Pages

Dec 11, 2012

ዛሬ Mitu Abebe የምትባል እህታችን “ዱባይ ውስጥ ከ38ኛ ፎቅ ላይ ወርውረዋት ህይወቷ ላለፈው እህታችን ለቤተሰቧ መጽናናትን እንመኛለን ጓደኞቿ” ብላ በዚሁ በፌስ ቡክ ግድግዳ ላይ የለጠፈችውን የሟች ፎቶና የሐዘን መግለጫ ተመልክቼ እጅግ አዝኛለሁ፡፡ ወገን ኧረ መጨረሻችን ምንድን ነው????????????????

ዛሬ Mitu Abebe የምትባል እህታችን “ዱባይ ውስጥ ከ38ኛ ፎቅ ላይ ወርውረዋት ህይወቷ ላለፈው እህታችን ለቤተሰቧ መጽናናትን እንመኛለን ጓደኞቿ” ብላ በዚሁ በፌስ ቡክ ግድግዳ ላይ የለጠፈችውን የሟች ፎቶና የሐዘን መግለጫ ተመልክቼ እጅግ አዝኛለሁ፡፡ ወገን ኧረ መጨረሻችን ምንድን ነው????????????????

ዋ! ለኔ!
ዋይ! ዋይ! ልበልልሽ፣ እስኪ ደረት ልድቃ፤
የእኔም ተራ ደርሶ፣ መኖሬ እስኪያበቃ፤
ለምዷል እምባም ይርገፍ፣ ሙሾዬም ይደርደር
ዛሬም እንደ ትናንት፣ እ’ቴ ወጥታ ስትቀር፡፡

በዛ በበረሃ በዛ በሃሩሩ፣ ያ ሁል መንከራተት፤
ቢያልፍልኝ ብላ እንጂ፣ መች ለዚህ ነበረ፣ በሰው ጐዳና ላይ፣ ተደፍቶ ለመቅረት፡፡

ዋይ! ዋይ!
ማንም በሌለበት፣ ለሷ ተቆርቋሪ፤
እውነት በሌለበት፣ በደሏን መስካሪ፤
አዛኝ በሌለበት፣ አንስቶ ቀባሪ፤
ምነዋ ፈጣሪ!
እንዲህ እንባ ነጥፎ፤
በዳይ በግፍ ገዝፎ፤
ያንተው የእጅህ ስራ፣ እንደ ቅጠል ‘ረግፎ፤
ምነዋ ፈጣሪ! ኢትዮጵያን ዝም አልካት፤
በልጅ ሞት ስትከስል፣ ስታር እያየሃት?????????

No comments:

Post a Comment

Total Pageviews

Translate