንኛውም ሰው የማሰብ ፣ የሕሊና እና የሃይማኖት ነጻነት አለው፡፡ ይህ መብት ማንኛውም ሰው የመረጠውን ሃይማኖት ወይም እምነት የመያዝ ወይም የመቀበል ሃይማኖቱንና እምነቱን ለብቻ ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን በይፋ ወይም በግል የማምለክ የመከተል የመተግበር የማስተማር ወይም የመግለጽ መብትን ያካትታል፡፡ በአንቀጽ 90 ንዑስ አንቀጽ  2 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ(ስለአስኮላ ትምህርት ቤት የትምህርት ይዘታቸው በሚመለከት የሚናገር አንቀጽ ነው) የሃይማኖት ተከታዮች ሃይማኖታቸውን ለማስፋፋትና ለማደራጀት የሚያስችላቸው የሃይማኖት ትምህርትና የአስተዳደር ተቋማት ማቋቋም ይችላሉ” ይላል፡፡(ጽሑፉን ያወፈርንና ያሰመርንበት ልብ ይሉት ዘንድ እኛው ነን)
እንደገናም አንቀጽ ዘጠኝ በ “ሕገ መንግስት የበላይነት” በሚለው አንቀጽ ሥር ንዑስ አንቀጽ 4 ላይ “ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የሃገሪቱ ሕግ አካል ናቸው፡፡” በሚል ተቀምጧል፡፡ በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው ዓለም አቀፋዊ ሕጎችና ቃልኪዳኖች እኤአ የ 1966 የሲቪልና የፓለቲካ መብቶች ዓለም አቀፋዊ ቃልኪዳን ስምምነቶች ውስጥ ሃይማኖታዊ መብትን እውቅና ይሰጣል፡፡
ስለዚህ በሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ 5 በግልጽ እንደተቀመጠው “መንግሥት ሃማኖትና እምነትን የመግለጽ መብትን ሊገድብ የሚችለው የሕዝብን ደህንነት፣ ሰላም፣ ጤናና ትምህርት፣ የሕዝብን የሞራል ሁኔታ የሌሎችን ዜጎች መሠረታዊ መብቶች፣ ነጻነቶች እና መንግሥት ከሃይማኖት ነጻ መሆኑን ለማረጋገጥ” ካልሆነ በቀር በምንም መልኩ የሃይማኖትን የትምህርትና የአስተዳደር ተቋማዊ ቅርጾቻቸውን ሊወስንላቸው፣ ደንብ ሊቀርጽናቸውና እኔ በምፈልገው መልኩ ተደራጁ ሊላቸውና ሊወስንላቸው በመካከላቸውም ጣልቃ እየገባ እንደ ዳኛ ሊሆን አይችልም፡፡
ይሁን እንጂ መመሪያው እነዚህን ተፈጥሯዊና ሕገ መንግስታዊ የሃይማኖት መብት ክፉኛ የሚጥስ ብቻ ሳይሆን ዕውቀት ጎደል መሆኑ ጭምር ጥቂት ክፍሎችን ብቻ ለዋቢነት እየጠቀስን እንመልከት፡፡
በአንቀጽ 5 የሚንስቴሩ ስልጣንና ተግባር በሚለው ርእስ ሥር በንዑስ አንቀጽ 2 ላይ “በድርጅቶቹ ወይም በማኅበራቱ በሚቀርብ ደንብ ላይ የማሻሻል አስተያየት መስጠት፣ ማጽደቅና መመዝገብ” የሚንስቴሩ ሥልጣንና ተግባር እንደሆነ ይናገራል፡፡ ይህ ማለት ሃይማኖታዊ ድርጅቶችም ሆኑ ማኅበራት በሚኒስቴሩ ለመመዝገብ በሚቀርቡበት ወቅት እነርሱ ከሚከተሉት ሃይማኖታዊ  አስተምህሮ አንጻር የቀረጹትን ደንባቸውን ከመቀበልና ከመመዝገብ ይልቅ ሚኒስቴሩ ደንባቸውን እርሱ በሚፈልገው መሰረት እንዲያሻሽሉ ሃሳብ ያቀርብባቸዋል ማለት ነው፡፡ ይህ “የማሻሻያ አስተያየት መስጠት” የሚለው ቃል ሚኒስቴሩ ለሃይማኖት ተቋማቱ የሚያቀርበው “የማሻሻያ አስተያየት” ምን አይነት አስተያየት እንደሆነ ግልጽ ያልሆነ፣ ገደብ የሌለው በራሱ ህሊናና በራሱ ፈቃድ ላይ ብቻ የተመሠረተ በመሆኑ ለራሱ የሚመች ሃሳብ አቅርቦ ደንባቸውን ቀርጸው እንዲያመጡ ሊያስገድዳቸው የማይችልበትና ሃይማኖታዊ ድርጅቶችንና ማኅበራትን ወደፈለገው መስመር ለማስገባት የሚገድበው አይደለም፡፡
ይህም አንድ ሃይማኖት የሚከተል ተቋም ወይም “ሃይማኖታዊ ድርጅትና ማኅበራት” ባቀረቡት ደንብ ላይ ካስተካከለና ከጠመዘዘ አለዚያ ያቀረበላቸውን “አስተያየት” አንቀበልም ካሉ መመዝገብ እንደማይችል ከገለጸ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 11 እና 27 ንዑስ አንቀጽ 2 የተቀመጠውን በተለይም ደግሞ መንግሥት በሃይማኖት ትምህርትና በአስተዳደር ተቋማት ላይ አይገባም የሚለውን ይጥሳል ማለት ነው፡፡
ሃይማኖታዊ ድርጅትም ሆነ ማኅበር የሚወለደው የሃይማኖቱ ተከታዮች ከሚያምኑበት ሃይማኖታዊ እሳቤና ምንጭ አንጻር በመሆኑ እምነትና ማኅበር ወይም ሃይማኖትና ድርጅታዊ አወቃቀር የአንድ አካል  ክፍሎች በመሆኑ በመነጣጠል በተለይም ደግሞ እነርሱ የሚተዳደሩበት ደንብ ቀርጾ ማውጣትም ይሆን ባወጡት ላይ “የማሻሻያ አስተያት” እንዲቀበሉ ማድረግ መንግሥት ሃይማኖት ውስጥ አልገባሁም የሚልበት ምክንያት አይኖረውም፡፡ ስለዚህም “የማሻሻያ አስተያየት” ከሰጠበት ደቂቃ ጀምሮ ሕገ መንግስቱን ይጥሳል ማለት ነው፡፡
ሌላው በዚሁ በአንቀጽ 5 የሚንስቴሩ ስልጣንና ተግባር በሚለው ርእስ ሥር በንዑስ አንቀጽ 9 ላይ “ሞዴል መተዳደሪያ ደንቦች የማዘጋጀት” ስልጣንና ተግባር የሚኒስቴሩ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ይህ ደግሞ የሃይማኖት ድርጅቶችም ይሁኑ ማኅበራቱ ደንብ ይዘው ሲመጡ “የማሻሻያ አስተያየት” ከመስጠት አልፎ ደንብ የሚያዘጋጅላቸውም እራሱ እንደሆነ ይናገራል፡፡ “ሞዴል መተዳደሪያ ደንብ” ማለት እርሱ በሚፈልገው መልኩ የተቀረጸ ይዘት ያለው ሆኖ የተዘጋጀ ማለት ነው፡፡
በመሆኑም ደንብ የየሃይማኖቱ ከሚከተሉት እምነት አንጻር ለራሳቸው የሚመች የሚያወጡትና የሚከተሉት እንጂ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሃይማኖት ተቃማትና መተዳደሪያ ደንብ ማውጣትና መቅረጽ አይችልም፡፡ የመንግሥት ሚና የፖለቲካ ወይም ሃይማኖቶች ራሳቸው በራሳቸው እንዲዋቀሩና እንዲመሩ መንገድ መክፈት እንጂ ደንብ የመቅረጽና በሚፈልገው መልኩ እንዲያምኑና እንዲዋቀሩ ማድረግ አይደለም፡፡
ሌላው በዚሁ በአንቀጽ 5 በንዑስ አንቀጽ 10 ላይ ሚኒስቴሩ ባወጣው በዚሁ መመሪያ መሰረት “ለሚሰጣቸው ለምዝገባና ተዛማጅ አገልግሎቶች ክፍያ እንደሚያስከፍል” ያናገራል፡፡ እንዲሁም በአንቀጽ 6 በንዑስ አንቀጽ 5 ላይ ደግሞ “ህጋዊ የምዝገባ ፈቃድ ሳያገኝ በምስረታ ላይ እያለ ከመስራች አባላት በስተቀር ህዝብን በመጥራት ሃይማኖታዊ ስብሰባ ማካሄድ ማስተማር ወይም መስበክ እና ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊቶችን መፈጸም አግባብነት ባለው ሕግ የሚያስጠይቅ ይሆናል” ይላል፡፡ በመሆኑም መክፈል ሳይችሉ ቀርተው መመዝገብ ያልቻሉ ሃይማኖቶች በግልም ይሁን በቡዱን ሃይማኖታቸውን ማራመድ፣ መስበክ፣ መሰብሰብ፣ ማስተማር ወይም ሌላ ተመሳሳይ ሃይማኖታዊ ድርጊት መፈጸም እንደማይችሉ የሚናገር ብቻ ሳይሆን ይህን ያደረጉ ድሆች ሃይማነተኞች በሕግ የሚጠየቁ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡ ይህም ተፈጥራዊና ሕገ መንግስት የሰጣቸውን አንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ 1 በግልም ይሁን በቡድን በመሆን በይፋ የማምለክ፣ የመከተል፣ የመተግበር፣ የማስተማር ወይም የመግለጽ መብታቸውን በመንጠቅ ሕገ መንግሥቱን ይጥሳል ማለት ነው፡፡
በሌላ መልኩም ይህ አንቀጽ 6 በንዑስ አንቀጽ 5 የተቀመጠው  “ህጋዊ የምዝገባ ፈቃድ ሳያገኝ በምስረታ ላይ እያለ ከመስራች አባላት በስተቀር ሕዝብን በመጥራት ሃይማኖታዊ ስብሰባ ማካሄድ ማስተማር ወይም መስበክ እና ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊቶችን መፈጸም አግባብነት ባለው ሕግ የሚያስጠይቅ ይሆናል” የሚለውን ስንመለከት አንድ የግል እምነት ያለው ዜጋ የሚያምነውን እምነት ለሌሎች በመስበክ በማስተማርና ተከታይ በማፍራት ወደ ሃይማኖታዊ ማኅበርነት ስለማይቀየር ሃይማኖቱን በነጻ የመግለጽ ብሎም የማስፋፋት ተፈጥሯዊና ሕገ መንግስታዊ መብቱን ያፍናል ይገድባል፡፡ እርሱን ብቻ አይደለም በንዑስ አንቀጽ 6  ደግሞ ይሄ እንደማኅበር መመዝገብ ደረጃ ላይ ያልደረሰ ዜጋ እርሱ ለሚያደርገው የመስበክ የማስተማር ወይም ሌሎች ሃይማኖታዊ ድርጊት “የደገፈና መሰል ትብብሮችን ያደረገ ማንኛውም ሰው በተመሳሳይ አግባብነት ባለው ሕግ የሚጠየቅ” እንደሚሆንም መመሪያው ይገልጻል፡፡ ይህም ሕገ መንግሥቱን ሳይጥሱ ጤናማ ሃይማኖታዊ ሥራ ሲያካሂዱና ሲደግፉ የነበሩትን በወንጀል መጠየቅ ከሕገ መንግስታዊ ድንጋጌዎች መንፈስ የሚጻረርና ወንጀል ባልተፈጸመበት ወንጀል እንደመፍጠር ነው፡፡
እንዲያውም ሃይማኖታዊ ድርጅቶችና ማህበራት ዓለማቀፋዊ ግንኙነት ለማድረግና ምቹ መንገድ እንዲኖራቸው ራሳቸው ከማሳብ አንጻር ሊመዘገቡ ወደ ሚኒስቴሩ ይሄዳሉ እንጂ ካልተመዘገባች ሃይማኖት አይደላችሁም ማለት ተገቢ አይደለም፡፡ እነዚህ ሃይማኖታዊ አገልግሎቶች የሕገ መንግሥቱን ድንጋጌ እስካልጣሱ ድረስ ሊከለከሉ አይገባም፡፡
ሌላው ይሄው መመሪያ በአንቀጽ ሰባት “አደረጃጀት” በሚለው ሥር በንዑስ አንቀጽ 1 ላይ “ማንኛውም የሃይማኖት ድርጅት ወይም ማኅበር በመተዳደሪያ ደንብ መሠረት ጠቅላላ ጉባኤ፤ የስራ አስፈጻሚ / አመራር ቦርድ ፣ ስራ አስኪያጅ / ፕሬዝዳንት ፣ ዳይሬክተር ፣ ኦዲተር ፣ ሂሳብ ሹምና ሌሎች እንደድርጅቱ ወይም ማኅበሩ አደረጃጀት አስፈላጊ የሆኑ የሥራ ክፍሎች ሊኖሩት ይገባል ይላል፡፡” ይህም የሃይማኖት ድርጅቶችና ማኅበራት ከሚከተሉት እምነትና ከመንፈሳዊ መርህ አንጻር አደረጃጀታቸውን ያወጣሉ እንጂ መንግሥት አደረጃጀታቸውንና የስልጣን ተዋረዳቸውን እንዲሁም የማዕረግ ስሞቻቸውን ሊያወጣላቸው አይችልም፡፡ ለምሳሌ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ብንወስድ ሃይማኖቷዊ ቀኖናዋና የራሷ ሕገ ቤተክርስቲያን እንደሚያዘው ቀድሞ በፓትሪያሪኩ የበላይ ጠባቂነትና አመራር ሰጪነት በኋላም ተሻሽሎ  በብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት ምልአተ ጉባዔ እንድትመራ ከወሰነችበት እለት ጀምሮ አሁን በዚሁ እየሄደች ያለችን ቤተክርስቲያን ፣ ወደ ፊትም ቤተክርስቲያኗ እንደ ቀኖናዋ መሰረት እንዳመቻትና ለራሳ በምታምነው አደረጃጀትና አስተዳደራዊ መዋቅር ዘርግታ ብትሄድ መንግሥት ጣልቃ ገብቶ እንደ ሃይማኖት ድርጅት ወይም ማኅበር ተዋቅረሽ ጠቅላላ ጉባኤ፤ የስራ አስፈጻሚ / አመራር ቦርድ ፣ ስራ አስኪያጅ / ፕሬዝዳንት ፣ ዳይሬክተር በሚል መዋቅር ውስጥሽን ካላደራጀሽ ሃይማኖት አይደለሽም ሊላት እንደሆነ ይሄው መመሪያ ያስረዳል ማለት ነው፡፡
ይህ መመሪያ የያዘው እነዚህ ስያሜዎች ማለትም ጠቅላላ ጉባኤ፤ የስራ አስፈጻሚ / አመራር ቦርድ ፣ ስራ አስኪያጅ / ፕሬዝዳንት ፣ ዳይሬክተር ፣ ኦዲተር ፣ ሂሳብ ሹምና ሌሎች ተብለው የተቀመጡት መዋቅራዊ ስያሜዎች  በራሳቸው “ዓለማውያን” ቋንቋዎችና ትርጓሜዎች ያሏቸው እንጂ ሐይማኖታዊ ቋንቋዎች ለመሆናቸው በራሱ አነጋጋሪ ጉዳዮች ናቸው፡፡
ሌላም እንደምሳሌ የወንጌላውያን አብያተክርስቲያናትን ይዘትና አወቃቀር ብንመለከት አንዱ ቤተክርስቲያን ከሌላው በመሰረታዊ ክርስትና አስተምህሮ አንድ ቢሆንም በአስተዳደራዊ አወቃቀሩ ግን የተለያየ ሲሆን አንዳንዱ በ “ሐዋርያዊ አመራር” የሚያምንና የተዋቀረ ሌላው  በ “ሽማግሌያዊ አስተዳደር” የሚያምንና የተዋቀረ ሌላው ደግሞ በ “ፓስተራል አስተዳደር” የሚያምንና የተዋቀረ ወዘተርፈ በመሆኑ እነዚህን በአንድ አስተምሯቸውን ተከትሎ ካዋቀሩት አስተዳደራዊ አደረጃቸት አውጥቶ እንደልማት ማኅበር ጠቅላላ ጉባኤ፤ የስራ አስፈጻሚ / አመራር ቦርድ ፣ ስራ አስኪያጅ / ፕሬዝዳንት ፣ ዳይሬክተር ብላችሁ ተደራጁ ብሎ በ “ማሻሻያ ሃሳቡ” ጠምዝዞ ካላዋቀራቸው አትመዘገቡም እንደሃይማኖትም መንቀሳቀስና ማስተማር መስበክ አትችሉም ሊል እንደሚችል በግልጽ ያሳያል፡፡  ይህም  “መንግስት በሃይማኖት አይገባም” የሚለውንና “የሃይማኖት ተከታዮች ሃይማኖታቸውን ለማስፋፋትና ለማደራጀት የሚያስችላቸው የሃይማኖት ትምህርትና የአስተዳደር ተቋማት ማቋቋምይችላሉ” የሚለውን በአንቀጽ 11 ንዑስ አንቀጽ 3 እና አንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ 2 የተቀመጠውን የራሳቸውን መብት በመንጠቅ ሕገ መንግሥቱን የሚጻረር መሠረታዊ ስህተት መሆኑን ያሳያል፡፡
ለነገሩ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ይህ አዲሱ መመሪያ ከመውጣቱም በፊት በነበረው መመሪያ መሠረት እንደልማት ተቋማትና ድርጅት ይመዘገቡና ስራቸው ሃይማኖታዊ ይሁን ልማታዊ ሳይታወቅ የስራና የሂሳብ ሪፖርታቸውን እንዲሁም የቀጣይ የበጀት ዓመት የሥራ እቅዳቸውን ጭምር ካላቀረቡ በቀር የሥራ ፈቃድ ስለማያገኙ ይህን ለማቅረብ ይገገደዱ ነበር፡፡ መንግስትም የሃይማኖት የስራ ሪፖርትና እቅድ የበጀት አስተዳደራቸውንም ጭምር የማየትና የመቀበል በውጭ ኦዲትርም እንዲመረመሩ የማድግ ምንም ሕገ መንግስታዊ ሥልጣን የሌለው ቢሆንም ለረጅም ዘመናት ሲያካሂድባቸው ኖሯል፡፡ ይህም መንግስት በሃይማኖቶች ውስጥ በትምህርታቸውም ሆነ በአስተዳደር ስልጣናቸውና አወቃቀራቸው ውስጥ ገብቶ እንደነበረ በሚንስትሩ የሃይማኖትና የእምነት ዳሬክቶሪት የተጨናነቁ መዝገብ ቤትን ማየት በቂ ምስክር ነው፡፡ በዚህም በመንግስት ጣልቃ ገብነትና የአወቃቀር ውሳኔ ምክንያትና የወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት እርስ በርሳቸው በመዋቅሩ እንዳይስማሙ የመካሰስ የመለያየት እንዲሁም አላግባብ የቤተዘመድ አመራር እንዲፈጥሩ ወዘተ ጭምር ተገደው እንዲገቡ ተደርገዋል፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሌላው መነሳት ያለበት ነጥብ በዚሁ መመሪያ በአንቀጽ 3 “ትርጓሜ” በሚለው ሥር በንዑስ አንቀጽ 6 ላይ “መንፈሳዊ አገልጋይ ወይም ሰባኪ ወይማ ዳኢ ማለት በሃይማኖት ድርጅቶቹ ወይም ማኅበራት ውስጥ እውቅና ኖሯቸው በክፍያ ወይም ያለክፍያ የሃይማኖት ትምህርት የሚያስተምሩ ወይም የሚሰብኩ አገልጋዮችን ያጠቃልላል፤” ይላል፡፡ እዚህ ላይ መመሪያው በየሃይማኖታዊ ድርጅቶችና ማህበራት ውስጥ ያሉትን ልዩ ልዩ ስያሜዎችና የአገልግሎት ማዕረጋትን በአንድ መጠቅለሉና መጥራቱ መሠረታዊ ስህተት ነው፡፡ ይህ ጠቅልሎ የመጥራት ሥራና ኃላፊነት የየሃይማኖቱ ድርጅቶችና ማኅበራት ተግባርና ሥልጣን እንጂ እንዴትስ እንዲህ ብሎ መጠቅለልና መጥራት ይችላል? የሚሉ ብዙዎች ናቸው፡፡
ሌላው አነጋጋሪ ጉዳይ በዚሁ መመሪያ አንቀጽ 13 “የውጭ ዜጎችን ማሰማራት”  በሚለው አርእስት ሥር ንዑስ አንቀጽ 5 ላይ  ሃይማኖታዊ ድርጅቱ ወይም ማኅበሩ “ ያሰማራው የውጭ ዜጋ ከመጣበት ዓላማ ውጪ በመንቀሳቀስ ለሚፈጽመው ጥፋት በተናጠልና በጋራ በሀገሪቱ ህግ ተጠያቂ ይሆናል” የሚለው ነው፡፡ ይህም ማለት አንድ ፈረንጅ ከሃይማኖታዊ ተቃሙ ወይም ማህበሩ ጋር በመሆን መንፈሳዊ ሥራ ለመስራት ተስማምቶ በመግባት መንፈሳዊ ሥራው ጋር ባልተገናኘ ሁኔታ ባለው ትርፍ ጊዜም ሆነ በግሉ ሌላ ወንጀል ቢሠራ ለፈጸመው ወንጀል ተቋሙ ወይም ማኅበሩ በወንጀል መጠየቁ አግባብ አይደለም፡፡ ሃይማኖታዊ ድርጅቱ ወይም ማኅበሩ ላለው ሃይማኖታዊ ተግባር ተስማምቶ አሰማራው እንጂ ሌላ የግል ስህተቱን ሁሉ ተቋሙን ወይም ማኅበሩን አይመለከትም፡፡
በአንቀጽ 18 “የተከለከሉ ተግባራት” በሚለው ርእስ ሥር ንዑስ አንቀጽ 8 ደግሞ ብንመለከተው መመሪያው ሌላ አስገራሚ ነገርንም ይዟል፡፡ “ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኙ ከአምልኮ ቦታ ውጪ ሰዎችን በማሰባሰብ ባልተፈቀደ ቦታ የሃይማኖት ትምህርት ማስተማር ወይም መስበክ” በንዑስ ቁጥር 12 ደግሞ ከሌሎች ጋር “አብሮ መስራት” ፣  በንዑስ አንቀጽ 13 ደግሞ “የሃይማኖት ተግባርን ከበጎአድራጎት ዓላማና ተግባር ጋር ቀላቅሎ መሥራት” ይከለክላል፡፡
ይህም ማለት እንደምሳሌ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነትና አስተምህሮን  ብናይ ለረዥም ዘመናት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን የህዝቡን የቤት ለቤት ጽዋ ማህበራት ያለፈቃድ ሰብስቦ እንደወትሮው ማስተማር መስበክና ሃይማኖታዊ ተግባራት መፈጸም ይከለክላል ማለት ነው፡፡ ቄሱም የነፍስ ልጆቻቸው ከአምልኮ ቦታ (ከቤተክርስቲያን ቅጥር ጊቢ) ውጭ ሰብስቦ ቢሰብክ ቢያስተምር በሕግ ያስጠይቀዋል ማለት ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም የአደባባይ ክብረ በዓላትንም ጭምር ያለ መንግስት ፈቃድ እንደወትሮ ቢያካሂዱ መሰብሰብ በዓላቱንም ማካሄድ አይችሉም ማለት ነው፡፡ ይህን ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውን ከሚመለከተው የመንግስት ቢሮ ሄደው “ይሁንታ” ማግኘት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ካላገኙም ቀረ ማለት ነው፡፡
ወደ ካቶሊኩም ወደ ወንጌላውያኑም ተመሳሳይ እጣ ፈንታ ይገጥመዋል፡፡ ከተፈቀደላቸው የአምልኮ ቤቶች  (ይህም ተከራይተው የሚያመልኩበትን ቤት ያካትት አያካት መመሪያው ግልጽ አያደርግም ) ውጭ የቤት ለቤት ጸሎት ፕሮግራሞች፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የጥናት ፕሮግራሞች በሀዘንና በደስታ ወቅትም በሚያደርጉት የቤትና የድንኳን አገልግሎቶች ሁሉ የተከለከሉ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡
ሌላው ሃይማኖት የሚወልደው ለሌሎች በጎ የማድረግ የመደገፍ ተግባር ነጥሎ እናንተ እንደ ሐይማኖት መጸለይ ብቻ ይገባችኋል እንጂ ሃይማኖትን ከምግባር አታቀላቅሉ ብሎ የሚገልጸው መመሪያ ለክርስቲያኑ ህብረተሰብ “ተርቤ አብልታችሁኛል ፣ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛል፣ ታምሜ ጠይቃችሁኛል፣ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋል ብሎ ጌታ በመጨረሻ  በማቴወስ ወንጌል 25፡34-46 እንደተገለጸው የሚጠይቀውን ቃልና “ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው” የሚለውን የያዕቆብ መልእክት ምዕራፍ 2፡18-26ን የእምነት መሠረት የሚጥስ አሊያም ነጣጥሎ በዚህ መልኩ ሥጡ ብሎ ያለ እምነት መሰረታቸው አካሄድ መግለጹ ሲሆን ለእስልምና እምነት ተከታይም ከአምስቱ የእስልምና ማእዘናት ውስጥ በሦስተኛ ደረጃነት “ዘካት” መስጠትን የሚከለክል ወይም ይህንን እንዴት መፈጸም እንደሚገባቸው ከሐይማኖታዊ አስተምህሯቸው ውጪ መንግስት መመሪያ እየሰጠ በመሆኑ መንግሥት ሕገ መንግስቱን ጥሶ በሐይማኖት ጣልቃ መግባቱን ያሳያል ፡፡
እንግዲህ ሕዝቡ ይህ ሃይማኖትን በነጻነት የመቀበል፣ በግልና በጋራ የማራመድ የማስፋፋትና የማደራጀት ሕገ መንግስታዊ መብቱን የገፈፈው መመሪያ ለውይይት ለመጀመሪያ ጊዜ መንግስት የሃይማኖት ተቋማትን በጠራና ሃሳቡን በገለጸ ጊዜ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን “አይመለከተኝም” ብላ ስብሰባውን ረግጣና ጥላ እንደወጣች ካቶሊክም “እኔ አለም አቀፋዊ አወቃቀር እንጂ ብሔራዊ ብቻ ስላልሆንኩ አለም አቀፋን ቤተክርስቲያኗን ጠይቁ” ብላ ጥላ እንደወጣች፣ እስልምናም በተመሳሳይ “አይመለከተኝም” ብለው ሲወጡ ጥቂት ፕሮቴስታንት አካላት ብቻ ቆይተው የመንግሥትን ይህን ሃሳብ እንዳዳመጡ የውስጥ ምንጮች ይገልጻሉ፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ የእምነት  ተቋማት ባይቀበሉትም ቅሉ መመሪያው ጸድቆ እንደመመሪያ እየተተገበረ ሲሆን ብዙዎችን ግራ እያጋባ ይገኛል፡፡
በመሆኑም ሕገመንግስቱ ሐይማኖቶችን “ሃይማኖት” ይላቸዋል እንጂ እንደዚህ መመሪያ ድርጅቶችና ማኅበራት ብሎ የማይጠራቸው ከመሆኑ ጀምሮ ማንኛውም ሃይማኖት እምነቱን ለመግለጽና ዓለማቀፋዊ ግንኙነት ለመፍጠር እንጂ የእምነት ነጻነቱን ለማስፈቀድ ወደየትም መሄድ አያስፈልገውም፡፡ እምነት ዲሞክራሲ ያጎናጸፈው ስጦታ ሳይሆን የዲሞክራሲ ጽንሰ ሃሳብ ሳይፈጠር ከሰው ማንነት ጋር የተገጠመ ተፈጥሯዊ በመሆኑ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ መግባቱን አቁሞ ሕገ መንግስቱን ሊያከብር ይገባዋል፡፡ በሃይማኖት ሽፋን ለሚደረጉ ወንጀሎች ካሉ ራሳቸው የሃይማኖት ተቋማቱ እንደዜጋ እንዲከላከሉ ሕገ መንግስቱን ማሳወቅና እንጂ በውስጣቸው ገብቶ አስተዳደራቸውን የመቆጣጠር የመምራት ወዘተ ተግባር አቁሞ ሕገ መንግስቱን ሊያከብር ይገባል፡፡

በኬንያ ስደተኞች ከተማ ልቀቁ ተባሉ ኢትዮጵያውያኑ እንታፈናለን ብለው ሰግተዋል


ወቅቱ 2003 አጋማሽ ላይ ነው። ሁለት የኢህአዴግ ሰዎች ድንበር አቋርጠው ናይሮቢ ይገባሉ። በናይሮቢ አድርገው ወደ ሌላ አገር ለመኮብለል ጊዜያዊ ማረፊያ መጠነኛ ሆቴል ይከራዩና ለሁለት አንድ ላይ ያርፋሉ። አንደኛው ከሰዎች ጋር ቀጠሮ እንዳለው አስታውቆ ወደ ጉዳዩ ይሄዳል። ቀጠሮው ቦታ ቆይቶ ለጓደኛው ስልክ ሲደውል “እንዳትመጣ፣ ጓደኛህን ከተኛበት ገብተው የማይታወቁ ሰዎች ወስደውታል” የሚል መልዕክት ይደርሰዋል። ከዚያን ቀን ጀምሮ ስለጓደኛው ሰምቶ አያውቅም። እሱም አገር ቀይሮ በስደት በመንከራተት ላይ ይገኛል።
ኬንያ ሶስት ዓይነት ስደተኞች አሉ። በኢኮኖሚ ድቀት የዕለት ጉርስ ፍለጋ የሚሰደዱ፣ በፖለቲካ ሳቢያ ኢህአዴግን ሽሽት አገር ለቀው የወጡ፣ በኢህአዴግ ልዩ ተልኮ ስደተኛ መስለው ኬንያ የሚኖሩ፤ ከናይሮቢ በስልክ ለጎልጉል መረጃ የሰጡት ወገኖች እንደደሚሉት በየጊዜው እየታፈኑ ወደ አገርቤት የሚላኩ ጥቂት አይደሉም። ይህ የሚሆነው ደግሞ በኬንያ ውስጥ ኢህአዴግ እጀ ረጅም በመሆኑ ነው። በዚህም ሳቢያ ለፖለቲካ ስደተኞች እያንዳንዷ ቀን የሰቀቀን ነች። ራስን የመጠበቅ!!
የኬንያ መንግስት “ለደህንነቴ ቅድሚያ” በሚል ሰሞኑንን ያስተላለፈው መመሪያ በስደት ናይሮቢ የሚኖሩትን ወገኖች ያስደነገጣቸውም ለዚሁ ነው። በኬንያ የሚኖሩ ስደተኞች ከተማ ለቅቀው ወደ ካምፕ እንዲገቡ በተላለፈው ትዕዛዝ መሰረት መመሪያው የሚመለከታቸው ኢትዮጵያዊያን የመፍትሄ ሃሳብ የላቸውም። ግን ጭንቀታቸውን ለማሰማት ያህል ይናገራሉ።
በናይሮቢ የዓለም የስደተኞች ኮሚሽንን ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ካሉት ስደተኞች መካከል አንዱ ብርሃኑ በየነ ይባላል። በዝዋይ ማረሚያ ቤት ታስሮ ተገርፏል። እሱ እንደሚለው የኬንያ መንግስት ሁሉንም ስደተኞች ባንድ መነጽር ሊመለከት አይገባም። በጅምላ ከዘጠኝ አገሮች ተሰድደው ኬንያ ለገቡት ጥገኝነት ጠያቂዎች በግል የፋይል ቁጥራቸው ወደ ካምፕ እንዲገቡ መመሪያ ተላልፏል።
በአዲሱ ዓመት ግርግር ጉዳዩ ተጓተተ እንጂ መመሪያው ተግባራዊ መሆኑ አይቀሬ ነው። የስደት ማመልከቻቸውን አስገብተው በተባበሩት የስደተኞች ኮሚሽን እውቅና ናይሮቢ እንደፍጥርጥራቸው ተቀምጠው ጉዳያቸውን የሚከታተሉም ሆኑ፣ በስደት ካምፕ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ከቀላል የርስ በርስ ጸብ በስተቀር በወንጀል፣ በግድያና በጸያፍ ተግባር አይታወቁም። ከዚህም በላይ ለናይሮቢ ነዋሪዎች ስጋት የሚሆኑበት አንድም አግባብ እንደሌለ ብርሃኑ ያስረዳል።
በኬንያ ስደት ካምፖች ሙቀታቸው ከፍተኛ፣ ለመኖሪያ የማያመቹ፣ ለአካባቢ ወለድ በሽታዎች የተጋለጡ፣ በቂ የመኖሪያ ግብአት ያላሟሉ ከመሆናቸው በላይ ትልቁ ችግር የደህንነት እንደሆነ ያመለከተው ብርሃኑ አብዛኞችን ስጋት ላይ ስለጣለው ጉዳይ “ተመሳስለው በስደተኛ ስም ኬንያ የገቡት የኢህአዴግ የስለላ ሰዎች በየቀኑ ሰዎችን ያድናሉ። ወደ ኢትዮጵያ ይወስዳሉ። በዚህ መልኩ የታፈኑ በርካታ ናቸው። አንድ ላይ ተሰባስበን እንዴት እንቀመጣለን? ይህ እጅግ አሳሳቢና ከፍተኛ መዘዝ የሚያስከትል የሰብአዊ መብት ጥሰት ነው” ሲል የኬንያ መንግስት ውሳኔውን ሊያጤን እንደሚገባው ያሳስባል።
ይህ ብቻ አይደለም በኬኒያ ያለው ሙስናም ሌላው ስጋት ነው። “በኬንያ ገንዘብ ካለ ሁሉንም ማድረግ ይቻላል። ኢህአደግ ገንዘብ አለው። ገንዘብ ከተከፈለ ዋስትናችንን አሳልፎ የመስጠት ውሳኔም ሊወሰን ይችላል” የሚለው ግርማ ጉተማ “ኦነግን ፍርሃቻ በየስርቻው የሚንቀሳቀሰው ኢህአዴግ ይጥቀመው እንጂ ማንኛውንም ነገር የማድረግ ሞራል ስላለው ዋስትናችን የተመናመነ ያህል ይሰማኛል” ይላል።
ሁሉም እንደሚሉት የኬንያ መንግስት ውሳኔውን ተግባራዊ ከማድረጉ በፊት ኢትዮጵያዊያን ወገኖች ድምጻቸውን በያሉበት ሆነው ሊያሰሙ ይገባል። በየአቅጣጫው ጉዳዩን በማስመልከት ለኬንያ መንግስትና ለሚመለከታቸው ክፍሎች የስጋቱን ደረጃ ማሳወቅ ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ጉዳይ እንደሆነ አበክረው ያስረዳሉ። በኬንያ ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከአማራና ከኦሮሚያ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር አብላጫውን ቁጥር ይይዛል።
Dadaab refugee camp, Kenya
ዳዳብ የስደተኞች ካምፕ ኬኒያ ሐምሌ 2003(ፎቶ:AlertNet)
በኬንያ በተደጋጋሚ በደረሰ የቦንብ ጥቃት ሳቢያ ዜጎች ከስደተኛ የሶማሌ ዜጎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውና፣ የሶማሌ ዜጎችን በመቃወም የኬንያዊያን ጥያቄ ገፍቶ በመምጣቱ መንግስት ሁሉም ስደተኞች ወደ ካምፕ እንዲገቡ የሚያስገድድ መመሪያ አውጥቷል። የኬንያ የመከላከያ ሃይል በሶማሌ የአልቃይዳንና የአልሸባብን ሃይል ከዩጋንዳ፣ ከብሩንዲና ከኢትዮጵያ ሰራዊት ጋር በመሆን ማጥቃቱ ለቦንብ አደጋው እንደ ምክንያት ቢገለጽም፣ የኬንያ መንግስት ውሳኔውን ያሳለፈው አጠቃላይ አገሪቱ ውስጥ ለገቡት ስደተኞች ሁሉ ነው።
በዓለም ትልቁ የሚባለውና አብዛኛዎቹ ከሶማሊያ የሚመጡት ስደተኞች የሚገኙበት የዳዳብ ካምፕ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን የሚገኙ በመሆናቸው ተጨማሪ ስደተኞችን ሊጨምር ባይችልም ሌሎች አዳዲስ ካምፖችን በማሰራት ስደተኞችን ወደዚያው ለማጎር እየታሰበ እንደሆነ ከኬኒያ የሚወጡ ዜናዎች ይጠቁማሉ፡፡

ተስፋ መቁረጥ የወለደው እርምጃ – መስጊድ ነጠቃ!


ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መሠረታዊ የእምነት ነፃነት መብታችን ተጥሶ ለተቃውሞ አደባባይ ከወጣን ድፍን አንድ አመት ሞላን፡፡ ይህ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን አንድ ላይ ያስተሳሰረ ተቃውሞ መነሻውም ሆነ መድረሻው የመንግስት በሐይማኖታችን ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነትና የህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች በይፋ መጣሳቸው ነው፡፡ አሕባሽ የተሰኘውን አንጃ ከሊባኖስ በማስመጣት በሙስሊም ዜጎች ላይ በኃይል ለመጫን የተደረገው ሙከራ ለዚህ የከፋ ድርጊት ዋነኛ ማሳያ ነው፡፡ተስፋ መቁረጥ የወለደው እርምጃ - መስጊድ ነጠቃ!
አሕባሽ በከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ ታጅቦ በመንግስት ጋባዥነት ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ሊፈፅማቸው ያሰባቸው በርካታ ፕሮጀክቶች ነበሩት፡፡ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ የአህባሽ የግዳጅ ጠመቃ ላይ በወጣው ባለ 15 ነጥብ የአቋም መግለጫ መሰረት ኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረግ ማንኛውም የሙስሊሞች እንቅስቃሴ በአህባሽ የመጅሊስ አስተዳደር ጥብቅ ቁጥጥር ስር እንዲውል፣ ማንኛውም የመስጂድ ኢማምም ሆነ ዳዒ ይህንን የአሕባሽን ስልጠና እንዲሳተፍ፣ የአሕባሽን ስልጠና ያልወሰደ ማንኛውም ኢማም ማሰገድ እንደማይችልና ስልጠናውን ያልወሰደ ኢማም ቦታም ስልጠናውን በወሰደ ሌላ ሰው እንደሚተካ፣ የአህባሽን ስልጠና ያልወሰደ እና ከአህባሽ የመጅሊሱ አስተዳደር ሰርተፊኬት ያልተሰጠው ማንኛውም ዳዒ በየትኛውም መድረክ የኃይማኖት ትምህርት እንዳይሰጥ፣ በሕብረተሰቡ ጉልበት፣ ሀብትና ጥረት የተገነቡ ማንኛውም ኢስላማዊ ተቋማት ለአሕባሽ እንዲሰጡ… አዋጅ መታወጁ ይታወሳል፡፡
ይህ አዋጅና በከፍተኛ የመንግስት ሁለንተናዊ እገዛ የተደረገው የአሕባሾች እንቅስቃሴ የህዝብን ቁጣ ቀስቅሶ እነሆ መብረጃ ወዳልተገኘለት ቀውስ ውሰጥ ገብቶ ይገኛል፡፡ ሕዝበ ሙስሊሙ በወሰዳቸው ቆራጥ የተቃውሞ እርምጃዎች የአሕባሽ ፕሮጀክቶች አንድ ባንድ ተንኮታከተዋል፡፡ ዛሬ ስለ አህባሽና አደገኛ ሴራው ያልተረዳ እና ራሱንም ቤተሰቡንም ከአደጋው ያልጠበቀ ሙስሊም ግልሰብ ማግኘት አዳጋች ነው፡፡ ይሁንና መንግስት በዚህ ተፀፅቶ እርምት ሊወስድ ሲገባው አላስፈላጊ እልህ ውስጥ በመግባት እነሆ የብዙ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች እጣ ፋንታ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም መሠረት የአህባሽ ፕሮጀክት የመጨረሻ ተግባራትን የፖለቲካ ኃይሉን ተገን አድርጎ ለማስፈፀም እየተጋ ይገኛል፡፡
መንግስት ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ያደራጃቸውን ቡድኖች ስትራቴጂካዊ ቅርጫ በማድረግ ነባሩን የአሕባሽ አመራር በሌላ የአሕባሽ አመራር አካላት ተክቷል፡፡ ይህም ለቀጣይ የመጨረሻ የአህባሽ ፕሮጀክት አፈፃፀም እንደሚረዳው በመተማመን እነሆ በአሁኑ ሰዓት ይህንኑ ድፍረት የተሞላበትን እርምጃ መውሰድ ጀመሯል፡፡ በሕዝብ ንፁህ ሀብት፣ ጉልበት፣ ደምና መስዋዕትነት የተገነቡ ኢስላማዊ ተቋማትም ሆኑ መስጂዶች ለሙስሊሙ ሕዝብ ትርጉማቸው ከ‹‹ግንብ›› ከ‹‹ሕን›› በላይ ነው፡፡ አይደለም ዛሬ የመጣበትን አደጋ ለመከላከል እጅ ለእጅ ተሳስሮ አንድነቱን ይፋ ባደረገበት ወሳኝ ጊዜ ላይ ይቅርና ያኔም በቀደመው ጊዜ በነኚህ ሀብቶቹ ላይ የመጣውን አካል ያለምንም ማቅማማት ሲጋፈጥ ቆይቷል – በዚህ ጉዳይ ተደራድሮም አያውቅም፡፡
ሰሞኑን በአንዳንድ አካባቢዎች በተለይም እዚህ በመዲናችን አዲስ አበባ እና ደሴ ከተማ እየተደረገ ያለው አደገኛ አካሄድ አፀፋ ከማውገዝም በላይ ሊሆን እንደሚችል ማንም ጤነኛ አእምሮ ላለው ሰው የሚጠፋው አይደለም፡፡ ህዝብ ጥሮ ግሮ ያፈራቸውና ለዘመናት ጠብቆ ያቆያቸውን መስጂዶች በፖሊስና በወታደር ኃይል በማስፈራራት፣ በመከብበብና በማገት ለመንጠቅና እና ለአሕባሾች አሳልፎ ለመስጠት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
በተለይም በደሴ ከተማ እየተስተዋለ ያለው ሁኔታ ትእግስትን የሚፈታተን ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው፡፡ የዚህ የመንግስት አካሄድም ተልዕኮውም ግልፅ ነው፤ ህዝብን ለአመፅ በማነሳሳት እልቂትና ፍጅትን መጋበዝ ነው፡፡ መስጂዶቻችንን መንጠቅ፣ ኢማሞቻችንን በማባረር በአሕባሾች መተካት በየትኛውም ሐይማኖት ተከታዮች ላይ ታስቦ እንኳን የማይታወቅ ድፍረት ነው፤ የዚህን ድርጊት መቀጠል ተከትሎ ለሚከሰተው ማንኛውም ጥፋት መንግስት ራሱ ተጠያቂ እንደሚሆን ቀድሞ ሊያምንበት ይገባል፡፡ መስጂዶቻችን የህልውናችን ጉዳዮች ናቸው፡፡
አሕባሾን ከማደራጀትና በሌላው ላይ በግድ ከመጫን ያልተቆጠበው መንግስት የህዝብ ንብረት በሆኑት መስጂዶቻችን ላይ ወረራ ከማካሄድ የራሳቸውን መስጂድ ሊገነባላቸው ይችላል፡፡ ከዚህ ቀደም በከሸፉት የአሕባሽ ፕሮጀክቶች፤ በተለይም ሕብረተሰቡ በአንድ ድምጽ የአሕባሽን አስተሳሰብ ከእውቀት በመነሳት አንቅሮ በመትፋቱ በመበሳጨትና በተስፋ መቁረጥ ስሜት ተውጦ ያለ የሌለ ሃይልን በመጠቀም በተጨባጭ እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ መዘዙ የከፋ እና የአገራችንንም ገፅታ እስከመጨረሻው ድረስ ሊያበላሽ እንደሚችል ሊታሰብበት ይገባል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙም መቼም ቢሆን መስጂዶቹን አሳልፎ እንደማይሰጥ ቢታወቅም በተዘጋጀለት ወጥመድም ላይ እንደማይወድቅም ሊታወቅ ይገባል፡፡
አላሁ አክበር!

Jan 4, 2013

የለንደኗ ማሪያም ቤ/ክን ወዴት እያመራች ነው? – ከታምሩ ገዳ (ጋዜጠኛ)




የለንደኗ ማሪያም ቤ/ክን ወዴት እያመራች ነው?

ከታምሩ ገዳ (ነጻ እና የግል አሰተያየት)

በምድረ እንግሊዝ በለንደን ከተማ የምትገኘው የርእሰ አድባራት ደብር ጽዮን  ቅድስት ማሪያም  ቤተክርስቲያን ፈታኝ የሆኑ ችግሮችን
በመጋፈጥ  ላይ ትገኛለች፡፡
የቤተክርስቲያኒቱን  ስም በግል ስማቸው  ለማዛወር  ጥረት አድርገዋል የተባሉ ሁለት  ምእመናን   ከአባልነት  ታገዱ፡
የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ለመስጠት ወደ ቤተክርስቲያኔቱ  ግቢ ያቀኑ  ሁለት አገልጋዮች  ተቃውሞ ገጠማቸው ፡
የጸጥታ ሃይሎች  በቤተክርቲያኒቱ ጉዳይ   ሰሞኑን ሁለት ጊዜ ተጠርተዋል፡፡
ከተመሰረተች  ከሶስት አስርት አመታት በላይ  ያስቆጠረችው  የደብረ ጽዮን  ቅድስት  ማሪያም  ቤተክርስቲያን   በሺዎች ለሚቆጠሩ
በለንደን እና  በአካባቢዋ ለሚገኙ የኢ/ኦ/ተ/ ቤ/ክን አማኞች  አምባ እና  መጠጊያ  በመሆን  ስታገለግል  ቆይታለች ፡፡የድንግል ማሪያምን
አምላጅነት  አምነው  የተማጸኗት  በርካታ  ምእመናን  አያሌ  ተአምራት ሲሰራላቸው  እንደቆዩ  በተቃራኔው  ድግሞ የማሪያምን  ጥቅሟን
የነኩ   ወገኖች   አይወድቁ አወዳደቅ እንደገጠማቸው  እነዚሁ  ማእመናን  የመሰክራሉ፡፡ ይህቺ ለአብዛኛው ስደተኛ  ማህበረሰብ  በሃዘን
ሆነ በደስታ ጊዜያት መሰባሰቢያ እና  መጽናኛ  የሆነች ቅድስት ቤ/ክን  ከአራት አመት  በፊት  በ1,700, 000 የእንግሊዝ  ፓውንድ
(47,600,000 ብር ) የራሷ የሆነ ህንጻ ቤ/ክን  ግዢ ሲፈጸም  ብዙዎች ህልማቸው እውን መሆኑን በማየታቸው የደስታ  እምባቸውን
አምብተዋል፡፡ ሁኔታውንም በጊዜው  በግንባር  ተገኝቼ ለተለያዩ ድህረ ገጾች ዘግቤዋለሁ ::
ከቅርብ ጊዚያት  ወዲህ ግን  ቤክርስቲያኔቱ በምን  መልኩ ትተዳደር?፡ የ ጊዜ ገደቡ ያለፈው የሰበካ ጉባኤው  መቼ ነው  ወርዶ አዲስ
አባላት የሚመረጡት?  ፡ ቤክርስቲያኔቱ ከየትኛው   ቅዱስ  ሲኖዶስ  ጋር ትሁን ?(በአገር ቤት   ካለው ሲኖዶስ ? ወይስ  በውጪ ካለው
ሲኖዶስ?  ወይስ   አሁን ባለችበት በገለልተኛነት አቋሟ ትጽና?...  ወዘተ) የሚሉ ሃሳቦች ዙሪያ  የተካረሩ እሰጣ ገባዎች በሃሳቦቹ ደጋፊዎች
እና በተቃዋሚዎች  መካከል በአውደ ምህረት ላይ: በኪራይ አዳራሾች  እና  በተለያዩ ደህረገጾች  አማካኝነት ሲንሸራሸሩ   ተስተውለዋል፡፡
ወደ ዋና የጽሁፊ  መነሻ  ወደሆነው  ወቅታዊ የቤተክርስቲያኒቱ ችግሮች  ሰመለስ  አንድ ወር ባልሞላ  ጊዜ ውስጥ  ሰለተከሰቱ አንኳር
የቤተክርስቲያኒቱ  ችግሮች  መካከል በሁለቱ ጉዳዮች  ዙሪያ ትንሽ የግሌን አሰተያየት  ልሰንዝር ፡፡
ባለፈው ታህሳስ 13 ቀን 2005 አ/ም (22 ታህሳስ   2012 እኤአ )የቤተክርስቲያኒቱ አሰተዳደር ጉባኤ  በ Ref DTM 568 Ext-Msl
00568/ 12 ያወጣው  ደብዳቤ  እንደሚያመለክተው  “አቶ ግርማ  ተሊላ  እና  አቶ ጥላዬ የሻነው   የተባሉ ምእመናን በመስከረም 2
2012 እ ኤ አ የቤተክርስቲያኒቱን  ስም በመጠቀም ኩባንያ  ካምፓኔ ቁጥር 8200045 የሚል  በአቶ ግርማ  ተሊላ  የመኖሪያ ቤታቸው
አድራሻ  በማውጣት  ላለፉት  ሶስት  ወራት  ያህል  ጉዳዩን  ደብቀው  አንደቆዩ  በመደረሱ ሁለቱ ግለሰቦች   ከቤተክርስቲያኒቱ
አባልነታቸው  ለጊዜው እነደታገዱ” ይፋ አድርጎ ወደፊትም  በህግ እንደሚጠየቁ  የቤ/ክኗ ማህተም እና ፊርማ  ያዘለው  መግለጫ
ያትታል፡፡  ይህ መግለጫ ባለፈው እሁድ እለት (ከሁለት ሳምንት በፊት ) ለምእመናኑ   በአውደ ምህረት ላይ ይፋ በተደረገበት  ወቅት
“የሁለቱ ግለሰቦች  ሃሳባችው መደመጥ አለበት በሚሉ እና የለበትም” በሚሉ ወገኖች መካከል  የተካረረ አስጣ ገባ  እንደነበር ፡
ሁኔታውንም ለማርገብ የጸጥታ ሃይሎች  ጣልቃ እንደገቡ በእለቱ የተገኙ ምእመናኖች ሁኔታውን በሃዘኔታ አጫውተውኛል ፡፡ጉዳዩም
በህግ የተያዘ በመሆኑ  ለጊዜው  ብዙ  አስተያየት መስጠት ባይቻልም  ሁለቱ  “ተወቃሽ ግለሰቦች” በ 19 ታህሳስ  2012 እኤአ  በ ኤ-ሜል
አማካኝነት አሰተላለፉት የተባለ እና ስማቸው  የሰፈረበት  ነገር ግን ፊርማቸውን ያላካተተ   ጸሁፍ አንዳመለከተው ከሆነ
“ቤተክርስቲያኔቱን  በቻሪተእብሌ  ካምፓኒይ   ሊሚትድ ባይ  ጋራንቲ   ለማቋቋም ወራት የፈጀው  እና  እስከአሁን ድረስ  እልባት  
ያላገኘው ድርድር ባለመቋጨቱ  ለቤተክርስቲያኒቱ  ተገቢው  የሆነውን ሰው ሌላ ግለሰብ ወይም ድርጅት  እንዳይወስድባት  በማሰብ
የቤተክርስቲያኒቱን ስም ተጠቅመናል ፡፡ሁኔታዎች  ሲረጋጉ  ያስመዝገብነውን  ድርጅት በነጻ  ለቤተክርስቲያኒቱ  በቻሪተብል ካምፓኒ
ሊሜትድ ባይ ጋራንቲ  አትመዘገብም   ከተባለ በስማችን  ያስመዘገብነው  ድርጅትን   ወዲያውኑ  እንደምንዘጋ  ለሰበካ አሰተዳደር
ለማስተዋወቅ እንወዳለን::” ይላል፡፡  ሁለቱ ግለሰቦች  እስከ አሁን ድርስ ለምን ዝምታን መረጡ? እነርሱን ይህንን ታላቅ ሃላፊነት በግል

እንዲቀበሉ ማን መረጣቸው? ቤተክርስቲያኒቱ   የውሳኔ መግለጫ ካወጣች በሁዋላ  ለምን የማስተባበያ    ደብዳቤ ማውጣት አሰፈለገ
?ለሚሉት እና  መሰል ጥያቄዎች ተጠቃሾቹ ግለሰቦች ሆኑ በእነርሱ ስም የጻፉት ወገኖች ለጊዜው ያሉት ነገር የለም፡፡  የእነዚህን ሁለት
ግለሰቦች ተግባር “እንደግፋለን”  የሚሉ ነገር ግን ሰማቸውን እና ማንነታቸውን በውል ያልገለጹ ወገኖች ያሰራጩት  መልእክት  በበኩሉ
አንደሚያትተው ከሆነ  “ሁለቱ ግለሰቦች የከፈቱት  ድርጅት  ከለንደኗ ጽዮን  ማሪያም   ቤ/ክን  ጋር አይገናኝም”  የሚል መልእክት ያዘለ
ሲሆን  ይሄው ጽሁፍ  ወረደ ብሎ “ሁለቱ  ግለሰቦች  ( አቶ ግርማ እና አቶ ጥላዮ)  ይህንን አርምጃ የወሰዱት  ሌሎች  ግለሰቦች
የቤተክርስቲያኒቱን   ስም  እንዳይጠቀሙ ወይም እንዳይወስዱ  ለማድረግ  አስበው ነው::” የሚል ድጋፍ  አይነት  መልክት
እስተላልፏል፡፡
ሌላኛው   አራሳቸው የቤተክርስቲያኔቱ  ካህናት እና ምእመናን በሚል ሰም  በኤ-ሜል አማካኝነት  ሰሞኑን የተሰራጨ የቅስቀሳ  እና
ማስጠንቀቂያ   መልእክት  የተሰራጨ ሲሆን የዚህ  ወቀሳ ሰለባዎች መካከል  የደብሩ አሰተዳዳሪ  የሆኑት ቆሞስ አባ  ግርማ ከበደ   አንዱ
ሲሆኑ   ይሄው  ጽሁፍ “የማሪያም ቤ/ክን   ከስላሴ ቤ/ክን ጋር ያላትን የአቋም ልዩነት  ወደ ጎን አደርገው  ከስላሴ ቤ/ክን  እና  ከሌሎች
የሟቹ ፓትሪያርክ አባ ጳውሎስ  ደጋፊዎች  ጋር  በመወገን የቤተክርስቲኗን  ህልውና  አሳልፎ የሚሰጥ  ተግባር  እየፈጸሙ ሲሆን  ይህ
ድርጊታቸው   በቤተክርስቲያኒቱ  አባላት  ፈጥኖ ካልተገታ  ቤተክርስቲያናችንን  ከእጃችን ወጥታ ልትቀር አንደምትችል በሚገባ መረዳት
ያሰፈለጋል… ወዘተ፡፡ “  ይላል፡፡  ይሄው  የቅስቀሳ ኢ-ሜል ጽሁፍ አንገብጋቢ ችግር ነው ያለውን ጉዳይ  ሲያብራራ “ በርእሰ  አድባራት
ለንደን ጽዮን  ማሪያም ቤ/ክን  የሚደረገው ቅዳሴ:  ቁርባን:  ክርስትና  ሁሉ የማይሰራ እና   የተወገዘ ነው በማለት  ቤተክርስቲያናችንን
የኮነነ  እና  ስሟን   ያረከሰ   ዲያቆን  ብርሃኑ  የተባለ ሰባኪን ከስላሴ ቤ/ክን  በ16 ታህሳስ   2012 እኤአ   በማምጣት   ዲ\ን ብርሃኑ የአባ
ግርማ ከበደን  አላማን  ሊያሳካ   የሚችል ስብከት  እንዲያደርግ  አባ ግርማ ጥረት  በማደረግ ላይ ናቸው…  ወዘተ፡፡ “የሚል  ነው
በአጭሩ፡፡
እውን አባ ግርማ ከበደ  360 ዲግሪ ተቀየሩ?
  የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳዳሪ የሆኑት ቆሞስ አባ ግርማን እስከ ቅርብ ጊዜ እስከ ማቃቸው ድረስ በኢትዮጵያ ያላውን የሰብአዊ መበት  እና
የሃማኖታዊ ጭቆናን በተመለከተ   በርካታ ወገኖች ከአገዛዙ ጋር ያላቸው የጥቅም እና የቅርርቦሽ ትስስር እንዳይቋረጥቧቸው   ዘምታን
በመረጡበት በአሁኑ ወቅት   አባ ግርማ  ግን ድርጊቱን   በአደባባይ በማውገዝ በተለያዩ ሃዝባዊ የተቃውሞ  ሰልፎች እና ስብሰባዎች ላይ
በመገኘት ለጸረ- የሰባዊ መብት ዘመቻው አጋርነታቸውን  በገሃድ  የገለጹ መነኩሴ ናቸው፡፡  የቤተክርስቲያኒቱን  እንቅስቃሴ  በተመለከተ
ደግሞ መረጃን እንኳን ለዜና ሰዎች ለመስጠት  ሙሉ ነጻነት  የሌላቸው   አባት  ለመሆናቸው  ከአንዲም ሁለት ጊዜ ላነጋግራቸው  ሞክሬ  
“ጥያቄህ ማእከላዊነቱን መጠበቅ  ስላለበት በጽሁፍ አቅርብ…ወዘተ”   ያሉኝ  የቅርብ ጊዜ ትዝታዪ ነው ፡፡ ታዲያ  እኛ በቤተክረስቲያኒቱ
አስተዳደራዊ  ጉዳዮች ዙሪያ እንቅስቃሲያቸው  ሆነ አነጋገራቸው  በአመዛኙ ውሱን መሆኑ የሚታወቀው አባ  ግርማን አንዳንድ ወግኖች
በቅርቡ “አቦይ ግርማ “አስከ ማለት  ደረሰው ሲጠሯቸው  ስሰማ  እውን  ቆሞስ አባ ግርማ  መሰረታዊ የአቋም  ለውጥ አሳዩ?   ወይስ
በታላቁ መጽሃፍ ቅዱስ  ውስጥ  በየዋህነት የተመሰለው በጉ ካመረረ… የሚለውን  ቃል ተግባራዊ አደረጉት?  ስል ከእይምሮዩ ጋር ሙግት
ገጥሜ ስንብቻልሁ፡፡ በነገራችን ላይ አባ ግርማ ፍጹም  ሰው ናቸው የሚል  እምነት የለኝም ፡፡አርሳችውም ቢሆኑ  “ፍጹም  ነኝ “የሚሉ
አይመስለኝም፡፡ ታዲያ  በአበዛኛው የለንደን  ሰላማዊ እና ህዝባዊ ስብሰባዎች እና  የተቃውሞ ሰልፎች  ላይ የማይጠፉት አባ ግርማ  ምን
አይነት “የሚያማልል   አለማዊ”   ነገር አገኙ ተብሎ ነው “ቤተክርስቲያኒቱን እያመሷት ናቸው …ወዘተ” የሚሉ በረካታ ወቀሳዎች
ሰሞኑን የሚሰነዘሩባቸው?
ከላይ የቀረበውን  የኤ-ሜል  ጽሁፍ በመንተርሰስ  በምስራቅ ለንደን ከተማ  ለምተገኘው እና በአብዛኛው የካሪቢያን ተወላጆች    እና
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን  ተከታዮች የሆኑ የ ጸራጼዮን ማሪያም ቤ/ክን  በቅርቡ ለገዙት  አዲስ ህንጻ ቤ/ክን የማስፋፊያ  የገቢ ማሰባሰቢያ
ፕሮግራም ከአዲስ አበባ ለስበከት ወንጌል  አገልግሎት ተጋብዘው ወደ ለንደን የመጡት ዲ/ን መምህር ብርሃኑ   አድማስ እና ዘማሪ ዲ/ን
ምንዳዮ ብርሃኑ  በአባ ግርማ ከበደ የግል ጥሪ ወይስ  በራሳቸው መንገድ ወደ  ማሪያም ቤ/ክን ሄዱ? የሚል ጥያቄ በአይምሮዬ ውስጥ
ተጭሮ ነበር ፡፡ ለጥያቄዬም ያገኘሁት ምላሽ  ሁለቱ አገልጋዮች (ዲ/ን በርሃኑ እና ዲ/ን ዘማሪ  ምንዳዮ ) በለንደን አና በአካባቢዋ የሚገኙ
የኢትዮጵያ  ፡የካሪቤያን  አና የኤርትራ ተወላጆች የሆኑ የኦርቶዶክስ  ተዋህዶ ቤተክረሰቲያኖች  በመዘዋዋር የስብከተ ወንጌል  ትምህርት
እና አገልግሎት  በመስጠት  እና  ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር በህብረት በማዜም መሰንበታቸውን  የተረዱ  በለንደን  ደበረ ጽዮን ማሪያም
ቤተክርስቲን የሚገኙ  ምእመናን   ለቤተክርስቲያኒቱ የካህናት  ጉባኤው ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት አንደተጋበዙ እና  የሁለቱንም አገልጋዮች
ወደ ማሪያም ቤ/ክን   መምጣት በመቃወም ረገድ  መሪ ጌታ   አዲስ  አዱኛ   የተባሉ የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋይ   ብቻ ሲቃወሙ የመሪ
ጌታ አዲስ ተቃውሟቸው ተመዘግቦ  የግብዣ ሃሳቡ በድምጽ ብልጫ  ተቀባይነት ማግኘቱን  ለማወቅ ችያለሁ፡፡

ሁለቱ አገለጋዮች (ዲ/ን በርሃኑ እና ዲ/ን ዘማሪ  ምንዳዮ )  በግብዣው  መሰረት ወደ ማሪያም ቤ/ክን ሲያመሩ  የጠበቃቸው የዘንባባ
ዝንጣፊ ሳይሆን ሁለቱ አገልጋዮች “ ወደ ቤ/ክኗ ይገባሉ… !! አይገቡም…!!  “የሚሉ የሁለት ወገኖች የከረረ  አለመግባባት የታየበት እና
ሁኔታውን ለማርገብ እና ለምቃኘት የጸጥታ ሃይሎች  ወደ ቤተክርስቲያኒቱ  የጋበዘ  ሁኔታ  ተስተውሏል፡፡ ለሶስት ቀናት ይካሄዳል
የተባለው የስብከተ ወንጌል ፕሮግራሙ ሁለቱ  ሰባኪያኑ ከነበራቸው የተጣበበ  ፕሮግራም የተነሳ ለሁለት ቀናት  ብቻ  ተካሄዷል፡፡
ዲ/ን ብርሃኑ  አድማስ ማናቸው ?
በዚህ ሰብከተ ወንጌል ላይ የተገኙት ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ  “ሰለ ማሪያም  ቤክርስቲያን  መጥፎ  ስብከት  ሰጥተዋል”  ተብሎ   ወቀሳ
የተሰነዘረባቸው ሲሆን   በመሰረቱ  ዲ/ን ብርሃኑ  በአገር ቤት ምን አይነት ስብከት እንደሚሰጡ ለመታዘብ አጋጣሚውን ባላገኝም በባህር
ማዶ ሰብከታቸው  ግን  ዘወትር  በስብከተ ወንጌል ትምህርታች  ላይ   ጥቁሩን  ጥቁር:  ነጩን  ነጭ : ጎባጣውን ጎባጣ :ቀጥ ያለውን
ሸንቃጣ  ብለው በስሙ   ከሚጠሩ ጥቂት የዘመናችን  ወጣት ሰባኪያን መካከል አንዱ እንደሆኑ  እና   በተለያዩ ጉባኤዎች ላይ
አሰረገጠው ሲናገሩ ከሰማሁዋቸው  መልክቶቻቸው  መካከል  “የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን  የራሷ የሆነ ሰርአት እና  ደንብ ያላት :  የማትከፋፈል
ሃይማኖታዊ ተቋም በመሆኗ  ይህንን  ሰርአቷን  በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የሚያፈርሱ ወይም  የሚጻረር መንገድ  ላይ የቆሙ
በየተኛውም  ጎራ የተሰለፉ ፖለቲከኞች ሆኑ የሃይማኖት መሪዎች ነን  የሚሉ ወገኖች  አካሄዳቸውን ሊመረምሩ ይገባል  ፡
ቤተክርስቲያኒቱም  የሰላም እና  የፍቅር መድረክ  እንጂ  የጸብ እና የንትርክ ቦታ  ልናደርጋት  አይገባም ፡ በቤተክርስቲያናችን ህግ እና
ደምብ መሰረት   ጳጳስ ካልባረከው በሰተቀር  አንድ ቄስ ተነሰቶ አዲስ ቤ/ክን  ሊከፍት ወይም የድቁና ማእረግ ለአገልጋዩች ሊሰጥ በፍጹም
አይችልም …ወዘተ “ በማለት   አስረግጠው ሲሰብኩ  አዳምጫለሁ፡፡ ይህ ሰብከታቸው   ሁሉንም ምእምናን ሊያስድስት  የችላል ማለት
ባይቻልም ከስርአተ  ቤ/ክን አንዱ አካል በመሆኑ መቀበል አለመቀበለ  በእያንዳንዱ ምእመን  የሃይማኖታዊ ግንዛቤ  ደረጃ  ላይ ይወደቃል
፡፡ ዛሬ አውነታውን ፍርጥርጥ አደርግው ለምናገር የሞራል ብቃቱ ሆነ ብልሃቱ የጎደላቸው  በረካታ  መሪዎች  ሆኑ ሰባኪያን
በተበራከቱበት አለም ውስጥ ስንገኝ  ከወገንተኝነት የጸዳ ስብከት  እና ስርአተ ቤ/ክን ትምህርት  የሚሰጡ ወገኖችን እንዲያው  በደፈናው
ማሳጣቱ ወይም ለወቀሳ መዳረጉ ልዪነቶችን ከማስፋቱ በተጨማሪ  እንዴ ጎብዝ ምን አይነት ዘመን ላይ ደረሰን? ፡ወዴትስ እያመራን ነው?
የሚል ጥያቄ ማስነሳቱ  አይቀርም ፡፡ይህ ማለት ግን    የአገር እና  የሃይማኖት ጉዳይ የጥቂት  አዋቂዎች ወይም መሪዎች   ብቻ ስለሆነ ዝም
በሉ ወይም  የሚሰጣችሁን  መምሪያ ሆነ ውግዘት አሜን ብላችሁ ተቀበሉ ማለት  ሳይሆን  ለሁለት ሺህ  አመታት ስርአቷን  እና ትውፊቷን
ጠብቃ የቆየች  ሃይማኖትን   “የእነ አባ እገሌ ደጋፊዋች  እና ተቃዋሚዋች  ወይም  ከዚያ ዝቅ ሲል የዚህ እለት  እና  የዚያኛው እለት
ጉባኤተኞች…  ወዘተ”   በሚሉ  ልዩነቶች በመተብተብ  ወደ ማያባራ  ልዩነት ለመውስድ መሯሯጡ   በየትኛውም  መንገድ ሊደገፍ
የሚገባ አይመስለኝም፡፡ ቢቻል ልዩነቶችን  ለማጥበብ  መሞከር ብልህነት  እና የሚያጸድቅ ስራ ሲሆን ካልሆነ ደግሞ ጊዜ ፈቅዶ ወደ
አንድነት እስኪመጣ ድረስ  እንኳን  ላለመነቋቆር  እናኳን  በጨዋ ደንብ ተወያይቶ መለያየት ሲቻል   ነጋ ጠባ  በነገር ቁርቃሶ
መውነጫጨፉ  ጉዳቱ ለተፋላሚ ወገኖቹ ብቻ ሳይሆን ሃይማኖቱን  ሃይማኖቴ ብሎ   ከፈጣሪው ጋር ለመገናኘት ዘወትር ማልዶ  ወደ
ቤተክርስቲያን የሚሄደውን ህዝበ ክርስቲያንን  ማሳዝን እና ከሃይማኖቱ አንዲርቅ  እንደሚያደርገው  መዘንጋት የለብንም ፡፡
ፖለቲካኛ ገዢዎች በተፈራረቁ ቁጥር  የጨፍልቀህ ወይም የከፋፍለህ ግዛው ፖሊሲያቸውን ለማሳካት ሲሉ ዛሬ ድርሰ  እጃቸውን
ያላነሱባት ቅድስት  ቤተክርስቲያንን ከተደቀነባት የመከፋፈል እና የመለያየት አደጋ  ለምታደግ የህዝበ ክርስቲያኑ  የጋራ ጾም ፡ጸሎት እና
ስርአት ያለው የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት  አግባባነት  ያለው እና  ሊደገፍ የሚገባው መንገድ  ለመሆኑ ጥርጥር የለውም ፡፡ ይህ ሳይሆን
ቀረቶ  “አኛ ካልነው  ሃሳብ ውጪ  ምንም አይነት  ሃሳብ  አይበጀንም  ፡ ከየትኛው ወገን ይሁን ወደ ቤተክርስቲያን የሚመጡ  ወገኖችን
ዘወትር በጥርጣሬ  አይን ማየቱ … ወዘተ “ ቤተክርስቲያን  ከተመሰረተችበት   ሃዋሪያዊ ተልእኮዎች   መካከል አንዱ የሆነው   ጠላትህን
እንደ ራስህ አድርገህ ውደደው  የሚለውን  ከባድ ትእዛዝን  ለመተግበር ቀረቶ  “የገዛ ወንድምህን  እንደራስህ  ለማየት ሞክር “ በሚል
እንኳን ብንተካው  ከፊታችን  በርካታ የቡድን እና የግል ፈተናዎች   የተደቀኑብን  ይመስለኛል ፡፡   ( tamgeda@gmail.com)

Total Pageviews

Translate