Pages

Mar 22, 2013

የወያኔ/ኢህአዴግ ጉባኤ ውሃ ቢወቅጡት እሞቦጭ

ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይና በተለምዶ ተለጣፊ እየተባሉ የሚጠሩት ሎሌ ድርጅቶቹ ሰሞኑን በጉባኤ ሽርጉድ ላይ ተጠምደዋል። የድግሱ፣ የፌስታውና የካርኔባሉ አይነትና ብዛት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህዝቦች በቀን አንድ ጊዜ ለመብላት በሚቸገሩበት ሀገር ውስጥ የሚደረግ አይመስልም። ይሔው የፈረደበት የኢትዮጵያ ድሃ ግብር ከፋይ ይህን በብዙ መቶ ሚሊየኖች ብር የሚቆጠር ወጭ ይሸፍናል። ማን ከልካይና ጠያቂ አለ? ሌሎች በህግ የተመዘገቡ የፖለቲካ ድርጅቶች ለአንድ ደቂቃ እንኮን በአጠገቡ ዝር እንዳይሉ የሚከለክለው የመንግስት ሚዲያ ይህንን የግፈኞች የውሸት ዲስኩርና ፌሽታ በቀን 24 ሰአት ያጋፍራል። እንጨት እንጨት የሚል ፕሮፖጋንዳ ሊግተን፣ ሊያደነቁረን ይታገላል፡፡ ልብ ብሎ ለተመለከተው ጠቅላላው የወያኔ የጉባኤ ሽርጉድ ከጆርጅ ኦርዌል “የእንስሳት እርሻ” (Animal Farm) የስላቅ ድርሰት ተወስዶ የሚሰራ ትያትር ይመስላል።
የወያኔ መሪዎችና ሎሌዎቻቸው ለሆድ አደሮች እግዚያብሄር እንደ ፀጋ ሰጥቷቸዋል። እፍረትና ይሉኝታ የሚባል ነገር ከልክሎ ፈጥሯቸዋል። ትዝብት አይፈሩም። ህዝቡ አንጀቱ እያረረ እብሪታቸውን ሲመለከት በደስታ ፈንድቆ የሚጨፍር ይመስላቸዋል። ኢትዮጵያን ወደ ፖሊሲያዊ መንግስትነት ቀይሮ የሞተውን አለቃቸውን ለአፍሪካና ለአለም የሚያጎድል መሪ ነው ይሉናል። መለስ በምን ህመም እንደሞተ እንኩዋን አጣርተው የማያውቁ ጀሌዎች ትግል ላይ የተሰዋ ኣርበኛ ኣስመስለው ሲያወሩ አያፍሩም።
ይህንኑ እንዲመሰክርላቸው ከዚህ ቀደም በሙሁር ሸቃጭነት (intellectual prostitution) የገዛ ጎደኞቻቸው ሙሁር ከከሰሳቸው የኮሎምቢያ ሙሁራንም  አንዱን አስመጥተዋል። በነዚህ ሰዎች ግምት መለስ ዜናዊ በግፍ የጨፈጨፋቸው ወገኖቻችን፣ የዝምብ ያህል ክብር የላቸውም።   በእስር የታሰሩት ንጹሃንና ሀገራቸውን ጥለው የተሰደዱ ወገኖቻችን በነሱ ቤት ሰዎች አይደሉም። እናም ጉባኤው አይናችሁን ጨፍኑልንና እናሞኛችሁ ከሚል  ቡዋልት የተለየ አይደለም።
እንዳለፉት ጉባኤዎች ሁሉ የዚህንም ጉባኤ ተብዬ  ውጤት አስቀድሞ መናገር ይቻላል።አሁንም አይናቸውን አጥበው ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር እየሰራን ነው የሚል መግለጫ ያወጡልናል። መለስ ዜናዊ ቀድሞውኑ ራሱን አዋቂ አድርጎ በመሳል ከሱ የተቀራረበ ችሎታ ያላቸውን ሰዎች ሁሉ ጠራርጎ በደካሞች ራሱን ከቦ ከበሮ እያስደለቀ መቆየቱ ለከንቱ የሙት ውዳሴ ጠቅሞታል። እነዚህ ደካማ ጀሌዎች አሁንም ምንም የራሳቸን እውቀት ስለሌለን በሞተው መለስ ራእይ በሚሉት ነገር እንደሚመሩ በጉባኤው መጨረሻ የአዞ እንባ ያለበት መግለጫ ያወጣሉ።
እድገትና ትራንስፎርሜሽን የሚባለው ነገር ከሁለት አመት በኋላ ህብስተመና ከሰማይ ይወርዳል የሚል የጉባኤ ውሳኔም እንሰማለን። መብታቸውን የሚጠይቁ ኢትዮጵያውያንን ለማስፈራራትና አስጎንብሶ ለመግዛት ይጠቅማሉ የተባሉ መግለጫዎችም በጉባኤው መጨረሻ ይጠበቃሉ። አሸባሪ፣ ጸረ-ልማት፣ አክራሪ፣ ወዘተ ወዮላችሁ ይሉናል። ስልጣንና ስልጣንን መከታ በማድረግ የዘረፉት ሀብት ይቀርብናል የሚል የሚያባንን ፍርሃት ስላደረባቸው ባስፈራሩን ቁጥር ሰላም ያገኙ ይመስላቸዋል። በህዝብ መሃል ልዩነት መፍጠርና አንዱን በአንዱ ላይ ማነሳሳት ሰላም ይሰጠናል ብለው ስለወሰኑ እርስበርሳችን እንድንጋጭ ጥሪ ያቀርቡልናል።
ዛሬም እንዳምና ካቻምናው የነሱ ምቾት ስለጨመረና ስለተመቻቸው ኢኮኖሚው እየተመነደገ ነው እንደሚሉን ይጠበቃል። የህዝባችን ኑሮ የከዘራ ያህል እንኳን ቀና እንዳላለ ህዝቡ ራሱ ያውቀዋል።
ወገን ይሄ ግፍ ለከቱን አልፏል። ከወያኔ አገዛዝ በጎ ነገር መጠበቅ ከእባብ እንቁላል ርግብ መጠበቅ  መሆኑን ካወቅን ውለን አድረናል።
ግንቦት 7 የፍትህ የነትጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ  በሀገራችን ዴሞክራሲ ሰፍኖ በገዛ ሀገር ተዋርዶ መኖር ቆሞ፣ በኩራትና በሰባአዊ ክብር ሁላችንም የምንኖርበት ሀገር ወያኔና ሎሌዎቹ ሥልጣን ላይ እስካሉ ድረስ ፈጽሞ የማይታሰብ ነው ብሎ ያምናል ። በመሆኑም የወደፊቱ እጣችንና ተስፋችን ያለው በራሳችን መዳፍ  ውስጥ ብቻ  እንደመሆኑ   ለነጻነቱና ለክብሩ ቀናዕ የሆነ ሁሉ በራሱ   አነሳሽነት ትግሉን ለማቀጣጠል መነሳት ያለበት ጊዜው አሁን ነው ።
ከወያኔ በጅጉ የተሻለ ስርዓት የሚገባን ህዝብና ሀገር እንደመሆናችን ህዝባችን  በወያኔ አገዛዝ ላይ በቃኝ በማለት ዛሬውኑ እንዲነሳና ! በየአቅጣጫው ለነጻነት የሚካሄዱ እንቅስቃሴዎችን እንዲቀላቀል ግንቦት 7 የፍትህ የነትጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ  የትግል ጥሪውን ያቀርባል!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Mar 18, 2013

ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም ታሠሩ (የታሰሩትን 34 ሰዎች ስም ዝርዝር ይዘናል)

ዛሬ መጋቢት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 3 ሰዓት ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪ የግል
ተነሳሽነት ማህበር፣ ሰማያዊ ፓርቲ እና ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር በጋራ በመሆን
“ለፋሽስቱ የጦር ወንጀለኛ ለማርሻል ግራዚያኒ ክብር መስጠት የአባቶቻችን
መስዋዕትነት ማራከስ ነው” በሚል የተጠራውን ሰልፍ አምባገኑ የኢህአዴግ
መንግስት በርካታ የፌደራል ፖሊስ፣ የደህንነት አባላትን እና የአዲስ አበባ
ፖሊሶችን በማሰማራት ሲበትን፣ የተቋማቱን ከፍተኛ አመራሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች
እና በርካታ ወጣቶች ማሰሩ ታወቀ። አሁንም የታሳሪዎች ቁጥር ሊጨምር ይችላል
የሚሉት የዜና ዘጋቢዎች የቀድሞውን የቅንጅት አመራር ዶ/ር ያዕቆብ
ኃይለማርያምን ጨምሮ 34 ሰዎች መታሰራቸው በወጣው ስም ዝርዝር ላይ
ተገልጿል፡፡ ትላንት እለት ለተቃውሞ ሰልፉ የቅስቀሳ ስራ ሲሰሩ ከነበሩት ውስጥ 2 የሰማያዊ ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ
አባላትን እንዲሁም የባለራዕይ ወጣቶች የስራ አስፈጻሚ አባላትን ጨምሮ 8 ሰዎችን በማሰር የተጀመረው ይህ የማሰር
ተግባር ዛሬ ቀጥሎ የታሳሪዎቹ ቁጥር 34 ደርሷል።
ለጊዜው ስማቸው የታወቀና የታሰሩ ሰዎች ስም ዝርዝር የሚከተለው ነው።
1. ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም
2. አቶ ታዲዎስ ታንቱ
3. አቶ ይልቃል ጌትነት (የሰማያዊ ሊቀመንበር)
4. ስለሺ ፈይሳ (የሰማያዊ ም/ሊቀመንበር)
5. ይድነቃቸው ከበደ (የሰማያዊ የህግ ጉዳይ ሀላፊ)
6. ሀና ዋለልኝ (የሰማያዊ የሴቶች ጉዳይ ሀላፊ)
7. ጌታነህ ባልቻ (የሰማያዊ የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ)
8. ብርሀኑ ተክለያሬድ (የባለራዕይ ወጣቶች ተ/ምክትል ሊቀመንበር)
9. ያሬድ አማረ (የባለራዕይ ወጣቶች ማህበር ጸሀፊ)
10. ኤልሳቤጥ ወሰኔ
11. ሰለሞን ወዳጅ
12. ወይንሸት ንጉሴ
13. እየሩሳሌም ተስፋው
14. ለገሰ ማሞ
15. ትዕግስት ተገኝ
16. አማኑኤል ጊዲና
17. አለማየሁ ዘለቀ
18. አገኘሁ አሰገድ
19. ሻሚል ከድር
20. አሸብር ኪያር
21. ጌታቸው ሽፈራው
22. ግሩም አበራ
23. አቤል ሙሉ
24. ዩሀንስ ጌታቸው
25. ስማቸው ተበጀ
26. ፍቃዱ ወንዳፍራው
27. ባህረን እሸቱ
28. ሄኖክ መሀመድ
29. እንቢበል ሰርጓለም
30. አለማየሁ በቀለ
31. ዩናስ
32. የመኪናው ሹፌር
33. ዮዲት አገዘ
34. ጥላዬ ታረቀኝ

Mar 17, 2013

ውድ የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላትና ወዳጆች ሁሉ ይህ አልባሌ የቅስቀሳ ወረቀት ሳይሆን እጅግ አስፈላጊ መልዕክት ስለሆነ በጥሞና አንብባችሁ ተረዱ።

ሕዝብ ሃብትና ጉልበት የቆመችው ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ለኢትዮጵያ መንግሥት (ኢህአዲግ) ለማስረከብ የተወሰኑ ካህናት ከኤምባሲ ጋር ድርድር እያደረጉ ነው።

አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው የእግዚአብሔር ቤት የሆነውንና ሕዝብ በሃብቱና በጉልበት ገዝቶ ያቆመውን ቤተ ክርስቲያን በአብይ ጾም ሕዝብ እንዳይጸልይበት ከ11/03/2013
London Ethiopian Orthodox Church
ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን
ጃምሮ ከዘጉ በኋላ ለንደን ወደሚገኘው የኢትዮጵያ (የኢህአዲግ) ኤምባሲ በስውር በመሄድ በኤምባሲው አደራዳሪነት ቤተ ክርስቲያኑን የኢትዮጵያ (ኢህአዲግ) መንግሥት እንዲረከበው ለማድረግ ድርድር መጀመራቸውን በተጨባጭ ማረጋገጥ ተችሏል።
አባ ግርማ ከበደ፤ መሪ ጌታ አለማየሁ ደስታና ድቁናውን ያፈረሰው የቀድሞ ሊቀ ዲያቆን ዳዊት ገ/ዮሐንስ በመሆን ከአሁን በፊት የማርያም ቤተ ክርስቲያንን ገንዘብ በመዝረፉ፤ ከዛም እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1998 ዓ/ም ቤተ ክርስቲያኗን ለኢህአዲግ አሳልፎ ለመስጠት ሲል አገልግሎቷን አቋርጣ እንድትዘጋ አድርጎ የነበረውና ከዚህም ሁሉ በላይ ደግሞ የኦርቶዶክስ እምነቱን ክዶ ጴንጤ በመሆን ጴጤ ቤተ ክርስቲያን ሄዶ የኦርቶዶክስ እምነት የበሰበሰና የገማ ነው በማለት ምሥክርነት መሥጠቱ የሚታወቀው ሙሉጌታ አሥራትን በኤምባሲ ውስጥ በማግኘት ለተንኮል ሥራቸው እንዲተባበራቸው ማድረጋቸው ታውቋል።
ከሃገሩ ኢትዮጵያ ተሰድዶ በUK የሚኖረው ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ባደረገው 40 ዓመታትን ያስቆጠር ድካምና ጥረት በእግዚአብሔር ተራዳኢነት ሃብትና ጉልበቱን አስተባብሮ ህንፃ ቤተ ክርስቲያን በመግዛት ሁለተኛ ኢትዮጵያ የምትሆነውን ቤተ ክርስቲያን ካቆመ ብዙም ሳይቆይ ቤተ ክርስቲያኑን ከእጁ ነጥቀው አሳልፈው በመሥጠት መሾሚያና መሸለሚያ ለማድረግ የሚጥሩ አባ ግርማ ከበደን የመሰሉ ባላንጣዎች ተነሱበት።
ሕዝብ ሃብትና ጉልበቱን አስተባብሮ ህንፃ ቤተ ክርስቲያን መግዛት ብቻ አይደለም የካህናቱን ደምወዝና አበልም ሆነ የቤተ ክርስቲያኑን ጥገናና እድሳት ጨምሮ እያንዳንዱን የቤተ ክርስቲያኑን የዕለት ተዕለት ወጪ ከኪሱ እያወጣ በሚሰጠው ገንዘብ ሸፍኖ የሚያኖረው ይኸው ሕዝብ ሆኖ ሳለ አባ ግርማ ከበደ በመጀመሪያ የምእመኑ ተወካይ የሆኑትን 4 የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አባላት በተጽዕኖ ሥራቸውን እንዲለቁ አደረጉ። ቀጥሎም የምእመኑ ተወካዮች በሌሉበት ተከታዮቻቸው የሆኑትን ከህናት በመያዝ ሕዝብ አንዳችም ነገር ሳያውቅና ምንም ዓይነት ፍንጭ ለሕዝብ ሳያሳዩ 15 ሕዝብ የመረጣቸውን የኮሚቴ አባላትና ቤተ ክርስቲያንን ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ የቤተ ክርስቲያን አባላትን ቅጥር ግቢው ውስጥ እንዳይደርሱ ብለው በደብዳቤ አባረሩ። ይህንን በመሰለ ሁኔታ ከቤተ ክርስቲያን ምንም አይነት ጥቅም ሳይፈልጉ የሚያገለግሉና ለእውነት የቆሙ የምእመናኑን ተወካዮች ካስወገዱ በኋላ እነሆ አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው ብቻ የቤተ ክርስቲያኑ ሃብትና ንብረትም ሆነ የወደፊት እጣ ፋንታዋ ወሳኞቹና ፈላጭ ቆራጮቹ እኛ ነን ብለው በመቅረብ ቤተ ክርስቲያኗን ከነ ንብረቷ ለኢህአዲግ መንግሥት በማስረከብ በምትኩ ሹመትና ሽልማት ይሰጠን በማለት ከኤምባሲ ጋር በመደራደር ላይ ይገኛሉ።
ይህ ለማመን የሚያዳግት ሕዝብንም ሆነ እግዚአብሔርን የተዳፈረ ተግባር በሕዝብ ላይ ሲፈጸም የቤተ ክርስቲያኗ ባለቤትና ባለንብረት የሆነው ሕዝብም ሆነ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዝም ብሎ ስለማያይ አጠቃላይ ሕዝቡ በአንድነት ተንቀሳቅሶ ሕዝብን ከነ ቤተ ክርስቲያኑ ለመሸጥ በማስማማት ላይ የሚገኙትን የአባ ግርማ ከበደና የተከታዮቻቸውን ደባ በማስቆም የጥፋት ዓላማቸውን ሊያከሽፍባቸው ይገባል።
ይህ ሳይሆን ቀርቶ ግን ሕዝብ በፈራ ተባና በመዘናጋት ለአባ ግርማና ተከታዮቻቸው ጊዜ ከሰጣቸው “ቁጭ ብለው የሰቀሉት ቆሞ ማውረድ ያቅታል” ነውና ዓይናችን እያየና ጆሮአችን እየሰማ ቤተ ክርስቲያን ከሕዝብ እጅ ወጥታ የማትሄድበት ምክንያት ስለሌለ ሕዝበ ክርስቲያን ሁሉ ከምንግዜውም በበለጠ በመነሳት ቤተ ክርስቲያንህን ለመከላከልና ለማዳን ከአስተባባሪ ኮሚቴው በሚሰጥህ መረጃና መመሪያ መሠረት በአስፈላጊው ቦታ ሁሉ በመገኘት የሚጠበቅብህን ሁሉ እንድታደርግ በማርያም ስም ጥሪአችንን እናስተላልፋለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
አስተባባሪ ኮሚቴው

ሰንሰለቱም ይጠብቃል፤ እርግጫውም ይከፋል …ካልተነሳን!

ሉሉ ከበደ

አስተዳደር በየፈርጁና በየደረጃው፤ ከብሄራዊ መንግስት እስከ ታች የቀበሌ አመራር በመጥፎም ይሁን በደግ መልኩ በዜጎች ህይወት የለት ተለት እንቅስቃሴና አኗኗር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ እንደሚኖረው ሁሉም ሰው እየኖረው ስለሚያየው ማስረጃ መደርደር ላያስፍልገው ይችላል።
በሀገርና በህዝባዊ ጉዳዮች ውሳኔ አሰጣጥ ላይ እናም ውሳኔውን በማስፈጸም ሂደት ላይ ዋናው ተዋናይ በመንግስትነት የተሰየመው አካል ሲሆን፤ እንደየ ሀይላቸውና ቅቡልነታቸው፤ በመንግስት ውሳኔ ላይ ተጽእኖ ማሳደር የሚችሉ ወገኖች መኖራቸው የተለመደ ነው። ለምሳሌ የፖለቲካ ድርጅቶች፤ የሰራተኛ ማህበራት፤ የገበሬ ማህበራት፤ የሙያ ማህበራት፤ ተደማጭ ግለሰቦች እናም አለም አቀፍ ሀይላት፤ የመገናኛ ብዙሀን፤ የገንዘብ ተቋማት፤ ወዘት……ከሁሉም  በላይ ደግሞ ሕዝብ!!..ዲሞክራሲ ባለበት ሀገር ውስጥ በመንግስት ውሳኔ ላይ ተጽእኖ ማሳደር ይችላሉ።
ወደእኛ ሀገር ጉድ የመጣን እንደሆነ በተለይም በደርግና በዘረኛው የወያኔ አስተዳደር ዘመን ፍጹም በሆነ ወደር ያልተገኘለት አንባገነንነት ስር በመውደቃችን፤ የምንታገልለትና የምንመኘው ዲሞክራሲ ጭላንጭሉም እስከወዲያኛው በመጥፋቱ፤ እንኳን የፖለቲካ ድርጅት፤ እንኳን የሙያ ማህበር፤ ህዝብ በነቂስ ከቤቱ ወጥቶ አደባባይ ውሎ አድሮ አቤቱታ፤ሮሮም ሆነ ተቃውሞ ቢያሰማ ወያኔ ከጥፋት አቋሙ ፍንክች እንደማይል ለኢትዮጵያ ህዝብ በተግባር አሳይቷል። ሙስሊም ወንድሞቻችን ከአመት በላይ በሰላም እየታገሉለት ያለው የሀይማኖት ነጻነት ምላሽ ማግኘት ቀርቶ ጭራሽ ይህን አንገብጋቢ ህዝባዊ ሰብአዊ ጥያቄ ወደ ወንጀልነት ቀይሮ፤ ንጹሀን ዜጎችን ወህኒ መቀመቅ ለማጎር ወያኔ የሚያደርገውን ሩጫ እየተመለከትን ነው አዲስ ነገር ባይሆንም።
የሙስሊም ወንድሞቻችን ትግል አርአያነቱ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሳይሆን በእልህና በድንቁርና ለሚታመሰው ለሚተራመሰው አለም በሀገራችን ቢሳካም ባይሳካም እየሞቱ እንዴት ሰላምን ማምጣት እንዴት መብትና ንጻነትን ማስከበር እንደሚቻል የሚያስተምር አጋጣሚ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ ይህንን የሙስሊማን ወርቃማ የትግል ስልት ለመቀላቀል የዘገየበት ምክንያቱ ግራ የሚያጋባ ነገር ነው። ሰላማዊ ትግል መርጠናል የሚሉን የፖለቲካ ድርጅቶች ደጅም ሆነ እቤት ያሉት፤ ከዚህ የተሻለ ሰላማዊ ትግል ምን አለ ብለው ይሆን የራሳቸው አንሶ ህዝቡንም ይዘው የተኙት? ኢትዮጵያ የሙስሊምና የክርስቲያን ሀገር አይደለችም እንዴ? ፖለቲከኞች እስላም ወይ ክርስቲያን አይደሉም እንዴ?…ጥያቄው እኮ የመብት የነጻነት ነው?….የአምልኮ ነጻነት… የፖለቲካ ነጻነት….የኢኮኖሚ ነጻነት….የመኖር ነጻነት… የመደራጀት…..የመሰብሰብ….ሁሉም ልንታገልላቸው የሚገባ ሊኖሩን የሚገቡ የህይወት እሴቶች፤ እስትንፋሶች ናቸው።
መልካም አስተዳደር የሚባለው የአመራር አይነት ቢያንስ ሊኖሩት የሚገቡ ግብአቶች  በግልጽ ተቀምጠው እያለ፤ የተባብሩት መንግታት ድርጅትም ሆነ የአለም ገንዘብ ድርጅት፤ የአለም ልማት ድርጅቶች፤ ሀያላን መንግስታት እነ አሜሪካም ሆኑ እንግሊዞች በተለይም ከአፍሪካ አገሮች መንግስታት ጋር የሚኖራቸው የእርዳታና የልማት ትብብር የሚወሰነው የመልካም አስተዳደር መስፈርቶችን ማሟላት ሲችሉ ነው ቢሉም የግል ጉዳያቸውንና ጥቅማቸውን እስከጠበቁላቸው ድረስ ከማንኛውም ዘረኛና ጨፍጫፊ ቡድን ጋር እንደሚተባበሩ በተግባር አሳይተውናል።
ለዚህም አንድ ቁልጭ ያለ ማስረጃ አሜሪካ በየአለሙ ያሉ አንባሳደሮቿ በሚስጥር ለመንግስታቸው የሚያስተላልፉትን መረጃ ያዝረከረከው ዊኪሊክ  ይፋ እንዳደረገው፤ አዲስ አበባ ያለው የአሜሪካ ኢንባሲ እለት በእለት ወያኔ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚፈጽማቸውን ወንጀሎች፤ ሰባዊ መብት ረገጣዎች፤ ግድያዎች፤ በአዲስ አበባ ያካሄዱትን ፍንዳታዎች ሁሉ በየእለቱ ለአሜሪካ መንግስት ያስተላልፍ ነበር። ያ ማለት እለት በእለት የምትሰራዋን ወንጀል በሙሉ ያውቁ ነበር። ያውቃሉም። ነገር ግን ባካባቢው የራሳቸውን ጥቅምና ፍላጎት ስለሚጠብቅላቸው ብቻ፤ በሀገሩና በህዝቡ ላይ ይህን አደረሰ ብለው፤ ትብብራቸውንና እርዳታቸውን አላቋረጡም። አያቋርጡምም። እንግሊዝ በቅርቡ በብዙ ሚሊዮን ዶላር ወጪ በሱማሌ ክልል ሀዝቡን የሚያሰቃዩበት ፖሊስ በብዛት አሰልጥኖላቸዋል።
ለውስጥ ችግራችን መፍትሄ ወደ እነሱ መመልከት ሳይሆን እኛው የጉዳዩ ባለቤቶች የችግሩ ገፈት ጨላጮች፤ በመናበብ፤ በመደማመጥ፤ በመተያየት፤ ከየትኛውም የሀገሪቱ ጥግ የበደል ጩኸት ሲሰማ፤ እንደ ንብ አብሮ መቀስቀስና ባንድ ድምጽ በመጮህ የወያኔን ዘረኛ አጥፊ ቡድን መታገልና ከስልጣን ማስወገድ ያስፈልጋል።
በሀገራቸው ፖለቲካና ኢኮኖሚ እንዲሁም ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ዜጎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሙሉ የተሳትፎ መብትና እድል ሲኖራቸው፤ የመደራጀት ነጻነት ያለገደብ፤ ኢንፎርሜሽን የማግኘት ነጻነት ያለገደብ ሲኖራቸው፤ በሚወከሉበት ድርጅትም ሆነ በግላቸው በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ደህንነታቸውን፤ ሀብታቸውን፤ ግዛታቸውን፤ መንግስታቸውን፤ በተመለከተ ሊናገሩ ሊደመጡና ውሳኔም ሊያስተላልፉ ሲችሉ፤ ሊሾሙና ሊሽሩ ሲችሉ፤  ቢያንስ መሰረታዊ መብት አላቸውና ወደው ወይም መርጠው ስለተቀበሉት ስርአት የሚያስጨንቅ ነገር የለም፤ ካልበጃቸው ያንኑ መብታቸውን ተጠቅመው ይለውጡታልና!
አለመታደል ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ ቢያንስ ለግማሽ ምእተ አመት ለዲሞክራሲና ለተሻለ መልካም አስተዳደር ትግል ቢያደርግም ባለፉት ሁለት አጋጣሚዎች ድሉን እየተነጠቀ ለእኩይ አላማና ግብ የተነሱ፤የሀገርና የህዝብ  የውስጥ ጠላቶች አሸናፊ ሆነውበት፤ ለባሰ ውድመትና መከራ ዳርገውት፤ ሀገራዊ ህልውናውንም ማጥፋት በሚያስችል የታሪክ አዘቅት አፋፍ ላይ አቆሙት። ዲሞክራሲው ቀርቶ የአንዲት ኢትዮጵያ ህዝብነታችን፤ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር ባለቤትነታችን በቀጭን ክር ላይ የተንጠለጠለ እጣፈንታ ሆኖ አረፈው። ዜጎች ተወልደው ካደጉበት አገር እንደ ባእድ ስደተኛ ሀብትና ንብረታቸውን እየተቀሙ ሲባረሩ፤ በተፈጠሩባት ምድር መድረሻ እንዲያጡ ተደርገው በየጎዳናው ሲወድቁ እያየን ምንም ማድረግ ተስኖን አፍጠን ተቀምጠናል።
በደቡብ ኢትዮጵያ፤ አማራ የተባለ ዜጋ፤ በሶማሌ ክልል  ጂጂጋ ሱማሌ ያልሆነ ሁሉ ንብረቱ እየተቀማ፤ እየታሰረ ቶርች እየተደረገ፤ እዚያው ተወልደው ያደጉ አማሮችና ሌሎች ብሄረሰቦች ግፍ እየተፈጸመባቸው ይህንን ተከታታና የማይቆም በእቅድ የተያዘ ጥቃት ማስቆም የቻለ የፖለቲካ ድርጅትም ሆነ የሰብአዊ መብት ጥበቃ ድርጅት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ብቅ ባለማለቱ የኢትዮጵያውያኑ ሰቆቃ እየባሰ በመሄድ ላይ ይገኛል። ወያኔና የክልሉ የወያኔ ጉዳይ አስፈጻሚ  የሱማሌ ባለስልጣናትና ፖሊሶች በመተባበር ይህን ዘመቻ ሲያንቀሳቅሱ፤ ተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅቶችም ሆኑ አለም አቀፍ ሰብአዊ ድርጅቶች ድርጊቱን ለማስቆም ያንቀሳቀሱት ሁለገብ ዘመቻ የለም። የህውሀትና የክልሉ ቅጥረኞቻቸው ዘመቻ ግን አላቋረጠም። ባጠቃላይ ወያኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለውን ህዝብና ኢትዮጵያን የማጥፋት ቀጣይ ተግባሩን ያለምንም እንቅፋት ማከናወኑን ቀጥሏል።  እራሳችንንና ሀገራችንን ለማዳን መነሳት ያስፈራን በሚምስል መልኩ የወያኔ መንጋ መጨፈሪያ መሆናችን ቀጥሏል።
ያለ ህዝብ ምክርና ዝክር መላውን የሀገራችንን መሬት ለባእዳን አሳልፎ መስጠቱ ቀጥሏል። ነገ ልጆቻችንን በገዛ ምድራቸው ላይ እያሳደዱ እሚገሏቸው ባእዳንን በብዛት እያስገቡ ማስፈሩ ቀጥሏል። በፍርሀት ተውጠን፤ ሀሞታችን ሸንቶ፤ እኛ አባቶቻቸው፤ ወንድሞቻቸው ተቀምጠን የልጆቻችንን ቅርስ ምድር ኢትዮጵያን ወያኔ ሲቸበችበው ዝም ብለናል።
ጀግና ህዝብ ታግሎ ዜጎች ነጻ ዳኝነት የሚያገኙበት ሉአላዊ የሆነ የፍትህ ተቋም ይገነባል። ዜጎች ሁሉ በህግ ፊት እኩል የሚዳኙበት፤ መብታቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ ከሙስናና ከወገንተኝነት በጸዳ የፖሊስ ሰራዊት የአካልና የህግ ጥበቃ የሚያገኙበት፤  ስርአት ይገነባል። ዳኞች ከሙስናና ከአንድ ወገን ጉዳይ አስፈጻሚነት በጸዳ ህሊና ለዜጎች ደህንነት የቆሙ  መሆኑን ያለ ማንም ባለስልጣን ጣልቃ ገብነት በሚሰጡት  ነጻ ፍትህ ያረጋግጣሉ። ይህ በትግላችን እውን ሊሆን የሚገባው ስርአት ሀገራችንን እንደሰማይ እየራቃት፤ በመሄድ ላይ ይገኛል። በራሳችን ደካማነትና ፍርሀት።
በሀገርና በህዝብ ጉዳይ ላይ የሚተላለፉ ውሳኔዎች፤ የሚተገበሩ እርምጃዎች፤ ህግና ደንብን የተከተሉ መሆናቸውን እርግጠኛ ለማድረግ፤ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው ህዝብ እያያቸው፤ እየሰማቸው፤ እየተነገረው፤ እየተነጋገረባቸው ሲሆን ፍትሀዊነት ይሆናል። በመንግሰትነት የተሰየመው አካል ያስተላለፈው፤ የሚያስተላልፈው ውሳኔ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚነካው የህብረተሰብ አካል፤ ቀጥተኛ ኢንፎርሜሽን ቀድሞ ሲያገኝና የሀሳቡ ተካፋይ ሲሆን፤ ጥቅሙንም ደህንነቱንም ለመጠበቅ እድል ያገኛል። በህብረተሰብ ህይወት ላይ የሚተላለፍ ውሳኔ ሰፊና ጥልቅ ምክክር ያስፈልገዋል።
ልንታገሰው የሚገባ መንግስት፤ አስተዳደር፤ ከህዝብ ለሚመጡ ሮሮዎችና አቤቱታዎች የመብት ረገጣ፤ የፍትህ ጉድለት፤ የመሳሰሉ ችግሮችን ፈጥኖ መስማትና መፍትሄ ለመሻት መንቀሳቀስ የሚችል መሆን ይጠበቅበታል። በንቅዘት የበሸቀጡ ባለስልጣናት ከደሞዛቸው ጋር የማይመጣጠን ኑሮና ንብረት ሲያደረጁ ያየ ህዝብ፤ የሀገር ሀብት ለግል ጥቅም እየዋለ ነው ብሎ ቢያመለክት፤ መንግስት ውሎ ሳያድር እነዚያን ግለሰቦች የሀብታቸው ምንጭ ምን እንደሆነ እንዲያስረዱ ለዳኝነት የሚቆሙበትን የህግ ተቋም ማደራጀትና ጉዳያቸው ታይቶ ለጠያቂው ህዝብ ምላሽ የሚሰጥበትን ሂደት እውን ያደርጋል። ሌባውና ወንጀለኛው፤ ሙሰኛው እራሱ መንግስት ነኝ ብሎ ስልጣን ላይ የተጣበቀው ወገን በሆነበት ሀገር ከላይ የጠቀስኩት ነገር የማይታሰብ ነው። ብቸኛው አማራጭ አንባገነኑን ቡድን ከስልጣን አስወግዶ፤ በከርሰ መቃብሩ ላይ ህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ስርአት መገንባት ነው።
ቀጣይነት ላለው የህብረተሰብ እድገትና ሰላም አስፈላጊ የሚሆነው፤ የህዝብን ታሪክ፤ ባህል፤ ማህበራዊ አኗኗርና መስተጋብር፤ የለት ተለት ያኗኗር ዘይቤን ግንዛቤ ውስጥ የሚያካትት ውሳኔና እርምጃ የሚያራምድ አስተዳደር መኖር ነው።

በህብረተሰብ ውስጥ እጅግ የተለያዩና አንዳንዴም የተራራቁ ፍላጎቶች አመለካከቶች መኖራቸው የተፈጥሮ ህግ ነው። እያንዳንዱን የህብረተስብ ክፍል እኩል ማስደሰት አይቻል ይሆናል። እስላምና ክርስቲያን በጋራ በሚኖሩባት ሀገር ውስጥ የክርስትያኑን ህዝብ ፍላጎትና መብት ከግምት ውስጥ ባለማስገባት አንድ ገዢ ቡድን ተነስቶ በሸሪአ ህግ ነው መተዳደር ያለብን በሚል፤ የእስላም መንግስት ቢያውጅ፤ በአንዲት የጋራ ሀገር ውስጥ ያንዱ ወገን ፍላጎትና ጥቅም የሌላውን ወገን ጉዳትና ቅሬታ አስከተለ ማለት ነው ። ለእንዲህ ያለ ህዝብ ሁሉንም የሚያስማማው አለማዊ መንግስት ይሆንና ሁሉም የማምለክ ነጻነቱ ተከብሮለት ሲኖር ማለፊያ አሰራር ይሆናል።
የህብረተሰብ ደህንነት የሚረጋገጠው፤ እያንዳንዱ ክፍል ከህዳጣን እስከ ብዙሀን ሕዝቡን የገነቡ ብሄረሰቦች  እኩል መብትና ነጻነት ሲኖራቸው፤ በሀገራቸው እኩል የባለቤትነት ስሜት ሲኖራቸው፤ በባህላቸው፤ በቋንቋቸው፤ በሀይማኖታቸውና በኑሮ ደረጃቸው ምክንያት ያለመገፋት፤ ያለመገለል፤ መኖሩን በተጨባጭ ማየት ሲችሉ ነው።
በዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ቀና ብሎ እንደልቡ እየተናገረ መኖር የያዘ ዜጋ ወያኔ ብቻ ሆኗል። ሰፊው ህዝብ ተሸማቆ በመኖር ላይ ነው። በግል መኖሪያ ቤቱ ውስጥ እንኳ እንደፈለገ የፈለገውን ጮክ ብሎ ማውራት እያስፈራው መቷል። የወያኔ ጆሮ ጠቢዎች በየሰዉ ጣራ ስር ጨለማ ለብሰው እየተለጠፉ ዜጎች የሚያወሩትን ወሬ እየሰበሰቡ ለቅርብ ሀላፊያቸው ያቀርባሉ። ፈጥኖ ፈጥኖ ከውጭ አገር ስልክ የሚደወልላቸው ሰዎች ይተኮርባቸዋል። አንዳንዶች በቤታቸው ዙሪያ ማንም እንዳይቆም ስልክ ሲደወልላቸው ልጆቻቸውን አሰማርተው ነው እንደልብ የሚያወሩት።
ተጠያቂነት የጤናማ መንግስት ያስተዳደር ስራ ደንብ ነው። የመንግስት ተቋማትና  ባለስልጣናት ብቻም አይደሉም፡ የግል ድርጅቶች ማህበራትና ተቋማት ጭምር የሀይማኖት የእምነት እና የሙያ ማህበራት ጭምር ሀላፊነት ለጣለባቸው ወገን፤ ለሚያገለግሉት ህዝብና ለሚተዳደሩበት ህግ ተጠያቂ ናቸው። ተጠያቂነት ግልጽነትንና ለህግ ተገዥነትን ያካትታል። ተጠያቂነት የዲሞክራሲ ስርአት አንኳር ግብአት ነው። የመንግስት ባለስልጣናትና ሀላፊዎች እንደየደረጃቸው በህግ የሚሰጣቸው ስልጣንና ሀላፊነት አለ። ያ ህጋዊ ስልጣንና ሀላፊነት ለሚያስተዳድሩት ህዝብ አገልግሎት የሚሰጡበት ልክና ደረጃ ነው። ተጠያቂነቱ ስልጣናቸውን ባግባቡ እየተጠቀሙ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድዳቸው ያሰራር ፈርጅ ነው።
አሁን በሀገራችን ጥያቄው ተጠያቂነት አለ ወይስ የለም አይደለም። በሀገራችን ተጠያቂነት የለም። ስርአቱን ሙሉ ለሙሉ እከምናስወግድ ድረስ እንኳን ቢሆን እስካሁን ለፈጸማቸው ወንጀሎች ይህን ገዢ ቡድን እና ባለ ስልጣናቱን እንዴት ተጠያቂ ማድረግ ይቻላል? ተቆጥሮ ከማያልቀው ወንጀላቸው የቅርቡን “ጂሀዳዊ ሀረካት” እንውሰድና የዜጎችን መብትና ነጻነት፤ ሰብአዊ መብት በእጅጉ የረገጠ፤ ለይስሙላ አለ የተባለውን ፍርድ ቤት ውሳኔ በመሻር፤ በፍርድ ሂደት ላይ ያለን ጉዳይ በመገናኛ ብዙሀን በማሰራጨት ተራ የፖለቲካ ጠቀሜታ ለማግኘት መንግስት ነኝ ያለ ቡድን  የፈጸመው ወንጀል ነው። ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ማስታወቂያ ሚኒስትሩን በተዋረድ የተሳተፉትን በሙሉ ለፍርድ ማቅረብ ያስፈልጋል። ይህ ፊልም የታለመለት ወንጀል የሙስሊም ወንድሞቻችንን ሰብአዊ መብትና  የሀይማኖት ነጻነት መጋፋት ብቻ ሳይሆን ህዝብን ከህዝብ፤ ክርስትያንን ከሙስሊም ለማጋጨት ሆን ብሎ ይህ ስልጣን ላይ ያለው ማፊያ ቡድን ያዘጋጀው ወንጀል ነው። የህውሀት ምግብ ለስራ ሰራተኞች የተሰበሰቡበት ምክር ቤት፤ ስልጣኑ የሚፈቅድለትን ነገር ባለማድረጉ፤ የዚህን ወንጀል ፈጻሚዎች ለጥያቄ ባለማቅረቡ ለራሱም መጠየቅ የሚገባው፤ መበተን የሚገባው የመንጋ ጥርቅም ነው።
የወያኔው ተረት ተረት ህገመንግስት አንቀጽ 12 ንኡስ አንቀጽ 2 ማንኛውም ሀላፊና የህዝብ ተመራጭ ሀላፊነቱን ሲያጓድል ተጠያቂ ይሆናል ይላል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪዎች ናቸው። ሚኒስትሮችም በውሳኔአቸው ተጠሪዎችና ተጠያቂዎችም ናቸው። በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ወንጀል ይፈጸማል። ጠያቂም ተጠያቂም የለም። ወያኔን ከስልጣን በማስወገድ ለፈጸሙት ወንጀል ሁሉ ሁሉንም ለፍርድ በማቆም ተጠያቂነትን ማስተማር ይገባናል። ፖሊስ የህሊና እስረኞችን ቶርች በማድረግ፤ ያልፈጸሙትን ወንጀል እንደፈጸሙ አድርጎ በስቃይ እንዲናገሩ በማድረግና ያንን በቴፕ በመቅዳት፤ ማስረጃ አድርጎ ማቅረብ፤ ህዝብ በመገናኛ ብዙሀን እንዲሰማውና መቀጣጫ አድርጎት አርፎ እንዲቀመጥ ለማድረግ፤ ወደር የማይገኝለት ግፍ በንጹሀን ዜጎች ላይ በመፈጸሙ፤ የደህንነቱ ክፍል የዜጎችን የግል ሚስጢር ለመሰብሰብ፤ የስልክ፤ የኢሜል፤ የፖስታ መልክቶችን በመጥለፍ፤ በመስረቅ፤ በከፍተኛ ወጭ አንድ ሰላይ ለአምስት ዜጋ በመመደብ ህዝቡ የህሊና ሰላም አቶ እንዲኖር፤ በጭንቀት ተወጥሮ ስለግሉ ደህንነት እየሰጋ በወያኔ ገዢ ቡድን ላይ እንዳይነሳ ለራሱ ተሸብሮ እንዲኖ ሴራ በመኖንጎን፤ ዳኞች ህሊናቸውን ለጥቅም በመሸጥ የሀሰት ምስክርና የውሸት ክስ፤ የሀሰት ማስረጃ ተቀነባብሮ ሲመጣላቸው ህሊናቸው እያወቀ፤ የአረመኔዎቹ መንግስት ጠባቂና ተንከባካቢ በመሆን ንጹሀን ዜጎችን በሞትና በእድሜልክ እስራት ፍርድ በመቅጣታቸው፤ ሁሉም የጃቸውን ማግኘት ይገባቸዋል። ለፍርድ መቅረብ ይገባቸዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ እነዚህን በጉልበት ስልጣን ላይ ተጣበቀው፤ እየገደሉ፤ እያፈኑ፤ ወህኒ እያጎሩ፤ እያሸበሩ ስልጣን ላይ ለመዝለቅ የቆረጡ የህውሀት  አመጸኞችን በአመጽ አስወግዶ፤ እውነተኛው ፍትህ ርትእ የሚነግስበትን ስርአት ገንብቶ፤ ዛሬ ግፍ እየፈጸሙበት ያሉትን ወያኔና ቅጥረኞቻቸውን ሁሉ እግር ተወርች አስሮ ለዳኝነት ማቆም ያስፈልጋል።
የጊዜ ጉዳይ ነው። እድሜልኩን ተኝቶ ሲረገጥ የኖረ ህዝብ በአለም ላይ የለም።  የኢትዮጵያ ህዝብም ተረግጦ ለመኖር አይደለም የተፈጠረው:: ታፍኖ፤ ተረግጦ፤ ተገድሎ በዚህች በሰለጠነች አለም ውስጥ ለምእተ አመት ያህል በመኖር ሁሉንም መከራ አጣጥሞታል። ብዙ የግፍ ጽዋ ተጎንጭቷል፤ እየተጎነጨም ነው። አሁን የቀረው ነገር ማንንም ሳይጠብቅ አንድ ቀን መገንፈል። የቀረው ነገር…. በቃ! ብሎ በአንድ ድምጽ፤ አንድ ቀን መፈንዳትና እነኚህን የወረሩትን ትንኞች ከትከሻው ላይ ማርገፍ…. ማውረድ ብቻ ነው!
ኢትዮጵያ ለዘለአለም ትኑር!…ሞት ለዘረኞች!
lkebede10@gmail.com

ቦሌ ለሚ ኮብልስቶን በሚሰሩ ሰዎችና በአካባቢው ነዋሪዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት 8 ሰዎች ሞቱ

  በአዲስ አበባ ከተሰሩ የኮብልስቶን ሥራዎች መካከል (ፎቶ)
አዲስ አበባ በሚገኘው ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ስሙ ቦሌ ለሚ በሚባል አካባቢ ማክሰኞ መጋቢት 3 ቀን
2005ዓ.ም. ኮብልስቶን በሚሰሩ ሰዎችና በአካባቢው ነዋሪዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት 8 ሰዎች መሞታቸውንና
በርካታ ሰዎች መቁሰላቸው ተጠቆመ፡፡
በፍኖተ ነፃነት ዘጋቢዎች የተጠናቀረው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ የግጭቱ መንስኤ የሞባይል መጥፋት
እንደሆነ እና በዚህም ኮብልስቶን ትሰራ የነበረችን የአንዲት የአካባቢው ነዋሪ ሴት ጡት ሌላው ሰራተኛ በመቁረጡ
ህይወቷ ማለፉን ተከትሎ በአካባቢው ነዋሪዎችና በኮብል ስቶን በአዲስ አበባ ከተሰሩ የኮብልስቶን ሥራዎች መካከል(ፎቶ)ሰራተኞቹ መሀከል ግጭት ተነስቷል፡፡ በዛው ዕለት
ፀቡን ለማረጋጋት የሞከረ ፖሊስም በኮብልስቶን ተመቶ ወዲያው ህይወቱ ማለፉን ጠቁመዋል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ጉዳዩ ወደ ብሔር ግጭት ተለውጦ ፀቡ እስከ ሐሙስ መጋቢት 5 ቀን መዝለቁንና ህይወቷ
ያለፈው ወጣት የአካባቢው (ኦሮሚያ) ተወላጅ በመሆኗ ጉዳዩ ወደ ማኀበረሰቡ በመድረሱ በርካታ የአካባቢው ሰዎች
ከአያት ኮንዶሚኒየም እስከ ቦሌ ለሚ ድረስ ከበባ በማድረግ በሰራተኞች መካከል የኢህአዴግ አደራጅና ሰላይ
ናቸው የተባሉ 6 የወላይታ ተወላጆችን በመግደልና በርካታ ሰዎችን በማቁሰላቸው በአካባቢው ከ3 ተሸከርካሪ ያላነሱ
የፌደራል ፖሊሶች ግጭቱን ለማረጋጋት ቢገኙም ለማረጋጋት እንዳልቻሉ ሆኖም በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችን
ወስደው እንዳሰሩ የዓይን እማኞች ገልፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ እስከ አሁን ከፖሊስ ወገን የተሰጠ ማረጋገጫ
የለም፡፡
የዝግጅት ክፍሉ ጉዳዩ በቀጥታ ይመለከተዋል ወደ ተባለው ቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መረጃ ክፍል ስለጉዳዩ
ለማረጋገጥ ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም ለጊዜው አልተሳካም፡፡ ዘገባው ወደ ህዝብ እንዲደርስ እስከተደረገበት
መጋቢት 7 ቀን 2005ዓ.ም. ድረስ ቀደም ሲል በርካታ ሰዎች የኮብልስቶን ስራ ይሰሩበት የነበረው አያት ጨፌ እና
ቦሌ ለሚ
የሚባል አካባቢ ማንም ሰው እንዳይገባ የተደረገ ሲሆን ከሰራተኞች ጋር እዛው በሚገኝ ቀበሌ ለጊዜው ማንነታቸው
ያልታወቁ የመንግስት ባለስልጣናት እያወያዩ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
ችግሩ እስኪፈታም በአካባቢው እስከ ሰኞ መጋቢት 10 ቀን 2005ዓ.ም. ድረስ ስራ እንደለሌም ምንጮቻችን
ከስፍራው ጠቁመዋል፡፡

(ምንጭ፡ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ከአዲስ አበባ)

“ልጄ በእሳት ተቃጥላ እንድትሞት ተደርጋ፣ ቤቴን ተነጥቄና ንብረቴ ወድሞ ከሀረር ተባረርኩ” – የ67 አመቷ እናት

“ልጄ በእሳት ተቃጥላ እንድትሞት ተደርጋ፣ ቤቴን ተነጥቄና ንብረቴ ወድሞ ከሀረር ተባረርኩ ሲሉ አንዲት የ67 አመትባልቴት በተለይ ለፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ አስታወቁ፡፡
ወ/ሮ ኢትዮጵያ ይልማ የሚባሉት እኚሁ እናት የ75 ዓመት አዛውንት የሆኑት ባለቤታቸውም እንደ እሳቸው ሁሉ ጎዳና ላይ መውደቃቸውን ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዘጋቢ
ከዕንባቸው ጋር እየታገሉ አስረድተዋል፡፡
“በሐረር ከተማ ቀበሌ 17 ውስጥ ከ30 ዓመት በላይ ኖሬ፤ ሀብትና ንብረት አድርቼ እኖር ነበር አሁን ግን በአካባቢው
እንዳልኖር ተደርጌያለሁ” የሚሉት ወ/ሮ ኢትዮጵያ ይልማ “ከ30 ዓመት በላይ የኖርኩበትን ቤቴን የወረዳው
አስተዳዳሪ እና የወረዳው ፓሊስ አዛዥ አስጠርተው ቤትሽን ለወ/ሮ አኒሳ መሐመድ ሸጠሽ ግቢውን
እንድታስረክቢያት አሉኝ፡፡ እኔ ቤቴን የመሸጥ ሐሳብ የለኝም፡፡ ቤቴን ሸጪ የት እወድቃለሁ? አልሸጥም አልኳቸው
እንቢ ካልሽ ከአገራችን እናባርራሻለን በገንዘብ አልሸጥም ካልሽ በባዶሽ ተባረሽ ወደ አገርሽ ትሄጃለሽ አሉኝ፡፡ እኔ ሌላ
አገር የለኝም የምሄድበትም ቦታ የለኝም መንግስት ባለበት አገር ቤትሽን ተቀምተሽ ውጪ የሚለኝ የለም ብዬአቸው
ተመለስኩኝ” በማለት የችግሩ መነሻ ነው ያሉትን ጉዳይ ወደኋላ መለስ ብለው ያስረዳሉ፡፡ ጎስቋላዋ የ67 ዓመት
ባልቴት በመቀጠልም “በማግስቱ እኔ ቡና አፍልቼ፣ ባለቤቴም ጫማውን አውልቆ ፍራሽ ላይ አረፍ ብሎአል፤ አንድ
ፓሊስ በሩን በሰደፍ እና በእርግጫ መቶት በሩን በረገደው፡፡ ምንድነው? ብለን ስንወጣ ከ30 በላይ ፓሊሶች
ቤታችንን ከበውታል፡፡ ይህች ናት፡፡ ነይ ውጭ! ብሎ ለሁለት ሶስት ሆነው ጎተቱኝ፡፡ እባካችሁ ምን አደረኩ ብዬ
ስለምናቸው አንቺ ለህግ አልገዛ ያልሽ አመጸኛ ነሽ! ወንጀለኛ ነሽ እያሉ መሬት ለመሬት ጎተቱኝ፡፡ እባካችሁ ምንም

የሰራሁት ወንጀል የለም ብዬ ጮኩኝ፡፡ ጎረቤት ተሰበሰበ ምንድነው ብሎ ጠየቀ ማንም ምላሽ አልሰጠም” የሚሉት ወ/
ሮ ኢትዮጵያ ይልማ ሟች ልጃቸውን በሀዘን ተውጠው እያስታወሱ ይቀጥላሉ “ልጄ ባል አግብታ የምትኖረው ሌላ ቦታ
ነው፡፡ ቀን ቀን ምግብ እየሰራች ትሸጣለች ፓሊሶች እናትሽን ከበው እየደበደቡ ናቸው ብሎ ጎረቤት ሲደውልላት ሮጣ
መጣች፡፡ ደርሳ ምን አድርጋ ነው ብላ ብትጠይቅ ቤቱን አስረክቢ ስትባል እንቢ ብላ ነው አሏት፡፡ የተወለድንበትና
ያደግንበትን ቤት ከህግ ውጭ እንዴት እንነጠቃለን ብላ ስትጮህ ጥላው ሄዱ” በማለት በለቅሶ ያስረዳሉ፡፡
ወ/ሮ ኢትዮጵያ ይልማ በመቀጠልም “ያንለቱኑ ማታ ልጄ ምግብ የምትሸጥበት ቦታ ሁለት ሰዎች ተመጋቢ መስለው
ከገቡ በኋላ (ረመዳን የተባለ ፓሊስና እንዳለ ወ/ሮ ኢትዮጵያ ይልማ(ከሀረር ጠሰብአዊ መብት ጥሰት ተፈፅሞባቸው
የተባረሩ አዛውንት) ግርማ የተባለ ወጣት) ቤቱን አስረክቡ ስትባሉ አናስረክብም የምትሉት ለምንድነው ብለው
ረመዳን ልብሷና ሰውነቷ ላይ ጋዝ ሲደፋባት እንዳለ ግርማ የተባለው ላይተር ለኩሶ አቃጥለዋታል፡፡ ሳትሞት ሆስፒታል
ደርሳ ነበር፡፡ በማግስቱ አዲስ አበባ አምጥቼ ላሳክም መኪና ተከራይቼ ይዤ ስወጣ ፓሊስ እዚህ ትታከም እንጂ ከሐረር
አትወጣም ብሎ ከለከለኝ፡፡ እኔም ገንዘብ ካለኝ እንኳን አዲስ አበባ አሜርካን ወስጄ ባሳክም ለምን እከለከላለሁ ብዬ
ብጮህ ባለቅስ ማንም ሊደርስልኝ አልቻለም፡፡ ልጄ ህክምና አጥታ ሞተች፡፡” ብለዋል፡፡ ባልቴቷ ከልጃቸው ሞት በኋላ
የደረሰባቸውን በምሬት ያወጋሉ “እኔንም ከቤቴ አስወጥተው ቦታውን ሺጭላት ላሏት ሴት ሰጧት፡፡ አሁን ቦታዬ ላይ
ፎቅ እየተገነባ ነው፡፡ እኔና ባለቤቴ ግን ጎዳና ተጣልን፡፡ የአካባቢው ህብረተሰብ አዋጥቶ የሰጠኝን 3ሺ ብር እንድ
ፓሊስና አንድ ደላላ መጥተው ነጠቁኝ፡፡ ሐረር ውስጥ አደሬ ወይም ኦሮሞ ካልሆንክ አቤት የሚባልበት ቦታ የለም፡፡
አማራ ነው ከተባለ ሁሉም ባለስልጣን በደረሰበት ግፍና ስቃይ ይስቅበታል፡፡ በደርግ ጊዜ የሐረር ፓሊስ አዛዥ ትግሬ
ነበር፤ የማረሚያ ቤት አዛዥም ትግሬ ነው፡፡ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ትግሬ ነው፡፡ ለምን ትግሬ ሆነ ያለ አንድም ሰው
የለም፡፡ ዛሬ በሀረር በየትኛውም መስሪያ ቤት አማራ ባለስልጣን የለም፡፡ ባለቤቴ ኦሮሞ ነው፡፡ ልጆቼም ኦሮሞ ናቸው፡፡
እኔ አማራ በመሆኔ ብቻ ይህ ሁሉ ጉዳት ተፈጸመብን፡፡” የሚሉ ወይዘሮዋ የተፈፀመባቸው የሰብአዊ መብት ጥሰት
ዘራቸውን መሰረት ያደረገ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ አክለውም “አዲስ አበባ መጥቼ ለእንባ ጠባቃ ተቋም አመለከትኩኝ፡፡
ፌደራል እንባ ጠባቂ ተቋም እንዴት እንዲህ ይፈጸማል ብለው ይዘውኝ ሐረር ተመለሱ፡፡ የቤቴ ካሳ እንዲከፈለኝ
ተወሰነልኝ፡፡ የክልሉ ባለስልጣናትም እሺ ይፈጸምሎታል ብለው ቃል ገቡልኝ፡፡ እንባ ጠባቂዎቹ ወደ አዲስ አበባ
ተመልሱ፡፡ እነሱ ከተመለሱ በኋላ ግን ምንም መፍትሄ አልሰጡኝም፡፡ በድጋሚ አዲስ አበባ መጥቼ ለእንባ ጠባቂ
ተቋም ባመለክት እነሱም ውሳኔያቸውን እንደ አጀማመራቸው ሊያስፈጽሙልኝ አልቻሉም፡፡ ጉዳዬንም ለመስማት
ፍቃደኛ አልሆኑም፡፡” በማለት የበደላቸውን ስፋት ለፍኖተ ነፃነት ዘጋቢ በዝርዝር አስረድተዋል፡፡
“ዛሬ እኔ አዲስ አበባ ላይ ባለቤቴ ደግሞ ሐረር ላይ ጎዳና ላይ ነን፡፡ መፍትሔ ማግኘት አልቻልኩም” ሲሉ ተስፋ
መቁረጥና ምሬት ተሞልተው በለቅሶ የመንግስት ያለህ … የህዝብ ያለህ በማለት ጥያቸውን ያቀርባሉ፡፡
የወ/ሮ ኢትዮጵያ ይልማን ጉዳይ አስመልክቶ የፌደራሉ እንባ ጠባቂ ተቋም ለሐረሪ ክልላዊ መንግስት ጸጥታ ቢሮ
የጻፈውን ደብዳቤ እንደተመለከትነው ደብዳቤው ከዚህ በፊት ስለጉዳዩ ተጠይቆ መልስ አለመስጠቱን በማስታወስ
አሁን በድጋሚ በ 15 ቀን ውስጥ መልስ እንዲሰጥ ያለበለዚያ በህግ በተሰጠው ስልጣን መሰረት አስፈላጊውን እርምጃ
እንደሚወስድ የሚገልጽ ነው፡፡ ሆኖም የእምባ ጠባቂ ተቋም ውሳኔ ባልቴቷንና ባለቤታቸውን ከጎዳና ተዳዳሪነት
የሚታደግ አልሆነም፡፡ በጉዳዩ ላይ የፊደራል እንባ ጠባቂ ተቋም አስተያየት እንዲሰጥበት ወደ ተቋሙ ህዝብ ግንኙነት
ክፍል በማምረት ባለሙያዎችንም አነጋግረን ነበር፡፡ በቅድሚያ ያነጋገርናቸው የህዝብ ግንኙነት ባለሞያ ጉዳዩን
ከስሙንና በእጃችን ያለውን መረጃ ከተመለከቱ በኃላ ወደ ሌላው የህዝብ ግኑኝነት ባለሙያ መሩን፡፡እሳቸውም
በተመሳሳይ ሁኔታ ማስረጃችንን ከተመለከቱ በኃላ ይህንን ጉዳይ የሚያውቁት ዋና አማካሪው አቶ ቀነአ ሶና ናቸው፡፤
እሳቸውን አነጋግሩ አሉን፡፡ አቶ ቀነአን በወቅቱ ማግኘት አላቻልንም፡፡ በሌላ ጊዜ ተመልሰን ቢሮአቸው ያሉትን
የተቋሙን ሰራተኛ አቶ ቀነአን እንደምንፈልግ አስረዳናቸው፤ አቶ ቀነአን ወደ መስክ ወጥተዋል፡፡ ሰሞኑን ቢሮ
አይገቡም አሉን፡፡ በዚህ ምክንያት የፌደራሉን እንባ ጠባቂ ተቋም አስተያየት ማካተት አልቻልንም፡፡ ጉዳዩ ተከቷል
ወደ ተባለለት ወረዳ ፖሊስ ደወልን የሐኪም ወረዳ ፖሊስ ወንጀል መከላከል ሀላፊ የሆኑትን ሳጂን ተሾመ ሰይፉን
አግኝተናቸዋል፡፡ ወ/ሮ ኢትዮጵያ ይልማ ደረሰብኝ የሚሉትን በደል ወቅቱን ጠቅሰንም አስረድተናቸዋል፡፡ ሆኖም
ሳጂን ተሾመ ሲመልሱ ‹‹እኛ ፖሊሶች በየሁለት ዓመቱ እንቀያየራለን፡፡ አሁን በዚህ ወረዳ ያለነው ከሁለት ዓመት
ወዲህ ተዛውረን የመጣን ነን፡፡ ስለዚህ ጉዳይ የሚያውቅ ሰው የለም፡፡ በአሁኑ ወቅት በወረዳችን ሮመዳን የሚባል
ፖሊስ የለም፡፡ ምናልባት የወረዳው መስተዳድር የሚያውቁት ነገር ካለ እነሱን ብትጠይቁ ይላል፡፡›› በማለት
መልሰውልናል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ያሉትን የወረዳውን አስተዳዳሪ አቶ ኢስማኤልንም ስለጉዳዩ ጠይቀን በሰጡን መልስ
‹‹እኔ በቅርብ ጊዜ ነው የመጣሁት ስለዚህ ጉዳይ የማውቀው ነገር የለም፡፡ የሚያውቁት ነገር ካለ ከእኔ በፊት የነበሩትን
ጠይቋቸው›› ብለውናል፡፡ ከእሳቸው በፊት የወረዳው አስተዳዳሪ የነበሩትን አቶ ጀማል አህመድን አፈላልገን
ጠየቅናቸው፡፡ “እኔ ድርጊቱ ተፈፀመ በምትለኝ ወቅት እዚያ ወረዳ አልሄድኩም፡፡ ስለዚህ ጉዳይ የማውቀው ነገር
የለም፡፡ ከእኔ በፊት የነበረውን ሰው አፈላልጋችሁ ጠይቁ ብለውናል፡፡” ከእሳቸው በፊት የነበሩትን አስተዳዳሪ ማንነትና
አድራሻ ማግኘት ባለመቻላችን ዜናውን በተገቢው ሁኔታ ሚዛናዊ ማድረግ አልቻልንም፡፡
ምንጭ፡ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ከአዲስ አበባ

Mar 16, 2013

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች የትምህርት ማቆም አድማ መቱ፤ ኮሌጁ በፖሊስ ተከቧል

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እየታመሰ መሆኑ ተሰማ። ኢሳት ራድዮ ዛሬ እንደዘገበው ተማሪዎቹ የአስተዳደር
ጥያቄ በማንሳት ረቡዕ እለት የተጀመረው የትምህርት ማቆም አድማ እስከዛሬ አርብ ድረስ ዘልቋል። የመንፈሳዊ ኮሌጅ
ተማሪዎች ለዚህ ዓመት ካነሳሳቸው ምክንያቶች መካከል ከአስተዳደር ጥያቄ፣ ከምግብ ጥራት፣ ከአስተማሪዎች ብቃት
በተጨማሪ የአዲሱ ፓትርያርክ ጉዳይም ሊያያዝ እንደሚችልም ኢሳት ዘግቧል። ተማሪዎቹ ምግብ ተከልክለዋል።
የኢሳትን ዘግባ እንደሚከተለው አቅርበነዋል።












ዜናውን ላልሰማ ያካፍሉ

Mar 15, 2013

ትግላችን ይቀጥላል

ድምፃችን ይሰማ

አንዋር መስጊድ ነገ ጭር ይላል!
የድምጻችን ይሰማ ሕዝባዊ መነሳሳትና ተቃውሞ በግፍ ለእስር በተዳረጉት መሪዎቹ ቃል ኪዳን ታስሮ የስኬት ጉዞውን ቀጥሏል፡፡ ትግላችን ድንበሮችን አቋርጦ ክልሎችን ከክልሎች፣ ከተሞችን ከከተሞች እንዲሁም ሕዝቦችን ከሕዝቦች ከምንም በላይ ልቦችን ከልቦች ጋር አስተሳስሮ እየነጎደ ነው፡፡ አልሀምዱሊላህ! ይህን ክብር እና ስኬት ያሳየን አላህ (ሱ.ወ) ምስጋና ይገባው፡፡ በዚህ ሳምንት በሚደረጉ ሁሉን አይነት ተቃውሞዎች የምናንጸባርቀዉ ዋነኛ ሀሳብም ትግላችን እያደገ፣ መስዋእትነታችንም እያየለ ግን ደግሞ ጥንካሬያችንና ስኬታችን በአስተማማኝ መሰረት ላይ እየተገነባ መሆኑን ማሳየት እና ትግላችንም እንደሚቀጥል ማስገንዘብ ነው፡፡ትግላችን ይቀጥላል
በዚህም መሰረት በአዲስ አበባ የሚኖረው ተቃውሞ ወደ ታላቁ አንዋር መስጊድ ባለመሄድና መስጊዱን ጭር በማድረግ የሚገለጽ ነው፡፡ ዘወትር ለተቃውሞም ሆነ ለጁምአ ሰላት የምንሄድ ሁሉ የነገውን የጁምአ ሰላት በሌሎች አማራጭ መስጊዶች በመስገድ ብቻ የሚገለጽ ይሆናል፡፡
ተቃውሞአችን በድምጽ በሚደረግባቸው ከተሞች የሚኖረው ጠንከር ያለ ተቃውሞ ዝርዝር የአፈጻጸም መርሐ ግብሩ ይህን ይመስላል፡፡
ኢማሙ የጁመዓ ሰላት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ በአንድ ከፍ ያለ ድምፅ:-
• የአላህን ታላቅነት ለማሳየት ለሦስት ደቂቃ ‹‹አላሁ አክበር!››
• የተቃውሞችንን መሪ ቃል እና የተቃውሞችንን መንፈስ ለመግለጽ ለሦስት ደቂቃ ‹‹ድምፃችን… ይሰማ!››
• መንግስተ የመብት ጥያቄ ሂደታችንን ከሽብር ተግባር ጋር በማያያዝ ሕዝቡን አሸባሪ ለማለት ደፍሯል እኛ ግን ሰላም መርሁ የሆነው የኢስላም ተከታዮች መሆናችንን ለማስገንዘብ ለሦስት ደቂቃ ‹‹ኢስላም… ሠላም!››
• መሪዎቻችንን ጨምሮ ያለጥፋታቸው ሙስሊም በመሆናቸው ብቻ ታስረው በመላዋ አገሪቱ ወህኒ ቤት የሚገኙ ሁሉ እንዲፈቱ ለሦስት ደቂቃ ‹‹የታሰሩት….ይፈቱ!››
• ብሄራዊ ውሸታቸውን በየእለቱ እየጋቱን ላሉት መንግስት ብዙሀን መገነኛዎች ከሀሰተኛ ዘገባዎች እንዲቆጠቡ ለመንገር ለሦስት ደቂቃ ‹‹ውሸት …. በቃን!››
• ጥያቄዎቻችን በማያዳግም መልኩ እስካልተመለሱ ድረስ ትግላችን እንደማይቋረጥ እና ሕዝባዊ መሰረት ላይ የተገነባ መሆኑን ለማመልከት ለሦስት ደቂቃ ‹‹ትግላችን….ይቀጥላል!››
• በመጨረሻም ሁላችንም ባለንበት ለሦስት ደቂቃ ወደ አላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ የመጣብንን በላእ እንዲያነሳልን ዱዓ በማድረግ የዕለቱ ተቃውሞ ይጠናቀቃል-ኢንሻ አላህ፡፡
ይህን በቁጥር በርካታ በሆኑ ከተሞች የሚደረገው ተቃውሞ ላይ ሁሉም በተጠቀሱት ከተሞች ላይ የሚገኝ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ሁሉ በነቂስ ወጥቶ እንደሚሳተፍበት ጥርጥር የለንም፡፡ ይህ እለት ዳግም አንድነታችንን፣ ጥንካሬያችንና ለመሪዎቻችን ያለንን ታማኝነት የምናሳይበት ነው፡፡
አላሁ አክበር!

Mar 13, 2013

Tamagne Beyene: Ethiopian Hero


by MeKonnen H. Birru, PhD

Artist Tamagne Beyene Ethiopian Hero
The thing about a hero, is even when it doesn’t look like there’s a light at the end of the tunnel, he’s going to keep digging, he’s going to keep trying to do right and make up for what’s gone before, just because that’s who he is.
Joss Whedon
A hero is a defender. A hero is a protector. A hero is a rescuer. The legendary Ethiopian writer Dr. Haddis Alemayehu (1902 – 2003) portrayed Gudu Kassa as a ‘hero’ in his classical work Fiqir Iske Meqabir (Love Unto Grave’. Gudu Kassa (Kassa Damte) was a nobleman by birth but refused all for the sake of his progressive ideas. He fought for individual liberty and freedom. He became a defender of his people, not his class, nor his race, nor his family power. He fell in love and married a working class woman while he was a noble because he saw love in her, nothing else. To him and so many millions of Ethiopians, love is the essence of life and the root of every particle, motion, foundation, liberty, freedom and expression. Love is our Ethiopian culture and our norm. And now these three remain; faith, hope, and love. But the greatest of these is love (1 Corinthians 13:13).
In our times too, we have several heroes who believe in such love, liberty, faith, and peace. They are crying for our liberty. They are crying for our believed country: Ethiopia. They cry for love, equality, and fairness. Tamagne Beyene is one among many. Tamagne was born in Ethiopia; grow up in Ethiopia, and becoming Ethiopia. His entire families were from Ethiopia. They all love their country and understand the beauty of love, kindness, respect, and compassion. They are the true faces of Ethiopia.
On the other hand, we have brothers and sisters who decided to be dark and evil. They want us to go back. They want us to count our bones. They want us to be divided in terms of race, power, province, and religion. I tell you such are not from God but evil. ‘Turn from evil; do good; seek peace and pursue it (Psalms 34:14). I tell you again anyone who purposefully tries to deprive our liberty, unity, and one nation for the sake of security are wrong and from evil. Benjamin Franklin stated any society that would give up a little liberty to a gain a little security will deserve neither and lose both.’
Lord Acton wrote, “Liberty and good government do not exclude each other, and there are excellent reasons why they should go together. Liberty is not a means to a higher political end. It is itself the highest political end. It is not for the sake of a good public administration that it is required, but for the security in the pursuit of the highest objects of civil society, and of private life.”
Long live mother Ethiopia.
God be with us.

Mar 11, 2013

ለኢትዮጵያ እንድረስላት ይህን ሳናደርግ የቀረን እንደሆነ ግን ህሊና ቢስ ነን ፍሬ ቢስ ነን ወይም ደግሞ ከሃዲ ነን

በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁናቴ ህዝቡ ዕድሉን አግኝቶ ወደውጭ የወጣ እንደሆነ ወደ ዓገር ቤት ተመልሶ ቢገባ የጭንቅላት በሽተኛ ወይም እንደ እብድ አልያም እንደ ሞተ

autor yared elias Brehane
ያሬድ ኤልያስ
ሰው ተቆጥሮ የህድር ጡሩንባ ተለፍፎ ዘመድ አዝማድ ተሰባስቦ የሚላቀስበት አልያም ደግሞ ከቤተሰብ ትዳር አንስቶ የሰፈር ሰው ትንሽ ትልቁ የስራ ባልደረባ ከታክሲ ሹፌር እስከ ዶክተር እስከ ትልቁ የወያኔ አገዛዝ ሚኒስቴር ድረስ እንደዘመኑ በሽታ ታይቶ የምትገለልበት ወሬው ሁሉ እንትና ደቡብ አፍሪካ ጠፋ በሞያሌ በሱዳን ሊቢያ  እየተባለ ስንቱ  ተስፋ ቆርጦ የሱሰኛ ተገዢ የሚደረግበትዘመን። ሌላው ይቅርና  እትብቱ ወደተቀበረበት ሃገር ለመመለስ እንኳን የወያኔ ገዢ ፓርቲ 10 ግዜ እንድናስብ የሚነግረን ወቅት  እንደነገሩ ተበልቶ አንዲት ለስላሳ ለመጠጣት 20 ግዜ የሚታሰብበት ቢራ ለመጠጣት ዱቤ ለመጠየቅ 40 ግዜ የሚታሰብበት ሃገር።  ስለ እውነት ስለነጻነት ቢጠየቅ ደግሞ ምን ሊሆን እንደሚችል መልሱን ? ..ለነሱ……… fየሚባለበት ግዜ ።
መቼስ አገሩ ላይ መኖር የሚጠላ ስው ያለ አይመስለኝም ግና ገና አካሉ አገሩ ላይ ቍጭ ብሎ መንፈሱ ውጭ አገር ያለውን ስንቱ ይቍጠረው። በውጭ ሃገር የሚኖረውማ  ወደ ሃገሩ ተመልሶ ሃገሩ ላይ ሃገሩን ወገኑን ለማገልገል የፈለገ ሰው ሃገሪቷ ላይ መኖር የማይችልበትን የጥቂት ዘረኛ ወያኔ አገዛዝ መንግስት የሚኖርባት በመሆኑ ለማድረግ አይችልም። በዛ ላይ ሰሞኑን ያየሁት የሰለሞን ቦጋለ እና ሳምሶን ቤቢ ፊልም በጣም ሲከነክነኝ ነው የዋለው አዎ የዚህ ደራሲ በፈለገው መልኩ ይጻፈው እኔ በተረዳውት ግን ለዚያች አገር ለዛ ህብረተሰብ ነጻነት ያስፈልገዋል ። መልዕክቱን በፈለጉት መልኩ ያስተላልፉት ግን በደንብ የሚታይ ነገር ነበረበት ስለነጻነት ብሩህ ተስፋ ።
ለነገሩ ወያኔዎች አገራቸው አይደልም  የመጡበትን ዓላማ አሳክተዋል።  የስራውን ይስጠውና ሟቹ ስሙን ቄስ ይጥራውና አገሪቷን በዘር በዓይማኖት በብሄር ከፋፍሎ ሰዉ በጎሪጥ እንዲተያይ አድርጎት እሱ ወደማይቀረው ሄዷል ምን አለ የሱ ተከታዮችም ይሄ መኖሩን አውቀው ወደ ህዝቡ በተመለሱ። አገሪቷማ  ስንቱን አሳድጋ እንጡራ አብቷን አውጥታ ያስተማረችውን የተማረ ዓይል ስንት ድግሪ ፕሮፌሰር ያደረገችውን ሃገር እየተወ መመለሻም መቀበሪያም ላትሆነው ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ተሰድዶ በአሁኑ ሰዓት በስደት ላይ ይኖራል ። እንዲህም ሆኖ ለሃገር የተቆረቆሩ የሚመስሉ ከሃዲ ሆዳም እነዚህን ሰዎች ባሉበት ቦታ እንኳን እንዲቀመጡ አያደርጓቸውም እንዲያውም ብለው ወያኔ ለሃገር እንደሚቆረቆር ያወራሉ  ለነገሩ የትኛው የወያኔ ሃገዛዝ መንግስት ነው ለሃገሩ የሚቆረቆረው በዛ በበረሃ የማንም ተኩስ መለማመጃ ሆነው እነደሻማ ቀልጠው ሲቀሩ ሴት እህቶቻችን ማንም ሳይደርስላቸው እንደበግ መሬት ለመሬት ሲጎተቱ ዝም ብሎ  በደፈናው ሃገር ሃገር ማለት መብራትና ውሃ በሌለበት ሰዉ በፈለገውና በሚታየው መልኩ የራሱን ሃሳብ መግለጽ የማይችልበት ከታክሲ ዳቦና ወዘተ የመሳሰሉት ሰልፍ በስተቀር 3 ሰው እንኳን አብሮ ቆሞ ማውራት የማይቻልበት ወያኔ ለህዝቡ ካልሰረቀና ሙስና ካልሰራ መሻሻል የማይቻልበት ሃገር ለዚች አገር ነው ተቆረቆረ የሚባለው። ውድ ወገኖች ስለዚህ ለዘመናት ባአባቶቻችን በጥረታቸው የተገነባች የገነቧትን ሃገር ወያኔ ደግሞ በግዴለሽነት በዘረኝነት እየፈራረሳት ይገኛል ። ህዝቡንም በትልቅ የሞራል እስር ቤት ውስጥ አስረውት ይገኛል ከዚህ እስር ቤት የሚያወጣው አንዳች አይል ያስፈልገዋል ። የኢትዮጵያን ህዝብ ክብር በማንኛውም መንገድ ማስመለስ ይኖርብናል ህዝቡ በእየለቱ በሚሰማው ነገር ልቡ  ሸፍቷል ከጥቂት ሆዳሞች በስተቀር ስለዚህ ይኼ የነገዋ ኢትዮዽያ ቀን ነዉ የኔ የእናንተ ብ ቻ ሳይሆን የመላዉ ኢትዮዽያ ጥያቄ ነዉ እንድረስላት ይህን ሳናደርግ የቀረን እንደሆነ ግን ህሊና ቢስ ነን ፍሬ ቢስ ነን ወይም ደግሞ ከሃዲ ነን።  click here more
እግዚሃብሄር ኢትዮጵያንና ተከባብሮ የሚኖረውን በማንኛውም ዓይማኖት ላይያለውን ህዝብ ይባርክ
አሜን
ያሬድ ኤልያስ
nome telemark dagsrud

Mar 9, 2013

you want buy children from ethiopia ?

Every agency defines and lists fees differently, which causes confusion when comparing costs. Despite the wide-ranging variables, we have compiled an estimated total that we hope includes every necessary expense related to the adoption. No additional adoption service fees will be required to be paid in Ethiopia. 

Fees and Estimated Adoption Expenses 
Application $ 300 
Adoption study * $ 2,500 - 2,900 
Dossier fee $ 3,000 
Program Fee $ 11,900 
Documents, Certifications and Notarizations $ 100 – 300 
USCIS fees $ 830 
Post placement * $ 1,200 - 1,400 
Travel cost $ 8,000 - 15,000 
Estimated total $ 25,820 - 33,620
* if provided by Holt International Children's Services 

Adoption Expenses Explained

Application 
Holt will open a file for your family and conduct an preliminary assessment that provides initial assurance that we will be able to place a child with you. Due when first applying. Non-refundable


Adoption Study

Often called a “homestudy,” a professional social worker will help your family understand international adoption and assess your ability to parent a child not born to you. The social worker will prepare a document (the adoption study), which is required by virtually ever
y country in the world in order to adopt.





Holt performs the adoption study if you live in a state served by a Holt branch office (Arkansas, California, Iowa, Kansas, Nebraska, Missouri, New Jersey, Oregon, South Dakota). If you live in another state, the adoption study will be provided and billed by an agency approved by Holt. 

Due before the start of group meetings or adoptive study interviews. 


Dossier fee

This fee covers Holt costs to facilitate your adoption with government officials and our partner agencies both in the United States and abroad, coordinating services with your local social worker, administrative/office expenses and telephone expenses. 

Due when Holt approves your adoption study. Non-refundable if you withdraw.


Program fee

This fees covers costs in your child’s country of birth: 


• background investigation and identification of child
• social services
• legal fees
• accepting legal responsibility for the child
• working with government and agency authorities
• translation
• child care, medical expenses (portions not covered by sponsorship)
• passport and U.S. visa fees in the child's country
• in country travel arrangements and assistance 
A small portion of the fee will help develop Holt Ethiopian childcare projects.

Due when you accept the assignment of a child.

Documents, Certifications and Notarizations 
These are expenses related to obtaining legal and vital documents and getting the necessary certifications and notarizations to complete your dossier. These fees are paid to the appropriate government authority.


Postplacement fee

Several official reports are required after your child is home. This fee pays for social worker visits and documentation. If you live in a state not served by a Holt branch office, postplacement services will be provided and billed by an agency approved by Holt.
 

Travel

Holt staff will guide you through making travel arrangements, and provide assistance throughout your stay in Ethiopia. Airfare, lodging and meal expenses are paid directly to the vendors you select.
you can watch here more

ጥቃት በየተራ እስከመቼ?

ባለፉት 21 የወያኔ የግዛት አመታት አይነቱና መጠኑ ይለያይ እንደሆነ እንጅ ጥቃት፣ ግፍ፣ በደልና እብሪታዊ የመብት ገፈፋ ያልደረሰበት ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ክፍል የለም። ገበሬው፣ የመንግስት ሰራተኛው፣ የፋብሪካ ሰራተኛና በየዘርፉ የእለት ጉርሱን አሳዶ የሚኖረው ሁሉ የወያኔን የሰቆቃ ግፍ በትር በየተራ አይቶታል፣ እያየውም ይገኛል። የኢትዮጵያ ህዝብ በድህነት አንጀቱ ለፍቶ ያቋቋማቸው ተቋሞቹ እየፈራረሱ ለወያኔ አገዛዝ እንዲመቹ ሆነው ሲጨፈላለቁም አይተናል።
ወያኔ ይህን ሁሉ ያደረገው “አንዱን በአንዴ” በሚል ስልት ነው። መምህራንን ሲያጠቃ የፋብሪካውን ሰራተኛ ተመልካች ያደርገዋል፤ ገበሬውን ሲያጠቃ ከተሜውን ዝም ይለዋል፤ ከተሜው ላይ ሲዘምት ገበሬው ተመልካች ይሆናል፤ ቤተክርሰቲያን ላይ ሲዘምት ቤተ ሙስሊሙ ይመለከተዋል፤ የቤተ ሙስሊሙ የበደል ተራ ጊዜ ቤተክርስቲያን ተመልካች ትሆናለች። ይህ ወያኔን እስከዛሬ ያደረሰው ስልት ነው።
አራዊታዊው የወያኔ አገዛዝ በተመቸውና ይጠቅመኛል ብሎ በአሰበ ሰአት ሁሉ የውብ ህዝብነት ምልክታችን የሆነውን የባህልና የቋንቋ ስብጥርነታችንን እርስ በርስ ለማናከሻነት ሊጠቀምበትም ሞክሯል፤ በተወሰነ ደረጃ አልሰራላቸውም ማለት ያስቸግራል፡፡
ወያኔዎች ከፋፍሎ መግዛትንና በየተራ ማጥቃትን በኪነ ጥበብ ደረጃ አሳድገነዋል ብለው ያምናሉ። በህዝብ ወገን ያለነውም የዲሞክራሲና የነጻነት ሃይሎች ለዚህ አልተመቸንም ማለት ያስቸግራል፡፡ ይህንን ከፋፍሎ የማጥቃት ግፍ በጋራ ለመመከት ያደረግነው ጥረት ህዝባችን ላይ እየደረሰ ካለው ጥቃት ጋር ቢያንስ የሚመጣጠን አይደለም።
የወያኔ መሪዎች ዛሬ ስልታቸውን በማሻሻል አደገኛ ጭዋታ በቤተ እምነቶቻችን ዙሪያ መጫዎት ጀምረዋል። የቤተክርስቲያን እና የአቢያተ መስጊዶችን አስተዳደር በካድሬዎቻቸው ለመቆጣጠር ከሚያደርጉት ሳይጣናዊ ተግባር በተጨማሪ ህዝቡ ሃይማኖት ለይቶ እንዲባላ ለማድረግ በእጅጉ የሚቀፍ ፕሮፖጋንዳ እያካሄዱ ነው። ፍጹም ምሳሌያዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የሲቪል መብት ጥያቄ እንደባዕድ መሳሪያነትና እንደ ሽብርተኝነት ለማሳየት እየሞከረ ይገኛል። በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሙሉ እጁን በማስገባት የተጀመረውን እርቀ ሰላም በማፍረስ የራሱን እንደራሴ ሰይሟል። ይህም አልበቃ ብሎት ለዘመናት በመከባበር የኖረውን ሙስሊሙንና ክርስቲያኑን እርስ በርስ ለማጋጨት ሌት ተቀን እየሰራ ይገኛል።
ዛሬ ከመቸውም በበለጠ ሀገራችን ወደማትወጣው አደጋ እየተገፋች ነው። ይህንን ወያኔ ያዘጋጀልንን የክፍፍልና ግጭት ድግስ ለመመከት ይበልጥ በአንድነት የምንቆምበት እና የምንታገልበት ግዜ ዛሬ ነው፡፡
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ለወያኔ የ”ከፋፍለህ በየተራ ቀጥቀጥ” ፖሊሲ መድሃኒቱ አንድ ሆኖ በአንድነት አሻፈረኝ ብሎ መነሳት መሆኑን ያምናል፡፡ ወያኔ ጉልበቱ የኛ መከፋፈልና ለክፍፍሉ መመቸት መሆኑን ያምናል፡፡ እኛ ስንተባበርና ልዩነታችንን ለመጠቀም የሚያደረገውን ሙከራ ስናከሽፍና አንዱ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት የሁላችንም ነው ብለን የተነሳን እለት ወያኔ የለም።
ግንቦት 7 ንቅናቄ ወያኔ በፈቃዱ የማይታረም ፋሺስታዊ አምባገነን መሆኑን ከተረዳ ሰንብቷል። በመሆኑም ወያኔን በማስገደድ ወይም በማስወገድ ነጻነታችንን መቀዳጀትና ነጻ ሀገር እንዲኖረን ማድረግ አለብን ብለን እናምናለን። ለዚህ ትግልም ማንኛውንም መሰዋእትነት ለመክፈል ተነስተናል። ነጻነትና ኮርተህ በነጻነት የምትኖርባት ሀገር እንድትኖርህ የምትወድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ተቀላቀለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ጋምቤላ አሁንም በወያኔ ወራሪ ሠራዊት እየታመሰች መሆኗ ተሰማ


በ1996 ዓም ከ400 በላይ አኝዋኮችን በግፍ የጨፈጨፈዉ የወያኔ ወራሪ ሠራዊትና ልዩ ኃይል ከሰሞኑ በብዛት ወደ ጋምቤላ በመዝመት ሠላማዊ ዜጎችን በተለይ የአካባቢዉን አርሶ አደሮች እየያዘ ማሰርና መግደል መጀመሩን ከአካባቢዉን እየሸሹ ጫካ የገቡ ዜጎች ለኢሳት ሬድዮና ቴሌቪዥን ስልክ እየደወሉ በሚልኩት ዜና ገለጹ። በተለይ ካለፈዉ አርብ ጀምሮ ፌዴራል ፖሊስ፤ መከላከያ ሠራዊትና የደህንነት ልዩ ሀይሎች ተቀናጅተዉ በጋራ በወሰዱት የማጥቃት እርምጃ ከቤት ቤት እየተዘዋወሩ ተቃዋሚዎችን ይረዳሉ ወይም ታጣቂዎችን ሊቀላቀሉ ይችላሉ ብለዉ የጠረጠሯቸዉን ሠላማዊ ዜጎች ማሰራቸዉንና እራሳቸዉን ለማዳን የሞከሩ ሰዎችን ተኩሰዉ መግደላቸዉን ከአካባባዉ የደረሰን ዜና ጨምሮ ያስረዳል። በአሁኑ ወቅት የወያኔ ወራሪ ሠራዊት በብዛት ወደ ጋምቤላና አካባቢዉ እየዘመተ ሲሆን የአካባቢዉ ህዝብም እራሱን ለማዳን ጫካ እየገባ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የወያኔ ወራሪ ሠራዊት ካለፈዉ ዐርብ ጀምሮ በወሰደዉ የማጥቃት አርምጃ ከአስራ ሁለት በላይ ሠላማዊ ዜጎችን የገደለ ሲሆን ከሟቾቹ ዉስጥ አንድ የአካባቢዉ ተወላጅ የሆነ የአሜሪካ ዜጋ ይገኝበታል። የግንቦት ሰባት ድምጽ ዝግጅት ክፍል የወያኔ ጦር በአካባቢዉ ያደረገዉ ጭፍጨፋ እንደተሰማ በክልሉ የሚገኙ አንዳንድ ባለስልጣናትን ሰልክ ደዉሎ ሁኔታዉን ለማጣራት ሞክሮ ነበር ፤ ሆኖም የዝግጅት ክፍላችን ያናገረዉ ከፍተኛ የክልሉ ባለስልጣን በአካባቢዉ ምንም አይነት ግጭት የለም በማለት በአለም ዙሪያ የተሰራጨዉን እዉነት ለመካድ ሞክሯል። በሌላ በኩል አዲስ አበባ ዉስጥ የሚገኙ ከፍተኛ የወያኔ አገዛዝ ባለስልጣኖች የጸጥታ ሀይሎች ጋምቤላ አካባቢ የአማጽያንን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር በሚል በወሰዱት እርምጃ አንድ የአሜሪካ ዜግነት ያለዉ ሰዉ መገደሉን ለአሜሪካ ኤምባሲ ተናግረዋል።
የአዲስቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መሪ የሆኑት አቶ አባንግ ሜቶ ከኢሳት ሬድዮ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ በጋምቤላና በአካባቢዉ ያለዉን ወታደራዊ ዉጥረት ድርጅታቸዉ በቅርብ እንደሚከታተለዉ ተናግረዉ ከሰሞኑ በወያኔ ወታደሮች ተገደለ ስለተባለዉ የአሜሪካ ዜጋ አስፈለገዉን የክትትል መረጃዎች ለአሜሪካ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መስጠጣቸዉን ተናግዋል። ዜጎችዋ በዉጭ አገር በሚደረጉ ወታደራዊ ግጭቶችና አመጾች ሲገደሉ ወይም ደብዛቸዉ ሲጠፋ ክፍተኛ ክትትል የምታደርገዉ ዩ ኤስ አሜሪካ አሁንም ጋምቤላ ዉስጥ በወያኔ ወታደሮች ተገደለ የተባለዉን ዜጋዋን ጉዳይ መከታተል መጀመሯን ለማወቅ ተችሏል። በቅርቡ የኦባማ አስተዳደር ከአሸባሪዎች ጎን ተሰልፈዉ በሚዋጉ የአሜሪካ ዜጎች ላይ የሚወስደዉን አርምጃ በተመለከት ሾልኮ የወጣዉ መረጃ ኮንግሬሱን ጨምሮ አያሌ አሜሪካኖችን እንዳስቆጣ የሚታወቅ ሲሆን፤ ይህ ከሰሞኑ ጋምቤላ ዉስጥ የተገደለዉ አሜሪካዊ ጉዳይ ይበልጥ በተሰማና በታወቀ ቁጥር ወያኔ ላይ መዘዝ ይዞ ሊመጣ እንደሚችል ብዙዎች በመናገር ላይ ናቸዉ።

Mar 8, 2013

እኛም እንድገመዋ… ርዕዮትን እያሰሩ … ቐሽ ገብሩን ቢዘክሩ… “ሼም” የለም በአገሩ…!?

አቤ ቶኪቻው

ተዓምረኛው ኢቲቪ ለማርች ስምንት የሴቶች ቀን መታሰቢያ አንድ ዶክመንተሪ ፊልም አሳይቶናል። ፊልሙ የዛሬ አመት ተላልፎ እኛም የአቅማችንን አስተያየት ሰጥተንበት ነበር። ታድያ ዛሬም ኢቲቪዬ ፊልሙን ደግሞ አሳይቶናል። ታድያ መድገም ብርቅ ነው እንዴ… እኛም አስተያየታችንን እንድገመዋ!
በመጀመሪያ አበሻ እንደመሆኔ መጠን ጭቆናን “እምቢ” ብለው ፋኖን ለዘመሩ ታጋዮች ትልቅ አክብሮት እንዳለኝ ያለ ሽሙጥ እገልፃለሁ።
ተስፋዬ ገብረ አብ ከተረካቸው ትረካዎች በሙሉ “የቁንድዶ ፈረስ” ትረካ በጣም የመሰጠችኝ ናት። እስቲ ለማስታወስ ልሞክር…
ሐረር አካባቢ፤ የጋሪ ፈረሶች የሚደርስባቸው የስራ ጫና እጅግ በጣም ከባድ ነበር። ከስራ ጫናው እኩል ደግሞ ዱላም አለው። ልክ አሁን አሁን ደሞዛችን አነሰ ብለን “ኡኡ” ስንል “ለአባይ እና ለሌሎች ልማቶች ደግሞ መዋጮ አዋጡ” ተብለን መከራችንን እንደምናየው ማለት ነው። በዚህ ላይ እነዚህ የጋሪ ፈረሶች ስራውና ዱላ የሚደራረብባቸው አንሶ ጌታቸው (አባ ፈርዳው) ቀለባቸውንም በአግባቡ አይሰፍርላቸውም ነበርና ከሰውነት ጎዳና ወጥተው ክስት ጉስቁል አሉ።እኛም እንድገመዋ… ርዕዮትን እያሰሩ … ቐሽ ገብሩን ቢዘክሩ… “ሼም” የለም በአገሩ…!?
ይሄን ግዜ “እምቢኝ” አሉና “ቁንድዶ” ወደተባለ ጫካ ገቡ። ከዛም ባህሪያቸው ተለውጦ እንደፈረስ ሳይሆን እንደ እንደ አውሬ ሆኑ። ማን ወንድ መጥቶ ዳግም ወደዛ የጋሪ ባርነት ይመልሳቸው? ማንም።
ታድያ ፈረሶቹ እዛው ጫካ ውስጥ መሽገው እንዳሻቸው እየበሉ እንዳሻቸው እየቦረቁ አማረባቸው። ወዘናቸውም “ጢም” አለ።
“በአሁኑ ግዜ የሀረር አካባቢ ነዋሪዎች የኦህዴድ አባላትን እስከ መቼ የጋሪ ፈረስ ትሆናላችሁ? አንዳንዴ እንኳን የቁንድዶ ፈረስ ሁኑ እንጂ…! እያሉ ያሽሟጥጧቸዋል።” ብሎናል ተስፋዬ። (ልክ ነኝ አይደል ተስፋዬ…? “ይሄንን እኔ አላልኩም” ካልክ እኔ ለማለት እገደዳለሁ…!(ፈገግታ))
እናም እኔ በበኩሌ የቁንድዶ ፈረስነትን አደንቃለሁ። አላማው ልክ ነው አይደለም የሚለው ጥያቄ በይደር ይቆይ። ነገር ግን በደል ሲበዛ “እምቢ” ማለት ከአባት የወረስነው ነው። ዛሬ የሽብረተኝነት አዋጅ ወጥቶ ሳይከለከል አይቀርም እንጂ አንድ ዘፈን ትዝ ይለኛል…
“ደብቆታል መሰል ሶማ በረሃው
“እምቢ” ያለው ጎበዝ የታል ሽፈራው” የሚል ዘፈን።
በአሁኑ ወቅት፤ ይህንን ዘፈን በይፋ መዝፈን የሚቻል አይመስለኝም። ምክንያቱም በሽብርተኝነት አዋጁ አንድ ግለሰብ፤ በዘፈን በፅሁፍ እና በተለያዩ መንገዶች “ሽብርተኛን” እንኳንስ ሲያበረታታ ተገኝቶ ይቅርና፤ “አበረታቷል” ተብሎ ሲታሰብም “ጉዱ ይፈላል” ይላል። በተጨባጭ እንደምናየው ደግሞ እንኳንስ እምቢ ብለው ሶማ ጫካ ገብተው ይቅርና በከተማው ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች ራሳቸው “አሸባሪ” ስለመሆናቸው መረጃው አለ። ማስረጃው ጠፍቶ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩም እኛም የጨነቀን…! ስለዚህ “ደብቆታል መሰል ሶማ በረሃው እምቢ ያለው ጎበዝ የታል ሽፈራው…” ብሎ ማዜም አይቻልም ማለት ነው።
ለማንኛውም፤ ዘፈኑ ግን “እምቢ” ባይነትን እኔ ብቻ ሳልሆን ብዙሃን የሀገሬ ሰው እንደሚያደንቅ ያስረዳልኛል። አዎ አንዳንዴም እምቢ ማለት ጥሩ ነው። “እምቢ… እምቢ ለሀገሬ! እምቢ… እምቢ ለክብሪ! እምቢ… ታታታታ” ፉከራው ራሱ ማማሩ።
ስለዚህ ቐሽ ገብሩ፤ አሞራውና ሌሎችም “እምቢ” ባይ ታጋዮች “እምቢ” በማለታቸው አደንቃቸዋለሁ። እንኳንም እምቢ አላችሁ!
ወደ ቐሽ ገብሩ ስንመጣ የዶክመንተሪው አዘጋጆች ልብ ያላሉት ወይም ደግሞ “ምን ታመጣላችሁ” ብለው ችላ ያሉት አንድ ስህተት የፌስ ቡክ ወዳጆቼ አግኝተው ነበር። ልብ በሉልኝ ህውሃት ሆዬ ቐሽ ገብሩን መትረየስ ሲያሸክማት ገና የአስራ ሶስት አመት ልጅ ነበረች። ከፈለጋችሁ አስሉት በአስራ ዘጠኝ ስድሳ አንድ ተወለደች። በአስራ ዘጠኝ ሰባ አራት ወደ ትግል ገባች። ማነው ሂሳብ የሚችል…? በሉ እስቲ አስሉልኝ። ሰባ አራት ሲቀነስ ስድሳ አንድ እኩል ይሆናል፤ አስራ ሶስት። ዘጋቢው ፊልም ሲቀጥልም “…ትግሉን በተቀላቀለች በጥቂት ወራት ውስጥ እጇን ተመታች። እንደዛም ሆና መትረየስ ትሸከም ነበር።” ይላል። ጉድ በል ህውሃት…! አይሉኝም?
በዛ ሰሞን አለም ሲነጋገርበት ከሰነበተባቸው ነገሮች ውስጥ በኡጋንዳ የሚገኘው የሎርድ ሬዚስታንት አርሚ መሪ፤ ጆሴፍ ኮኒ ህፃናትን ጦርነት ውስጥ እየማገደ ነው በሚል ታድኖ ይከሰስ ዘንድ የተጀመረው “ኮኒ ሁለት ሺህ አስራ ሁለት” የሚል እንቅስቃሴ ነው። በአለም አቀፍ ህግ፣ አረ በኢትዮጵያ ህገ መንግስትም ቢሆን ህፃናትን ለጦርነት ማሳተፍ የለየለት ወንጀል ነው። በእግዜሩ ዘንድም ያስጠይቃል።
እና ህውሃት የአስራ ሶስት አመቷን ህፃን ሙሉ “ቐሽ ገብሩ” ን በጦርነት ማሳተፉ ሳያንስ የግፉ ግፍ ደግሞ ለማርች ስምንት የሴቶች መብት ክብረ በዓል ላይ ታሪኳን እንደ ጥሩ ነገር ዘገበልን። እውነቱን ለመናገር ይሄ ትልቅ የወንጀል መረጃ ነው። እንደኔ እምነት ይህንን መረጃ ያጠናከሩ ሰዎች የውስጥ አርበኝነት ስራ እየሰሩ ነው። ይሄ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ገና በርካታ መረጃዎችን ያወጣል። እዝችው ላይ ሙሉ ወይም ቐሽ ገብሩ ገና አስራ ስምንት አመት እንኳ ሳይሞላት አንድ ጎረምሳ በፍቅር ስም አስረግዞ እስከማስወረድ እንድትደርስ እንዳደረጋትም ዶክመንተሪው ይዘግባል። ሰውየው ከሷ ጋር ያሳለፈውን ፍቅርም ሲናገርም በኩራት ነው። እንዴት ነው ነገሩ… እኛ መሀሙድ አህመድ በአንድ ዘፈኑ ላይ “ሸግየዋ ጉብሊቷ… የአስራ አምስት አመቷ እንዴት ነሽ በሉልኝ የምታውቁ ቤቷን” ብሎ ስለዘፈነ አይደል እንዴ ከህፃናት መብት አንፃር ወንጀል ነውና ይቅርታ መጠየቅ አለበት እያልን የምንሟገተው? እንዲህ የባሰውን ነውር በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አየነው። ለዚህ ነው አይናችን የተርገበገው…?
ወዳጄ እንዴት ሰነበቱ አይገርምዎትም ይሄ ሁሉ መንደርርደሪያ መሆኑ… ይበሉ ወደ ዋናው ጉዳይ ተያይዘን እናምራ
እናልዎ… ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በተለያየ ግዜ የተለያየ ዘጋቢም አወዛጋቢም ፊልሞችን ያቀርብልናል።
በዛ ሳምትን ያየነውም የቐሽ ገብሩ ዶክመንተሪም የዚሁ አካል ነው። እንግዲህ ከላይ ያነሳነውን በቐሽ ገብሩ የተጋለጠውን ህፃናትን ወደ ጦርነት የማሰማራት እና ለአቅመ ህይዋን ያልደረሱ ሴቶችን የማማገጥ ወንጀል እንዲህ ያለውን ጉዳይ ለሚከታተሉ አካሎች እንተወው እና የፈረደባትን ይቺን ህፃን “እምቢ” እንዳለች ጀግና እንቁጠራት። ቆጠርናት…!
ኢህአዴግ ደርግን ብዙ ግዜ ደርግ በጦርነት የማረካቸውን ታጋዮቼን የማያምኑበትን እንዲናገሩ ያሰቃያቸው ነበር፤ ከዛም እምቢ ሲሉት ያስራቸዋል፤ ይገድላቸዋል። ብሎ ይወቅሳል። ይቀጥልናም ቢሆንም ግን፤ “እንደ አሞራው ሁኑ እንደ ቐሽ ገብሩ ሁኑ ብሎ ይመክረናል። እኛም ምክር የምንሰማ ልባሞች ነንና እሺ ብለን እንደ አሞራው፤ እንደ ቐሽ ገብሩም ለመሆን እንታትራለን ከዛ ውጤቱ ምን ይሆናል አይሉኝም…? ለምን እጠይቅሀለው እያወቅሁት…? አሉኝ እንዴ!?
ሰሞኑን አቶ አንዷለም አራጌ ላይ የሆነውን ነገር ሰምተዋል። አንዷለም አራጌ እንደ አሞራው ሁኑ ከመባሉ በፊትም እንደ አሞራው “እምቢ” ባይ ነበር። ለዛውም ጫካ ሳይገባ ፊት ለፊት እምቢ ብሎ የተጋፈጠ ደፋር የተቃማዊ ፓርቲ አመራር ነው። ምን ዋጋ አለው አንዷለም እንደ አሞራው “እምቢ” ቢልም ኢህአዴግ ደግሞ እንደ ደርግ “እምቢ” ማለት አይቻልም ብሎ አሰረው። ማሰር ብቻ ቢሆን በስንት ጣዕሙ ጎረምሳ አስገብቶ አስደበደበው እንጂ!
ማርች ስምንት የአለም ሴቶች ቀን ነው። በአለም ላይ ያሉ ሴቶች ቀደም ሲል ሲደርስባቸው የነበረ ጭቆና ይብቃ የተባለበት ቀን። ይህ ቀን፤ የህውሃት ሴቶች ቀንም የአንድነት ሴቶች ቀንም፤ የጋዜጠኛ ሴቶች ቀንም፣ የሁሉም ሴቶች ቀን ነው።
ርዕዮት አለሙ አሳሪዎቿ የጠላነውን አብረሽን ከጠላሽ ትለቀቂያለሽ ብለዋት ነበር። ቃል በቃል ሲነገር “ኤልያስ ክፍሌ የተባለው ጋዜጠኛን አሸባሪ ነው መሰስክሪበት እና ትለቀቂያለሽ” ተባለች። እርሷም እኔ “በወንጀለኝነት አላውቀውም” ብላ ድርቅ አለች። እንግዲያስ ብሎ ኢህአዴግም አስራ አራት አመት ፈረደባት። ቐሽ ገብሩን ደርግ የያዛት ግዜ “የህውሃት ሰዎችን ወንጀለኛ ናቸው ብለሽ መስክሪባቸው” አላት እምቢኝ ብላ ድርቅ አለች ሞት ፈረደባት። እንግዲህ ቐሽ ገብሩ እና ርዮት አለሙ አንድ ናቸው “እምቢኝ” ብለዋልና። ደርግ እና ኢህአዴግስ…? የመጣው ይምጣ ደፍሬ ልናገር ነው..! አዎ ደርግ እና ኢህአዴግም አንድ ናቸው። እምቢ ያላቸው ላይ ሁሉ ይፈርዳሉና። በነገራችን ላይ የደርግ ፕሮፖጋንዳ ሰራተኞች ቐሽ ገብሩን ለማናገር መከራቸውን ሲያዩ የነበረውን ያህል የኢህአዴግ ጋዜጠኞችም በተደበቀ ካሜራ ሳይቀር ርዮትን ለማናገር አበሳቸውን ሲያዩ ነበር። ነገር ግን ቐሽ ገብሩም ርዮትም አለሙም ፍንክች የአባ ቢላው ልጅ ብለዋል። ወይ መገጣጠም…! አይሉልኝም?
እና ታድያ የሴቶች ቀን ክብረ በዓል ሲዘከር መንግስት ርዕዮትን አስሮ ስለ ቐሽ ገብሩ ሲተርክ የአራዳ ልጆች ሰሙ። ሰምተውም ጠየቁ “ሼም የለም እንዴ በአገሩ!?” አሉ ዝርዝር ያለው የስራ ሂደት ካለ መልስ ያምጣ…!
በጥቅሉ መንግስት እነ ርዕዮትን፣ እነ እስክንድርን፣ እነ ውብሸትን፣ እነ ሂሩትን፣ እነ አንዷለምን እነ ናትናኤልን፤ ስንቱን ጠርቼ እዘልቀዋለሁ? በጅምላው እምቢ ያሉትን ሁሉ እያሰረ እና እየገረፈ “ደርግ ታጋዮቼን አሰረ፣ ገረፈ፣ ገደለ” ብሎ ዋይ ዋይ ማለት ውሃ የማያነሳ ወቀሳ ነው። መፅሐፉም ይላል “የሌሎችን ጉድፍ ከማየትህ በፊት በአንተ አይን ውስጥ ያለውን ቆሻሻ ተመልከት…”
በመጨረሻም
ያወጋነውን ለፍሬ ይበልልን
አማን ያሰንብተን!

Mar 7, 2013

Watch and share. Two young Ethiopian immigrants physically abused by Arab human traffic smugglers

Watch and share. Two young Ethiopian immigrants physically abused by Arab human traffic smugglers




“ድህነታቸውን ህዝቡ ላይ አራግፈው ለራሳቸው ባለፎቆች ሆነዋል” ስማቸው ያልተገለጸ እናት

ከሉሉ ከበደ

ሰሞኑን ከአገር ቤት አንዲት እናት ልጃቸውን ሊጠይቁ መተው ነበር። ልጃቸው የባለቤቴ ጓደኛ ነች።..የኔም ጓደኛ!…እኒህ አናት አንደበተ ርቱእና ተደምጠው የማይጠገቡ ጨዋታ አዋቂ ቀልደኛም ናቸው። ሑሉም ነገር የገባቸው ፍጹም ፖለቲካ አዋቂ ብሩህ እናት ናቸው። ጨዋታቸው ንግግራቸው ሁሉ ይማርካል። ሰማንያ አመት አይሞሉም። ጥንክር ያሉ፤ የነቁ ፍጹም ጤናማ እናት ናቸው።

ወይን ቢጤ ገዛሁና ባለቤቴ ድፎ ዳቦ ጋግራ (እናቶች አዚህ አገር ሲመጡ ድፎ ዳቦ ሲቀርብላቸው ደስ እንደሚላቸው ታውቃለች) እንኳን ደህና መጡ ልንል ሄድን።
ለሁለት ሰአት ያህል አብሬ ስቆይ ከናታችን የገበየሁት ትምህርትና ቁም ነገር በቀላል የሚገመት አይደለም። የኢትዮጵያ ህዝብ እየጠላቸው ዛሬ ስልጣን ላይ የተጣበቁት የወያኔ ደናቁርት፤ addis-ababa-2013የኢትዮጵያን ህዝብ ምንም አያውቅም ብለው፤ የሚገምቱትና የሚንቁት፤ወደ ታች ወደ ህብረተሰቡ ዝቅ ብለው፤ስለነሱ አገዛዝ፤ ስለ መልካም አስተዳደር ያለውን ግንዛቤ ቢረዱ ምን ያህል ከህብረተሰቡ ኋላ ኋላ እየሄዱ እንመራሀለን እንደሚሉ በተረዱና ባፈሩ ይበጃቸው ነበር።
እኒህ እናት ድህነትን እኩል ያካፈለን ደርግ ተሻለ ነው ነው የሚሉት፤ “እነዚህ ድህነታቸውን ህዝቡ ላይ አራግፈው ለራሳቸው ባለፎቅ ሆነዋል። ደርግ አንዱን ልጅ አንዱን እንጀራ ልጅ አላደረገንም። ቢበድለንም አልለያየንም።”
ጎዳና ላይ ለፈሰሱ ለማኝ ህጻናትና ወላጆች ዘወትር ያለቅሳሉ። ኑሮአቸውን የከተማው ቆሻ ክምር ላይ የመሰረቱ ወላጆችና ልጆች ያስለቅሷቸዋል። “ይሄ ሁሉ ፎቅ ይገነባል። የእያንዳንዱን ፎቅ ባለቤት አስር አስር ልጅ ከጎዳና ወስዶ እንዲያሳድግ ቢያስገድዱት ጽድቅ ነበር። ላለው ሰው ምንም ማለት አይደለም” ይላሉ።
ስለቤተሰብ ስለዘመድ አዝማድ፤ስአየርንብረትና ሌላ ትንሽ ከተጨዋወትን በኋላ ወዲያው ነበር ስለ ሀገር ጉዳይ የተነሳው።
“ኑሮ አንዴት ነው?.. እትዬ… አገር ቤት ” አልኩ ።
“…አየ… ልጄ .. ምን ኑሮ እንዴት ነው ትለኛለህ? …ወያኔው እንዴት አደረጋችሁ በለኝ እንጂ? …”
አነጋገራቸው ያስቃል። ሁላችንም ሳቅን። ሳቄን ገታ አደረኩና.. “ወያኔው ምን አደረገ?.. እስቲ ያለውን ነገር ያጫውቱኝ…” አልኩ።
“ከየቱ ጋ እንደምጀምርልህ አላውቅም ልጄ….ያላየነው ታሪክ የለም …በነዚህ ሰዎች ዘመን ያየነው ጉድ ብዙ ነው።”
“ ምን ጉድ አለባቸው?”
“ደግ ጠይቀኸኛል ልጄ…ምን ጉድ አለባቸው አልከኝ? …. ይሔውልህ እኔ ያንተ እናት… ሶስቱንም መንግስት በልቻለሁ።.. አንድ ነገር ልንገርህ ..ጃንሆይን ክፉ …አድሀሪ ስትሉ.. ክፉ መንግስት ስትሉ …ደርግ መጣና ክፉ መንግስት ምን አይነት እንደሆነ አሳየን.. ደርግን ክፉ ስንል ስንጠላ..ስንጠላ..እነዚህ መጡና የባሰ ክፉ መኖሩን አሳዩን..” ድንገት አቁዋረጥኳቸውና…
“የነዚህ ክፋት ምንድንው?”
“ደግ ብለሀል ልጄ… የነዚህ ክፋት.. ደርግ ወንበሬን ቀና ብላችሁ አትዩ ብሎ ነበር ያን ሁሉ ሰው የፈጀው፤…አማራ አላለም፤… ትግሬ አላም። እስላም ክርስትያን አላለም። ደርጉ ይል የነበረው፤ አገራችሁን ጠብቁ፤ ተስማምታችሁ አንድ ሆናችሁ ኑሩ፤ ወንበሬን ግን ቀና ብላችሁ አትዩ…”
ፊቴን ትኩር ብለው እያዩ
“..ያኔ እናንተም በየከተማው ጦርነት ከፈታችሁበት..እሱም ጦርነት ከፈተ…ያሁሉ በልቶ ያልጠገበ ልጅ አለቀ። ቀድሞውንም ያኔ ወይ ጫካ ሂዳችሁ በተዋጋችሁት ደግ… ወይ አርፋችሁ በተቀመጣችሁ… ያንን ሁሉ የልጅ ሬሳ አናይም ነበር..በኢሀፓ ጊዜ…”
“..እነዚህ መጡ …ያገሬ ሰው ተረተ። … ‘ምንሽር ልገዛ ወይፈኔን  ሳስማማ፤መጣ የትግሬ ልጅ በነጠላ ጫማ’… ገና ሲመጡ ጀምሮ የወደዳቸውም የለ… እግዚአብሄር ያመጣውን ፍርጃ መቀበል እንጂ  የሚደረግ የለም… መጡልህና ወንበራችንንም ቀና ብላችሁ እንዳታዩ፤ ለራሳችሁም እንዳትትያዩ… በየዘራችሁ ተበታተኑ አሉ። ለሁሉም በየዘሩ ማህበር አበጀለትና ሁልህም በዚህ ቀንበር ውስጥ ትገባለህ..ግባ አለው።”
“ማን ነው ያለው?’’
“ሟቹ…”
“አልገባም ያለ፤ እነሱን የሞገተ፤ የጥይት እራት ይሆን ጀመር። አንድም ሰው ጠመንጃ አንስቶ የተኮሰባቸው የለም። በያለበት ሰው መግደል ሆነ ስራቸው። አንዱን ካንዱ ማባላት፤ አሉባልታ ውሸት በራዲዮን፤ በቴሌቭዥን ሲነዙ መዋል ሆነ። እንዲህ እንዲህ አድርገው ሰዉን ሁሉ አደናግረው ሲያበቁ፤ አስፈራርተው ሲያበቁ፤… የራሳቸውን ሰው ሁሉ  ቦታቦታውን አስያዙ። ዛሬ ያለነሱ ነጋዴ የለም። ያለ እነሱ የቢሮ አለቃ የለም። ያለነሱ የቀበሌ አለቃ የለም። ያለ እነሱ ፎሊስ የለም። ሰው ሁሉ ሀሞቱ ፈሶ እነሱን እየፈራ መኖር የዟል። ….ወንዱም ሴቱም….ታዲያ ልጄ ደርጉ እንደዚህ ባይተዋር አድርጎናል?” አሉና በንዴት እራሳቸውን እየነቀነቁ ጠየቁኝ።
“ልማቱስ እትየ?…አገሩን አልምተዋል ይባል የለ እንዴ?”
“ሀሰት!.. ሀሰት ልጄ!…አገር ቢለማ፤ አገሬው ሁሉ ከነልጁ ለልመና ጎዳና ላይ ይፈስ ነበር?…ልማቱንስ ቢሆን እነሱ እንጂ ሌላው ሰው የታለ?..የታለ ጉራጌ ባለፎቅ ?..የታለ አማራ?..የታለ ኦሮሞ?….ያ ፎቅ የማነው ስትል… እነሱ….ያፎቅ የማነው ስትል እነሱ…..ልጄ ከየት አመጡት ያሰኛል እኮ? እነሱና አላሙዲ እንጂ ሀብታም አለ እንዴ ዛሬ?..”
“ዛሬ አንድ ሺህ ብር ይዘህ ገበያ ወተህ….. አንዲት ዘንቢል ሞልተህ አትመለስም እኮ!…ልማት ማለት ድህነትና እራብ ነው እንዴ?… ጦሙን የሚያድረው ህዝብ ተቆጥሮ አያልቅም እኮ…. እዚችው አዲስ አበባ…..”
“…ጭራሽ ጥጋባቸው… ቤት ዘግተው፤ ዊስኪ አውርደው ሲጨፍሩ የሚያድሩ እነሱ… ጠግበው በሽጉጥ ሲታኮሱ የሚያድሩ እነሱ… መጠጥ ቤት የፈለጋቸውን ደብድበው አድምተው የሚሄዱ እነሱ….”
“…የኛ ሰፈር መደዳውን ቡና ቤት ነው።…አንድ ቀን ጠዋት ወደ ክፍለ ሀገር አውቶብስ ተራ ልሄድ አስር ሰአት ተነስቼ ታክሲ ስጠብቅ….አንዲቷን ድሀ ጸጉሩዋን ይዞ መሬት ለመሬት እየጎተተ በግንባሯ ያዳፋታል፤ ከቡና ቤት አውጥቶ አስፋልት ላይ ይረግጣታል።..ኡ ኡ እያለች…ገደለኝ እያለች…ሊገላግላት የመጣ ወንድ ጠፋ። ሰው ሁሉ ሰምቶ እንዳልሰማ እየሆነ ብቅ አላለም። በስካር መንፈስ እንኳ እነዚህን ሰዎች የሚደፍር ጠፋ? አልኩና እንባዬን እርግፍ አድርጌ አለቀስኩ። ልጄ ድሮ ሴት ልጅ ድረሱልኝ ብላ ስትጮህ እንዲህ  ነበር እንዴ?..”
“..ወዲያውኑ አንድ ታክሲ ሲበር መጣ… አስቆምኩና ገብቼ… እንዳው ልጄ ይህን ሰውየ እላዩ ላይ ንዳበት!…ንዳበት!…ገደላት እኮ…ንዳበት! አልኩት። ለካንስ ያም ባለታክሲ የነሱ ሰው ኖሯል…አንዳንድ ደግ መቸም አለ…ሽርርር አደረገና መኪናዋን እላዩ ላይ  አቁሞ፤ ወርዶ፤ እንደብራቅ ጮኸበት አልኩህ።ተጯጯሁ..ተጯጯሁ..ተሰዳደቡ፤ተሰዳደቡ..በግርግር እሷ እመር አለችልህና ደሟን እያዘራች ተነስታ አመለጠች…ያም ከባለታክሲው ጋር እየተሰዳደበ ወደ መሄጃየ አቀናን …”
“..ዛሬ አሁን የፈለገ ነገር ቢመጣ የአዲስ አበባ ሰው ቤት ለነሱ አያከራይም….”
“ለምን?” አልኩ።
“ለምን ማለት ደግ..ይኽውልህ ልጄ ቤት ታከራያቸው የለም?…ልቀቁ ስትል አይለቁም፤ …ወደየትም  ሄደህ ከሰህ አታስለቅቃቸውም።…አንዲቷ እንዳደረገችኝ ልንገርህ..”  አሉና ፎቴው ላይ እየተመቻቹ፤ የተደረበላቸውን ብርድ ልብስ ወደላይ እየሰበሰቡ፤ “… እግዚአብሄር ብድሩን ይክፈላቸውና ልጆቼ ቤት ሰሩልኝ ብየህ አልነበር?…”
ውድ አንባቢያን ወደጨዋታችን መጀመሪያ ላይ ልጆቻቸው ቤት እንደሰሩላቸው ነግረውኝ  ነበር። አምስት ልጆች አሏቸው። ሁሉም በየአለሙ ተበትነው ይገኛሉ። ኖርዌይ፤ ጀርመን፤ አሜሪካ፤ካናዳ..እና ሁሉም እንደየአቅሙ አዋቶ አራት ዋና ዋና ክፍሎች ከየመኝታ ቤት ያላቸው ባለ አንድ ፎቅ ሰርተውላቸው ነበር። እሳቸው አሮጌው ቤት እየኖሩ ይህን ቤት አከራይተው በሚያገኙት ገቢ ስድስት የእህት የወንድም ልጅ ከገጠር አስመጥተው እያስተማሩ ያሳድጋሉ። እናም ልጆቻቸው እንደገና ገንዘብ እንስጥሽ ብለው እንዳይቸገሩ በማለት ለነሱ ያልነገሯቸው፤ ነገር ግን ከቤቱ ኪራይ ቆጥበው ምድር ቤት ባንዱ ክፍል ምግብና መጠጥ ሊነግዱ ሀሳብ አላቸው። ዛሬ ነገ እጀምራለሁ ሲሉ አንዱን ቤት አላከራዩትም ነበር። ኋላ ላይ ግን ለማከራየት ወሰኑ።
“…ቤት ሰሩልኝ ብየህ አልነበር?…ታዲያ ያችን አንዷን የቀረችውን ለአምስት ወርም ቢሆን ላከራይ አልኩልህና….አንዱ ደላላ አንዲቷን ወያኔ ሴት ይዞ መጣ። ቤቱ መንገድ ዳር ነው ለንግድ ይመቻል …አንባሻና ሻይ ቡና ልሸጥ ነው አለችኝ።…..አይ ልጄ እኔም እንዲህ፤ እንዲህ ላደርግ ሀሳብ አለኝ። …ባከራይሽም ለአምስት ለስድስት ወር ነው። ከፍተሽ የምትዘጊው ንግድ ምንም አያደርግልሽም። ሌላ ብትፈልጊ ይሻልሻል አልኳት።”
“…ሞቼ እገኛለሁ። ልቀቂ ባሉኝ ቀን እለቃለሁ። እንደው እትዬ..እትዬ..” አለች።
“ኮሎኔል ወንድም አላት አሉ። እሱ ነው ካገሯ ያስመጣት። ላገሩም እንግዳ ነች። አይ እንግዲህ እለቃለሁ ካለች ትግባ ብየ በሰው ፊት ተዋውለን ገባች።”
“እርግጥ ጎበዝ ሴት ናት። የኛ ሰፈር አላፊ  አግዳሚው ይበዛል። በጠዋት ተነስታ ቄጠማውን ጎዝጉዛ፤ አጫጭሳ፤ ቡናውን አቀራርባ፤ ሞቅ ሞቅ ስታደርገው፤  መንገደኛው ሁሉ ቁርሱን በልቶ ቡናውን ጠጥቶላት ወደየስራው ይሰማራል።”
“..እንዲህ እንዲህ እያለ ያች አምስት ወር ደረሰች። አይ ይች ሰው አሁን እንዲህ ገበያው ደርቶላት ልቀቂ ብላት ትቀየመኝ ይሆን? አልኩልህና እኔው ተጨንቄ አረፍኩት። …እሷም ቤት ልፈልግ አላለች፤ እኔም ትንሽ ትቋቋም ብየ ሶስት ወር ጨመርኩላት። ከዚያ በኋላ ደሞ ሶስት ወር አስቀድሜ ቤት እንድትፈልግ ነገርኳት። እሺ አለች። ወር አለፈ። ሁለተኛውም አለፈ። ሶስተኛው ተገባደደ። እየፈለኩ ነው ትላለች። ወሩ አለቀ። ቤቴን መልቀቅ የፈለገች አትመስልም። …በይ እንግዲህ ካጣሽ እኔው እፈልግልሻለሁ አልኩና ከኔ ቤት ወረድ ብሎ ሌላ አገኘሁላትና በይ በዚህ ወር  መጨረሻ ላይ ቤቱን እፈልገዋለሁ አልኳት። ወሩ ሲሞላ ደህና የነበረችው ሴትዮ ድንገት ተለዋወጠችብኝና አልወጣም ሂጂ ክሰሽ አትለኝ መሰለህ?…አበስኩ ገበርኩ…አልኩና ያዋዋሉንን ሰዎች ጠራሁና ይችን ሽፍታ ገላግሉኝ አልኩ። ጭቅጭቋን ቀጠለች። አንድ አስራ አምስት ቀን ስታምሰን ከረመች አልኩህ…በኋላ አንድ ቀን ጠዋት ወደዚሁ ቤት ስመጣ ሌሊት እቃ ታግዝ ነበር ሲሉኝ አምላክ በሰላም ሊገላግለኝ ነው አልኩና ገብቼ ቤቴን አየዋለሁ….ልጄ አፍርሳዋለች አልኩህ…ግርግዳውን ሁሉ ቧጣ፤ቧጣ ቧጣ…..እንደው ልጄ በምን ይሆን ስትቧጥጠው ያደረችው?…ሸንትራ፤ሸንትራ፤ ግርግዳውን ልጅ ያረሰው መጫወቻ ደጅ አስመስላዋለች። ሽንት ቤቱን ሰባብራ አግማምታ፤ አበስብሳው፤ የአንድ ወር የቤት ኪራይ ሳትከፍለኝ ኮተቷን ሰብስባ ውልቅ አለች። ክሰሻት አሉኝ። ማን ላይ ነው የምከሳት?…ጭራሽ አሸባሪ ትብየ እኔው ልታሰር?…”
የእናታችን ጨዋታ ፈርጀ ብዙ ነበር። አንዱን ጨርሰው ወደ ሌላው ሲያልፉ አንደበተ ርቱእነታቸውና ለዛቸው አፍ ያስከፍታል።
“..አንድ ጉድ ደሞ ላጫውትህ….ስራ አጥተው ችግርርርር ያላቸው አስር የሚሆኑ የሰፈራችን ወጣቶች ተሰበሰቡልህና ስራ ፈጠሩ። ምንድነው ስራው ብትለኝ…ሆቴል ቤቶች ሞልተዋል ብየሀለሁ ሰፈራችን….ከባለቤቶቹ ጋር ይነጋገሩልህና  በቀን ሶስት ጊዜ ቆሻሻ መድፋት፤ በቀን አንድ ጊዜ ግቢ መጥረግ፤ ይህን ለመስራት ተዋውለው ….ባለ ሆቴሎቹም ሁሉ ደስ ብሏቸው….ሲሰሩ የሚለብሱት ልብስም ገዝተውላቸው…ጋሪም ገዝተውላቸው ስራ ጀመሩ። የሰፈሩ ሰው ሁሉ ደስ አለው። ልጆቹ ገንዘብ አገኙ፤ እናትና አባታቸውን ማልበስ ለራሳቸውም ደህናደህና ነገር መልበስ ጀመሩ። ስራቸውንም እያስፋፉ በቁጥር አስራ አምስት ደርሰው፤ በሰላም ተረጋግተው በመስራት ላይ እንዳሉ፤ ህገ ወጥ ስራ ነው የምትሰሩት አቁሙ ይላቸዋል አንዱ…”
“ማን? “
“እዚያው ቀበሌ ውስጥ ….የምንትስ ሀላፊ ነው ያሉት ትግሬ…”
“ለምን አስቆማቸው?”
“ስራውን ቀበሌው ሊሰራው በእቅድ የያዘው ስለሆነ በቀበሌ ታቅፋችሁ ነው መስራት ያለባችሁ። ቀበሌ ለናንተ ይከፍላል። ግብር ለመንግስት መክፈል አለባችሁ፤ ፍቃድ ያስፈልጋችኋል….አለና አስቆማቸው። ልጆቹም ለምንድነው እኛ የፈጠርነውን ስራ የምንከለከለው ብለው ሲጨቃጨቁ ሁለቱን አስረው፤ የቀሩትን አስፈራርተው በተኗቸው።”
“…ትንሽ ቆየት ይሉልህና… ልጆቹን አደናግረው አስፈራርተው ከበተኗቸው በኋላ ያንኑ ስራ በቀበሌው የማይኖሩ የራሳቸውን ወጣቶች ሰብስበው ….”
“የራሳቸውን ወጣቶች ማለት?” አቋርጨ ጠየኩ።
“ትግሬዎቹን… ሰበሰቡና ከመጀመሪዎቹ ሁለቱን ቀላቅልው ስሩ አሏቸው …እነዚያ ሁለቱ ደሞ ጓደኞቻችን ተባረው እኛ አንሰራም ብለው ትተውላቸው ሄዱ። ባለሆቴሎቹ ቀድሞ የሚያስጠርጉትን ልጆች ሲያጡ፤ ምንድነው  ነገሩ ብለው ቢያጠያይቁ፤ የመጀመሪያዎቹ ልጆች የሆነውን ሁሉ ነገሯቸው። ባለሆቴሎቹም አደሙ ። ቆሻሻችንን እኛው እንደፋለን እንጂ አናስጠርግም አሉ። የተተኩትን ልጆች ስራ የለንም እያሉ መለሷቸው። ”
“ያ አለቃ ተብየው ቀበሌ ሰዉን ሰብስቦ አሉ… ጸረ ልማት ሀይሎች እያለ ሲሳደብ ከረመ አሉ። ባለ ሆቴሎቹም እንዳደሙ ቀሩ። ሗላ ላይ ሥሰማ በመጀመሪያ ያጸዱላቸው የነበሩትን ልጆች ሁሉንም ተከፋፍለው ቀጠሯቸው አሉ። እነዚያም ጋሪያቸውንና ጓዛቸውን ይዘው ወዴት እንደሄዱ አላውቅም እልሀለሁ …..ልጄ..ወያኔ እንዲህ እያመሰን ነው እልሀለሁ…..” እንደ መተከዝ አይኖቻቸውን ወለሉ ላይ ተክለው ለአፍታ ዝምም አሉ።
ውድ አንባቢያን የህብረተሰብ ደህንነት የሚረጋገጠው፤ እያንዳንዱ ክፍለ ህዝብ ከህዳጣን እስከ ብዙሀን ምልአተ ህዝቡን የገነቡ ብሄረሰቦች ሁሉ እኩል መብትና ነጻነት ሲኖራቸው፤ በሀገራቸው እኩል የባለቤትነት ስሜት ሲኖራቸው፤አንባ ገነንም ይሁን ዲሞክራሲያዊ ..ያለውን መንግስት የኛ ነው ሲሉት፤ በባህላቸው፤ በቋንቋቸው፤ በሀይማኖታቸው፤ የተነሳ ምንም አይነት መገፋት እንደሌለ ሲያረጋግጡ ዜጎች ደህንነት ይሰማቸዋል።
የናታችንን ጨዋታ ለማጫር ይችን ጥያቄ ጣል አደረኩ።
“ወያኔ..ወያኔ ይባላል… ኢህአደግ ነው መባል ያለበት… አይደለም እትየ?”
ከት አሉና ሳቁ ። ሳቃቸው አስቆን ሁላችንም ፍንድት አለን።
“አየህ ልጄ…በቆሎ እሸት ታውቃለህ አይደል?..በቆሎ እሸት..” አሉ እጃቸውን ቀና ቀጥ አድርገው፤ “..በቆሎ እሸት የምትሸለቅቀው ልባሱ አለ። ያ ልባሱ ገለባ ነው። ይጣላል። ዋናው በቆሎው ነው። ፍሬው። እነዚህ ኢህአደግ  ያልካቸው ገለባ ናቸው (ሶስቱን የወያኔ ፍጡራን ድርጅቶች ማለታቸው ነው፡ ኦህዴድ፤ ብአዴን….) ዋናዎቹ ትግሬዎቹ ናቸው። ገባህ ልጄ…”
በአዎንታ ራሴን ነቀነኩ።
“..የአማራው ነን፤ የኦሮሞው ነን፤ ማነው ይሄ ደሞ የበየነ ጴጥሮስ አገር…ብቻ ሁሉም ከነሱ ጋር ያሉት ገለባዎቹ አሽከሮቻቸው ናቸው። ማፈሪያዎች ናቸው፤…..እንዳይመስልህ ልጄ…ጌቶቹ ትግሬዎቹ ናቸው፤….የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም እነዚህ ኢህአደግ ያልካቸው ከምንም አያስጥሉንም……”
ውድ አንባቢያን ያለፈ አንድ አመት አካባቢ አንዲት ሌላ እናት እንዲሁ መተው ለመጠየቅ ሄጄ ዘጠና በመቶ ማለት ይቻላል ተመሳሳይ አይነት ጨዋታ አጫውተውኝ ነበር። ካንድ ሰው ብቻ የተገኘ ኢንፎርሜሽን ለሌላው ማስተላለፍ ያስቸግራል፡፡ ሁለት ይማይተዋወቁ ሰዎች፤ የተለያየ አካባቢ የሚኖሩ፤ በተለያየ ጊዜ አንድ አይነት ነገር ከተናገሩ እውነትነት ያለው ጉዳይ አለ ማለት ነው።
ይህ ስርአት መለወጥ እንዳለበት ዜጎች ይስማማሉ። ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር የሚታሰብ ነገር አልሆነም።  እንዴት ነው እነዚህን ሰዎች ከስልጣን የምናስወግደው ነው ጥያቄው፤ መላ መምታት የእያንዳንዱ ዜጋ ግዴታና ፈንታ ነው። እናታችንን ጠይቄአቸው ነበር።
“ይህንን መንግስት ለመለወጥ ምን ቢደረግ የሚበጅ ይመስሎታል እትየ?”
“መተኮስ….መተኮስ ነዋ!…እነሱ ተኩሰው አይደል ለዚህ የበቁት?…..ግን እኮ ልጄ… ወንዱ ሁሉ ሀሞቱ ፈሰሰ…በጥቁር አህያ ነው አሉ ያስደገሙብን…የሱዳን መተት ቀላል እንዳይመስልህ ልጄ…ሱዳን አልነበረ የሚኖሩት…ያኔ አሉ…. ሲገቡ፤ ሕዝቡ ሁሉ እንዲፈዝላቸው……ወንዱ ሁሉ ወኔው እንዲሰለብ…. በጥቁር አህያ አድርገው አስደግመው ገቡ አሉ። ይኸው ሀያሁለት አመት….አገር መሬቱን ሲሸጡ፤ እስላም ክርስቲያኑን ሲያምሱ፤ ሲገሉ ….ቤት ሲያፈርሱ.. ንብረት ሲቀሙ…ማን ወንድ ሸፍቶ አስደነገጣቸው?…..ሀያ ሁለት አመት…ሀያ ሁለት ዓመት… መተኮስ … መተኮስ ነው ልጄ…”  lkebede10@gmail.com

Total Pageviews

Translate