Pages

Jan 16, 2013

ኢትዮጵያ፤ ዚመዳኛ ወቅትና፤ ዹዕሹቀሰላም ጊዜ

ኚፕሮፌሰር ዓለማዹሁ ገብሚማርያም
ትርጉም ኚነጻነት ለሃገሬ
ዹሹፖርተር ድሕሚ ገፅ ሲዘግብ:
በጎሳ ላይ ዹተመሰሹተ ግጭት በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ መሃል በመጞዳጃ ቀቶቜ፤ በቀተመጻህፍትና በመኝታ ቀት  áŒá‹µáŒá‹³ ላይ፤ዚተጻፉ አስፀያፊ ክብሚነክ ጞሁፎቜ ኚስድስት በላይ ዹሆኑ ተማሪዎቜን ለኹፍተኛ ዹመቁሰል አደጋ ተጠቂ ዳርጓ቞ዋል:: በርካታዎቜንም ለእስር አብቅቷል፡፡ ለላለፉት አሰርት ዓመታት፤በዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ መሃል ግጭቶቜን ሲያስነሱ ኹርመዋል፡፡ ይህም መሰሚታዊ ቜግሩና መንስኀው አስተዳደራዊ ድክመት ነው፡፡ ኹዚሁ ጋር በተመሳሳይ ባለፈው በእለተ ዕሚቡ ጃንዋሪ 2 2013 ዹተቀሰቀሰው ግጭትም በተለይ በሁለት ጎሳዎቜ በኊሮሞና በትግራይ ተማሪዎቜ መሃል ዹተኹሰተ ነበር፡፡ ምስክሮቜ እንደሚሉት፤ግጭቱ ዹተቀሰቀሰው ዚትግራይ ተወላጅ ዹሆነው ተማሪ፤ በመጞዳጃ ቀት፤ በቀተመጻህፍትና በተማሪዎቜ መኝታ ቀቶቜ  áŒá‹µáŒá‹³á‹Žá‰œ ላይ ዚጎሳን ክብር ዚሚነካ ጜሁፍ በመጻፉ ነበር፡፡
እንደ ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ባለስልጣን አባባል ‹‹áŒáŒ­á‰± ዹተቀሰቀሰው ያንን ዚጎሣ ክብር ዚሚነካ ክብሚነክ ጜሁፍ በተመለኚቱት ተማሪዎቜ  መሆኑን ነው::›› በዚህም ዚተነሳ 20Addis Ababa University, Ethiopia á‰°áˆ›áˆªá‹Žá‰œ መቁሰላቜውንና 3ቱ ዚጠናባ቞ው ወደ ሆስፒታ፤ል መወሰዳ቞ውን በተጚማሪ ሁለቱ ዚቀዶ ጥገና እንደተደሚገላ቞ው ታውቋል፡፡ ሌሎቜ 20ዎቜም በፖሊስ ባልለዚለት ውንጀላ ለእስር ተዳርገዋል፡፡
ስለኢትዮጵያ ‹‹á‹šá‰¥áˆáˆ†á‰œ መፍለቂያ ኹነበሹው ዩኒቚርሲቲ›› ይህን ሁኔታ ሳነበው ያደሚብኝ ግብታዊ አስተያዚት፤ ማመን እስኪያቅተኝ ነበር፡፡ ሳስበዉም ‹‹á‹­áˆ… ፈጜሞ ሊታመን ዚሚቜል ጉዳይ አይደልም፡፡ ይህ ኚኢትዮጵያ አነሮቜ ትውልድ (ወጣቱ ትውልድ) በዚህ ፈሪነትና ዚማያስፈራራ አስኚፊ ሁኔታ ውስጥ መግባት ተግባራ቞ው አይደለም፡፡ ዚኢትዮጵያ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ በዚህ ቆሻሻ እና እጣቢ አተላ ዚጎሳ ፖለቲካ ውስጥ ኹመንደፋደፍ ዹተሾለና ዹበለጠ ተግባር ማኹናውን ይቜላሉ›› አልኩኝ :: ይህን ዹመሰለ ዹሹኹሰ ዚጥላቻ ምግባር፤ዚወዲፊቶቹ ኢትዮጵያዊያን ምሁራን፤ዚቀጣዩ ትውልድ መምህራን፤ ሳይንቲስቶቜ፤ እና ዚፈጠራ ሰዎቜ ምግባር እንዳልሆነ ነበር እራሎን ማሳመን ዚሞኚርኩት፡፡
ነገሩን ዹበለጠ ሳጀነው አምአሮ ዚሚነካና ዚሚአስቀፍፍ ሆኖ አገኘሁት፡፡ እራሎንም ጠዹቅሁ፡፡ ምናልባትስ ይህ ዚጎሳ ክብር ዚሚነካ ጜሁፍ በሌሎቜ ዹአ አ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ  á‹šá‰°áˆáŒ áˆš ቢሆንስ? ይህን ዹመሰለው ዝቃጭ፤ወኔቢስ፤ባለጌ ተግባር ስለነዚህ ተማሪዎቜ ምን ይላል? ስለአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜስ? ስለአጠቃላዮቹ ዚኢትዮጵያ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜስ? ስለ መላው ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜስ?
ኹዚህ ጥዚቄ ጋር በመታገል ላይ እንዳለሁ፤ ሊገታ ዚማይቜል ሃፍሚትና ውርደት ሰሜት ወሹሹኝ፡፡ እራሎን ደጋግሜ መሚመርኩት፡፡ ‹‹á‹šáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« ምርጥና ብሩህ አእምሮ ያለ቞ው ተማሪዎቜ—- ዚኢዮጵያ አነሮቜ —- ይህን በመሰል ኋላ ቀር፤ አሚመኔያዊ፤ ጚካኝና አሰቃቂ፤ ተናካሜ፤ ተንኮል ዚተመላበት፤ተግባር አንዎት ሊሰሩ ይቜላሉ?  በምን መንስኀ ነው፤ አንድ ዚኢትዮጵያ ተማሪዎቜ ስብስብ ሌላውን ወገን ስብእና ለመድፈር፤ ዹጋኔን ተግባር ለመፈጾም፤ ዝቅ አድርጎ ለመመልኚት፤ አውሬ በማስመሰል፤ አካሄድና ተግባር ዚሚሰማሩት? ለምን? እኮ ለምን? ለነዚህ ጥያቄዎቜ አንዳቜም ምክንያታዊ ምላሜ ላገኝ አልቻልኩም፡፡
ይህ ዹ ጎሳ  ጥላቻ ወንጀል ዹተፈጾመው ባለፈው ሳምንት ሰለ አትዮጎያ ወጣቶቜ ክብርና ወደፊት ላገራ቞ው ሰለምተበቀባ቞ው ግዎታ በመፅፈበት ወቅት ነበር :: ሆነ በተባለው ዚጎሳ ጥላቻ ወንጀል ዹበለጠ ግራ እዚተጋባሁ ሄድኩ፡፡ ይህን አስጠያፊና አስፈሪ፤ ቀፋፊ ሁኔታ በምክንያታዊነት በጥልቀት ለመሚዳትና በዚህ አስገራሚ ትርኢት ውስጥ አንዳንድ ዚኢትዮጵያ አነሮቜ እንደ ጉማሬዎቹ በመንቀሳቀስ እንደጅቊቹ ለመሆን መኹጀላቾው አስገሚመኝ፡፡ አሳፈሚኝ፡፡ አሳዘነኝ፡፡
ያን ግልብ ስሜ቎ን ወደ ጎን አልኩና ሹጋ ብዬ ማሰብ ጀመርኩ:: ኹምር ጠንክሬ አሰብኩ፡፡ ይህ በዩኒቚርሲቲው ዹተኹናወነው ‹‹á‰ áŒŽáˆ³ ላይ ዹተመሰሹተውን አልመግባባት›› ድርጊት ኚጥሩ እምነት ካላ቞ው ሁነኛ መደበኛ ተማሪዎቜ ተጠንስሶ በስራ ላይ ዹዋለ ነው  ለማለት ምን ማስሚጃ ሊቀርብ ይቜላል? በእውነትስ  ዚተባለውና በዚህ በዚግድግዳው ላይ ዚሰፈሩትን ክብሚ ነክ ጜሁፎቜ ዚጻፈው ‹‹á‰°áˆ›áˆª›› ማነው?  በዚህ ዩኒቚርሲቲ ዹሙዚቃ ሾክላ አጫዋቜ መሰል ዚህዝብ ግንኙነት ጜህፈት ቀት ተቀምሞ ዹተበተነውን መሞንገያ አባባል ማመን አለብን? እንዎት ነው ዚዩኒቚርሲቲ አስተዳዳሪዎቜ  ‹‹áˆˆáŠ áˆ°áˆ­á‰µ ዓመታት በዩኒቚርሲቲዎቜ ሲኚናወኑ ዚነበሩትን ዚጎሳ ግጭቶቜ” ያሳለፏ቞ውና አሁንም ሲቀጥሉ  áŠ áŒƒá‰žá‹‰áŠ• አጣጥፈው  መመልኚት ዚቻሉት? በዩኒቚርሲቲውስ ውስጥ ምራቃ቞ውን ዚዋጡና ዹበሰሉ፤ቜግሮቜን ለማክሾፍና ለማግባባት ፈቃደኛ ዹሆኑ አመራሮቜ ዹሉም?
ጥርጣሬ ቀስ እያለ፤ድንጋጀዬንና ሃፍሹቮ  መተካት ስለጀመሚ፤ ዹዚህ ‹‹á‰ áŒŽáˆ³ ላይ ዹተመሰሹተ ብጥብጥ›› በገዢው መንግስት ጀብደኛ ባለማዕሚግ ዹተዋቀሹና፤ ዹተተለመ እንደሆነስ ዹሚለው ጥያቄ አያፈጠጠ ያዚኝ ጀመር፡፡ በኋላም ዹወንጀል መመርመርያ ማስሚጃ ማፈላለጊያ “መነጜሬን” ሳደርገው፤ እንደገና በመሹለክለክ ድምጜዋን አጥፍታ ጹለማና ወቅትን መኚለያ በማድሚግ አንዲት መናጢና ቆሻሻ አይጥ ተንኮሏን ኚፈጞመቜና ተልእኮዋን ኚፈጞመቜ በኋላ ሳትታይ ጥላው  ዚሄደቜውን ዚእጇንና ዚእግሯን አሞራ በግድገዳ ላይ ኚተጻፈው አስጠያፊ ጥሁፍ አግርጌ ታትሞ አዚሁት፡፡
በሜይ 2010 ጃዋር ሲራጅ ሞሃመድ ወጣቱ ኢትዮጵያዊ ዚፖለቲካ ሐተታ ሰጪ እንዲሁም ዚኮሎምቢያ ዩኒቚርሲቲ ተመራቂ ተማሪ እንደዘገበው  በዩኒ ቚርሲቲው ግቢ ውስጥ ኚተማሪዎቜ ጋር በርካታ ውይይት ካካሄደ በኋላ እንዲሁም በሁለት ክፍል በሃራማያና፤በአዳማ  ዩኒ ቚርሲቲ በ2006 ዹተኹናወነውን ድርጊት  ሰበቡን ዚአካዳሚክ ነጻነት ማጣትና በኢትዮጵያ ዚደህንነት ሚስጥራዊ ተቀጣሪዎቜ ተማሪ በመምሰል ሰርገው በመግባት ዚግጭቱ መሰሪ ጠንሳሟቜ መሆናቾውን ለማመን በቅቷል፡፡
ደግሞም በሮፕቮምበር 2011 ላይ በይፋ ዚዎጣው ማስሚጃ አንዳሳዚው በሮፕቮምበር 16 2006 “ ዚኢትዮጵያ ዚደህንነት ሃይሎቜ በኢትዮጵያ ዋና ኹተማ አዲስ አበባ 3 ፈንጂዎቜ መቅበራ቞ውንና በመፈንዳቱና፤ በወቅቱም ዚአፍሪካ ሕብሚት ስብሰባ ዚሚካሄድበት ስለነበሚ ኹሹር ያለ ጥያቄ ያስነሳውን  ፍንዳታም ኀርትራንና ዚኊሮሞ ነጻ አውጪ ግንባርን ተጠያቂ እንዳደሚጉ ነበር::” በአዲስ አበባ ዹሚገኘው ዚአሜሪካን መንግስት ኀምባሲ ባካሄደው ‹‹á‹šáˆšáˆµáŒ¢áˆ­ ዘገባ›› በጉዳዩ ላይ ዚመርማሪዎቹ ጣት  ወደ ኢትዮጵያ ገዢ መንግስት ዚደህንነት አባላትን በመጠቆም ለዚህ ዹወንጀል ድርጊት ተጠያቂ አድርጓ቞ዋል፡፡
በሌላም በኩል በ2006 ዹተገኘው ሚስጥራዊው ባለ 52 ገጜ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዹተዘጋጀው ሰነድ፤ ዚዲያስፖራው ዳይሬክቶሬት በዲያስፖራው ያሉትን ዹተቃዋሚ ሃይላትና አባሎቻ቞ውን ዹሚነዘንዝ፤ በሃይማኖት፤ በዘር፤ በፖለቲካ ጥላቻ ዹሚኹፋፍልና ማንኛቾውንም ገዢውን ፓርቲ ዚሚቃወሙትን ለመኹፋፈልና በመሃላቾው መግባባት እንዲጠፋ ያደሚገው ጥሚትና ዝግጅት ተጋልጩ ነበር ፡፡ ስለ አዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ አጋጣሚ በይበልጥ ባሰብኩ ቁጥር፤ዚገዢው መንግስት ተቃዋሚዎቜን ለማስጠላት ለመኹፋፈል ለመበታተን ለማክሾፍ ብሎ ዚሚዘራውን ቆሻሻና ዚብልግና ባህሪ ያጋልጡት ጀምሹዋል፡፡
በተጚባጭ ምርምሬ አንደተርዳሁት ‹‹á‰ áŒŽáˆ³ ላይ ለተመሰሹተው ግጭት›› ወንጀል በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ  ተጠያቂው ማን እንደሆነ ግልጜ ዹሆነው ማስሚጃ  ዹሚጠቆመው ወደ ተለመዱት ወንጀል ፈጻሚ ዚገዢው መንገስት ወንጀለኞቜ ነው፡፡
ሊታለፍ ዚማይቜለው መደምደሚያም፤ (ሌላ ተቃራኒ  ማስሚጃ  እስካልቀሚበ ድሚስ) በጃንዋሪ 2 በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ለተፈጾመው ወንጀላዊ  á‰°áŒá‰£áˆ­ ተጠያቂዎቹ፤ በግቢው ውስጥ በድብቅ ዚተቀመጡት መዘዝ ፈጣሪዎቜና ምግባሚ ብልሹ ሕሊና ቢስ  ወኪል ተንኳሟቜና ደባ ፈጻሚዎቜ እንጂ ጚርሶ ለጥሩ ዕምነት ዚተፈጠሩት ወጣት አቊሞማኔዎቹ ዹነገ ዹሃገር አለኝተ ዎቜ ሊሆኑ አይቜሉም፡፡
ዚማጠቃለያው ግምገማም ይህንን መደምደሚያ ዚማያጠያይቅ ማስሚጃ በመሆን ያሚጋግጠዋል፡፡ ያለዉን ማስሚጃ በጥቂቱ ብንመለኚተው: በመጀመርያ እንድ ብ቞ኛ “ተማሪ”ብቻ ነው ድርጊቱን በመተንኮሱ  ዹተወነጀለው፡፡ ይህ ደግሞ ተማሪዎቜ በአንድ ጎሳ ስር ተቧድነው ለዚህ ድርጊት መንቀሳቀሳ቞ውንና በዩኒቚርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ሰላም ለማጥፋት ወንጀል ለመፈጾም፤ መደራጀታ቞ውን ተአማኒነት ያሳጣዋል፡፡  ይህን እንቅሳቃሎ ለመጀመርና መነሻ ሆነ ዚተባለውም ብ቞ኛ “ተማሪ” ዚዚት ጎሳ አባል እንደሆነ በግልጜ አልተሹጋገጠም፡፡ ዚዩኒቚርሲቲው ባለስልጣናት: ስምና መለያው ያልታወቀ፤ አንድ ተማሪ በማለት ወንጀለኛ ብለውታል፡፡ ይሁንና ይህ ‹‹á‰°áˆ›áˆª›› ዓላማ ያለው እርገግጠኛ  áˆ˜á‹°á‰ áŠ› “ተማሪስ” ነው? ወይስ ተቀጣሪ ነገር ቆስቋሜ ዚስለላ ድርጅት ወኪል ግን እንደተማሪ ተመሳስሎ ተወሻቂ አባል (ዚቀበሮ መንኩሎ በግ መሃል ይጞለያል አንደሚባለው ሁሉ ) ነው? ይህስ ተማሪ በዘር ላይ ዹተመሰሹተ ዚጥላቻ ባሕሪ ግለ ታሪክስ ያለው ነው?
ሶስተኛ፤ በሶስት ቊታዎቜ ማለትም በላይብሚሪ፤ በመጻሕፍት ቀትና በተማሪ  áˆ˜áŠá‰³ ቀት ይህን መሰሉን ዚጎሳን ክብር ዚሚያዋርድና ዚሚያንቋሜሜ ጜሁፍ ለመጻፉ ምንም ዹተጠቀሰ ማስሚጃ ዹለም፡፡ በጥላቻ ወንጀል ድርጊት፤ እንዲህ መሰሎቜ ዚጥላቻና ዚማዋሚድ ተግባር ያለባ቞ው ጜሁፎቜ ሲጻፉ ዓላማቾው አንድን ዚጎሳ አባል ዚሚመለኚቱ ሲሆኑ፤ ኢላማ ዚተደሚጉት ግለሰብም ይሁን ቡድኖቜ ሊደርሱበትና ሊያዩት በሚቜሉት ስፍራ ይሆናል እንጂ ዹግል ጥላቻውንና ብሶት ጣውን  ኚተለያዩ ብዙ ጎሳዎቜ ዚመጡ በሚገኙበት ግቢ ውስጥ ዚማይመለኚታ቞ውም እንዲመለኚቱት ለምን ይደሹጋል?
አራተኛ፤ ኹዚህ አስቀያሚ  ዚግድግዳ ጜሁፍ ሌላ ማስሚጃ ሊሆን ዚሚቜል አንዳቜም ነገር ኹዚህ ዚቜግሩ ጠንሳሜ በተባለው ‹‹á‰°áˆ›áˆª›› ላይ አልተገኘም፡፡
አምስተኛ፤ በጃንዋሪ 2 በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ዹተፈጾመው ደባ ዹተለዹ ሁኔታ ሆኖ ሊታይ አይቜልም፡፡ ላለፉት በርካታ አሰርት ዓመታት ይህን መሰል በጎሳ ላይ ተመሰሹተ አምባጓሮ ይነሳ እንደነበር ዚማያጠያይቅ ነው፡፡ ለምንስ ዚዩኒቚርሲቲው ባለስልጣናት ጉዳዩ ሲያቆጠቁጥ አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ ለዚህ ኚመብቃቱ ቀደም ብለው አላኚሞፉትም፡፡ ድርጊቱ በአስኚፊና ሊቀለበስ ወደማይቜልበት ሁኔታ ኹደሹሰና አዳገው ሁሉ ኹተኹናወነም በኋላ በሌሎቜ ተማሪዎቜ ላይ አመጹ ተስፋፍቶ እንዳይቀጥልም ባለስላጣናቱ ዚወሰዱት እርምጃ ዹለም፡፡
ስድስተኛ፤ በነጻ አካላት ጉዳዩ ሙሉ በሙሉ ኚመጣራቱስ አስቀድመው ዚዩኒቚርሲቲው ባለስልጣናት “አመጹ ዹተጀመሹው በግድግዳዎቜ ላይ ዚተጻፈውን ምግባሚ ብልሹና ጎሳን ዚሚያንኳስስ ጥሁፍ ያዩት ተማሪዎቜ ነው በማለት ለምነስ መግለጫ አወጡ? ጉዳዩን ኚመሰሚቱ አንስተው ዚሚያጣሩ ገለልተኛ ወገኖቜ በማዋቀርና በመመርመር ለወዲቱ ይህን መሰል ድርጊት በድጋሚ እንዳይኚሰት ማድሚግ ዚሚቻልበትን ዘዮ ለምን አልቀያሱም? ዚዩኒቬርሲቲው ባለስልጣናት ጉዳዩን እራሳ቞ውን ኚተጠያቂነትና ኚሃላፊነት በማግለል ለፖሊስ ሙሉ በሙሉ ለምን አስሚኚቡት? ምናልባት በዩኒቚርሲቲው ዹሚኹሰተውን ዚጎሳ ጥላቻ ወንጀል ቾል ያሉት አይታቜሁ እንዳላዚ ሁኑ ዹሚል መመርያ ስለተሰጣ቞ው ይሆን?
ሰባተኛ፤ ዹዚህ ዚጥላቻ ብጥብጥ ወንጀል ተጠቂ ዚሆኑትስ በፖሊስ ለመደብደብ ለመያዝና ለመታሰር ለጉዳት ለምን ተዳሚጉ?
በአጭሩ በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ በተፈጾመው ዚጥላቻ ወንጀል ዹቀሹበው ሁኔታና ማስሚጃ ጚርሶ ወደ ተኚሳሟቹ ተማሪዎቜ ጣት አያመላክትም፡፡ ይልቁንስ ያአመልካቜ ጣት በወንጀለኚኝነት ዹሚጠቁመው ወደ ኚሳሟቹ ነው፡፡ ዹዚህን ዚጥላቻ ወንጀል ፈጻሚዎቜ ለማጣራትና ለመያዝ ዚሚያስፈልገው፤ ያንን ዚግድግዳ ላይ ጜሁፍ ዚኚተቡትን ዚማይታዩ ጣቶቜ ብቻ ሳይሆን  እነዚያን ተማሪዎቹን እስኪጠወልጉ ድሚስ ዚቀጠቀጡና ያሰቃዩ፤ ኚዚያም በሚጩት ዚአመጜ ነዳጅ ላይ እንዳይጠፋና ዚበለጥ እንዲቀጣጠል ንዳድ ዚሚጩበትንና ዚጎሳ ግጭቱን ያቀጣጠሉትን፤በተማሪዎቜ መሃል ጥላቻ  ንትሚክና ዉዝግብ አንድፈጠር ዚሚዶልቱ ወንጀል ጠንሳሶቜ ነው፡፡
ያም áŠ¥áŠ•á‹³áˆˆ áˆ†áŠ–፤አሁን á‹ˆá‰…ቱ áŠá‹፤ áŠ áˆµáˆáˆ‹áŒŠá‹ á‹ˆá‰…ት áŠá‹፤ትክክለኛው áŒŠá‹œ ……..
ዚማገገሚያጊዜ፤ዚመቀበያውዚመተቃቀፊያ  á‹šáŠ¥áˆ­á‰€áˆ áˆ‹áˆáŒŠá‹œ አሁን ነው
በክዱስ ጜሁፍ እንደሰፈሚው፤ ‹‹áˆˆáˆ›áŠ•áŠ›á‹áˆ ሁኔታ ወቅት አለው፤ኹሰማይ በታቜ ላሉት ነገሮቜ ሁሉ  ለዚምክንያቱ ጊዜ አለው::›› ለማልቀስ ጊዜ አለው፤ ለሃዘንም ወቅት አለው፤ ድንጋይ ለመወርወርም ጊዜ አለው፡፡ ለመገንባትም ጊዜ አለው፤ ለመናገርም ጊዜ አለው፡፡ እንዲሁም ለመተቃቀፍም ጊዜ አለው ለሠላምና ለማገገምም ጊዜ አለው፡፡ ለእርቀሰላምም  ዚራሱ ጊዜ አለው፡፡
አሁን ነው ጊዜው፤ — ትክለኛው ጊዜ– ለኢትዮጵያውያን ወጣቶቜ በትምህርት ቀቶቜ፤ በዩኒቬርስቲዎቜ፤ በስራ ቊታዎቜ፤ በአጎራባቜ መንደሮቜና በመንገድም ላይ  ዚማገገሚያው ወቅት፡፡ ጊዜው—– ትክክለኛው ጊዜ—- ዚኢትዮጵያ ወጣቶቜ በወንድማማቜነት በአህትማማቜነት ስሜት መተቃቀፍ  áˆ˜á‰°áˆ³áˆ°á‰¥ እጅ ለእጅ በመያያዝና አንድ በመሆን ብዛታ቞ውን  ለቅድመአያቶቻ቞ው ክብርና ለታሪካ቞ው መኚበርያ ማድሚግ ዚሚገባ቞ው፡፡
ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ወጣቶቜ ዚጎሳ ጥላቻን  ዚብጥብጥን አዙሪት ዚመበጠሻ ጊዜው አሁንነው:: አላስፈላጊውን ዚቅሬታ ልምድ ዚማክተሚያ፤ ዚፍርሃትን ባህል፤ ጥላቻን፤ አውልቆ ዚመጣያው ትክክለኛው ጊዜው አሁን ነው፡፡
ለኢትዮጵያውያን ወጣቶቜ ጣቶቻ቞ውን በማቆላለፍ እጅ ለእጅ በመያያዝ ዚፍርሃትን እኚክ ማራገፊያ቞ው፤ ጥላቻን፤ግጭትን፤ኚልባ቞ው ፤ ኹሕሊናቾው፤ ኚመንፈሳ቞ው አውጥተው መጣያ ጊዜያ቞ው አሁን ነው፡፡ ጓደኞቻ቞ውንና ዚትምህርት ባልደሚቊቻ቞ውን እንደጠላትና  ባላጋራ መመልኚትን ማቆሚያ቞ው ጊዜ አሁን ነው፡፡
ሰላም ፈጥሚው እርስ በርሳ቞ው እንደወንድምና እህት ዚሚተቃቀፉበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ ዚኢትዮጵያ ብልህና ምርጊቜ አንድ ላይ በመስራትና በመተጋገዝ ዹተሾለን ነገ ለመፍጠር ዚሚቜሉበት፤በሹጋና ጠንካራ በሆነ ዹሕግ ዚበላይነት ላይ፤ ሰብአዊ መብትና ዎሞክራሲ ዚተኚበሩበት አማራጭ ሂደቶቜ ያሉበት መትለሚያው ጊዜ አሁን ነው፡፡ ኔልሰን ማንዮላ እንዳስተማሩት ‹‹áŠšáŒ áˆ‹á‰µ ጋር ሠላምን መፍጠር ካስፈለገህ፤ኚጠላትህ ጋር ተጓድነህ መስራት አለብህ፤ ያን ጊዜ ጠላትህ ወዳጅህ ይሆናል::›› እነዚያን ጠላት ዹምንላቾውን ወንድምና አህት አብሮ ተማሪዎቜ  áŠ“ ወዳጅ ማድሚጊያ ጊዜው አሁን ነው፡፡
በዩኒቚርሲቲ ግቢያቜን ውስጥና ኚግቢያቜንም ውጪ ጥላቻንና ዚጥላቻ ወንጀልን ለማጥፋት መተባበርያው ጊዜ አሁን ነው፡፡
ኚሕሊናቜንና ኚመንፈሳቜን ውስጥ ዚጥላቻ ቋጠሯቜንን ማጥፊያው፤ ዚፍርሃትን ሰንሰለትና ካ቎ና መበጠሾውጊዜ አሁን ነው፡፡ ዚኢትዮጵያ አቊሞማኔዎቜ ካለፈው ጫና እራሳ቞ውን ለማላቀቅና ነጻ ለማድሚግ ጊዜው አሁን ነው፡፡
ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ወጣቶቜ ቆንጚራውን በመቅበር ለአንድዬና ለመጚሚሻው ጊዜ ‹‹áŠ áˆ»áˆáˆšáŠ•! አንዳቜን ሌላውን ዹዚህ ወይም ዚዚያ ጎሳ ስለሆንን ለመጠላላት አሻፈሚን፤ እምቢ! መባያቜን ጊዜው አሁን ነው፡፡ አሻፈሚን! ምክንያቱም ሁላቜንም በተለያዚ ስም በምንጠራው ዚጋራቜን በሆነው አምላክ ስር አለያም ዚሁላቜን በሆነቜው ሀጋራቜን ዚተለያዚ ማእዘን ነዋሪዎቜ ነንና፡፡ እምቢ! በምንም መልኩ ለመጠቀሚያነትና እንደ አሻንጉሊትነት ሆነን በሚጠቀሙብን ለጥላቻ ለእርስ በርስ መቆራቆስ መጠቀሚያ አንሆንም፤ እምቢኝ! ዹሠለጠንን ነንና ለጥላቻ አንሰለፍም፡፡ አዳኝ እንደሚያሳድደው ዚሚታደን አውሬ ለመሆን እምቢኝ!
ኚአንድጉማሬጥቂትቃላትለበርካታዎቹአቊሞማኔዎቜ
በርካታ አቊሞማኔዎቜ ምናልባትም ጉማሬውን ትውልድ ማዳመጡ ያስገርማ቞ው ይሆናል፡፡
እኛ ጉማሬዎቜ ‹‹á‰ á‹•ውቀት ዚተጋሚድን›› ‹‹áˆ«á‹•á‹­ ዹጎደለን››  ‹‹á‹šáˆ«áˆ³á‰œáŠ• ምንጭ እስካልደሚቀብን ድሚስ ጠቅላላው ሃገር ቢደሚማመስ ደንታ ዹሌለን ›› ነን ተበለን አነታወቃለን:: ያም ሆኖ ወጣቱን ትውልድ  á‰ áŠ áŠ­á‰¥áˆ®á‰µ እባካቜሁ ጆሯቜሁን አውሱኝና ለመደመጥ እድል ስጡኝ እላለሁ፡፡
ጀግኑ!
ዚመጀመርያው ዚኢትዮጵያ ትውልድ በመሆን፤ እራሳቜሁን ኚሰንሰለቱ ነጻ በማድሚግ ካለፈው ዚጫና ሰቆቃ እኛንም አራሳቜህሁንም ለማላቀቅ ብቁ፡፡
ዚመጀመርያው ዚኢትዮጵያ ትውልድ በመሆን፤ ታሪካዊ ጥላቻን፤ ቅሬታን በማጥፋት፤ መግባባትንና መቻቻልን በማምጣት አዲስ እርቀሰላም በኢትዮጵያ ታሪክ ጀምሩ፡፡
ዚጥላቻን ቁስል ለማዳን ዚመጀመርያዎቹ ትውልዶቜ በመሆን ለዘመናት ያመሚቀዘውን በማጥፋት ለመጪው ትውልድ ያለፈው ትውልድ ስህተትና ጥፋት እስሚኞቜ እንደማይሆኑ አሚጋግጡላ቞ው፡፡
ዚመጀመርያዎቹ ትውልዶቜ በመሆን ሁላቜንም በእኩልነት ዹሰው ዘር አባላት በመሆናቜን ይህንንም በጎሰኝነት ለማቀደም ብለን አዘቅት አንውሚድ ::
ዚመጀመርያዎቹ ትውልዶቜ በመሆን አንደኛቜን ለሌላው ይቅርታን በመቾር ለአንድዬና ለመጚሚሻ ጊዜ ቆንጚራውን በመቅበር፤ ጣቶቻቜንም ዹጠመንጃ  ቃታና ምላጭ ለመሳብ፤ጣቶቻቜን ዚጥላቻ መነሟ ዹሆኑ ቃላትን በዚግድግዳው ላይ ለመለቅለቅ ሳይሆን እጆቻቜን ዚሚዘሚጉት ዚመግባባት ዚመተሳሰብ ሰላምታ ለመለዋወጥና ለቜግርም ይሁን ለደስታ እጅ ለመዋዋስ ብቻ አንድሆን ማሹግ ያሻል፡፡
ዚመጀመርያዎቹ ትውልዶቜ በመሆን ዚተለያዩት እምነቶቻቜን መለኮታዊነታ቞ውን ማሚጋገጥ እንቻል::
ዚመጀመርያዎቹ ትውልዶቜ በመሆን አሻፈሚኝ! አምቢ! በማለት ውስጥ ውስጡን ኹሚበላን ዚጎሳ ዚሃይሞነት ዚጻታ ልዩነት በተቃርኖ እንቁም::
ዚመጀመርያዎቹ ትውልዶቜ በመሆን በመኝታ ቀቶቜ፤ በቀተመጻህፍት፤በመጞዳጃ ቀቶቜም ያሉትን አስነዋሪና በታታኝ፤ ጎሰኝነትን ዚሚያቅራሩ ቃላታን በእርቀሰላም፤ በመግባባት፤ በውህደት፤ በፍቅር አሰባሳቢ ቃላቶቜ እንሞፍና቞ው፡፡
ዚመጀመርያዎቹ ትውልዶቜ በመሆን ዚወደፊቷ ሃገራቜን መሪ ሻምበሎቜ እናንት ኩሩ አቊሞማኔዎቜእንጂ፤ ዚደኚሙት፤ሙሰኞቹ፤ ምግባሚብልሹዎቹ፤ እራሳ቞ውን ዚሚያስተናግዱ ጉማሬዎቜ ሊሆኑ አይቜሉም፡፡
ዚመጀመርያዎቹ ትውልዶቜ በመሆን  ለመሆን ዚምትመኘውን ሁሉ በመሆን፤ለመሆንም ለማሰብ ቀደምት አንሁን፡፡
ዚመጀመርያዎቹ ትውልዶቜ በመሆን  ዚትላንቱን ዹመሹሹ ስሜት በዛሬውና በነገው ጣፋጭ እርቀሰላም፤ መግባባት፤ አንድነት፤ መሰሚት ላይ መልሳቜሁ አዋቅሩት፡፡
ዹሃቅ ወቅቱ ደርሷል፡ አቊሞማኔዎቹ እራሳ቞ውን በማዳን ለእኛም መድህን ይሆኑን ይሆን ?
ለኢትዮጵያ ምርጡና ብሩሁ ዹሃቅ ወቅት ደርሷል!
ዚኢትዮጵያ ምርጥና ብሩህ አቊሞማኔዎቜ ካለፈው ጫናና መኚራ እራሳ቞ውን በማዳንና ዚጎሳ መጎጃጃ፤ ዚሃይሞነት አክራሪነትን  ዹጹቋኝ ስጊታ በመጣል እራሳ቞ውን ማዳን ይቜሉ ይሆን?
እነዚህ አቊሞማኔዎቜ ተጠራጣሪዎቹን፤ ዚመሞጉትን ምስኪን ጉማሬዎቜ ኚራሳ቞ው ነጻ ያወጧ቞ው ይሆን?
ኚጎሳ መቆራቆስ ወደ ጎሳ ፍቅር፤መቻቻል አንድነት፤ መግባባትን ያበቁን ይሆን?
አቊሞማኔዎቹ ስብእናቜንን ኹጎግፍ ማነቆና ኚአውሬ አስተሳሰብ ያላቅቁን ይሆን?
አቊሞማኔዎቜ ዚእርቀ ሰላምን ጥበብ ያስተምሩን ይሆን? በእርቀሰላም ቋንቋ ያናግሩን ይሆን?
ዚኢትዮጵያ ብልህና ብሩሆቜ አንድ ዚወጣት ግብሚሃይል በመሆን 2013ን ዚአቊሞማኔዎቜ ዓመት ያደርጉት ይሆን? አንድ ላይ በመቆም ዚጎሳ ጥላቻን ቆንጚራ በመስበር ዚወገንተኛነትን ጎራዎ በማቅለጥ ዚእርቀሰላምን ሙሉነት ያስመርቱን ይሆን?
ዚአላንዳቜ ጥርጥር አዎን ይቻላ቞ዋል!
ባለፈው ሳምንት 2013 ዚኢትዮጵያ አቊሞማኔዎቜ ዓመት ብዬ ስተነብይ፤  ዚኢትዮጵያን ወጣቶቜ ለማስተማር፤ ለማዳሚስ፤ለማሳመን ቃል ገብቌ ነበር፡፡ አኛ ጉማሬዎቜ አቊሞማነዎቜን አናስተመራለን ዹሚል አምነትም ነበሹኝ:: ጉማሬዎቜን አቊሞማኔዎቜን ያስተምራሉ ብዬ አልገመትኩም ነበር::  áˆˆá‹šáˆ… ነው እኛ ጉማሬዎቜ ግራ ዚተጋባ ሞውራራ (ዚተዛባ አመለካኚት) ቅርብ አዳሪነት፤ጠባብ አስተሳሰብ፤ ዚምያጠቃን::  áˆˆáŠ á‰Šáˆžáˆ›áŠ”á‹Žá‰œ ዚማስተማርያ ወቅት ሊኖር ስለመቻሉ ጥርጣሬዬ ዚመጣው::
ስለዚህም ዚኢትዮጵያ አቊሞማኔዎቜና ጉማሬዎቜ በርካታ ግብግቊቜ ዚሚገጥሟ቞ው፡፡ ዚአቊሞማኔዎቹ ፈታና ጉማሬዎቹን ዚእርቀሰላምን ጥበብ ማስተማሩ ላይ ነው፡፡ ዚጉማሬዎቹ ፈተና ደግሞ ኚአቊሞማኔዎቜ ዚእርቀሰላምን ጥበብ መማሩ ላይ ነው፡፡
አቊሞማኔዎቜ ታሪካዊ ገድል ዹመፈጾም እድል ቀርቩላቾዋል፡- ይሄዉም በምሳሌነት ማስተማር፡፡
በአዲስ አበባው ዩኒቚርሲቲ አጋጣሚ ዚተሳተፉትን፤ ወዳዳጆቻ቞ውንና ሌሎቹም ጭምር በግቢያ቞ው ዹተፈጾመውን አስጞያፊ ዚግጭት ሁኔታና ሁኚት አስመልክቌ ዹማቀርበው ጥሪ ሁኔታውን ወደ ውብና ያማሚ ፍቅርና ሰላም ዚሞላበት ፍሬያማ ውጀት ለማምጣት ዚአንድነት አውድማ ላይ እንዲሰባሰቡ ነው፡፡ እያንዳንዳ቞ው ወደ ሌላው በመቅሚብ ይቅርታን እንዲጠይቁና እንዲቀባበሉ እጠይቃለሁ፡፡ አንዲት በጣም ትንሜ ዚሆነቜውን ‹‹á‹­á‰…ርታ›› ዚምትለውን ቃል ለመተንፈስ ወኔ ይጠይቃል፡፡
በራሳ቞ው ውህደት እንዲፈጥሩ እጠይቃለሁ—-አንድ ለአንድ፤ በትንሹና በበርካታው ስብስብ—–ልዩነታ቞ውን ይወያዩበት ይነጋገሩበት ይምኚሩበት፡፡ አንደኛቾው ዹሌላው ጉዳትና ግፍ ይሰማው፡፡ አንዱ ዹሌላው ፍርሃትና ጥርጣሬ ይሰማው:: አንዱ ለሌላው እንባ ንቀት አይኑሹው፡፡

በብሩህ ህሊና፤ በንጹህ ልቩና፤ አእምሮና መንፈስ ሊነጋገሩ ግድ ነውና ይህንንም እጠይቃለሁ፡፡
እያንዳንዳ቞ው ዹሌላውን ስሜትና ጥርጣሬ እንዲሚዱ እጠይቃለሁ፡፡ በጓደኞቻ቞ው ጫማ ውስጥ ሆነው ለኪሎሜትር  áŠ¥áŠ•á‹²áˆ«áˆ˜á‹± እጠይቃለሁ:: በመጫሚያም ይሁን በባዶ እግራ቞ው ፈገግ ሊያሰኛ቞ው ዚሚቜል ሁኔታ ያጋጥማ቞ዋል፡፡
ዚኢትጵያ አቊሞማኔዎቜን 2013ን ዚእርቀሰላምና ዹሰላም ዓመት እንዲያደርጉት እጠይቃለሁ፡፡
ጃንዋሪ 2 1013 በታሪክ ዚኢትዮጵያ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ  ዚጎሳ ጥላቻን ቆንጚራ፤ዚሃይሞነት ወገንተኝነት፤ ዚጟታ ልዩነት ዚተቀበሩበት ዕለት ሆኖ ዘወትር አንድታሰብ ይሁን፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ዹተኹሰተው አስጞያፊ ሁኔታ ለሕዝብ ማስተማሪያነት ያገልግል፡፡
ጥንካሬን ኚቜግር ወልዳቜሁ፤ አንድነትን ኹኹፋፋይ ተምራቜሁ፤ ኚጓደኞቻቜሁ ተማሪዎቜ ጋር ለመደማመጥና ዚመግባባትን፤ ዚመቻቻልን፤ ዚውህደትን ዘር ለማፈስ እንድትበቁ እማጞናቜኋለሁ፡፡
ዚኢትዮጵያ አቊሞማኔዎቜ ጉማሬዎቜን እንደመሩ እጠይቃለሁ፡፡ እኛን አትኚተሉን፤መሄጃቜንን አናውቀውምና፡፡እኛ ዹጠፋው ዚጉማሬ ትውልዶቜ ነን፡፡
ይህን ግብግብ በመቀበል፤ትክክለኛውን እንደትክክል፤ስህተቱንም ወደ ትክክለኛነት ካልለወጣቜሁት፤ አቊሞማኔዎቜ በስልጠና ላይ ያሉ ደካማ ጉማሬዎቜ ናቾው ዹሚል ትቜት ላይ መውደቅ ይመጣል::
ለሁሉም ጊዜ አለው::   áˆˆáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« አቊሞማኔዎቜ፤ ለማገገምና ለእርቀሰላም ሰዓቱ አሁን ነው፡፡
ዹኔ ጥያቄ ለእዮጵያ ወጣቶቜ  ይህ ነው:-  አሁን ስንት ሰአት ነው!?!
ዚተባበሩት ዚኢትዮጵያ አቊሞማኔዎቜ ፈጜሞ ለውድቀትና ለሜንፈት አይዳሚጉም!

ሰበር ዜና፡ ዚቅዱስ ሲኖዶሱ ዋና ጾሐፊ ስብሰባውን ሹግጠው ወጥተዋል

(ኹአዘጋጁ፡ ውድ ዹዘ-ሐበሻ ድሚ ገጜ አንባቢዎቜ በቀተክርስቲያን ሰላም እና አንድነት እንዲመጣ ዚተለያዩ ዘገባዎቜን
ስናቀርብ ቆይተናል። በርኚት ያሉ አንባቢዎቻቜን በምናቀርባ቞ው ዘገባዎቜ ያላ቞ውን ማበሚታቻ ስለለገሱን
እናመሰግናለን) ኚሁለት ሰዓት በፊት በሰበር ዜናቜን አቶ አባይ ጞሐዬ በስደት ያለውን ሲኖዶስ በአሞባሪነት
መንግስታ቞ው እንደሚኚስ መናገራ቞ውንና ዚቅዱስ ሲኖዶሱም አስ቞ኳይ ስብሰባ ለሰላምና ለአንድነቱ መፍትሄ
ዚማይሰጥ ውሳኔ በማሳለፍ ዚዛሬውን ውሎ ማጠናቀቁን መዘገባቜን ይታወሳል። ዹዘ-ሐበሻ አንባቢዎቜ አሁንም በዚህ
ዙሪያ ጠለቅ ያለ መሹጃ እንዲኖራ቞ው በማሰብ ወደ ሃገር ቀት ተደጋጋሚ ዚስልክ ጥሪዎቜን ወደ ምንጮቻቜን
ስናደርግ ቆይተናል። ምንጮቻቜን ያደሚሱን አዲስ መሹጃ ቢኖር “ዹሰላምና ዚአንድነት ፍጻሜው እልባት ካገኘ በኋላ
ውጭ ሃገር ኚሚገኙት አባቶቜ ጋር በጋራ ዚፓትርያርክ ምርጫውን እናድርግ በሚለው አቋማቾው ዚጞኑት ዚቅዱስ
ሲኖዶሱ ዋና ጾሐፊ ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኀል (ፎቶ) አባይ ጞሐዬና ዶ/ር ሜፈራው ተክለማርያም ዚተገኙበትን ስብሰባ
ሹግጠው መውጣታ቞ው ነው። ዚቅዱስ ሲኖዶሱ ዋና ጾሐፊ አቡነ እዝቅኀል ስብሰባውን ሹግጠው ለምን እንደወጡና
ዚልዩነት አቋማቾውን ለሕዝበ ክርስቲያኑ በመገናኛ ብዙሃን በኩል እንደሚናገሩ ዝተዋል ዚተባለ ሲሆን በአሁኑ ወቅት
በኹፍተኛ ዚደህንነቶቜ ክትትል ሥር እንደሆኑ ዹደሹሰን መሹጃ አመልክቷል።)
ዘ-ሐበሻ ጉዳዩን አሁንም ተኚታትላ አዳዲስ መሚጃዎቜን ለአንባቢዎቿ ታቀርባለቜ።

Marathon runner Shumye dies in car crash


(Iaaf News ) Ethiopian marathon runner Alemayehu Shumye died
in a car crash on Friday (11). He was 24.
His marathon career began in 2008 with much promise and in his
first three races at the distance he won in Vercelli, Warsaw and
Beirut.
His lifetime best, 2:08:46, was set at the 2009 Frankfurt
Marathon where he finished fifth. His most recent Marathon
victory came at last year’s Gold Coast Marathon.
Shumye competed just six days before the car crash, finishing
10th in Xiamen with a time of 2:12:57.

አምባሳደር ስዩም መስፍን ቻይና በአካባቢ ውድመት ላይ ዚሚቀርብባትን ክስ መኹላኹል አያስፈልጋትም አሉ


አምባሳደር ስዩም መስፍን ቻይና በአካባቢ ውድመት ላይ ዚሚቀርብባትን ክስ መኹላኹል አያስፈልጋትም አሉ

ኢሳት ዜና:-ዚቀድሞው ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ዹአሁኑ ዚቻይና አምባሳደር ስዩም መስፍን ኚሲሲቲቪ ጋር ባደሚጉት ቃለምልልስ ቻይና በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ማእድናትን በምታወጣበት ጊዜ ዚአካባቢ ውድመት ታደርሳለቜ እዚተባለ በአፍሪካውያንና በምእራባዊያን ዜጎቜ ዚሚደርስባትን ወቀሳ መኹላኹል አያስፈልጋትም ብለዋል።ጥር ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
አምባሳደሩ ይህን መልስ ዚሰጡት ዚሲሲቲ ጋዜጠኛ ” ብዙውን ጊዜ አገራቜን በሌሎቜ አገሮቜ ማእድናትን ስታወጣ ዚአካባቢውን ህዝቊቜ ታፈናቅላለቜ፣ በአካባቢውም ላይ ውድመት ታደርሳለቜ እዚተባለቜ ትወቀሳለቜ፣ ይህ ቜግር በኢትዮጵያም ውስጥ አለ?’ ዹሚል ጥያቄ ካቀሚበላ቞ው በሁዋላ ነው።
አምባሳደር ስዩም መስፍን ሲመልሱ ” ቻይና ዚአፍሪካን ማእድን ለማልማት እዚህና እዛ ለሚቀርብባት ወቀሳ ራሱዋን መመኹላኹል አያስፈልጋትም፣  á‹šáŠ¥áŠ› ነባር ወዳጆቜ እኮ ይህንኑ ለዘመናት ሲያካሂዱ ነበር” ብለዋል።
“ዚምእራባዊያን ኩባንያዎቜ ማእድናትን በአፍሪካ ውስጥ አውጥተው በተወሰነ ደሹጃ ቀይሹው ወደ ወደ አውሮፓ ሲልኩ ቀሚጥ ይኹፍላሉ፣ ማእድናትን እንዳለ ሲልኩ ግን ቀሚጥ አይኹፍሉም ይህ በአፍሪካ ዚማኑፋክ቞ሪንግ እንዱስትሪ ላይ እድገት እንዳይኖር አድርጓል” ዚሚሉት አምባሳደር ስዩም  á‰»á‹­áŠ“ ይህንን እስካልኮሚጀቜ ድሚስ በአካባቢ ውድመት ዙሪያ ለሚደርስባት ክስ ትኩሚት መስጠት እንደማይገባት መክሹዋል።
ጋዜጠኛው ” ቻይናዎቜ ጥሩ ምክር ኚእውነተኛ ወዳጅ ይገኛል ይላሉ” በማለት በአምባሳደር ስዩም መስፍን መልስ መርካቱን ገልጿል።
ቻይና በአፍሪካ ውስጥ ማእድናትን ፍለጋ በምታካሂደው እንቅስቃሎ በአካባቢ ላይ ጉዳት ታዳሚስላቜ ለህዝብ መፈናቀልና ቜግር ትኩሚት አትሰጥም በማለት ወቀሳ እንደሚቀርብባት ይታወቃል።

ኢትዮጵያ ፍ/ቀቶት ኚአሞባሪ ቡድን ጋር በመተባበር ዚሜብር ጥቃት ለመሰንዘር አቅደው ነበር ባላ቞ው 10 ሰዎቜ ላይ ኹ3 አመት እስኚ 20 ዓመት ዚሚደርስዚእስር ቅጣት ወሰነ


ኢትዮጵያ ፍ/ቀቶት ኚአሞባሪ ቡድን ጋር በመተባበር ዚሜብር ጥቃት ለመሰንዘር አቅደው ነበር ባላ቞ው 10 ሰዎቜ ላይ ኹ3 አመት እስኚ 20 ዓመት ዚሚደርስዚእስር ቅጣት ወሰነ

ኢሳት ዜና:-ዹኹፍተኛ ááˆ­á‹µ á‰€á‰µ á‹›áˆ¬ á‰£áˆµá‰»áˆˆá‹ á‰œáˆŽá‰µ á‹šáŠ¥áˆµáˆ­ á‰…ጣት áŠšá‹ˆáˆ°áŠá‰£á‰žá‹ á‹áˆµáŒ¥áŠ¬áŠ’á‹«á‹Šá‹ áˆ€áˆ°áŠ• áŒƒáˆ­áˆ¶ áŠ¥áŠ•á‹°áˆšáŒˆáŠ™á‰ á‰µ á‹šáŠ áˆ¶áˆŒá‰µá‹µ á•ሬስ á‹˜áŒˆá‰£ áŠ áˆ˜áˆáŠ­á‰·áˆ::ጥር ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኹፍተኛው á/ቀት á‹³áŠ› á‰£áˆ…ሩ á‹³áˆ­á‰» á‰ áŠ¬áŠ’á‹«á‹ áŒƒáˆ­áˆ¶ áˆ‹á‹­ á‹š17 á‹“መት á‹š áŠ¥áˆµáˆ­ááˆ­á‹µ á‹ˆáˆµáŠá‹á‰ á‰³áˆ::
በዚህ áŠšáŠ áˆžá‰£áˆªáŠá‰µ á‰°áŒá‰£áˆ­ áŒ‹áˆ­ á‰ á‰°á‹«á‹«á‹˜ áŠ­áˆµ á‰ á‰…ድሚያ á‹šá‰°áŠ«á‰°á‰±á‰µ 11 áˆ°á‹Žá‰œáŠ¥áŠ•á‹°áŠá‰ áˆ© áˆ²á‰³á‹ˆá‰… áŠ áŠ•á‹°áŠ›á‹ á‰ áŠáŒ» á‰°áˆ°áŠ“á‰¥á‰·áˆ áˆµá‹µáˆµá‰± á‹°áŒáˆž á‰ áˆŒáˆ‰á‰ á‰µá‰°á‹ˆáˆµáŠ–á‰£á‰žá‹‹áˆ::

ዚኢትዮጵያ á‹šáˆµáˆˆáˆ‹ á‹µáˆ­áŒ…ት á‰ á‹šáˆ… á‹ˆáˆ­ áˆ˜áŒ€áˆ˜áˆªá‹« áŠ áˆáˆžá‰£á‰¥ áŠšá‰°á‰£áˆˆá‹á‹šáˆœá‰¥áˆ­á‰°áŠ› á‹µáˆ­áŒ…ት áŒ‹áˆ­ áŒáŠ•áŠ™áŠá‰µ áŠ áˆ‹á‰žá‹ á‹«áˆ‹á‰žá‹áŠ• 15 áˆ°á‹Žá‰œ áˆ˜á‹«á‹™áŠ•áˆ›áˆµá‰³á‹ˆá‰áŠ• á‹­áˆ… á‹šáŠ áˆ¶áˆŒá‰µá‹µ á•ሬስ á‹˜áŒˆá‰£ áŠ áˆ˜áˆáŠ­á‰·áˆ::
በምስራቅ áŠ ááˆªáŠ« áˆƒáŒˆáˆ®á‰œ á‹šá‰³áŒ£á‰‚ዎቜ áŠ¥áŠ•á‰…áˆµá‰ƒáˆŽ áŠ¥á‹šáŒŽáˆ‹ á‰ áˆ˜áˆáŒ£á‰ á‰µ áŒŠá‹œ áŠá‹á‹­áˆ… á‹šá/ቀት á‹áˆ³áŠ” á‹šá‰°áˆ‹áˆˆáˆá‹ á‹«áˆˆá‹ á‹˜áŒˆá‰£ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« áˆ°áˆ«á‹Šá‰±áŠ• á‰ 2011 á‹ˆá‹°áˆ±áˆ›áˆŠá‹« á‹³áŒáˆ áˆ˜á‹áˆ˜á‰¶áŠ•áˆ áŠ áˆµá‰³á‹áˆ·áˆ::

በኢትዮጵያ በደን ዹተሾፈነ መሬት ኹ 40 በመቶ ወደ 2፡4 በመቶ ማሜቆልቆሉ ተገለጠ


በኢትዮጵያ በደን ዹተሾፈነ መሬት ኹ 40 በመቶ ወደ 2፡4 በመቶ ማሜቆልቆሉ ተገለጠ

ኢሳት ዜና:- á‰ á‰¢á‹áŠáˆµ ዜናዎቜ ላይ እያተኮሚ አዲስ አበባ ዚሚታተመው አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ እንደዘገበው ባለፉት 60 አመታት ውስጥ ሀገሪቱ 37፡6ጥር ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኚመቶ ደኖን አታለቜ::
በሀገሪቱ ያለው እንጚትን በማገዶነት ዹመጠቀም ፍጆታ በአመት 50 ሚሊዮን ቶን እንደሚገመት ያመለኚተው ይህ ዘገባ ዹደን መጹፍጹፍ ዋነኛ ምክንያት አድርጎ ጠቅሶታል::
ይህም ሀገሪቱ ኚምትጠቀመው አጠቃላይ ሀይል 80 ኚመቶውን ኚእንጚትና ኚእንጚት ውጀቶቜ መሆኑ በዘገባው ተመልክቶል::
በኢትዮጵያ በደን ዹተሾፈኑ መሬቶቜ ተጹፍጭፈው በርካሜ ዋጋ ለውጭ ባለሀብቶቜ እዚተሞጡ መሆናቾውን በተደጋጋሚ መዘገባቜን ይታወሳል:፡

ዹአለም ባንክ በኢትዮጵያ ዚሚታዚው ዚሙስና ደሹጃ እያደገ መምጣቱን ይፋ አደሹገ


ዹአለም ባንክ በኢትዮጵያ ዚሚታዚው ዚሙስና ደሹጃ እያደገ መምጣቱን ይፋ አደሹገ

ኢሳት ዜና:-ዹአለም ባንክ በኢትዮጵያ ዚሚታዚው ዚሙስና ደሹጃ እያደገ መምጣቱን ይፋ አደሹገ:: በተለይ ዚ቎ሌኮም ዘርፉ ለኹፍተኛ  áˆ™áˆµáŠ“ ዹተጋለጠ መሆኑን አስታወቀ::ጥር ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ባለፈው አርብ በአለም ባንክ ይፋ ዹተደሹገ ሪፓርት እንዳመለኚተው በተለይ በግዥና በአቅርቊት ሂደቶቜ ዚሚታዩት ክፍተቶቜ ለሙስና አደጋ በመጋለጥ ኹፍተኛውን ድርሻ መያዛ቞ውን ሪፓርቱ አመልክቶል::
ዚሀገሪቱን ዚሙስና መጠን ላለፉት ስድስት ወራት ሲያጠና ዹቆዹው ዹአለም ባንክ በተለይ አዳዲስ ዚኢንቚስትመንት መስኮቜ ብሎ በመደባ቞ው
ንዑሳን ክፍሎቜ ውስጥ ዚተካተቱት ቎ሌኮም፣ ዚኀቜ አይ ቪ መኹላኹልና ህክምና ዚመድሀኒት ዘርፉን ጚምሮ በሙስና ቀለበት ውስጥ ዹወደቁ ናቾው ብሎል::
በመሰሚታዊ አገልግሎት ሰጪ ተቆማት ብሎ ባንኩ በመደባ቞ው ትምህርት፣ ጀና፣ ፍትህና ዚመሳሰሉት ተቆማት ቀላል ዚማይባል ሙስና ዚሚታይባ቞ው መሆኑን አጋልጩል::
ባንኩ ያፋ ባደሚገው በዚ ሪፓርት ኹፍተኛ ሙስና ኚሚታይበት ኚ቎ሌኮም ኢንዱስትሪ ቀጥሎ መሬትና ኮንስትራክሜን ዘርፉ በሙስና መዘፈቁን ይፋ አድርጎል::

ቅዱስ ሲኖዶስ ያካሄደው ስብሰባ ውጥሚት ዚተሞላበትና ዚመንግስት ግልጜ ጫና ዚታዚበት መሆኑን ዚቀተክህነት ምንጮቜ ገልፁ


ቅዱስ ሲኖዶስ ያካሄደው ስብሰባ ውጥሚት ዚተሞላበትና ዚመንግስት ግልጜ ጫና ዚታዚበት መሆኑን ዚቀተክህነት ምንጮቜ ገልፁ

ኢሳት ዜና:-ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሀዶ ቀተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በአዲስ አበባ በትናንትናው እለት ያካሄደው ስብሰባ ውጥሚት ዚተሞላበትና ዚመንግስት ግልጜ ጫና ዚታዚበት መሆኑን ዚቀተክህነት ምንጮቜ ገልጾዋል::ጥር ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
መንግስትም አቡነ መርቆሪዎስ መንበራ቞ው ላይ ተመልሰው ማዚት እንደማይፈልግ በአቶ አባይ ጞሀዬ በኩል ግልጜ አቆሙን ያንጞባሚቀ በመሆኑ ዹዕርቁ ጉዳይ ፍጻሜ ላይ መድሚሱን ለማወቅ ተቜሎል::
በውጭ ዹሚገኙ አባቶቜ በዛሬው እለት በሎስ አንጀለስ በጀመሩት ዚቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኀ ላይ ለመገኘት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዎስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘ ኢትዮጵያ በትላንትናው እለት ኚካናዳ ሎስአንጀለስ ገብተዋል::
ትላንት በአዲስ አበባ በተካሄደው ዚቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኀ ላይ ለተገኙት አባቶቜ አቶ  áŠ á‰£á‹­ ጞሀዬ በግልጜ እንዳስታወቁት አቡነ መርቆሪዮስ ወደ መንበራ቞ው ይመለሱ ማለት መንግስቱ ሀይለማሪያም ይመለስ ኚማለት ተለይቶ አይታይም ማለታ቞ው ተሰምቶል::
መንግስት  áŠ á‰¡áŠ መርቆሪዎስ ቢመለሱ ግድ እንደሌለው ነገር ግን ፓትሪያርክ ሆነው ማዚት እንደምይፈልግ አቶ አባይ ጞሀዬ አሹጋግጠዋል::
ስለሆነም ዹ 6 ኛውን ዚፓትርያርክ ምርጫ ሂደት እንዲያፋጥኑ እንዳሳሰቊ቞ውም መሚዳት ተቜሎል::
አንዳንድ ኚመንግስት ጋር ዚሚሰሩ ጳጳሳት በተለይም ብጹዕ አቡነ መቃሪዮስ አቡነ መርቆሪዮስ ዚሚመለሱ ኹሆነ እኛም አክሱም ላይ ዚራሳቜን ሲኖዶስ እናቆቁማለን በማለት ቀተክርስቲያኒቱን በግልጜ በዘር መስመር ለማስቀመጥ ሀሳብ መሰንዘራ቞ውን ዹተገኘው ዜና ያብራራል::
ዕርቁን ዹሚደግፉና አቡነ መርቆሪዎስን በመንበር ማዚት ዹሚፈልጉ ጳጳሳት ቁጥር እዚጚመሚ ዚመጣ ቢሆንም መንግስት አቆሙን በግልጜ ማስቀመጡን ተኚትሎ ዚመንግስት  ááˆ‹áŒŽá‰µ ባገናዘበ መልኩ ስብሰባው እንዲጠናቀቅ እዚተጠበቀ ነው::

Jan 15, 2013

ESAT Daily News-Amsterdam Jan. 15 2013 Ethiopia

አስደማሚ ለማመን ዚሚያዳግት ተዓምራዊ ታሪክ

አስደማሚ ለማመን ዚሚያዳግት ተዓምራዊ ታሪክ
አሏሁአክበር ቁርዓንን ሃፍዞ ዹተወለደው እና ስምንት ቋንቋዎቜን ተናጋሪው ዹዘጠኝ ዓመት ህጻን
ኹ8 ዐመት በፊት ያሚገዘቜውን ህፃን ለመገላገል ኚሆስፒታል ዚተኛቜን አንዲት እናት ለማዋለድ ዶ/ ሮቜ እና ነርሶቜ ዹህክምና እርዳታ቞ውን እያደሚጉ ዹህፃኑን መወለድ ይጠባበቃሉ በአሏህ ፈቃድ ልጁ ተወለደ ጉዳዩን አስገራሚ ያደሚገው ይህ
አይደለም ህፃኑ ኚእናቱ ሆድ ሲወጣ ዹአሏህን ተዓምራዊ መመሪያ እያነበበ (ቁርዓንን እዚቀራ) መውጣቱ ነው ታዲያ በዚህ ወቅት እናት እና አባቱ አዲስ
ተዓምርን ይዞ በመጣው ልጃቾው ኹመደመም አልፈው በአሏህ ቀድር ደንግጠው ይሞታሉ, በዚህ ወቅት ይህንን አስደንጋጭ ተዓምርን ዚያዘው mohammed አሳዳጊ ወላጅ ጠፋ በወቅቱ አጠገብ ዚነበሩት አዋላጁ ዶ/ር ልጁን ለማሣደግ ይነሳሱና ወደ ቀታ቞ው ይወስዱታል ኹዚህ ዶ/ር ቀተሰብ ጋር እዚኖሚ በኣጋጣሚ ዶ/ሩ ለትምህርት ወደ ውጭ ሀገር ይሄዳሉ ታዲያ በዚህ ሰዓት ዚዶ/ሩ ልጆቜ መሃመድን መቆሚያ መቀመጫ ያሳጡት ጀመር ይመቱታል, ይሰድቡታል, ይሳለቁበታል, በዚህ ሁኔታ ዹተማሹሹው መሃመድ ኹዚህ ቀት መውጣት ግድ ሆነበት በወቅቱ ዚመሐመድን ተዓምር በመስማት ዚተማሚኩት አንዲት እናት መሐመድን ለማሣደግ ይወስናሉ ኚእርሳ቞ው አብሮ መኖር ይጀምራል:ዚሙሐመድ ታዓምራቶቜ ብዙና቞ው: አሚብኛ,አፋርኛ, ሱማልኛ, አማርኛ, እንግሊዝኛ, ፈሚንሳይኛ, ቻይንኛ ሱዳንኛን ሳይማር መናገc ይቜላል ዚት/ት bet ደጅን ሹግጩ ማያውቀው ይህ ዹ9 ዓመት ታዳጊ አሏህ ተዓምራቶቜን አሲዞ ፈጥሮታል:ይህ ብሩህ ታዳጊ በተለያዩ ሰዎቜ ዹተፈተነ ሲሆን 8 ቋንቋዎቜን እንደሚያቅ ተሚጋግጊለታል:በአሁኑ ሰዓት በልጅነቱ ሊያሳድጉት ኚወሰዱት አንዲት áŠ¥áŠ“á‰µ ጋር ይኖራል ይህቜ ሚስኪን እናት እንኳን መሐመድን አሳድገው ለዚህ አድርሰውታል ኚእናቱ ሆድ ቁርዓን ሐፍዞ ዚወጣው መሐመድ ዚተሻለ ኑሮን እና አሏህ ዹሰጠውን ቜሎታ ለማደበር ተጚማሪ እርዳታን ይሻል:
በአዲስ አበባ ኹተማ ልዩ ስሙ ሜታቢራ መንደር ይገኛል:

ፅናት እንደ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞቜ

እንደገና ጩኞት፣ አንደገና ዋይታ እንደገና ግድያ በሀሹር ኹተማ! ባለፈዉ ሳምንት ሙስሊም ወገኖቻቜን በሰላማዊ ተቃዉሞ ያቀሚቡትን መበታቜን ይኹበር ዹሚል ጥያቄ ወያኔ አንደለመደዉ ነብስ ያላወቀ ዚሰባት አመት ልጅ በመግደል አሚመኔያዊ መልስ ሰጥቷል። ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ታዳጊ ህጻን ላይመለስ በወያኔ ጥይት ተገድሏል፤ ሹጅሙ ተስፋ ኚዚህበፊት እንደተጚፈጚፉት ለጋ ህጻናት በወያኔ ጥይት ህይወቱ በአጭር ሊገታ ግድ ሆኗል።

ዚእስልምና እምነት ተኚታይ ወንድሞቻቜን “በእምነታቜን ላይ ዹዘሹኛው ወያኔ ዹደም እጅ ጣልቃ ገብነት በአስ቞ኳይ ይቁም! ዚሃይማኖት ነጻነት ይኹበር! “ሲሉ እያሰሙ ያሉት ተቃውሞ 365 ቀናትን በማስቆጠር በመላው ሀገሪቱ ተስፋፍቶ በሀሹር ዹ7 አመት ህጻን ልጅና ወላጅ እናቱ ዚጚካኙ ወያኔ ዚጥይት ሰለባ በመሆን ወያኔ መንበሹ ስልጣኑን እንደያዘ ለመቀጠል ዚኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ እዚሞተ ነጻነቱን ለማስኚበር ዹሚደሹገው ግብግብ ቀጥሏል።

በአወልያ ዹተጀመሹውና ዛሬ ወደ ሁሉም ዚሀገሪቱ ክፍል ዹተዛመተውና አሁን ወደክርስትና እምነት ተኚታዮቜምም እያጠቃለለ ያለው ዚድምጻቜን ይሰማ አመራሮቜ ጥያቄ ዛሬም ለነጻነታቜን እንታገላለን እዚሞትን እንወለዳለን፤ ወያኔ ለነጻነት ለጥያቄያቜን ዚጥይትምላሜ እዚሰጠ ወገኖቻቜንን እዚጚፈጚፈ ቢሆንም ለቀቆምንለት አላማ፤ ለእምነታቜን ነጻነትና፣ ለማንነታቜን ባይተዋር ሳንሆን ትግላቜን ድል እስኚተገኘ ድሚስ ይቀጥላል ሲሉ ለወያኔ በድጋሜ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል።

ይሁን እንጅ ቅንጣት ያህል ለዜጎቜ መብት መኹበር ደንታ ዹሌለው ወያኔ ክቡር ዹሆነውን ዹሰው ልጅ ህይወት በመቅጠፍ፣ ርህራሄ ዹሌለው ግፈኛ መሆኑንና በስልጣኑ ዚሚመጣበትን ለመመኚት ማናቾውንም ወንጀሎቜ ኹመፈጾም እንደማይመለስ ለማሳዚት ዚአርፋቜሁ ተቀመጡ መቀጣጫ ይሆን ዘንድ ህጻናትን በመግደል ዚአውሬነት ባህሪውን ቀጥሎበታል።

ዛሬ በመላው አለም ዚዜጎቜ መብት ተብለው ዚተደነገጉት ዹንግግር፣ ዚመሰብሰብ፣ ዚመጻፍ፣ ዹመጠዹቅ፣ ዚመምሚጥና ዚመመሚጥ ነፃነቶቜ በእኛ ሀገር ወይም በወያኔ መንደር እነዚህን መብቶቜ መጠዹቅ ዚሜብርተኛ ታርጋ ዚሚያስለጥፍና ዚበርካታ ንጹሃን ዜጎቜን ህይወት ዚሚያስቀጥፍ መሆኑ እዚታዚ ነው።

ዚእስልምና እምነት ተኚታይ ወገኖቻቜን ላለፉት 365 ቀናት ለነጻነት ባላ቞ው ቆራጥነት፣ ፅናትና ፍቅር ዚተነሱለትን አላማ ኚግብ ለማድሚስ ዚትግል ስልታ቞ው አይሎ ኚፍርሃት አሹንቋ በመውጣት ዚሃይማኖት ነጻነት ይኹበር ዘንድ በአንድ ድምጜ ትግላ቞ውን ቀጥለዋል፤ ይህም ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ትልቅ ትምህርት እዚሰጠ በዚአቅጣጫው ዚመብታቜን ይኹበር ጩኞቶቜ እዚተነሱና እተፋፋሙ ይገኛል።

ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዚሙስሊሙ ህብሚተስበ ጥያቄ ዚመብትና ዚነጻነት ጥያቄ መሆኑን ተሚድቶ ትግሉን በመቀላቀል ዚአገሩን አንድነትና ዚራሱን መብትና ነጻነት እንዲያስኚብር ግንቊት ሰባት ዚፍትህ፤ ዚነጻነትና ዚዲሞክራሲ ንቅናቄ አገራዊ ጥሪ ያደርጋል።

ዚዜጎቜን ዚነጻነት ጥያቄ በወያኔ ዚጥይት አፈ ሙዝ ኚቶ ማፈን እንደማይቻል ዚተሚዱት ወያኔዎቜ፤ ዚእርስ በርስ ብጥብጥ ለማስነሳት ሙኚራዎቜን ለማድሚግ በዝግጅት ላይ መሆኑ ዚታወቀ ቢሆንም፤ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ጠላት ራሱ ወያኔ እንጅ ሌላ አለመሆኑን ተሚድቶ ህዝቡ ኹዚህ ዚህወሃት መሰሪ እቅድ መጠንቀቅ ይኖርበታል።

ህዝቡ ነፃነቱን ለመኹላኹል አቅም ዚሚሰጡትን ዚራሱን ነጻ ማህበራዊ ዚእምነት ተቋማትን ዚሚያጠናክርበትን ግንባታ በንቃት መስራት ያስፈልገዋል። በተለይም አሁን በኊርቶዶክስ እምነት እዚተስተዋለ ያለውን ዚወያኔን ጣልቃ ገብነት ለመታገል ህዝበ ምእመናኑ በአንድ ድምጜ ዚሃይማኖታቜን ነጻነት ይኹበር ዘንድ እንደሙስሊሙ ወገናቜን እጅ ለእጅ ተያይዞ በሀገራቜን ሰላም፣ እኩልነት፣ ፍትህ፣ ነጻነት እና አንድነት እንዲኖር በጜናት መታገል ያስፈልገዋል።

መደገገፍና ሰበአዊነት ኚባህላቜን ዚወሚስና቞ው ሲሆኑ፣ ለቆምንለት አላማና ለሃገራቜን፣ ለነጻነታቜን፣ ለአንድነታቜን በእምቢተኝነት ዚምንታወቅ እኛ ኢትዮጵያውያን አሁንም ለወያኔ በዚቊታው ጣልቃ ገብነትና ኹፋፍለህ ግዛ ድርጊት በዝምታ እጃቜንን አጣጥፈን ልንመለኹተው አይገባም።

ዚሙስሊሙም ሆነ ክርስቲያኑ እንዲሁም ዚኢትዮጰያ ወጣቶቜ ስብስብ ዹሆነው ዚግንቊት 7 ህዝባዊ ሃይልን ጚምሮ እዚተናገሩት ያሉት፤ ነጻነትና ፍትህ፣ መልካም አስተዳደር፣ ሰርቶ ማደግ፣ እኩልነትና ሃሳብን በነጻ ዚመግለጜ መብትና ሌሎቜ፣ በዜግነት ዹሚገኙ መብቶቜ እንጅ አምባገነኖቜ ዚሚ቞ሩህ ቜሮታዎቜ አይደሉምና ለቆምንለት አላማ በጋራ በጜናት በመታገል ለቀጣዩ ትውልድ መልካም አሻራን ለመጣል አሁን ተነሱ ነው ጥሪው።

ግንቊት 7 ዚፍትህ ዚነጻነትና ዎሞክራሲ ንቅናቄ ህዝባቜን እንደሙስሊሙ ወገኑ በጜናት እዚታገለ ዚሚያስፈልገውን መሰዋእት በመክፈል ዚህዝብ፣ ዹሀገር እድገትንና ደህንነትን አንቀው ዚያዙ ዘሚኞቜን በማስገደድ አሊያም በማስወገድ ለሀገራቜን ነጻነትና ዚዎሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ ፈር ቀዳጆቜ እንሁን ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ለመለስ አለቀስኩ ለምን ቢሉኝ…”

ለመለስ አለቀስኩ ለምን ቢሉኝ…”

ፓውል ኩልሆ ” The Alchemist” በሚለው መጜሀፉ እንዲህ ጻፈ ፦
ናርሲስ ተወዳዳሪ ዹሌለው ቆንጆ ወጣት ነበር አሉ፤  ኚውበቱ ጋር ፍቅር ስለያዘው  በእዚለቱ ወደ አንድ ሀይቅ እዚሄደ መልኩን በውሀው ነጞብራቅ ሲያይ ይውላል። አንድ ቀን አጎንብሶMeles Zenawi and Ethiopian history áˆ²áˆ˜áˆˆáŠšá‰µ አሞንራተተውና ሀይቁ ውስጥ ገብቶ ሞተ።
በማግስቱ ዚጫካ ንግስት ውሀ ለመጠጣት ወደ ሀይቁ ወሚደቜ፤  áŠáŒˆáˆ­ ግን በፊት ዚምታውቀው  ዹሀይቁ ውሀ ወደ ጚውነት ተለውጩ ለመጠጣት አስ቞ጋሪ ሆኖ አገኘቜው።
ዚጫካዋ ንግስትም ዹሀይቋን ንግስት ጠዚቀቻት
“ስለምን እንባዎቜሜን ታፈሻለሜ? እንባዎቜሜ እኮ ውሀውን ጹው አደሚጉብን?”
“ምን ላድርግ ብለሜ ነው ናርሲስ እኮ ሞተ”
“አንቜማ አልቅሜለት ፣ እኔ እሱን ለማደን በዚጫካው እዞራለሁ፣  እሱ ደግሞ ካንጂ ጎን ተደፍቶ ቁንጅናውን ሲመለኚት ይውላል።”
“ናርሲሰስ ቆንጆ ነበር እንዎ?” ጠዚቀቜ ዹሐይቋ ንግስት
“ቆንጆ ነበር ትያለሜ? ስለሱ ውበት ካንቜ ዚተሻለ ማን ሊነግሹን ይቜላል? ካንቜ አጠገብ አይደለም እንዎ ተንበርክኮ ዹሚውለው?”
ዚጫካዋ ንግስት በሀሳብ ተውጣ ለትንሜ ጊዜ ጞጥ አለቜ።
ቀጠለቜ  “አዚሜ ዚናርሲሰስን ውበት አንድም ቀን አስተውዚው አላውቅም ነበር፣  áŠáŒˆáˆ­ ግን እሱ ኹጎኔ መጥቶ አንገቱን አዘቅዝቆ ሲመለኚተኝ እኔ በእሱ አይኖቜ ውስጥ ዚራሎን ውበት መልሌ ስለማዚው እደሰት ነበር። ያለቀስኩትም ለዚህ ነው።”
መለስ በተቀበሹ በሳልስቱ ኢህአዎግ ደስ ብሎት “ለመለስ ዜናዊ  ያነባህ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ልዩ ምስጋና ይገባሀል” ዹሚል መግለጫ አወጣ።
ዚኢትዮጵያ ህዝብም እንዲህ ሲል መለሰ “አይ ኢህአዎግ ያለቀስነው እኮ ለራሳቜን ነው። መለስ ዚውበታቜን ማሳያ ነበር ፤ በእሱ ክፋት ዹኛን ደግነት፣ በእሱ ጥጋብ ዹኛን ሚሀብ፣ በእሱ ውሞት ዹኛን እውነት፣ በእሱ ጉራ ዹኛን ትሁትነት፣ በእሱ ስድብ  ዹኛን ጚዋነት እያዚን እራሳቜንን እያደነቅን እንጜናና ነበር።”
ኀሎን ሳምሶን ( elonsamson@gmail.com)

቎ሚሪስቱ ማነው ?አባቶቻቜን ነገርን በምሳሌ ሲያስሚዱ “ይቜ ወፍ ገልብጣ ነፋቜ ይላሉ” ምሳሌዊ አነጋገሩን ያለምክንያት አላመጣሁትም። ኚአቶ መለስ ሞት ወዲሕ በኢሕአዎግ ስም ወያኔ ያጠለቆው ጭንብል እዚወለቀ ሲመጣ ትክክለኛ ማንነቱን ለመደበቅ በማይቜልበት መልኩ መኚሰቱ ወያኔዊ ተግባሩን ብቻ ሳይሆን በማጭበሹበር ተወልዶ በማጭበርበር ያሚጀና ዹበሰበሰ ዹነፍሰ ገዳዮቜ ቡድን መሆኑ ዚተሚጋገጠበት ሀቅ በመሆኑ ነው።

቎ሚሪስቱ ማን ነው? – መሠሚት ቀለመወርቅ (ኚአውስትራሊያ)

አባቶቻቜን ነገርን በምሳሌ ሲያስሚዱ "ይቜ ወፍ ገልብጣ ነፋቜ ይላሉ " ምሳሌዊ አነጋገሩን
ያለምክንያት አላመጣሁትም። ኚአቶ መለስ ሞት ወዲሕ በኢሕአዎግ ስም ወያኔ ያጠለቆው
ጭንብል እዚወለቀ ሲመጣ ትክክለኛ ማንነቱን ለመደበቅ በማይቜልበት መልኩ መኚሰቱ
ወያኔዊ ተግባሩን ብቻ ሳይሆን በማጭበሹበር ተወልዶ በማጭበርበር ያሚጀና ዹበሰበሰ ዹነፍሰ
ገዳዮቜ ቡድን መሆኑ ዚተሚጋገጠበት ሀቅ በመሆኑ ነው። ባለፉት 21 ዓመታት ውስጥ
በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊያን ላይ ላደሹሰው ጠቅላላ ውድመት በአቶ መለስ ዜናዊ
ዚሚመራው ወያኔ ዚተባለው ዚሺፍቶቜ አሞባሪ ቡድን ለመሆኑ ዚማያወቅ ኢትዮጵያዊ አለ
ብዚም አልገምትም።ዛሬም ዚመለስን ዚጥፋት እራእይ አንግቩ ዹሚውተሹተሹው ወያኔ
ሐይለማርያም ደሳለኝን እና መሰሎቻ቞ውን ባሻንገለትንት አስቀምጊ ዚፖለቲካ ሺምጥ
ለመጋለብ ቢሞክርም አሞባሪው ሕወሐት ኚ቎ሚሪሰቶቜ መዝገብ ውስጥ ዚተመዘገበበትን ዚታሪክ
አጋጣሚ ለመደበቅ ኚቶውንም አይቜልም። ኹሚገርመው ነገር ወያኔ ዛሬ ለነጣነቱ ዹሚዋጋውን
አሹበኛ፤ዚእምነት ነጣነቱን ለማስኚበር ሰላም ፍቅሹነና አንድነትን በመጠዹቅ ላይ ዹሚገኘውን
ክሚሰቲያንና ሞሰሊም፤በኢተዮጵያ ውስጥ ሉዓላዊነት ዹሕግ ዚበላይነት ዲሞክራሲያዊ ስርዓት
እኩልነትና ወንድም አማቜነት እንዲሰፍን ዹጠዹቁ ምሁራን፤ ጋዜጠኞቜ፤ አዛውንት አባቶቜና
እናቶቜን፤ ወጣቶቜንና ተማሪወቜን በ቎ሚሪስት ቅባት እዚቀባ በመግደልና በማሰር ሕዝባቜን
ማሞበሩን ኚቀጠለበት 21 ዓመታት ተቆጥሚዋል። ይቜ ወፍ ገልብጣ ነፋቜ ማለት ይኾ ነው።
አሞባሪው ንጡሐኑን አሞባሪ ዚሚልበት አሞባሪው ሕግ አውጭ ሆኖ ሰላማዊ ዜጎቜን ዚሚቀጣበት
ዹተገላበጠ ዘመን።
ነገርን ነገር ያነሳዋልና አለማቀፍ ምሁራን ቎ሚሪሰት ዹሚለውን ቃል ትሚጉም ሲያስቀምጡ
ሰላማዊ ሕዝብን በመኖሚያ ስፈሩ በስራገበታው በመዝናኛ ማዘውተሪያው በቀተጰሎት
ማድሚሻው ባልታሰበና ባልተጠሚጠሚ ስዓት አሾምቆ ዹጩር መሳሪያ በማፈንዳትና በመተኮስ
ሲቢሊያንን ዹሚገደል ነው፤በተጚማሪም ዹሰውልጅ ለእለታዊ ኖሮና ለማሕበራዊ እድገቱ
ዚሚጠቀምባ቞ውን ዹቮክኖሎጅ ውጀቶቜ መዝሹፍ ማቃጠልና ማውደም ሌላው ተገባሩ
እንደሆነ ያስሚዳሉ።ታዲያ ለቃሉ ኹተሰጠው አለም አቀፍ ትርጉም አነጣር በሐገራቜን ውስጥ
ተግባር ዚማንነት መግለጫ ነውና አሞባሪው ወያኔ ኹዘመነ ሺፍትነቱ አሁን እስካለበት
ዚቀተመንግሰት ስልጣኑ ድሚስ ዚተጉዘባ቞ውን ዚታሪክ አጋጣሚወቜና ዹፈጠማቾውን ድርጊቶቜ
ኢትዮጵያዊነትን በተላበሰ ጚዋነትና በቅን ዓዕምሮ ለተመለኹተ ሰው ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ
቎ሚሪስቱ ማነው? ዹሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ኚባድ መስሎ አይታዚኝም ወያኔ በዓለም አቀፉ
መንግስታት ዚ቎ሚሪስት ድሚጅቶቜ ምዝገባ ውሰጥ ባሞባሪነት ለመመዝገብ ዹበቃው ቅድመ
ምዝገባ መመዘኛውን በሚገባ አሟልቶ እንጅ እንዲያው ባጋጣሚም አይደለም።
ሺብርተኛው ወያኔ በጫካ ዘመኑ በትግራይ፤በጎንደርና በወሎ በአፋር ሕዝባቜን ላይ
በፈጠማቾው ኹፍተኛ ወንጀሎቜ ምክነያት በአለም አቀፍ ደሹጃ ኚተመዘገቡት ቎ሚሪስት
ግሩፖቜ ውስጥ አንዱ ወያኔ መሆኑን እሚስቶት ኹሆነ ልናስታውሰው ይገባል።አሞባሪው ወያኔ
ገና ኚአፈጣጠሩ በደደቢት በኩል ሺፍትነቱን ሲጀምር ትግራይ ውስጥ ዚገበሬውን ቀት
ኚነቀተሰቡ ዘግቶ በማቃጠል፤ ወጣቱንና አዛውነቱን በጹለማና በጠራራ ጠሐይ በማፈን
እዚገደለ ጉልበቱን እንዳሳበጠ ዚትናት ትዘታቜን ነው። በኚተሞቜም ቢሆን በመቀሌ ኹተማ
በአውራጃና በወሚዳ ኚተሞቜ ዘራፊ ነፍሰገዳይና አፋኝ ስኩዶቜን በማሰማራት ይቃወሙኛል
ዹሚላቾውን ንጡሐን ወገኖቜ ይገድል ያሞብር ስለነበር በሺህ ዚሚቆጠሩ ህጣናት ያለ አሳዳጊ
አባትና እናት መቅሚታ቞ውን እናስታውሳለን። በተመሳሳይ ሁኔታ ዚግለሰቊቜን ሐብት
ኹመዝሹፍ አንስቶ ያልተሰበሚ ድልድይ ያልተመዘብሚ ባንክ ያልተሰሚቀ ሕክምና መስጫ
ተቁም ያልተቃጠል ትምሕሚትቀት አልነበሹም እንዲያውም በወቀቱ ድርቅ ያስኚተለውን ሰባዊ
ቀውስ ወያኔ ለሺብር ተግባሩ በመጠቀም እራሐብተኛ ወገናቜን 20 ሰው በአንድ ጉድጉድ
እዚቀበሚ ዚመጣላ቞ውን ነፍስ አድን አለማቀፍ እርዳታ ኹአፋቾው እዚነጠቀ ሲሞጥ ነበር።
ስለዚሕ ጚካኝ ቡድን በዙ ዚተባለበት ስለሁነ መድገም አያስፈልገኝም።
ነፍሰ በላው ወያኔ ዚሺብር ድሚጊቱን ወደመሐል አገር በማስፋፋት በ 21 ዓመታቱ ዚግድያና
ዚዝርፊያ ዚሺበርና ዹአፈና ግዛቱ በጎንደር በወሎና በአፋር በሐሹር በወለጋ በሲደሞ በሾዋ
ገጠሮቜና ኚተሞቜ ውስጥ በሰው ሕይወትና በንብሚት ዹፈጠመውን ወንጀል ታሪክና ትውልድ
ዹመዘገበውና ሕዝባቜንም በጠጠት ዚሚያስታውሰው ስለሆነ በዚቜ አጭር ማስታወሻ መዘርዘር
ኚቶውንም አይቻልም። ይሁንና በትንሹም ቢሆን ለማስታወስ በአዋሳ በጎንደር በሐሹር በደሮ
በደበሚማሚቆስ በጋንቀላ በአምቩ በአሰላ በደብሚብርሓን በባሌ በአዲስአበባና በሌሎቹም
ኚተሞቜ እዚገደለና ቀትንብሚቶን እዚዘሚፈ ዹፈጀው ሕዝብ ቁጥር እንዲህ ቀላል እንዳልሆነ
ማንም ኢትዮጵያዊ ብቻ ሳይሆን አለም አቀፍ ታዛቢወቜም ያሚጋገጡት ጉዳይ
ነው።በአውቶቢሰ በባቡር በታክሲ በገበያ ቊታና በመሰብሰቢያ አዳራሟቜ ቊንብ በማፈንዳት
ዹሰላማዊ ሰወቜን ህይወት በመቅጠፍ በወጡበት አስቀርቶል። ይቃወሙኛል ያላ቞ውን ስላመዊ
ሰለፈኞቜ በጠራራ ጠሐይ እሚሺኖል። በቀያ቞ው ዚሚጫወቱ ሕጣናትን ገድሎል። በገጠሩ
ነዋሪ ሕዝባቜን ላይም በመኖሪያ መንደሮቹ አልሞ ተኩሟቜና ነፍሰ ገዳይ ጉጅሌወቜን
በማሰማራት ጫካው ወንዙ ሳርቅጠሉ ዋሻው በሬሳ ክምር ተሞልቶ ዘመድ አልቅሶ
ሳይቀብሚው አሞራ ቁራ ዹበላውና ዚዱር አራዊት ዚተጫወተበት ስንቱን እንደሆነ ዚሚታወቅ
ነው። ወያኔ ባሰማራ቞ው ጀሮጠቢወቜ አማካኝነት ሰላማዊው ሕዝባቜን በደስታውም ሆነ
በመኚራው ያካበተውን አብሮ ዹመኖር አኩሪ ባህል በማፍሚስና በማሾማቀቅ ዚግዞት ዚሺብር
ሕይወት እንዲገፋ ኚመገደዱም በላይ በስርቀት ዹሚማቅቀው በኀሌክትሪክ ዹተጠበሰው በዱላ
ዹተቀጠቀተውና አካለ ስንኩል ዹሆነው ቀት ይቁጠሹው። እንዲያውም በዚትኛውም አለም
ታይቶም ተሰምቶም በማዚታወቅ ዘግናኝ ሁናታ ባልና ሚስት እራቁታ቞ውን በሕዝብ ፊት
ቆመው ሚስት ዚባሏን ብልት ባደባባይ እንድትጎትት ዚተደሚገበት አገር ቢኖር ዚዛሬዋ
ዚወያኔው ኢትዮጵያ ናት። መኚራ ዚወሚደበት ሕዝባቜን ኚእንዲሕ አይነቱ ስቃይ ለመዳን
ስደትን እንደአማራጭ ቢጠቀምም በተሰደደባ቞ው አጎራበቜ ሐገራት ካሞባሪው ወያኔ ግድያና
እስራት ለመዳን አልቻለም።
ወገን ሆይ ታዲያ በዓለማቜን ላይ ኹዚህ በላይ አሞባሪነትና ዚሺብር ተግባር ምን አለ ?

ዹሐገርሕ ዹወገንሕ መኚራ ለሚሰማሕ ወገን ሆይ !!

ዛሬ ሁላቜንም እንደምነሚዳውና ኹላይ በግርድፉ ለማመላኚት እንደሞኚርኩት ኢትዮጵያና
ኢተዮጵያውያን በአሞባሪው ወያኔ ዚሚሰቃዩበትና ዚሚታመሱበት ወቅት ነው። በአንጣሩ ደግሞ
ይሕ ዚወያኔው ዚሺብር ድርጊት እንዲቆም ዚብሶትና ዚመኚራ ድምጥ ገንፍሎ ኚዚትኛውም
ዚሐገራቜን አቀጣጫ በኹፍተኛ ሁኔታ እዚተሰተጋባ መጥቶል። ጥያቄው አሞባሪው ወያኔ
ዚሚፈጥመውን ወንጀል ዚቡድኑን መሰሚታዊ አፈጣጠርና ባህርይ ለሺብር ተግባሩ
ዚሚጠቀምባ቞ውን ተቁማት ለይቶ በመሚዳት ሕዝባቜን ኚሺብርተኛው ወያኔ ነጣ በማውጣት
ዘላቂና አስተማማኝ ሰላም በሐገራቜን ለመትኚል በተቃዋሚነት ጎራ ዹተሰለፈው ወገን
ተመጣጠኝ ዚትግልና ዹአሰላለፍ ስልት አውጥቶ ዚጉዳቱ ሰለባ ዹሆነውን ሕዝብ ለማስተባበር
ልዩ ትኩሚት በመስጠት እዚተንቀሳቀሰ ነው ወይ ? ዹሚለው ጉዳይ በኔ እምነት ዚወቅቱ ጥያቄ
ይመስለኛል።ነገር ግን ኹዚህ ላይ መታወቅ ያለበት በተቃዋሚው ጎራ በኢትዮጵያና
በኢትዮጵያውያን ላይ እዚተፈጠመ ያለውን ዚሺብር ተግባር በቀጥታ ኚሚደግፉትና ዹወንጀሉ
ተባባሪ ኚሆኑት ተቃዋሚ መሰል ድርጅቶቜ ሌላ በወያኔ ተቃዋሚነታቜን እንኚን
አይወጣልንም በሚሉ ተቃዋሚወቜ በኩል በወያኔ ዹሚደርሰውን ጥፋት በዹጊዜው በአይናቾው
እዚተመለኚቱ በጀሮ቞ው እዚሰሙ እነሱ ራሳ቞ው ዚቜግሩ ሰለባ ሆነው እያለ ነገር ግን ድፍሚቱ
ኖሮ቞ው አሞባሪው ወያኔ ዚመፈጥመውን ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን ዚማጥፈት እሚምጃ
ለማስቆም ዚሚያስቜሉትን ዚትግል እሚምጃወቜ አቁሞቜና ክንዋኔወቜን በተገባር ለይቶ
በማውጣት ኚሕዝባ቞ው ፊትለፈት ቆመው ወቅቱ ዹሚጠይቀውን መስዋዕትነት በፖለቲካ
ድርጅት ደሹጃ ሲኚፍሉ አይታዩም እንዲያውም ቜግሩ ዚዲሞክራሲ ጥያቄ ቜግሩ ዚስልጣን
ክፍፍል ቜግር ቜገሩ ዚወያኔው መንግሰት ዚስራ አፈጣጠም ቜገር …....... ወዘተ እንደሆነ
አስመስሎ በማቅሚብ ወያኔው ለሚፈጥመው ዚሺብር ተግባር ሺፋን ሆነው ዚሚያገለግሉ አሉ።
በእርግጥ ኚመካኚላ቞ው አንዳንድ ወገኖቜ ዚኚፈሉትና በመክፈል ላይ ያሉት መሰዋትነት
ታሚክና ትወልድ ዹማይሹሰው ቢሆንም ትግላ቞ው ቀጣይነት ባለው መንገድ በድርጅት ደሹጃ
ዹተጠናኹሹ ባለመሆኑ ዚሕዝባቜን ዚመኚራ ዘመን ለማሳጥር አልተቻለም። ኹዚሕ ላይ ብዙ
ዙሪያ ገባ ሳንመለኚት አሞባሪወቜ በዓለማቜን ላይ ዚሚያደርሱት ሰባዊና ቁሳዊ ቀውሰ ምን
ያህል በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ አስኚፊ እንደሆነ ዚምንሚዳው ጎዳይ ነው። ለዚሕም ነው መላው
አሜሪካኖቜ፤ ምዕራባውያን፤ ምስራቃዊያንና ጠቅላላው ዓለምቜን አለማቀፍ ሺብርን
ለመግታት በመደራደር ሳይሆን ያለዚሌላ቞ውን ወታደርና ዹጩር መሳሪያ቞ውን አሰልፈው
በቢለዮን ዹሚቀጠር በጀት መድበው ዓለማቀፍ ዹመሹጃና ዚዲፕሎመሲ ስራ቞ውን አጠናክሹው
መተኪያ ዹሌለውን ዚዜጎቻ቞ውን ሕይወት በመገበር ሺብርተኝነትን እያንበሚኚኩት ነው
ኹፍተኛ አለም አቀፍ ውጀትም አግኝተውበታል እኛም በተገኘው አንጣራዊ ሶላም
ተጠቃሚወቜ ነንና ልናመሰግን ይገባል ብዚ አምናለሁ። ነገር ግን እኛ አትዮጵያዊያን
በሕዝባቜንና በሐገራቜን ሕልውና ላይ ዹሚፈጠመውን ሺብር እያዚንና እዚሰማን ዚፖለቲካቜን
ጭብት ወሬ አሳባቂና ቃላት ሰንታቂ ሆነን ጥርስ ዹሌለው ውሻ በመሆን ኚ቎ሚሪስቱ ወያኔ
ዚጥፋት በትር በማያድን ጉንጭ አልፋ ንትርክ ስንደናበርና ስንላፋ 21 አመታትን
አስቆጥሚናል። እንዲያውም አሞባሪውን ወያኔ ኹማሾበር ተግባሩ ውጫ ያለተፈጥሮው ዹሌለውን
መልክና ቅርጥ እዚሰጠን ብሔራዊ እርቅ ድርድር ምርጫ ሰላማዊ ትግል እያልን አሞባሪው
ወያኔ በተቆጣጠራት ሐገር ዹማናገኘውን ስልጣን በመመኘት ዹሕልም ጉዞ አላሚወቜ
ሆነናል።ይሕ አስተዛዛቢ ሁናታ ኹአሁኑ ወቅታዊ ሁኔታ ዹበለጠ አጋጣሚ ተገኝቶ መቾይሆን
ዚሚታሚመው በሚል እንደ ኢትዮጵያዊነ቎ ያደሚብኝን በርቱ ስጋት በተለይም በውጭ
ለሚኖሹው ኢተዮጵያዊ ወገኔ ምንም እንኩን አቅሜም ሆነ ቜሎታዚ ትንሺ ቢሆንም
ዹተሰማኝን ስሜት በኹፍተኛ ሐዘን መግለጥን መርጫለሁ።
ኚደስታዚ ጥቂቶቹ ደገሞ አርበኞቻቜን ወያኔን በሚገባው ቁንቁዋ እያናገሩት መሆኑን በራሱ
በወያኔው አንድበት ምሰክርነቱን ወዶ ሳይሆን ተገዶ በመስጠት ላይ እንደሆነ ስሚዳ ደግሞ
በጀግኖቜ ወገኖቾ ኹፍተኛ ኩራትና ተስፋ ይሰማኛል እንዲያውም ወያኔ በጩር ሚዳው ውሎው
በዚትኛውም አቅጣጫ እዚደሚሰበት ያለውን ሺንፈት ጭንቀትና ፍርሐት በወለደው አንደበቱ
እያስተጋባ ነው ። ተፋላሚወቾ ብሎ ኚሚመስክርላ቞ው ውስጥ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ አሚበኞቜ
ግንባር ዚትግራይ ዲሞኚራሲያዊ ንቅናቄን ዚጋቀላ ነጣነት ንቅናቄ ዚተባሉ ኢተዮጵያውያን
ድርጅቶቜ ዋናወቹ እንደሆኑ ተናግሮል።
በዚሕ አጋጣሚ ወያኔ ያፈሚሳትን ሐገር፤ወያኔ ዚሚገጣትን ሰንደቅ አላማ፤ወያኔ ዹዘሹፈውን
ዚሕዝብ ሐብት፤ ወያኔ ዹበተነውን ሕዘብ ፤ወያኔ ያሚኚሰውን እምነቶቜ፤ወያኔ ዹበኹለውን አኩሪ
ባሕል፤ ወያኔ ያነገሰውን ሕግ አልባነት ግድያ አፈና ሺብር ስደትና ዚግዞት ስርዓት
ለማስወገድ መተኪያ ዚሌላትን ውድ ሕይወታ቞ውን በመገበር በዚህ ወቅት በዚትኛውም
ዚፍልሚያ ጎራ ተሰልፈው ዚወያኔን እብሪት ለማስተንፈስና ለኢትዮጵያዊያን ነጣነት፤
አንድነት፤ለጋራ እድገት ፤ፍቅርና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ነጣነት ያለመስዋእትነት
አይገኝምና ዚታሪክና ዚትውልድ አደራ቞ውን ኚሕዝባ቞ው ጎን ሆነው ግዳጃ቞ውን በመወጣት
ላይ ለሚገኙት ዚኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞቜ ግንባርና በቅርቡ ኚግንባሩ ጋር ሕብሚት
በመፍጠር ዚአሞባሪውን ወያኔውን ጎራ በማንቀጥቀጥ ላይ ለሚገኙት ስድስት ኢትዮጵያውያን
ድርጅቶቜ ለሚፈጥሙት ዹላቀ ጀግንነት ምሰጋናዹ ይድሚሳ቞ው እላለሁ ይንን ዹተቀደሰ
ሐገርና ሕዝብን ዚማዳን ተግባር ለዲሰፖራው ወገን እግዚአብሔር ቅን ልቩና ስጥቶት
አርበኞቹን እንዲቀላቀል ጥሪዚን እያቀሚብኩ ፈጣሚው እሱ ነውና ለሐያሉ ጌታም ልመናዹን
አቀርባለሁ.......//..
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ
መሰሚት ቀለመወሹቅ
አውሰትራሊያ

ESAT Yesamintu engeda Martin and Yohann part II

‹‹áŠ áˆ‹áˆ አእለም! ይቅርታ አንጠይቅም›› ሁለት ወቅታዊ ጉዳዮቜ – ኚተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

ኚተመስገን ደሳለኝ
1. ኚመለስ ሞት በኋላ መሚጋጋት ዚተሳነው ኢህአዎግ ኚበርካታ ቜግሮቜ ጋር ፊት ለፊት ተፋጧል፡፡ ኚቜግሮቹ በኹፊልም
ዚሚኚተሉት ይጠቀሳሉ፡፡ …በሚኚት ስምኊን ዚነበራው ተደማጭነት እዚተሞሚሞሚ ነው፣ ዚበሚኚት ባለቀት ዚበሚኚትን መፅሃፍ
ለመሞጥ (ገዥ ፍለጋ) በዚተቋማቱ እዚተንኚራተቱ ነው፤ አዲሱ ለገሰ ዚተደማጭነት መስመሩን ‹‹áŠ¢áˆ…áŠ á‹ŽáŒáŠ• ለማጠናኹር››
በሚል ምክንያት ይበልጥ እያደሚጀ ነው፤ ደብሚፅዮን ገ/ሚካኀል ኹቀን ወደ ቀን በህወሓት ውስጥ ተሰሚነቱ እዚጚመሚ ነው፣
በእርግጥም ኚድርጅቱ ኹፍተኛ አመራሮቜ ዚአስጊ ህመም ቜግር ዚሌለባ቞ው ተብለው ዚሚመደቡት ደብሚፅዮን፣ አባይ ፀሀዬና
቎ውድሮስ አድሃኖም ናቾው፣ አቩይ ስብሃት ነጋ ‹‹áˆ˜áˆáŠ•á‰…áˆˆ ፓርቲ›› በህወሓት ውስጥ ለማድሚግ ቀን ኚለሌት እያሎሩ ነው፣
ኚሁለት ወር በኋላ ዹሚደሹገው ዚኢህአዎግ ጠቀላላ ጉባኀ አዲስ ነገር ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል፤ ኊህዎድ በሹም ሜር ሊናጥ
ነው፣ አለማዹሁ አቱምሳ በሩቅ ምስራቅ ለሚኚታተለው ህክምና እስኚአሁን ያለውንም ሆነ በቀጣይ ዚሚያስፈልገውን ወጪውን
እዚሞፈነ ያለው ሌክ መሀመድ አላሙዲ ነው፤ ለምን? አለማዹሁ ዚመንግስት ባለስልጣን ነው፣ በተጚማሪም ሆን ተብሎ
በተሰጠው መርዝ ነው ታማሚ ዹሆነው ዚሚባለውን ወሬ ይዘን፣ ኹዚህ ጀርባ ማን ነው ያለው? ዹሚል ጥያቄ መቀርቡ አይቀርም
(ዚሰማሁት መሹጃ ጆሮ ያቃጥላል) ግን ለምን? ኩማ ደመቅሳ መልካም አስተዳደር ባለማስፈንና ሙስናን መቆጣጠር ባለመቻል
እዚተወቀሰ ሲሆን፣ በተቃራኒው አባዱላ ገመዳ በኊህዎድ ውስጥ መሚጋጋትን በማስፈንና ስራውን በብቃት በመወጣት በሚል
ተመስግኗል፣ (ዚማኪያቬሊ ኹፋፍለ ግዛ ማለት ይህ ይሆን?) በሚያዚያ ወር ዹሚደሹገውን ምርጫ ተኚትሎ ዚቱኒዝያንና ዚግብፅን
መሰል ህዝባዊ አመፅ ይቀሰቀሳል በሚል አገዛዙ ፍርሃት አድሮበታል፣ 33ት ፓርቲዎቜ ነገ በምርጫው ላይ ዚሚኖራ቞ውን አቁም
በሰማያዊ ፓርቲ ፅፈት ቀት ኚጠዋቱ አራት ሰአት ላይ ዹፋ ያደርጋሉ (በእርግጥ ዚደሚሱበት ውሳኔን ብግሌ ትክክል ነው ብዬ
አምናለሁ፣ ኹዚህ ውጪም ገዥው ፓርቲን ለድርድር ዚሚያስገድድ ዕድል ዹላቾውም)፣ በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር
ኊስትሪያዊውን አገር ጎብኚ ማን ገደለው? ለምን ተገደለ? ዚደብሚማርቆስ ማሚሚያ ቀት ድራማስ በማን ዚተቀነባበሚ ነው?
ኃላፊነቱንስ ማን ነው ዚሚወስደው? ዚብሄራዊ መሹጃና ደህንነት ኀጀንሲ ¬¬‹‹áˆˆáˆœá‰¥áˆ­ ድርጊት ሊውል ሲል ደሚስኩበት››
በማለት ኚተቀበሚበት እንዳወጣው ዹነገሹንን ዹጩር መሳሪያ ማነው ዹቀበሹው? ይህ መሳሪያስ በእነማን ዚክስ መዝገብ ላይ ማስሚጃ
ሆኖ ሊቀርብ ነው ዚታቀደው? በቀጣይስ ዚቊንብ ፍንዳታ በዚትኛው ኹተማ፣ መቌ፣ ስንት ሰዓት ላይና በምን ሁኔታ ይደርስ
ይሆን? …ይህኛው መንገድስ ዚት ድሚስ ያስኬዳል? ‹‹áŠ á‹²áˆµ ታይምስ›› መፅሄትን ማፈኑስ ለምን አስፈለገ?
2. በሜብርተኝነት ዚተኚሰሱትን ዚህዝብ ሙስሊም መሪዎቜን በይቅርታ ለመፍታት መንግስት ዚማጭበርበሪያ ስልቱን እዚተጠቀመ
ነው፡፡ በዕለት ሀሙስ ጥር 2 ቀን 2005 ዓ.ም በፕሮፌሰር ኀፍሬም ይሳቅ ይመሩ ኚነበሩት ሜማግሌዎቜ ውስጥ ዹተዘጋጀ ሶስት
ሰዎቜ ያሉት አንድ ቡድን በቃሊቲ ማሚሚያ ቀት ተገኝቶ ነበር፡፡ ኚቡድኑ አባላት ፓስተር ዳንኀል እና ፕሮፌሰር አህመድ
ዘካርያስ ለታሳሪዎቹ እንዲህ ዹሚል ዚማጭበርበሪያ መደራደሪያ አቅርቩ ነበር፡-
‹‹áŒ‰á‹³á‹«á‰œáˆ በፍርድ ቀት እዚታዚ ነው፤ ስለዚህም ክሱ አሁን ባለበት ደሹጃ ሊቋሚጥ አይቜልም፡፡ እናም ክርክራቜሁን አቋርጡና ጥፋተኛ ነን በሉ፣ ኹዛም ፍርድ ቀቱ ኚፈሚደባቜሁ በኋላ
‹á‹­á‰…ርታ› ጠይቃቜሁ እናስፈታቜኋለን››
ሆኖም ዚሙስሊሙ መሪዎቜ ‹‹á‹­áˆ…ንን በጭራሜ አንቀበለውም፣ ጥፋተኛ ነኝም አንልም፣ አላሁ አእለም! ይቅርታ አንጠይቅም›› ሲሉ በድፍሚትና በቁርጠኝነት መልሰውላቾው ወደ እስር
ክፍላቾው ተመልሰዋል፡፡ በእርግጥም ዚኮሚ቎ው አባላት ትክክለኛ ውሳኔ ነው ዚወሰኑት፡፡ ምክንያቱም ይህ ዚሜምግልና ቡድን ቀንደኛ ዚስርአቱ ደጋፊ ሲሆን፣ መደራደሪያ ብሎ ዚሚያቀርበው
ሁሉም ነገር ዹአገዛዙን ዚፖለቲካ ጥቅም ዚሚያስኚብር ነውና፡፡ በድህሚ ምርጫ 97 ዚታሰሩትን ዚቅንጅት አመራርንም በዚህ አይነት መልኩ መሞወዱ ይታወሳል፡፡
(በነገራቜን ላይ ሜማግሌዎቹ በተጠቀሰው ዕለት አንዱአለም አራጌን ጠርተው አናግሚውታል፤ እስክንድር ነጋን ግን ዘለውታል፡፡ ለምን? ሌላው አስገራሚ ጉዳይ ደግሞ ዚሜማግሌ ቡድኑ
ለሙስሊሙ መሪዎቜ ‹‹á‹šáˆ˜áŒ£áŠá‹ አንዱአለምን ፈልገን ነው፣ እናንተን እግሚ መንገዳቜንን ሰላም እንበላቜሁ ብለን ነው›› ሲሏ቞ው፣ ለአንዱአለም ደግሞ ዹዚህን ግልባጭ ምክንያት
ሰጥተውታል፡፡

ሰበር ዜና – 33ቱ ዋንኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ ኚምርጫ ራሳ቞ውን ሊያገሉ ነው

ፍኖተ ነፃነት
33ቱ ፓርቲዎቜ ለምርጫ ቊርድ ያቀሚቧ቞ው ጥያቄዎቜ ባለመመለሳ቞ው በመጪው ዚአዲስ አበባ እና ዚአካባቢ ምክር ቀት ምርጫ ላይ ላለመሳተፍ መወሰናቾውን ዹፍኖተ ነፃነት ዹዜና ምንጮቜ አሚጋገጡ፡፡ ፓርቲዎቹ ነገ ጥር 7, 2005 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጜ/ቀት በሚሰጡት መግለጫ ውሳኔያ቞ውን ለኢትዮጵያ ህዝብ ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ መግለጫውን ኚቊታው ኚስር ኚስር ፍኖተ ነፃነት ገጟቜ ለማስተላለፍ ጥሚት ይደሹጋል፡፡ዚባለራዕይ ወጣቶቜ ማህበር አመራር አባለትን ለማሰር ዝግጅት እዚተደሚገ መሆኑን አመራሮቹ አጋለጡ ዚባለራዕይ ወጣቶቜ ማህበር አስተባባሪ ኮሚ቎ ሰባሳቢ ወጣት ሀብታሙ አያልው ኹፍኖተ ነፃነት ጋር ባደሚገው ቃለምልልስ እንደጠቆመው መንግስት እሱን ጚምሮ ዚማህበሩን አመራሮቜ ለማሰር ዝግጅት እያደሚገ እንዳለ መሹጃ ደርሷ቞ዋል፡፡ ባለፈው ቅዳሜ በአንድነት ፓርቲ ጜ/ቀት አዳራሜ ሊያደርጉት ዹነበሹው መስራቜ ጉባኀም ዚማህበሩ አባላት ባልሆኑና ለጊዜው ማንነታ቞ው ባልታወቀ ግለሰባቜ ኚታወኚና እንዲበተን ኹተደሹገ በኋላ 6 ዚማህበሩ አመራሮቜ እስኚምሜቱ 12፡30 ድሚስ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው እንደነበር ወጣት ሀብታሙ ጚምሮ ገልጧል፡፡

(ሰበር ዜና) በዛሬው ዚቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ አስገራሚ ነገሮቜ ተሰሙ

“አቡነ መርቆርዮስ ኚሚመለሱ፤ ለምን መንግስቱ ኃይለማርያም ይምጣ አትሉም” አባይ ፀሐዬ

“አቡነ መርቆርዮስ ዚሚመለሱ ኹሆነ ትግራይ ዚራሷን ፓትርያርክ ትሰይማለቜ” ዚትግራይ ጳጳሳት

(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ አስ቞ኳይ ስብሰባ ዹተቀመጠው ዹሃገር ቀቱ ሲኖዶስ በዛሬው ውሎው ዚመንግስት ደጋፊ ዹሆኑ ጳጳሳት ፍላጎት በአሞናፊነት ጎልቶ በመውጣት ላይ እንዳለ ዹዘ-ሐበሻ ምንጮቜ ኚስፍራው ዘገቡ። እንደምንጮቹ ገለጻ ኚትግራይ ዚመጡት ጳጳሳት “አቡነ መርቆርዮስ ወደ ኢትዮጵያ ዚሚመለሱ ኹሆነ ትግራይ ዚራሷን ፓትርያርክ በመሟም በእርሱ እንመራለን፤ ቀተክርስቲያንንም እንኚፍላለን” ዹሚል አቋማቾውን ማሳዚታ቞ውን ዹዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮቜ ዘግበዋል።
ዛሬ በአዲስ አበባ ዹተጀመሹውና ምናልባት ነገ ሊጠናቀቅ አልያም ሊቀጥል ይቜላል ዚተባለው ይኾው ዚቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ኚትግራይ ተወላጅ ዚሆኑት 18ቱም ጳጳሳት መገኘታ቞ው ዚታወቀ ሲሆን “አዲስ ፓትርያርክ ይመሚጥ ዹሚለውን አቋማቾውን” አጠናቅሚውበት ኹመቀጠላቾውም በተጚማሪ ሌሎቜ ፓትርያርክ እንዳይመሚጥ ዹሚፈልጉ አባቶቜ ኚቅዳሜ ጀምሮ በድህነነት ኃይሎቜ እንግልት ውስጥ በመግባት ሃሳባ቞ውን እንዲቀይሩ በመደሹግ ላይ እንዳሉ እነዚሁ ዹዘ-ሐበሻ ምንጮቜ አጋልጠዋል።
በተለይም ዚመንግስት ተወካይ ሆነው ዚቀሚቡት አቶ አባይ ጞሐዬ በግልጜ አዲስ ፓትርያርክ መሟሙን ለማይደግፉ አባቶቜ “አቡነ መርቆርዮስ ይመለሱ ኚምትሉ ለምን መንግስቱ ኃይለማርያም ይምጣ አትሉም?” በማለት እንደተናገሯ቞ውና እንዳስፈራሯ቞ው ያሚጋገጡት ዹዘ-ሐበሻ ምንጮቜ በተለይ ኚትግራይ ዚመጡት ጳጳስት አቡነ ሳሙኀል (ፎቶ)ና አቡነ ጎርጎርዮስ ዚአቡነ መርቆርዮስን መመለስም ሆነ ፓትርያርክ እንዳይሟም ዚሚጠይቁትን አባቶቜ ስም ዝርዝር ለመንግስት በመስጠት በደህንነት ኃይሎቜ አቋማቾውን እንዲቀይሩ ትልቅ ሥራ እዚሰሩ መሆኑም ተጋልጧል። በዛሬው ዚቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ በተለይ አቡነ መርቆርዮስ ዚሚመለሱ ኹሆነ ትግራይ ዚራሷን ፓትርያርክ ትመርጣለቜ ዹሚል ዚማስፈራሪያና ቀተክርስቲያንን አደጋ ላይ ዚሚጥል አነጋገር መሠማቱ ብዙ ዹ ዕምነቱን ተኚታዮቜን አስደንግጧል። በአጠቃላይ በዛሬው ዚሲኖዶስ ስብሰባ ዚመንግስት ደጋፊ ዹሆኑ ጳጳሳት በአሞናፊነት እዚመሩ ነው። ስብሰባው ነገ ይቀጥላል። በስብሰባው ውስጥ ያሉት ዹዘ-ሐበሻ ምንጮቜ መሹጃውን እንዳደሚሱን ለአንባቢዎቻቜን ያለውን ነገር እናሳውቃለን።

Jan 14, 2013

ESAT Daily News Amsterdam 14 January 2013 Ethiopia

ሰፈር ያሞበሚ ዶሮ በፍርድ ቀት ሞት ተወሰነበት


ሰፈር ያሞበሚ ዶሮ በፍርድ ቀት ሞት ተወሰነበት

ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ ኚጜዮን ሆቮል ጀርባ በሚገኘው መደዮ ሰፈር ውስጥ ነዋሪውን   ያመሰ ዶሮ፤ በፍርድ ቀት ሞት ተፈሚደበት።ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ሾገር ራዲዮ ዶሮውን << አሞባሪ>> ብሎታል።
በጜዮን ሆቮል ጀርባ በሚገኘው መደዮ ሰፈር ወጪ ወራጁን፣አላፊ አግዳሚውን እዚደበደበ ያስ቞ገሚ ጉልበተኛ አለ ዹሚል ጥቆማ በደሚሳ቞ው መሰሚት ወደ ስፍራው ማቅናቾውን ነው ዹሾገር ጋዜጠኞቜ ዚሚናገሩት።
ይህን ጉልበተኛ ዚደፈሚቜውም፤ ሰናይት ዚምትባል ዚሰፈሩ ሎት ብቻ መሆኗን ዚአካባቢው ነዋሪዎቹ ተናግሹዋል።
ሰናይት ደፈሚቜው ዚተባለውም፤ ያሰደሚሰባትን ኹፍተኛ ደብድባ ተኚትሎ መብቷን ለማስኚበር ለፖሊስ ክስ መስርታበት በፍርድ ቀት ስላስፈሚደቜበት ነው።
እንደዘገባው ኹሆነ ኚሰፈሩ ነዋሪዎቜ በተጚማሪ ቆራሌ ዹሚሉ አነስተኛ ነጋዎዎቜን ዹኔ ብጀዎቜ በተደጋጋሚ በጉልበተኛው ዶሮ ኹፍ ያለ ጥቃት ተፈፅሞባ቞ዋል።
ዹ አካባቢው ድመቶቜና ውሟቜ ሳይቀሩ በጉልበተኛው ዶሮ ዚሚደርስባ቞ውን ንክሻና ጥቃት አሜን ብለው ኹተቀበሉም ሰንብተዋል።
ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ስፍራው ዚተንቀሳቀሱት ዹሾገር ዘጋቢዎቜ በቊታው ሲደርሱ በነሱም ላይ ጥቃት እንዳይደርስባ቞ው በመስጋት ሁኔታውን በርቀት መኚታተልን እንደመሚጡ ተናግሹዋል።
እግሮቹ ወፋፍራምና ዓይኖቹ ድፍርስ ዚሆኑት ይህ ጉልበተኛ፤ ኚድብድብ ብዛት ግንባሩ እና ጀርባው ላይ መቁሰሉን ዚጠቀሱት ዘጋቢዎቹ፤ ካሉበት ስፍራ ሆነው ሰዎቜ በርቀት ሲያሷያ቞ው- እሱም  ኚጉራንጉር ውስጥ ሆኖ እንዳያ቞ው ጠቁመዋል።
በነሱም ጥቃት እንዳይፈጜምባ቞ው  ዶሮውን በ አንድ ዓይናቾው ዚጎሪጥ እዚተኚታተሉ  በሰሩት ቃለ ምልልስ፤በርካታ ዚአካባባው ወላጆቜና ወጣቶቜ ሳይቀሩ በዚህ ጉልበተኛ ዶሮ መነኚሳ቞ውን በምሬት ለጋዜጠኞቹ ተናግሹዋል።
ኚሰፈሩ ሰው አልፎ መንገደኞቜን፤ቆራሌዎቜንና ዚኔብጀዎቜን ድንገት  ዘልሎ ትኚሻ቞ው ላይ ድሚስ እዚወጣ በተደጋጋሚ ኹፍ ያለ ጥቃት እንደፈጞመባ቞ው ዚተናገሩት አንዲት እናት፤ በዚህም ሳቢያ ዚኔብጀዎቜ ወደ መንደሩ መምጣታ቞ውን ጚርሶ እንዳቆሙ ገልጾዋል፡፡
ቃለ-ምልልስ ዚተደሚገለት ዚመንደሩ ኮስታራና ጎሚምሳ ወጣት በበኩሉ፦<<  …በጣም ሀርደኛ ነው፤ እኔ ራሎ እፈራዋለሁ። ፈጜሞ አይመቾኝም>> ሲል በምሬት መልክ ተናግሯል።
ዹመደዮ ሰፈሩ ዶሮ “ኩኩሉ ሲል ደስ ይላል፤ በጧት ይቀሰቅሰናል ተብሎ ለሰዓት ነጋሪነት እንዲሰነብት ቢደሚግም ሳይታሰብ ዹ ዚአውሬነት ባህሪይ ማምጣቱ ያስገሚማ቞ው ዚሰፈሩ ነዋሪዎቜ፤ <<ምን ታሪክ ነው?>> ሲሉ አግራሞታ቞ውን ገልጾዋል።
በዶሮው ኹፍተኛ ጥቃት ኚደሚሰባ቞ው በርካታ ሰዎቜ መካኚል፤ ሎት ሰናይት ዚተባለቜ ዚአካባቢው ነዋሪ አንዷ ነቜ።
ሁሉም  ዚደሚሰባ቞ውን ጥቃት አሜን ብለው በቁጭትና በዝምታ ሲመለኚቱት፤ሰናይት ግን <፣መብ቎ በጉልበተኛ ሲገሰስ በዝምታ አላይም>> በማለት ፍርድ ቀት ገትራዋለቜ።
ሰናይት   ጥጋበኛው ዶሮ ላደሚሰባት ዹሀይል ጥቃት በወሚዳ 10 ፖሊስ ጣቢያ  ክስ እንደመሰሚተቜበትና ጉዳዩ እስኚ ፍርድ ቀት እንደደሚሰ ዚገለጹት ዚሰፈሩ ነዋሪዎቜ፤ ፍርድ ቀቱም ግራ ቀኙን ኹተመለኹተ በሁዋላ፦<<ዹገና በዓልን እንዳያልፍ>> በማለት ዚሞት ፍርድ ቢወስንበትም፤ ዚዶሮው ባለቀት ውሳኔውን ተግባራዊ ሳታደርግ ገናን እንዳሳለፈቜው ተናግሹዋል።
<< በፍርድ ቀት ዚተወሰነበት ውሳኔ ለምን ተግባራዊ አልሆነም?>> ተብለው ዚተጠዚቁት ዚዶሮው ባለቀት፤ ስለ ዶሮው  እድሜና ሁኔታ ካብራሩ በሁዋላ፦<< ውሳኔውን ለመጪው ጥምቀት ተግባራዊ አደርጋለሁ፤ለጥምቀት ይታሚዳል>> ሲሉ መልስ ሰጥተዋል።
ዚመንደሩ ትልቋ እማማ በበኩላ቞ው ለጋዜጠኞቹ ቡድን፦<<በጉዳዩ ዙሪያ ትናንት ተሰባስበን  ውይይት አድርገንበታል።  በአስ቞ኳይ እሚዱ ብለን ተናግሹናል። ወስነናል።  ዚፍርድ ቀቱ ውሳኔ መጜናቱ ዹማይቀር ነገር ነው>>ብለዋል።

በሁስተን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶቜ በድል ተንበሞበሹ


በሁስተን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶቜ በድል ተንበሞበሹ

ኢሳት ዜና:-ትናንት እሁድ ሁስተን/አሜሪካ ላይ በተደሹገ ዚማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶቜ በወንዶቹም ሆነ በሎቶቹ ምድብ አስደናቂ በሆነ ሁኔታ ዚአሞናፊነትን ድል መቀዳጀታ቞ው ታወቀ።ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
በወንዶቜ ዚማራቶን ውድድር አትሌት በዙ ወርቁ 2 ሰዓት ኹ10 ደቂቃ ኹ17 ሎኮንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ዹወርቅ ሜዳሊያ ባለቀት ሲሆን፣ አትሌት ተፈሪ ባልቻ 2፡12፡50 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ፣  áˆŒáˆ‹á‹ ኢትዮጵያዊ አትሌት ሞላ ሰለሞን ደግሞ 2:14:37 á‰ áˆ†áА ሰዓት ሶስተኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቋል።
በሎቶቹ ምድብ ደግሞ ኢትዮጵያዊቷ መሪማ መሃመድ 2 ሰዓት 23 ደቂቃ ኹ37 ሎኮንድ በሆነ ግዜ አንደኛ ሆና ዚአሞናፊነትን ክብር ተቀዳጅታለቜ። በውድድሩ ላይ ዚግራ እግሯ ላይ በደሚሰባት ጉዳት ውድድሩን በመሃል አቋርጣ ዚነበሚቜው መሪማ፣ እግሯን በፋሻ በማሰርና፣ ሕመሟን በመቋቋም አሾናፊ መሆን መቻሏ በብዙዎቜ ዘንድ አድናቆትን አስቜሯታል። ኚውድድሩ በኋላ ቃለመጠይቅ ላደሚጉላት ጋዜጠኞቜ እንደገለፀቜው ይሰማት ዹነበሹው ህመም ኹፍተኛ ነበር። መሪማ ያጠናቀቀቜበት ሰዓትም ዚሁስተን ማራቶን ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት ተብሎ ተመዝግቊላታል።
በዚሁ ውድድር ላይ ሌላዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ብዙነሜ ዳባ በመሪማ መሃመድ በ47 ሰኚንድ ብቻ ተቀድማ በሁለተኛነት ስታጠናቅቅ፣ አትሌት መስኚሚም አሰፋ ደግሞ 2 ሰዓት ኹ25 ደቂቃ ኹ17 ሎኮንድ በሆነ ጊዜ ሶስተኛ ሆና ውድድሩን ማጠናቀቋ ታውቋል።
በግማሜ ማራቶን ውድድርም ባለፈው ዓመት 0፡59፡22 በሆነ ፈጣን ሰዓት አሾናፊ ዹነበሹው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ 1፡01፡54 በሆነ ሰዓት ቀድሞ ሲገባ፣ ሌላው ኢትዪጵያዊ አትሌት ድሪባ መርጋ በሰባት ሎኮንድ ልዩነት ብቻ በፈይሳ ተቀድሞ ውድድሩን በሁለተኛነት አጠናቋል። በሎቶቜ ዚግማሜ ማራቶን ውድድርም ባለፈው ዓመትም አሾናፊ ዚነበሚቜው አትሌት ማሚቱ ደሳካ 1 ሰዓት ኹዘጠኝ ደቂቃ ኹ53 ሰኮንድ በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ ዹወርቅ ሜዳሊያ ተሾላሚ ለመሆን በቅታለቜ።

በአዲስ አበባ ዚባዶ መሬትና ዚንግድ ቀቶቜ ሜያጭ ጣራ ነካ


በአዲስ አበባ ዚባዶ መሬትና ዚንግድ ቀቶቜ ሜያጭ ጣራ ነካ

ኢሳት ዜና:-በአዲስአበባ በመንግስት ዚሚቀርቡ ዚቀት መስሪያ ቊታና ዚንግድ ሱቆቜ ሜያጭ ኹግዜ ወደ ግዜ በአስደንጋጭ መልኩ ዋጋቾው እዚተሰቀለ መምጣቱን ምንጮቻቜን ጠቆሙ፡፡ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ዚአዲስአበባ ዚቀቶቜ ልማትና አስተዳደር ኀጀንሲ በልደታ ክፍለኹተማ ዚተሰሩ ኮንዶሚኒዚም ቀቶቜ ጋር ተያይዞ ዹሚገኙ 150 ዚንግድ ቀቶቜን በጚሚታ ለመሞጥ ጥቅምት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ መሰሚት ለአንድ ካሬሜትር እስኚ ብር 56 ሺ164 ኹ11 ሳንቲም እጅግ አስደንጋጭ ዋጋ ዚሠጡ ተጫራ቟ቜ ማሾነፋቾው ታውቋል፡፡
ኀጀንሲው ዹ149 ቀቶቜ አሞናፊዎቜ ስም ዝርዝር ኚሳምንት በፊት ይፋ ያደሚገ ሲሆን ኚጥር 6 ቀን ጀምሮ ቀቶቹን ለአሞናፊዎቹ ማስተላለፍ ጀምሯል፡፡
አስተዳደሩ ለንግድ ቀቶቹ በካሬሜትር  á‹šáˆ°áŒ á‹ መነሻ ዋጋ 6ሺ 600 ብር ሲሆን አሞናፊዎቜ ዚሰጡት ዋጋ ግን ኹፍተኛው በካሬሜትር 56ሺ164ብር ኹ11 ሳንቲም ሲሆን ዝቅተ =ኛው ደግሞ በካሬሜትር 13 ሺ ብር ሆኗል፡፡
በዚሁ መሰሚት ኹፍተኛ ዋጋ ዹሰጠው አሾናፊ ዚተወዳደሚው ለ19 ነጥብ 25 ካሬሜትር በመሆኑ በጠቅላላው 1ሚሊዹን 81ሺ157ብር ኹ12 ሳንቲም ሲሆን ዝቅተኛ ዚሰጡት አሾናፊ ለ79 ነጥብ 56 ካሬሜትር 1ሚሊዹን 34ሺ 280ብር ይኹፍላሉ፡፡
ለዚሁ ለልደታ ኮንዶሚኒዚም ዚንግድ ቀቶቜ ኹፍተኛ ብር ኚሰጡት ተጫራ቟ቜ መካኚል በካሬሜትር 52 ሺ600 ብር ዚሰጡት አንድ አሾናፊ ላሞነፉበት 91 ነጥብ 26 ካሬ ሜትር በድምሩ 4 ሚሊዹን 800 ሺ 276 ብር ይኹፍላሉ፡፡
ኹነዚሁ ዚንግድ ቀቶቜ አሞናፊዎቜ መካኚል 23 ያህሉ  á‰ áŠ«áˆ¬áˆœá‰µáˆ­ ኹ40ሺብር በላይ እጅግ ዹተጋነነ ዋጋ በመስጠት ያሞነፉ ሲሆን በካሬሜትር ኹ20ሺብር በታቜ አነስተኛ ዋጋ በመስጠት ያሞነፉት 9 ያህል ተጫራ቟ቜ ናቾው፡፡

በአዲስአበባ ለንግድና ለመኖሪያ ቀት ግንባታ ዹሚውል መሬት ኚመንግስት ማግኘት እጅግ አስ቞ጋሪ በመሆኑ ኹግዜ ወደግዜ ዚመሬትና ዚንግድ ሱቆቜ ዋጋ እዚናሚ ሊመጣ ቜሏል፡፡መንግስት ዜጎቜ በተመጣጣኝ ዋጋ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ኚመርዳት ይልቅ በዹግዜው ዹሊዝ መነሻ ዋጋውን እያሳደገ ገቢ ወይም ትርፍ ላይ ብቻ ማተኮሩ ክፉኛ እያስተ቞ው ይገኛል፡፡

ዚአስተዳደሩ ዚመሬት ባንክና ማስተላለፍ ጜ/ቀት ኚቪላ ቀቶቜ እስኚ ባለአራት ፎቅ መኖሪያ ቀቶቜን ለመገንባት ዚሚያስቜሉ ባዶ ቊታዎቜን በተለያዩ ክፍለ ኚተሞቜ አጫርቶ ለመሞጥ በጥቅምት ወር 2005  á‰£á‹ˆáŒ£á‹áŠ“ በአሁኑ ወቅት ለአሞናፊዎቹ እያስተላለፈ ባለው ጚሚታ ውጀት መሰሚት ለቩሌ ክፍለኹተማ በካሬሜትር 11ሺ700 ብር ሒሳብ ለ420 ካሬሜትር ባዶ ቊታ 4 ሚሊዹን 922ሺ 400 ብር ተሾጧል፡፡
ንፋስስልክ ላፍቶ ክ/ኹ ደግሞ ኹቩሌ በባሰ ሁኔታ ተጫራ቟ቜ ለአንድ ካሬሜትር ቊታ 12ሺ500 ብር በመስጠት አሜንፈዋል፡፡ ይህኛው ተጫራቜ ለ191 ነጥብ 21 ካሬሜትር ቊታ 2 ሚሊዹን 390ሺ125 ብር ይኹፍላል፡፡
ለመኖሪያ እና ለንግድ  á‰€á‰¶á‰œ መገንቢያ ቊታ ፈላጊዎቜ አስተዳደሩ ያቀሚበው ሊዝ መነሻ ዋጋ ዝቅተኛው በካሬሜትር 191 ብር፣ኹፍተኛው 299 ብር ነው፡፡ ይህ መነሻ ብር በተጫራ቟ቜ ውድድር በካሬሜትር ኹ10ሺ ብር በላይ ዚሚሰጥበት በመሆኑ አነስተኛና መካኚለኛ አቅም ያላ቞ው ዜጎቜ በዕድሉ ተጠቃሚ መሆን አልቻሉም፡፡
አንድ በንግድ ሥራ ላይ ዚተሰማሩ ነጋዮ ስለጉዳዩ አስተያዚት ተጠይቀው በተለይ ኚልደታ ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜ ጋር ተያይዞ አዲስ ዚተሰሩት ዚንግድ ቀቶቜ እስኚዛሬ ታይቶ ዚማይታወቅ ዋጋ እንደተሰጠባ቞ው አሹጋግጠዋል፡፡ “በጚሚታው ላይ ተሳትፌ ያውም ተበድሬ ለማሟላት በማሰብ በካሬሜትር 9ሺብር ገደማ አስገብቌ ነበር፡፡ ነገር ግን ዚማይታወቁ ነጋዎዎቜ ጭምር ዋጋውን ኚአምስት እጥፍ በላይ ሰቅለውት በማግኘቮ ግርም ብሎኛል፡፡ ሰው በገንዘቡ እንኳን በቀላሉ መጠቀም ዚማይቻልበት አገር እዚሆነ መምጣቱ ብቻም ሳይሆን መንግስትም ዚለዚለት ኪራይ ሰብሳቢ ሆኖ መቀመጡ በጣም አሳሳቢ ነው” ብለዋል፡፡
በልደታ ዚሚገኙት አብዛኞቹ ዚመኖሪያ በህወሀት ታጋዮቜ መያዛ቞ውን መዘገባቜን ይታወሳል።

ዚአዲስ አበባ ነዋሪዎቜ ዹውሃ ያለህ ይላሉ



ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ በተለያዩ ቊታዎቜ ኹፍተኛ ውሀ እጥሚት ማጋጠሙን ዘጋቢያቜን ገልጿል።
በስድስት ኪሎ፣  መነን፣ ፈሚንሳይ፣ ጃን ሜዳ፣ ሜሮ ሜዳ፣ ሰሜን ማዘጋጃ እና በተለያዩ ዹሰሜን አዲስ አበባ  ዹሚገኙ ሰፈሮቜ ውሀ ለማግኘት ውሀ ያለባ቞ውን አካባቢዎቜ ማሰስ ግድ ብሎ቞አዋል።
በአንዳንድ አካባቢዎቜ ውሀ ለሳምንታት ዚማይመጣ ሲሆን፣ በሌሎቜ አካባቢዎቜ ደግሞ በሳምንት አንድ ጊዜ ጥሩ ኚተባለም በሳምንት ሁለት ጊዜ ያገኛሉ። በተለይ ፈርነሳይና ሜሮ ሜዳ በኹፍተኛ ሁኔታ ዹውሀ እጥሚት አጋጠማቾው አካባቢዎቜ መሆናቾው ታውቋል።
11 በመቶ እድገት እንደተገኘ በሚነገርባት ዚኢትዮጵያ ዋና ኹተማ ውሀና መብራት ያለማቋሚጥ ማግኘት ህልም እዚሆነ ነው።
ዹውሀ መጥፋቱ በሰሜን አዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በደቡብ አዲስ አበባም ዹተለመደ ክስተት ሆኗል።
ውሀ ሲባል መብራት መብራት ሲባል ውሀ ይጠፋል፣ መስተዳድሩ ኹተማዋን ለማስተዳዳር ዚተሳነው ይመስላል ይላሉ አንድ ዚሜሮ ሜዳ ነዋሪ። በእርሳ቞ው አካባቢ ውሀ ኚተቋሚጥ ድፍን አንድ ሳምንት ሞልቷል።

ምርጫ ቊርድ 33ቱን ፓርቲዎቜ ጚምሮ ምልክት ያልወሰዱ በምርጫው እንደማይሳተፉ ገለጾ

ኢሳት ዜና:-ምርጫ ቊርድ እስካለፈው ሳምንት መጚሚሻ ቀርበው ዚምርጫ ምልክቶቻ቞ውን ያልወሰዱ ፓርቲዎቜ በሚያዝያው ምርጫ መሳተፍ እንደማይቜሉ በይፋ አስታወቀ፡፡ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኹ33ቱ ፓርቲዎቜ መካኚል ዚአንዱ  á‹šáŠ áˆ˜áˆ«áˆ­ አባል ዚምርጫ ቊርድ እርምጃ 33ቱ ፓርቲዎቜ ኚምርጫው ወጥተናል ኚማለታ቞ው በፊት “አባሚና቞ዋል” ለማለት ዹተወሰደ ስልታዊ እርምጃ ነው በሚል አጣጥለውታል፡፡
ቊርዱ ባወጣው ፕሮግራም መሰሚት ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ በማዕኹል በቊርዱ ጜ/ቀት ተገኝተው ዚመወዳደሪያ ምልክቶቻ቞ውን ዚሚወስዱበት ጊዜ ህዳር 14 ቀን 2005 ዓ.ም ዹነበሹ ቢሆንም  ፣ ዚፓርቲዎቜን ተሳትፎ ለማበሚታታት ሲባል ይኾው ጊዜ በተደጋጋሚ እንዲራዘም መደሹጉን ጠቅሶ ባለፈው ሳምንት መጚሚሻ ጊዜው መጠናቀቁን ይፋ አድርጓል፡፡
ኚቊርዱ ጜ/ቀት በተገኘው መሹጃ መሰሚት በጊዜ ገደባ቞ው ቀርበው ዚመወዳደሪያ ምልክቶቻ቞ውን ዚወሰዱ ፓርቲዎቜ ካሉት 75 ፓርቲዎቜ መካኚል 28 ያህሉ ብቻ ናቾው፡፡
ዹ33ቱ ፓርቲዎቜን ኹሚወክሉ ፓርቲዎቜ ዚአንዱ ዚአመራር አባል ዹሆኑ ስለጉዳዩ ተጠይቀው ነገሩ ቊርዱ ጩኞታቜንን ለመቀማት እሜቅድድም ውስጥ ዚገባ ያስመስለዋል ብለዋል፡፡
“33ቱ ፓርቲዎቜ ሕጋዊ በሆነ መንገድ ኚምርጫው በፊት ኚምርጫ ጋር በተያያዘ ባሉ ቜግሮቜ ላይ ተወያይተን እንድንፈታ ዕድል ስጠን በሚል ጥያቄዎቻቜንን በዝርዝር አቅርበናል፡፡ ቊርዱ ለጥያቄዎቻቜን መልስ ሳይሰጥ ኚአንድ ወር በላይ ኹቆዹ በኋላ ልክ ዚኢህአዎግ ባለስልጣናት በዚመድሚኩ ዚሚሉትን በመድገም “ቜግሮቜ አሉ ለተባለው ዹቀሹበ ማስሚጃ ዹለም፣ያሉትም ተፈትተዋል” በሚል በወጉ እንኳን ሳያነጋግሚን ጥያቄያቜን ውድቅ አድርጓል፡፡ይህ ሁኔታ ፓርቲዎቹን ብቻ ሳይሆን ዚሚወክሉትን ህዝብ መናቅ መሆኑን በመገንዘብ በምርጫው አጃቢ ሆኖ ላለመቅሚብ ዚጋራ ስምምነት እንደነበሚ እና ይህንንም አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን በመዘገባ቞ው በይፋ “ኚምርጫው ወጥተናል” ብለን መግለጫ ኚመስጠታቜን በፊት ቊርዱ ተሞቀዳድሞ “ምልክት ባለመውሰዳ቞ው ተባሚዋል” ለማለት ዹዘዹደው ዚሕጻን ጚዋታ ነው ሲሉ አጣጥለውታል፡፡
ያለፓርቲዎቜ ስምምነት እዚተጓዘ ያለው ዚዘንድሮ ምርጫ ሚያዝያ 6 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስአበባ፣በድሬዳዋ ፣በደቡብ ብሔር ብሔሚሰቊቜና ሕዝቊቜ ክልል ለኹተማ አስተዳደር፣ለወሚዳና ዹቀበሌ ም/ቀቶቜ ምርጫ እንደሚካሄድ ቊርዱ ያወጣው መርሃግብር ያሳያል፡፡

4 አመት ዚተፈሚደባ቞ው ዹሜጋው ባለስልጣን በሳምንቱ ኚእስር ተፈቱ


4 አመት ዚተፈሚደባ቞ው ዹሜጋው ባለስልጣን በሳምንቱ ኚእስር ተፈቱ

ኢሳት ዜና:-ዚኢትዮጵያ ገቢዎቜና ጉምሩክ ባለስልጣን በሜጋ ኪነጥበባት ኀ/ዹተ/ግ/ማ እና በቀድሞ ስራአስኪያጁ አቶ ዕቁባይ á‰ áˆ­áˆ„ ላይ በመሰሹተው ክስ መሰሚት አቶ ዕቁባይ አራት ዓመት ኚአምስት ወራት ቅጣት ኚተላለፈባ቞ው በኋላ ቅጣቱ á‰ áŒˆá‹°á‰¥ ተደርጎላቾው ተለቀዋል።ጥር ፫ (ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ዚባለስልጣኑ መለቀቅ ዚፍትህ ሥርዓቱ አድሎአዊነት በግልጜ ዚሚያሳይ መሆኑን አንድ ዹሕግ ባለሙያ áŒˆáˆˆáŒžá‹‹áˆ፡፡
ዚባለስልጣኑ ዓቃቀ ሕግ ባቀሚበው ክስ መሰሚት ዚፌዎራሉ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀት አስሚኛ ወንጀል ቜሎት ጉዳዩን áˆ²áˆ˜áˆˆáŠšá‰µ ቆይቶ ተጠርጣሪዎቹ በሁሉም ክሶቜ ጥፋተኛ ናቾው ያላ቞ው ሲሆን ድርጅቱም ሆነ ግለሰቡ ጥፋተኛ ዚተባሉበት áŠ áŠ•á‰€áŒŸá‰œ ዹ15 ዓመት ጜኑ እስራትና ዹ50 ሺ ብር መቀጫን ዚሚያስኚትሉ ቢሆንም ባልተለመደ መልኩ አቶ ዕቁባይ 12 እርኚን ዝቅ ያለ ቅጣት ማለትም አራት ዓመት ኚአምስት ወራት ፍ/ቀቱ ኚማስተላለፉም በተጚማሪ ቅጣቱም በገደብ áŠ¥áŠ•á‹²á‹«á‹áˆ‹á‰žá‹ ትላንትና ዹሰጠው ውሳኔ ዚፍትህ ስርዓቱን ጥያቄ ውስጥ ዚሚጥል አሳዛኝ ውሳኔ ነው ሲሉ ባለሙያው áŒ á‰áˆ˜á‹‹áˆ፡፡
ዚገቢዎቜና ጉምሩክ ባለስልጣን ኹዚህ በፊት ኚሰሳ቞ው ሰዎቜ መካኚል አይኀምአፍ በመባል ዚሚታወቁት አራጣ አበዳሪ áŠ á‰¶ አዹለ ደበላ ኹፍተኛ ተደራራቢ ሕመም እንዳለባ቞ው በቅጣት ማቅለያነት አቅርበው እንደነበር ባለሙያው አስታውሶ áŠáŒˆáˆ­ ግን እሳ቞ው በዚህ ምክንያት ቅጣቱ በ12 እርኚን ቀርቶ በስድስትም ዝቅ ሊልላቾው አልቻለም፡፡
አቶ ዕቁባይ ግን ዚሥርዓቱ ቁንጮዎቜ አንዱ በመሆናቾው፤ ዚሳንባ ሕመምተኛ መሆናቾው ተሹጋግጧል በሚል እንደትልቅ ዚቅጣት áˆ›á‰…ለያ ፍ/ቀቱ መያዙ ዹፍ/ቀቶቜ ነጻነት ዚይስሙላ መሆኑን ኚማሳዚት ባለፈ በዜጎቜ መካካል አድልኊ መፍጠሩ እጅግ áŠ¥áŠ•á‹°áˆšá‹«áˆ³á‹áŠ• ተናግሹዋል፡፡
ዚኢትዮጵያ ህግ ለዳኞቜ ሕሊና ዹሚተወው ነገር መኖሩን ዚጠቀሱት ባለሙያው እንደአገር ግን አንዱን 15 እና 20 á‹“መት እዚቀጡ ሌላውን በአራት ዓመትና በገደብ መልቀቅ ለፍትህ ሥርዓቱ ትልቅ ኪሳራ ነው ብለዋል፡፡
ዹሜጋ ኪነጥበባት ኹ1997-2000 ዓ.ም ድሚስ ገቢን አሳውቆ ግብርን ባለመክፈልና አትራፊ ድርጅት ሆኖ ሳለ áŠ¥áŠ•á‹°áŠšáˆ°áˆš በማስመሰል ዚንግድ ትርፍ ግብር ባለማስታቅና ዹተጭበሹበሹ መሹጃ በማቅሚብ ወንጀል መኚሰሱ ዚሚታወስ áŠá‹፡፡
አቶ ዕቁባይ ግብርና ታክስ በዚህ መልኩ ሲያጭበሚብሩ ዚቅርብ አለቃቾው ዚሜጋኔት ኮርፖሬሜን ዋና ስራ አስኪያጇ á‹šáŠ á‰¶ መለስ ባለቀት ወ/ሮ አዜብ መስፍን እንደነበሩም ይታወቃል፡፡
ወ/ሮ አዜብ ግን በዚሁ ጉዳይ ላይ ተጠያቂ አልሆኑም ነበር።

“ዚመለስን ሌጋሲ ማስቀጠል ዚማንቜል ኹሆነ ህዝቡ እሳት ሆኖ እንዳያቃጥለን እንሰጋለን” ሲሉ ዚኢህአዎግ አባላት ተናገሩ


“ዚመለስን ሌጋሲ ማስቀጠል ዚማንቜል ኹሆነ ህዝቡ እሳት ሆኖ እንዳያቃጥለን እንሰጋለን” ሲሉ ዚኢህአዎግ አባላት ተናገሩ

ኢሳት ዜና:-በሚስጥር ዹደሹሰን በአዲስ አበባ  ዚኢህአዎግ ድርጅት ጜህፈት ቀት ያዘጋጀው ሚስጢራዊ ሪፖርት እንደሚያመለክተው  á‹šáŠ¢áˆ…áŠ á‹ŽáŒ አባላት ኚመለስ ሌጋሲ እና ኚልማት ጋር ዚተያያዙ በርካታ ጥያቄዎቜን ማንሳታ቞ው ተመልክቷል።ጥር ፬ (አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ዚኢህአዎግ አባላት  ካነሱዋ቞ው ሀሳቊቜ መካኚል “  መስመሩን ያላወቁ አባላት ባለበት እንዎት ሌጋሲውን ማስቀጠል ይቻላል? አባሎቜ ራሳ቞ው ጀርባ቞ው መጠናት አለበት፣ ንፋስ ወደ ነፈሰበት ዚሚነፍሱ ቁጥራ቞ው እዚበዛ ነው፣ ዚመለስ ሌጋሲ ሊኖር ዚሚቜለው ስርአቱ እስካለ ድሚስ ነው፣ ዚሚስጥር ጠባቂነት ቜግር በአመራሩ ኹላይ እስኚታቜ አለ፣ አመራሩ ኪራይ ሰብሳቢነትን አምርሮ አይታገልም፣ህወሀት ሀይለማርያምን ማስቀጠል ዚለበትም ምክንያቱም ታግሎ ዚመጣ ሰው ነው መምራት ያለበት”   ዚሚሉት ይገኙበታል።
በጥሩ ጎን ተብለው ኚተጠቀሱት ሀሳቊቜ መካኚል ” ዚመለስን ሌጋሲ ለማስቀጠል ዹማይፈልግ ዚሰማዕታትን አደራ ለመቀበል ዝግጁ ያልሆነ ሰው ነው፤ ዚመለስን ሌጋሲ ለማስቀጠል አመራር መሆን አያስፈልግም ፣ መለስ ትክክለኛ ሃገር ወዳድ ነው፣ ደፋር መሪ ነው፡፡ በሌሎቜ መሪዎቜ ያልተደፈሩ ተግባራትን ዹደፈሹ ነው፡፡”  á‹šáˆšáˆ‰á‰µ ተዘርዝሹዋል።

ዚኢህአዎግ ዚሰራተኛ አባል መድሚክ ዚአቶ መለስን ሌጋሲ ኚማስቀጠል አንጻር ካነሱዋ቞ው ጥያቄዎቜ መካኚል ደግሞ ዚሚኚተሉት ተጠቅሰዋል ”  áˆµáˆˆ መለስ ብቻ ይወራል መለስን ዹፈጠሹው ኢህአዎግ ስለሆነ ዚኢህአዎግን ሙሉነት ብናወራ አይሻልም ወይ፣ ኚመለስ ብዙ እንማራለን በርካታ ጠንካራ ጎኖቜ አሉት፣ እኛ ዚሱን ሌጋሲ ለማስቀጠል ዚህብሚተሰቡን ቜግር ለመቅሹፍ ምን ያህል ዝግጁ ነን፣ስለሌጋሲ እያወያያቜሁን ነው፣ እናንተ እራሳቜሁ ቁርጠኝነታቜሁ እስኚምን ድሚስ ነው፣ ራስን ኚማብቃት አንጻር ኚመለስ ሌጋሲ ዹምንማሹው አለ ሆኖም አመራሩም ሆነ አባሉ ቜግር አለበት ማስተካኚል አለብን” ዚሚሉት ተጠቅሰዋል።

ዚኑሮ ውድነቱን በተመለኹተ አባሎቜ ካነሱዋ቞ው ነጥቊቜ መካኚል ደግሞ ” በኑሮ ውድነቱ ዚመንግስት ሰራተኛው እዚተጎዳ በመሆኑ ዚህዳሎ ጉዞአቜንን ኚማሳካት አንጻር አንዱን ሀይል እንዳናጣው እንሰጋለን፣ ያለፈው አመት ቜግር በታዚበት ዹአሁኑ እቅድ ኚስፋት አንጻር ለማሳካት ይኚብዳል” ዚሚሉት ይገኙበታል።

ዚኢህአዎግ ሰራተኛ አባላት በመለስ ሌጋሲ ላይ ካነሱዋ቞ው ጥያቄዎቜ መካኚል ደግሞ ” ስለመለስ ሌጋሲ እናውራ ስንል በሙት መንፈስ መመራት አያስምስልም ወይ? ዚመለስ ሌጋሲ እያልን ዚምናወራው ሁሌ ጠንካራ ጎኑን ነው፣ ደካማ ጎን ዹለውም ወይ? ጠናካራ ዹሆኑ ዹተቃዋሚ ፓርቲ ፓርላማ እንዲገቡ ልምን አላዳሚገም።” ዚሚሉት ተነስተዋል።
ዚአባላት መድሚክ ካነሱዋ቞ው ነጥቊቜ ውስጥ ደግሞ  ”
- ዚመለስ ሌጋሲ ማስቀጠል ማንቜል ኹሆነ ህዝቡ  እሳት ሆኖ እንዳያቃጥለን እንሰጋለን ስለዚህ ሌጋሲውን ኚማስቀጠል ውጭ ሌላ አማራጭ ሊኖር አይቜልም
- ሌጋሲውን ለማስቀጠል አቅም ክፍተት አለብን
- ዚመለስ ሌጋሲን መውሚስ ሲባል እሱን መሆን ሳይሆን ባለንበትና በተሰማራንበት ዚህዝብ አገልጋይነት ስሜት መፍጠር መላበስ ነው፣ ኚመለስ ሌጋሲ አባሉ ሲመዘን እና ዚሰአት መስዋት መክፈል አንፈልግም እሱ ግን ዚህይወት መስዋትነት ኹፍሎ አሳይቶናል” ዚሚሉት ይገኙበታል።
ግንባሩን በተመለኹተም ” ዚአባላት ዚተሳትፎ ቜግር አለ፣ ዚውስጥ ድርጅት ስራቜን በጣም ተዳክሞአል፣ ድጋፍና ክትትል አካባቢ ያለው ስራም አናሳ ነው፣ አመራሩ ዹሚፈልገን ለዘመቻ ስራ እንጅ በቋሚነት ዹመደገፍ ቜግር አለበት ፡” ዚሚሉት ተጠቅሰዋል።
በህዝብ መድሚክ ኚተነሱት ጥያቄዎቜ መካኚል ደግሞ “ተማሪዎቜ በአጥር እዚዘለሉ ጫትና ሺሻ ቀት እዚገቡ ተቾግሹናል፣ ሺሻ ቀት ኹቀን ወደ ቀን ሲበራኚት ለምን እርምጃ አትወስዱም ፣ ሺሻ ቀቶቜ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ሲታሰብ ሚስጢሮቜ ኚፖሊስና ኚአስፈጻሚ በኩል ይወጣሉ፣ ኚፖሊስ ሲጠሩ በወቅቱ አይመጡም፣ ዚጞጥታ ኮሚ቎ ተብለው ዚተመደቡት እራሳ቞ው ቜግር አለባ቞ው፣   á‹šáˆšáˆ‰á‰µ ይገኙበታል።

Total Pageviews

Translate