Pages

Dec 24, 2012

ዚኊርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተኚታዮቜ ነገ ድምፃ቞ውን ያሰማሉ


ኢሳት ዜና:-<<ኚፓትርያርክ ምርጫ በፊት እርቅና ሰላም ይቅደም>>በሚል መሪ ሀሳብ ዹ ኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተኚታዮቜ በመጪው እሁድ ኚቅዳሎ በሁዋላ ዹተቃውሞ ድምፃ቞ውን እንዲያሰሙ ጥሪ ቀሹበ።
ደጀ ሰላም እንደዘገበው ላለፉት 20 ዓመታት በውግዘት ዚተለያዩ አባቶቜ አንድ እንዲሆኑ፣ አንዲት ቀተ ክርስቲያን፣ አንድ አስተዳደርና አንድ ቅ/ሲኖዶስ እንዲኖር ለማድሚግ ሲካሄድ ዹሰነበተው ዚእርቀ-ሰላም ሂደት በመልካም ውጀት ሊጠናቀቅ ጫፍ ላይ በደሚሰበት ጊዜ፤ ዚታዚውን ዚተስፋ ጭላንጭል በሚያዳፍን መልኩ በጥቂት ዹቅ/ሲኖዶስ አባላት ግፊት 6ኛ ፓትርያርክ ለመሟም “አስመራጭ ኮሚ቎” ተቋቁሟል።
“ዚቀተ ክርስቲያኔ ጉዳይ ያገባኛል” á‹šáˆšáˆ‰ ምእመናን በሙሉ ውሳኔውን በጜኑዕ በመቃወም ላይ ይገኛሉ>> ያለው ድሚ-ገጹ፤ይህንን “ኚኮምፒውተር ጀርባ” እና በስልክ ዹሚደሹግ ዚኢንተርኔት ተቃውሞን መልክ ለመስጠት፤ በመጪው እሑድ፣ ቅዳሎ ካለቀ በኋላ በዚአጥቢያቜን በመሰባሰብ  ሐዘናቜንንና መኚፋታቜንን እንዲሁም በውሳኔው ማዘናቜንን ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ለመግለጜ መሰባሰብ ይኖርብናል>>ብሏል።
<<ሰንበት ት/ቀቶቜ፣ ማኅበራት፣ ሰንበ቎ዎቜ እና ምእመናን በሙሉ ኚሚያውቋ቞ው ሰዎቜ በመጀመር ለእሑዱ ቀጠሮ መያዝ እና ዚመሰባሰቡን ሁናቮ መልክ መስጠት መጀመር ይኖርባ቞ዋል>>ያለው ደጀ ሰላም፤ << ዓላማቜን አንድ ነው። እርሱም <<ስብስባቜንን ዹሚጠሉ ሰዎቜ በፖለቲካ በማሳበብ በመንግሥት ዱላ ለማስደብደብ ዚሚያደርጉት ሙኚራ እንደሚኖር ስለምናውቅ ኚወዲሁ ለሚመለኹተው ሁሉ ዓላማቜንን መግለጜ እንፈልጋለን። መነጋገር ዹምንፈልገው ኹቅ/ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን አባቶቜ ጋር ነው።>> ብሏል።
<<ባልመሚጥነው መጂሊስ አንተዳደርም፣ መንግስት ዹማንቀበለውን ዹ አህባሜ አስተምህሮ በሀይል አይጫንብን!>> በማለት  እጅግ በርካታ ዹ እስልምና እምነት ተኚታዮቜ ያነሱት ተቃውሞ መፍትሔ ሳያገኝ  አንደኛ ዓመቱን እያስቆጠሚ ባለበት በአሁኑ ጊዜ ኚፓትርያርክ ምርጫ ጋር በተያያዘ  መንግስት  በቀተክርስቲያን አስተዳደር ውስጥም ጣልቃ መግባቱ ዚኊርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተኚታዮቜን ለተመሣሳይ ተቃውሞ እንዳይጋብዛ቞ው ተፈርቷል።
በስደት ዚሚገኙት አራተኛው ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ኹነ ሙሉ ስልጣና቞ውና ክብራ቞ው ወደ መንበራ቞ው እንዲመለሱ በፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ አማካይነት ደብዳቀ ኹተፃፈ በሁዋላ፤ ውሳኔው እንደገና እንዲቀለበስ መደሹጉና መንግስት አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ሆነው እንዲመጡ ፍላጎት ዹለውም መባሉ ይታወሳል።
ይህንንም ተኚትሎ በ ኢዮሩሳሌም ዹ ኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋህዶ ቀተ-ክርስቲያን ሊቀ-ጳጳስ ዚሆኑትን አቡነ ማትያስን ለማስሟም እዚተንቀሳቀሰ  እንደሆነ በተለያዩ ብዙሀን መገናኛዎቜ ተዘግቧል።
በዚህም ሳቢያ ቀተ ክርስቲያንን ወደ አንድ ለማምጣት ዚተጀመሚውናታላቅ ተስፋ ዚታዚበት ዚእርቀ-ሰላም  ጥሚት እዚተደናቀፈ ነው መባሉ ብዙዎቜን ዚቀተክርስቲያኒቷን ምዕመናን እጅግ ያሳዘነ ሆኗል።
<<ኚፓትርያርክ ምርጫ በፊት እርቀ-ሰላም ይቅደም >>በሚል መሪ ሀሳብ እሁድ ኹቅደሮ በሁዋላ ለሚደሹገው ተቃውሞ በተለያዩ ማህበራዊ ገፆቜ ጥሪዎቜ እዚተላለፉ ነው።

ዚብሔራዊ ቡድን ተጫዋ቟ቜ አድማ በመቱ ማግስት- መንግስት ለተጫዋ቟ቹ ጥያቄ ምላሜ እንደሚሰጥ ቃል ገባ


ኢሳት ዜና:-ኹ 31 ዓመታት በሁዋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ያለፉትና በመጪው ጥር ወር በደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው ዚአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዚተሻለ ውጀት ያስመዘግባሉ ተብለው ተስፋ ዚተጣለባ቞ው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን አባላት ኚክፍያና ኚአንዳንድ ጥያቄዎቜ ጋር በተያያዘ አድማ ዚመቱት ኚጥቂት ቀናት በፊት ነበር።
ዋልያዎቹን  አድማ ለመምታት ያነሣሳ቞ው፤ ቀደም ካለ ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድሚስ በእግር ኳስ ፌዎሬሜኑ በኩል  ዹተደሹገላቾው ምንም ዓይነት ድጋፍ አለመኖሩ፤እንዲሁም  በሜልማት መልክ ቃል ዚተገባላ቞ውን ገንዘብ ሊያገኙ አለመቻላ቞ው ጭምር ነው።
<<ሌላው ቀርቶ አሁን  ተቃውሞ ባደሚግንበት ጊዜ እንኳ ቜግራቜሁ ምንድነው ?ብሎ ቀርቩ ያነጋገሚን ዹለም>>ሲሉ ተደምጠዋል-ተጚዋ቟ቹ።
ዚአፍሪካ ዋንጫ ሊጀመር ኹ1 ወር ያነሰ ጊዜ በቀሹው በአሁኑ ወቅት ተጫዋ቟ቹ አድማ መምታታ቞ው ያስደነገጠው  ዚኢትዮዜያ እግር ኳስ ፌደሬሜን አርብ ዕለት አስ቞ኳይ  ስብሰባ በመጥራት ኚተጚዋ቟ቹ ጋር ተነጋግሯል።
በስብሰባው  áˆ‹á‹­ በብሄራዊ ቡድን ተጫዋ቟ቜ ኚተነሱት ጥያቄዎቜ መካኚል፤  <<ኚሱዳን ጚዋታ በፊት ቃል ዚተገባልን ዚገንዘብ ሜልማት ዘገይቷል>> ዹሚለው ቅሬታ እንደሚገኝበት ዚራዲዮ ፋና ዘገባ ያመለክታል።
ኹዚህም በተጚማሪ፦<< በሚሰጠን ገንዘብ ዚጋራ መኖሪያ ቀት መግዛት እንድንቜል ኹሚመለኹተው አካል ጋር ተነጋግራቜሁ ምላሜ ይሰጠን>> ዹሚል ጥያቄ ማቅሚባ቞ውም ተሰምቷል።
ዚፌዎሬሜኑ ተቀዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ተካ  አስፋው፤ ፌዎሬሜኑ ለሜልማቱ ዹዘገዹው በወቅቱ በካዝናው ተቀማጭ ገንዘብ ባለመኖሩ እንደሆነ በመጥቀስ ፥ በአሁኑ ወቅት ግን ስራ አስፈጻሚ ኮሚ቎ው ስለወሰነና ገንዘብም ስለተገኘ ሜልማቱ እንዲሰጥ መወሰኑን አስሚድተዋል ።
በዚህም መሰሚት ዚሜልማቱ ጣሪያ 100 ሺህ ብር ሆኖ ኚቀኒኑ ጚዋታ ጀምሮ ቋሚ ተሰላፊ ሆነው ዹቀጠሉ ተጫዋ቟ቜ ኹፍተኛውን ሜልማት እንደሚያገኙ  ፥ ሌሎቜም እንዳበሚኚቱት አስተዋጜኊ በዹደሹጃው ዚሜልማቱ ተቋዳሜ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።
<<ዚጋራ መኖሪያ ቀትን በተመለኹተ ዹሚመለኹተው፤ ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደርና በስሩ ለዚህ ጉዳይ ዹተቋቋሙ ተቋማት ናቾው>> ፤ያሉት አቶ ተካ <<ለዚህ ዚተጫዋ቟ቹ  ጥያቄ ዚፌዎሬሜኑ ምላሜ ፦ተቋማቱ በደንብና መመሪያ቞ው መሰሚት ምላሜ ዚሚሰጡ ይሆናል  ዹሚል  ነው >> ብለዋል።

ESAT Weekly News 23 December 2012 Ethiopia

“ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! ዚኢሮብ ሕዝብ ዚድሚሱልኝ ጥሪውን እያስተጋባልህ ይገኛል” – ዚኢሮብ መብት ተሟጓቜ ማህበር





                               á‹šáŠ¢áˆ®á‰¥ መብት ተሟጓቜ ማህበር (ኢመተማ)                                                                        áŒ¥áˆª ለ፦
       áˆ˜áˆ‹á‹ ዚኢትዮጵያ ህዝብ
        ኢትዮዜያ መንግስት
        ኢትዮጵያ አገር መኚላኚያ ሠራዊት
        ኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎቜ
       áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« ዚሲቪክና ሙያ ማህበራት

ኢመተማ ድምጜ አልባ ለሆነው ለኢሮብ ህዝብ መብት ለመሟገት ዹተቋቋመ ዚሲቪክ ማኅበር ሲሆን በኢትዮጵያ ሁሉንም ባለ ድርሻ ያለ
ምንም አድልዎ በእኩልነት ለማስተናገድ ዚሚቜል ዎሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲሰፍን በሚደሹገው ትግል ዚበኩሉን ድርሻ ዚማበርኚት
ዓላማ ያለው ማኅበር መሆኑ ለሁሉም ግልጜ ለማድሚግ ይወዳል።
ኹዚህም በተጚማሪ ኚተመሠሚተበት ጊዜ ጀምሮ በአሁኑ ጊዜ ፊት ለፊት አፍጩ ዚመጣውና ዚኢሮብ ብሔሚ-ሰብ ህልውና እጅጉን
ዚተፈታተነው ዚኢትዮ-ኀርትራ ዚድንበር ውዝግብ ተብሎ ዚሚጠራውን ዚድንበር ጉዳይና ኚወሚራው ዕለት ጀምሮ በዹጊዜው ውዝግብ
ኚተፈጠሚባ቞ው ዚኢትዮጵያና ኀርትራ ድንበሮቜ በሻዓቢያ እዚታገቱ ተወስደው መዳሚሻ቞ው ስላልታወቀው ኢትዮጵያዊያን በርኚት ያሉ
መግለጫዎቜን ሲያወጣ ቆይቷል። ሆኖም እስኚ ዛሬዋ ዕለት ድሚስ ጆሮ ዚሰጡንና ጮኞታቜንን ዹሰሙን ኢትዮጵያዊያን ቁጥር
ኹሚጠበቀው በታቜ ሆኖ አግኝተነዋል። ዚኢትዮጵያ መንግሥት እንደሆነ ጭራሜ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎናል።
ዹአገር ጉዳይ ዚጋራ ጉዳያቜን ነውና ዚምንመሰጋገንበት ባይሆንም ኚፖለቲካ ድርጅቶቜ ውስጥ፤ ጩኞታቜንን አድምጊ ላስተጋባልንና
ዚድንበር አኹላለልን አስመልክቶ ዚአልጀርሱን ስምምነት እንደማይቀበለው በፕሮግራሙ ውስጥ በግልጜ ያስቀመጠውን “ዓሹና ትግራይ
ለሉዓላዊነትና ዎሞክራሲ”ን ለማመስገን እንወዳለን። ኹመገናኛ ብዙሀን ደግሞ ምን ጊዜም ለጮኞታቜን ዋጋ በመስጠት ያለ ማወላወል
ሁሉም መግለጫዎቻቜንን በማስተናገድ አገራዊና ህዝባዊ ግዎታ቞ውን ዚተወጡትን, እነ www.ethiomedia.com ዚመሳሰሉትን ድሚ-
ገጟቜን እያመሰገን ሌሎቜ ድሚ-ገጟቜም ዚነሱን አርአያ ተኚትለው ዚምናወጣ቞ው መግለጫዎቜን እንዲያስተናግዱ፣ እንጠይቃለን።
እንዲሁም ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ነገሩ ዹአገርና ዚህዝብ ጉዳይ ስለሆነ፣ ዚኢሮብ ብሔሚሰብም ዚኢትዮዜያ ህዝብ ኣካል ነውና ትኩሚት
እንድያደርጉበት ጥርያቜንን እናቀርባለን።
ወደ ዋናው ጉዳያቜን ኚመግባታቜን በፊት ኢሮብ ዚሚባል ህዝብና አኚባቢ ዚት እንደሚገኝ ለማያውቁት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻቜን
ትንሜ ማብራሪያ እናስፍር። ኢሮብ በሰሜን ኢትዮጵያ በሰሜን ምሥራቅ ዓጋመ ውስጥ ዹሚገኝ  áŠ áŠšá‰£á‰¢ ነው። ይህ አኚባቢ ዚኢትዮጵያ
ታሪክ ኚተመዘገበበት ጊዜ ጀምሮ ኚኢትዮጳያዊነት ውጭ ዹሆነ ታሪክ ዹሌለው ኹመሆኑም በላይ ዚኢሮብ ህዝብ ዹውጭ ወራሪ ጠላት
በመጣ ቁጥር ዚኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስኚበር ኹወገኑ ኚኢትዮጵያ ህዝብ ጎን ተሰልፎ በጀግንነት ኚጠላት ጋር ተናንቆ ዹተዋደቀ ህዝብ
መሆኑ ታሪክ ዹማይዘነጋው ሀቅ ነው። ኹዚህም አልፎ ዚአብዛኛዎቹ ዹውጭ ወራሪዎቜ መግቢያ በር ላይ በመገኘቱ ምክንያት ዚመጀመርያ
ዚወሚራዎቜ ገፈት ቀማሜ እዚሆን እስኚዚቜ ቀን ዹደሹሰ ህዝብ ነው። ዚሩቁን ትተን በ1990 ዓ.ም ዚሻዓቢያ ወሚራ በተፈጞመበት ጊዜ፤
መሣርያ ኚጠላት እዚነጠቀ ያደሚገው ጀብዱ ዹመኹላኹል ጊርነት (ዕጡቃት-ሰንበት) እንደ ምሳሌ መጥቀሱ አገባብ ይሆናል።
ዚኢሮብ ህዝብ ዛሬ እንደ ብሔሚ-ሰብ ህልውናው በጣም አስጊ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ይገኛል። ኚትውልድ ወደ ትውልድ እዚተላለፈ
ዚመጣው መኖሪያ ቀዹው ዛሬ በአልጀርስ ስምምነት ተወጥኖ በሄግ ውሳኔ ጞድቆ በዚህ ድሚ-ገጜ ኚመግለጫው ግርጌ ዹሰፈሹው ካርታ
እንደሚያመለክተው ለም ኹሆነው ዚመሬቱ አንድ ሶሰተኛ ለወራሪው ዚሻዓቢያ አገዛዝ እንዲሰጥ ተበይኖብናል ተብሏል። (ካርታውን
ለማዚት http://www.irobmablo.org/IRAA_Statement_May26.pdf ይህንን አድራሻ ይጫኑ።) ዚኢሮብ ብሔሚ-ሰብ አዶሓ ኢሮብ
(ሶሰት ኢሮብ) በሚል መጠሪያ ዚሚታወቅ፤ ሓሳባላ፤ ቡክናይቲ-ዓሹና አድጋዲ-ዓሹ ዚሚያጠቃልል ሲሆን፤ በአልጀርስ ስምምነት መሰሚት
ዹተሰጠው ዹሄግ ውሳኔ ተግባራዊ ኹሆነ በተጠቀሰው ካርታ እንደተመለኚተው ለም ዹሆኑ ዚቡክናይቲ-ዓሹ ሰፊ ቀበሌዎቜን ጚምሮ
መላው አድጋዲ-ዓሹ ወደ ኀርትራ እንደሚካለል ግልጜ ነው። ይህ ማለት ወደ ኀርትራ በሚካለለው ግዛት ውስጥ ዹሚኖሹው ህዝብ
በአንጻራዊ መልኩ ሲታይ ዚአዶሓ ኢሮብ ግማሜ በመሆኑ ይህ ብሔሚ-ሰብ በሁለት አገሮቜ መካኚል ተኹፍሎ ለመጥፋት ዚተወሰነበት
ኹመሆን ተለይቶ ለመታዚት ፈጜሞ ዚሚቻል አይሆንም። በመሆኑም፤ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ይህንን ጥፋት ለመታደግ ዚሚቻለውን ሁሉ

እንዲያደርግ ዛሬም እንደትላንቱ ጥርያቜንን ለማቅሚብ እንገደዳለን። ይህንን ጥሪ ደግመን ደጋግመን ለማቅሚብ ዹምንገደደው አብዛኛው
ኢትዮጵያዊ ወገናቜን ኚኢትዮጵያ ለኀርትራ ስለሚለገሰው መሬት ያለውን ብዥታ ለመቅሹፍ ይሚዳል ኹሚል እሳቀ በመነሳት መሆኑ
ልብ ሊባልልን እንፈልጋለን።
ዛሬ ኚኢትዮጵያ ለኀርትራ ስለተበዚነው ግዛት ሲወሳ አብዛኞቹ ኢትዮጵያዊ ምሁራን በሚጜፏ቞ውና ለመገናኛ ብዙኃን በሚሰጧቾው
ቃለ-መጠይቆቜ ውስጥ ሲጠቅሱት ዹምናነበውና ዚምናዳምጠው በአብዛኛው ስለ ባድመ ነው። ስለባድመ መወሳቱና መኚራኚሩን
ዚኢትዮጵያ ግዛት ነውና ዚምንሰማማበት ይሆናል። ሆኖም እዚህ ላይ ዚተጠቀሱ ዚኢሮብ መሬቶቜና ሌሎቜ ለኀርትራ ዹተኹለሉ
ዚኢትዮጵያ ግዛቶቜም ቢጚመሩበትና ዚኢትዮጵያ ህዝብ ለወራሪ ለመሾለም ለድርድር በመቅሚብ ላይ ስላሉ ሉዓላዊ ግዛቶቹ እንዲያውቅ
ቢደሚግ መልካም እንደሚሆን ክልብ እናምናለን። ዚኢትዮጵያ መንግሥትም ቢሆን ኚባድመ ውጭ ለኀርትራ ስለተሰጡት ሌሎቜ
ግዛቶቻቜን ሲናገርም ሆነ ዚአኚባቢዎቜን ስሞቜ ሲጠቅስ አይሰማም። ይህ ያለምክንያት ነው ዹሚል እምነት ዹለንም። ኚአኚባቢው ነዋሪ
ውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ አኚባቢውን ስለማያውቀው ዚትኛው ቀበሌ ዚኢትዮጵያ ዚትኛው ደግሞ ዚኀርትራ እንደሆነ ለማወቅ
አይቻለውም። በመሆኑም በደፈናው ኹዚህ በፊት በአቶ ሥዩም መስፍን በይፋ እንደተነገሚን “በጩር ሜዳ ዹተጎናጾፍነውን ድል በዓለም
ዓቀፉ ፍርድቀትም ደግመነዋል” ዹሚለውን “በጩር ሜዳ ያስመዘገብነውን ድል በድርድር ደግመነዋል” በሚል ባዶ መፈክር እንዳይተካ
እንሰጋለን። ሆኖም እኛ ዚአኚባብው ተወላጆቜ ነንና እንኳን መላውን አድጋዲ ዓሹና ለም ዹሆኑ ዚቡክናይቲ ዓሹ መሬት እያንዳንዷን
ዚራሳቜን ዚሆነቜ ዛፍና ማሳን እናውቃታለን። ስለሆነም፤ ዚአኚባቢያቜን ዚኢትዮጵያ ግዛቶቜን በሚመለኚት ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዳር
ድንበሩን እንዲያውቅ ዚማድሚግ ሓላፊነት አለብን ብለን እናምናለን። ስለሆነም፤ ኢትዮጵያውያን ዚመጀመርያ ዚሻዓቢያ ወሚራ ሰለባ
ዚሆነቜው ባድመ በዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙሃን ትኵሚት በማግኘቷ ዚዚቜ ግዛት ወደ ኢትዮጵያ ዹመኹለልና ያለመኚለል እጣ ዚሌሎቜ
ሰፊ ግዛቶቻቜን እጣ ፈንታን ጋርዶት በነዋሪው ዜጋ ብዛት ኹማንም ካልበለጡ ዚማይተናነሱ ግዛቶቻቜን “በዓይንህን ሾፍን ላሞኝህ”
ዓይነት ተራ ፈሊጥ እንዳንሞኝ መልሰን መላልሰን ለማሳሰብ እንወዳለን። “እንኳን መሬታቜን በሆነ ምክንያት ዚመሬታቜን ድንጋይ ወደ
ኀርትራ ግዛት ቢሄድ ሞተንም እንመልሷለን” ዹሚለን አንድ ኵሩ ኢትዮጵያዊ ህዝብ ዹወገኑን ድጋፍ ዚመሻት መብት አለው ብለን
እናምናለን።
እንደገና ስለ ድንበር ጥያቄ ለማንሳት ዹሚገፋፉን ምክንያቶቜ በርካቶቜ ናቾው። ኹነዚህም ውስጥ በቅርቡ አቶ በሚኚት ስምዖን በአንድ
ዚኀርትራዊያን ‘ዚፓልቶክ’  áˆ˜á‹ˆá‹«á‹« መድሚክ ባደሚጉት ንግግር ባድመ ዚኀርትራ ናት ማለታ቞ው፣ ቀጥሎም ጠቅላይ ሚኒስትር
ኃይለማርያም ደሳለኝ ለአልጀዚራ ተሌቪጅን ጣቢያ ዚሰጡት ቃለ-ምልልስ በዋናናት ሊጠቀሱ ዚምቜሉ ናቾው። ዚቀድሞው ጠቅላይ
ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ አሰና ለሚባለው ዚኀርትራ ተቃዋሚዎቜ ደጋፊ ሬዲዮ ጣቢያ ዚሰጡትን ዚኢትዮጵያ ግዛቶቜን በድርድር
ለሻዓቢያ ለማስሚኚብ ዝግጁነታ቞ውን ያበሰሩበትን መግለጫ አስመልክቶ መኢተማ በወቅቱ ዹተቃውሞ አቋሙን ዚገለጞበት መግለጫ
ማውጣቱ ዚሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ “አስመራ ሄደህ ኚአቶ ኢሳያስ ጋር ትደራደራለህ ወይ
ብለሜ ኚጠዚቅሜኝ፤ መልሮ አዎ ነው” በማለት ያልተጠዚቁትን ኚመመለሳ቞ውም በላይ ኹዚህ በፊትም አቶ መለስ ዜናዊ አስመራ ድሚስ
በመሄድ ለመደራደር ኚሃምሳ ጊዜ በላይ ጥያቄ አቅርበው እንዳልተሳካላ቞ው በይፋ አሳውቀውናል። በተጚማሪም ዚአቶ መለስን ፖሊሲ
ሳይበሚዝ እንዳለ ተግባራዊ እንደሚያደርጉ በተደጋጋሚ ነግሹውናል። አቶ መለስ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ዙርያ ዚነበራ቞ው አቋም ደግሞ
ምን እንደነበሚ ሁሉም በግልጜ ዚሚያወቀው ስለሆነ እዚህ ላይ መድገሙ አንባቢን ማሰል቞ት ይሆንብናል። ሆኖም ዚዛሬ ኚትላንትናው
ለዚት ዚሚልበት ሁኔታ እዚተኚሰተ እንዳለ እንገነዘባለን። ይኾውም አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ ትላንት በአፍንጫዚ ይውጣ ሲሉ እንዳልነበሚ
ሁላ ዛሬ ኚኢትዮጵያ ጋር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ስለ ድንበር መካለል ለመሾማገል ዝግጁ ነኝ ማለታ቞ውንና ኹዛም አልፈው ኳታር
በኢትዮ-ኀርትራ ዚድንበር መካለል ጉዳይ እንድታደራድራ቞ው መጠዹቃቾው ዓዋተ ዚተባለው ዚኀርትራዊያን ድሚ-ገጜ ዘግቊት ይገኛል።
ስለሆነም ኢመተማ ነገሩ ሁሉም ዚሀገራቜን ዳርድንበርና በድንበሩ ዚሚኖሩ ዜጎቜ ጉዳይ ዚሚመለኚታ቞ው ወገኖቜ ዚዳር ድንብር ጥያቄ
ኹምን ጊዜም በላይ ነቅተው እንዲኚታተሉት በሚገባ ወቅት ላይ ነን ብሎ ስለሚያምን ነው ይህን ጥሪ አሁን ለማቅሚብ ዹፈለገው። ኹዚህ
በፊት ደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያና ኀርትራን ለማደራደር በዝግጅት ላይ እንደምትገኝ ገልጻ ነበር። ሆኖም፤ ዚማደራደሩን ሓሳብ ምን ላይ
እንዳደሚሰቜው ወይም በምን ምክንያት እንዳቋሚጠቜው ሳይታወቅ አሁን ኳታር ሾምጋይ ለመሆን እንደተጠዚቀቜ መወራት ጀምሯል።
ወሬው ትክክል ኹሆነ ዹጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ መንግሥት ምን አቋም እንዳለው ለመስማት እንጓጓለን። በነገራቜን ላይ
ኢትዮጵያና ኳታር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታ቞ውን ኳታር ኚሻዓቢያ ጋር በነበራት ግንኙት ምክንያት አቋርጠው እንደነበር ዚሚታወቅ
ነው። ዲፕሎማሲያዊ ግንኑነታ቞ውን ያደሱት አሁን በቅርብ ቀናት መሆኑም ይታወቃል። ዹሆነ ሆኖ ነገሩ በይፋ ሲወጣ ዹምንለው
ሊኖሹን ስለሚቜል ለጊዜው እዚሁ ላይ ለመግታት መርጠናል። ወደ ዋናው ጉዳይ ስንመለስ ግን ኹማንም ጋር ለህዝቊቜና አገሮቜ ሰላም
ሲባል ዹሚደሹገውን ሜምግልናና ድርድር ዹሚደገፍ ቢሆንም፤ ዚአንድን አገርና ህዝብ ጥቅምን ዚሚጎዳና ዚአንድን ብሔሚ-ሰብ ህልውና
ዚሚፈታተን ድርድር ውስጥ መግባት ዚሚያስኚትለውን አደገኛ መዘዝ ምን ሊሆን እንደሚቜል ዚአልጀርስ ስምምነት በሚገባ
አስገንዝቊናል። አቶ ኢሳያስ በብልጠታ቞ው ይሁን በአፍቃሬ ኀርትራ አስመሳይ ባለጋራዎቻ቞ው ይሁንታ፧ በኢትዮጵያ ልጆቜ ደም
ዹተኹበሹውን በወሚራ ይዘዋቾው ዚነበሩ ግዛቶቻቜንን አልጀርስ ላይ በወርቅ ሳህን ቀርቩላቾው በፈሚሙት ውል መሠሚት ኚአገባብ ውጭ
ዹተወሰነላቾውን ዹሰው ግዛት ካልተሚኚብኩ በማለት ዘራፍ በማለት ላይ እንደነበሩ ሁላቜን ዹምናውቀው ጉዳይ ነው። አሁንም አቶ
በሚኚት በአንድ ዚኀርትራዊያን ‘ፓልቶክ’ ክፍል ባደሚጉት ቃለ-ምልልስ ባድመ ዚኀርትራ ነው በማለት ዚሰጡት ቃል አቶ መለስ “አንድ

ቀት ለሁለት እንዳይኚፈል” መደራደር አለብን በማለት ሲያራምዱት ኹነበሹው አቋም ጋር ተዳምሮ ሲታይ አዲሱ ድርድር ጥያቄ
በ’ኖርማላይዜሜን’ ተሳቊ ግዛቶቻቜንን ዚሚያስሚክብ እንዳይሆን ስጋቱ አለን። ያም ሆነ ይህ ዚኢሮብ ሕዝብ ይህንን ለመቀበል በምንም
ዓይነት መንገድ ዝግጁ እንዳልሆን ጠላትም ሆነ ወዳጅ ሁሉ እንዲያውቅልን እንፈልጋለን።
ለመላው ዚኢትዮጵያ ህዝብ
ዳር እዚተቆሚሰ ሲጠፋ ማኾል ዳር ይሆናል እንደሚባለው፤ ኚኀርትራ ጋር ዹሚዋሰኑ ዚኢትዮጵያ ግዛቶቜ ለሻዓቢያ ሲለገሱ ዝም ብለን
መመልኚቱ ማኾሉን ዳር ወደ ማሹግ እዚተጠጋን መሆኑ ታውቆ ዚድንበራቜንን ጉዳይ በአንክሮ ሊኚታተለው እንደሚገባ ይገነዘበዋል
ብለን እናምናለን። ዹተጠቀሰውን ድንበር ለማስኚበር ብርቅዚ ልጆቜህን ገብሚህበታል። ያም አልበቃ ብሎ፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት
አናሳ ብሔሚ-ሰቊቜ አንዱ ዹሆነው ዚኢሮብ ብሄሚሰብ ወገንህ ለሁለት ተኹፍሎ ህልውናው አደጋ ላይ ዚወደቀበት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ
ዚድሚሱልኝ ጥሪውን እያስተጋባልህ ይገኛል። ስለሆነም ለዚህ ወገንህና ውድ ልጆቜህ ክቡር ህይወታ቞ውን ለገበሩለት ሉዓላዊ መሬትህ
ዘብ እንድትቆም፣ ካላንተ ሁለገብ ተሳትፎ ዹሚደሹገ ማንኛውም ዚዳር ድንብር ማካለል ሆነ ድርድር ተቀባይነት እንደሌለው በሚቻለው
መንገድ ሁሉ መንግሥትን እንድታስታውቅና እንድታስጠነቅቅ ጥርያቜንን እናቀርባለን።
ዚኢትዮጵያ ዚሙያና ሲቪክ ማህበራት፤
ዛሬ በሕወሓት/ኢህአዎግ መንግሥት በወጣው አዲሱ ‘ሕግ’ ምክንያት ህልውናቹህ ፈተና ውስጥ መውደቁ ዚሚታወቅ ነው። ሆኖም
ለህልውናቹህ መኹበር ኚምታደርጉት ትግል ጎን ለጎን ይህንን በአገር ዳር ድንበር ዹሚደሹገውን ግልጜነት ዹጎደለው ዚድብብቆሜ ድርድር
መደሹግ እንደሌለበት በማመላኚት ዚትግላቹህ አካል አድርጋቹህ እንድትንቀሳቀሱበት፣ በኢትዮጵያና በኀርትራ ጠሹፍ አኚባቢ
ዹሚኖሹው ህዝባቜን ሁኔታም በቅርበት እንድትኚታተሉት በትህትና እንጠይቃለን።
ጥሪ ለኢትዮጵያ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ
ዎሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲሰፍንባትና አንድነቷ እንዲጠበቅ ዚምትዋደቁላት አገርና ህዝብ ኚዳር እስኚ ዳር በአንድ ዓይን ታዩታላቹህ
ብለን እናምናለን። በመሆኑም፤ አሁን ኚሚታዚው ሁኔታ አንጻር በኢትዮጵያና ኀርትራ መካኚል ይደሹጋል ተብሎ በመናፈስ ላይ ያለው
ዚድርድር ዜና እጅጉን ዚሚያሳስበን መሆኑ እንድትሚዱልን እንሻለን። ስለ ዚኢትዮ-ኀርትራ ድንበር ጉዳይ ሲነሳ ሁሉም ቀድሞ
ዚሚያነሳውም ስለ ባድመ ብቻ መሆኑ ሌላውን አኚባቢ እንደተዘነጋ ሆኖ እንዳይታይ ስጋት ይፈጥርብናል። በመንግሥት ለመጥቀስ
ዹማይፈለጉ እንደ አድጋዲ-ዓሹ ዚመሳሰሉ ዚኢሮብ ሰፊ ግዛቶቜ ፍትሃዊ ባልሆነ መንገድ በሄግ ውሳኔ ወደ ኀርትራ መካለላ቞ው በግልጜ
ተቀምጩ ዚሚታይ ጉዳይ ነው። ዚሕወሓት/ኢህአዎግ መንግሥትም ዹሄግ ውሳኔን እንደተቀበለው በይፋ እዚነገሚን ነው። ስለሆነም፤
በድርድር ስም ለኀርትራ ዹሚለገሰው ግዛታቜን ዚኢሮብ ብሔሚ-ሰብን ለሁለት ኹፍሎ ዚሚያጠፋ ኹመሆኑም በላይ በአኚባቢው ዘላቂ
ሰላም እንዳይኖር እንቅፋት ሆኖ እንደሚዘልቅ አይቀሬ ክስተት ነው። በመሆኑም፤ በዚህ ዚዳር ድንበር ጉዳይ ላይ ያላቹህን አቋም ግልጜ
በማውጣት፤ ይህንን አገርንና ወገንን ለዘለቄታው ዚሚጎዳ ድርድር በይፋ እንድትቃወሙት ጥርያቜንን እናቀርባለን።
ለኢትዮጵያ አገር መኚላኚያ ሠራዊት፤
ሉዓላዊ ዳር ድንበርን ለማስኚበር መተኪያ አልባ ዚሆነቜ ህይወትህን በመክፈል ወሚራውን በጀግንነት ቀልብሰሃል። እነዚህን ዛሬ
ለድርድር በመቅሚብ ላይ ዚሚገኙትን ሉዓላዊ ዚኢትዮጵያ ግዛቶቜ ኚወራሪው ዚሻዓቢያ ኃይል ለማስመለስ በተካሄደው ውጊያ ምን ያህል
ጓዶቜህን እንዳጣህ ካንተ በላይ ዚሚያውቀው ዹለም። ዹፈሹጠመ ክንድህን ለጠላቶቜህ አሳይተሃል። ካንተ ዚሚጠበቅብህን ግዳጅም
በአኵሪ መንገድ ተወጥተሃል። ሆኖም፤ ዹጩር ሜዳ ድልህን በአልጀርስ ስምምነት ቀዝቃዛ ውኃ ተሰልቜቶበት እንዳልነበሚ ተደርጎ ደምህ
ዚኚፈልክበት ሉዓላዊ ግዛታቜን በፈሹጠመ ክንድህ ላዛልኹው ጥላት እንዲሰጥ ተወስኖበታል። ዛሬም ለአስራ ሶስት ዓመታት አንተን ዳር
ድንበር ጠብቅ ብለው በቀበሮ ጉድጓድ እንድትኖር ካደሚጉ በኋላ በስመ ድርድር አሳልፈው ለኀርትራ ለመስጠት እንደራደር እያሉ ዚአቶ
ኢሳያስ አፈወርቂን በር በማንኳኳት ላይ ይገኛሉ። ሕገ-መንግሥቱ ዚጣለብህን ዹአገርን ዳር ድንበር ዚማስኚበርና ዚኢሮብ ብሔሚ-ሰብ
ለሁለት እንዳይኚፈል ዹመኹላኹል ሐላፍነት አሁንም ባንተ ትኚሻ ላይ ዚተጣለ ግዳጅ መሆኑ ለደቂቃም ቢሆን ልትዘነጋው ዚማትቜለው
አገራዊ ጉዳይ መሆኑን በማመን በፖለቲካ ውሳኔዎቜ ተሳበው ዚሚቀርቡ ኢትዮጵያንና ህዝቊቿን ዚሚጎዱ ውሳኔዎቜን እንድትቃወም
ወገናዊ ጥሪያቜንን እናቀርባለን።
ለኢሮብ ብሔሚ-ሰብ  á‰°á‹ˆáˆ‹áŒ†á‰œ በሞላ፤
ኹኛ በላይ አኚባቢያቜን ዚሚያውቅ ሰው ሊኖር አይቜልም። በአልጀርስ ስምምነትና በሄግ ውሳኔ መሠሚት በርካታ ዚቡክናይቲ-ዓሹ
መንደሮቜና መላው አድጋዲ-ዓሹ ለኀርትራ መኹለላቾው ግልፅ ነው። ስለሆነም ባለቀቱ ካልጮኞ ጎሚቀት አይሚዳም እንዳይሆንብን
ስለተሰጠው መሬታቜንና ዳር ድንበራቜንን በሚመለኚት ኢትዮጵያዊያንን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉና በያለንበት ማሳወቅ ይኖርብናል።

በተጚማሪም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዚአገሩ ዳር ድንበር ዚት ድሚስ እንደሆነ በግልጜ አውቆ ኹኛ ኚአኚባቢው ነዋሪዎቜ ጎን በመሰለፍ
ድንበሬን አትስጡ ብሎ ለመቆም እንዲቜል፣ ዹሄግ ውሳኔና ዚድንበራቜን አጣብቂኝ ውስጥ መግባት፤ ኹዚህም አልፎ ዚኢትዮጵያ
መንግሥት ባለሥልጣናት እንኳን ዹኛ ነው ብለው ለመጠዹቅ ዚአኚባቢውን ስም ለመጥራት መጠዹፋቾውን፤ ዚኢሮብ መሬትና ህዝብ
ለሁለት መክፈል ማለት ዚብሔሚ-ሰቡን ህልውና ማክተም  áŠ¥áŠ•á‹°áˆ†áŠ በሚገባ ተገንዝበን አንደኛ በአንድ ድምጜ እንድንቃወም፣ በሁለተኛ á‹°áˆšáŒƒ ደግሞ  á‰ áˆá‰³áŒˆáŠ™á‰µ አጋጣሚ ሁሉ ኢትዮጵያዊን ሆነ ዓለም አቀፍ ማህበሚሰብን ዚጉዳዩን አንገብጋቢነት እንድታስሚዱ ጥሪያቜንን áŠ¥áŠ“á‰€áˆ­á‰£áˆˆáŠ•።

ለኢትዮጵያ መንግሥት፤

ዚአንድ አገር  á‹šáŒá‹›á‰µáŠ“ ዚህዝብ አንድነት ዚማስጠበቅ ሓላፊነት ዚሚጣለው በሚያስተዳድራት መንግሥት ላይ መሆኑ ግልጜ ነው።አሁን
ኢትዮጵያን ዹሚገዛ መንግሥት ግን ዹአገር መኚላኚያ ሠራዊታቜን ደም ገብሮ፤ ውድ ህወቱን በመሰዋት ወሚራውን ቀልብሶ ያስመለሰውን
ሉዓላዊ ግዛታቜን አልጀርስ ድሚስ ተጉዞ ለተሾነፈው ወራሪ ጠላት አስሚክቊ ተመልሷል። ሄግ ላይ በገላጋይ ዳኞቜ ፊት ቀርቩ ተገቢና
ተመዝግበው ዹሚገኙ ዚሰነድ ማስሚጃዎቜን ለማቅሚብ ባለመቻሉ ወይም ባለመፈለጉ ሉዓላዊ ግዛታቜንን ለሻዓቢያ ያስሚኚበው ይህ
መንግሥት ነው። ዹግልግል ፍርድ ቀቱ እነ ፆሮና ዚኢትዮጵያ ናቾው ብሎ ሲወስን ዚኢትዮጵያ አይደሉም ጥያቄም አላቀሚብንባ቞ውም
ብሎ ዚተኚራኚሚው ይህ መንግሥት ነው። በፍርድ ቀት ተሾንፈን እያለ አሾንፈናል ብሎ ሊያማልለን ዹሞኹሹ ይህ መንግሥት ነው።
ሻዓቢያ ዚተባበሩት መንግሥታት ድድርጅት ዹሰላም አስኚባሪ ኃይልን በማባሚር ዚሃያ አምስት ኪሎ ሜትር ጊዜያዊ ዹሰላም ቀጠና
በመቀልበስ ውሉን አፍርሶት እያለ፤ ሻዓቢያ ያፈሚሰውን ውል በመንኚባኚብ ዹሄግ ውሳኔን ተቀብያለሁ ብሎ ደጋገመው በማስተጋባት ላይ
ዹሚገኘውም ይህ መንግስት ነው። አሁን ድግሞ ሉዓላዊ ግዛታቜንን አሳልፎ ለሻዓቢያ ለመስጠት ለሜምግልና ዚሻዓቢያን በር
በማንኳኳት ላይ ዹሚገኘው ይህ መንግሥት ነው።   ስለሆነ መንግስት ሀገርንና ህዝብን ወክሎ ስለ ዳር ድንብርና ዹሀገር ሉዓላዊነት
መደራደር በመርህ ደሹጃ ዹሚንቀበለው ቢሆንም እስካሁን ድሚስ ኚህወሓት/ኢህአዎግ መንግስት ስለ ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት ካዚነው
ተመክሮ ይህ መንግስት በትክክል ዳር ድንበራቜንና ሉዓላዊት ኢትዮዜያን በሚጠቅም መንገድ ይደራደርልናል ብለን ለማመን
ይቾግሹናል። ስለሆነም ዚኢትዮጵያን ሉዓላዊ ግዛቶቜ በዘላቂነት ለማስኚበር ፍላጎቱ ካለ፤ አሁንም ቢሆን አልመሾምና ዚአልጀርስን ውልና
ዹሄግ ውሳኔን ውድቅ ማድሚጉ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለዓለም አቀፉ ማሕበሹ-ሰብ በይፋ እንዲያሳውቅ እንጠይቃለን።
እኛ ኢሮቊቜ ዚራሳቜንን አንሰጥም ዹሰውም አንፈልግም፤ ድንበራቜን ዚት እንደሆነ ኹማንም በላይ እኛ ነዋሪዎቹ እናውቀዋለን፣
ኚኢትዮጵያ መንግስትና ኚሻዕቢያ ጣልቃ ገብንት ነጻ ኹሆን በድንበር ኹሚዋሰኑን ኀርትራዊያን ወንድሞቻቜን ጋር ዳር ድንበሩን
ያለምንም ቜግር እኛው ራሳቜን በድንበሩ አኚባቢ ዹምንኖር ህዝቊቜ ዚዚራሳቜንን ቊታ በግልጜ ስለምናውቅ ያለምንም ቜግር ተወያይተን
ለመፍታት እንቜላለን። እኛ ዚነሱን እንደማንፈልግ እነሱ ያውቃሉ። እኛም እነሱ ዹኛን ይፈልጋሉ ብለን አንገምትም። ተጠቃልሎ
ሲመነዘር ዚድንበር ማካለል ጉዳይ፣ ለሁለቱ ህዝቊቜ መተው ያለበት ጉዳይ ነው። ኹዛ ውጭ አሁን በሚታዚው መልኩ ኹቀጠለ ለሁለቱ
አገዛዞቜ ጊዜያዊ ፖለቲካ ጠቀሜታ ሊኖሹው ይቜል እንደሆነ እንጂ፤ ዘላቂ መፍትሔና ዹተሹጋጋ ሰላም ለአኚባቢውም ሆነ ለሁለቱ አገሮቜ
ለማምጣት ፈጜሞ አይቜልም!
ኚኢ.መ.ተ.ማ
ታሕሣሥ 2005 ዓ.ም  

Dec 23, 2012

“ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! ዚኢሮብ ሕዝብ ዚድሚሱልኝ ጥሪውን እያስተጋባልህ ይገኛል” – ዚኢሮብ መብት ተሟጓቜ ማህበር


ዚኢሮብ áˆ•ዝብ መብት á‰°áˆ›áŒ“ቜ áˆ›áˆ…በር ለዘ- áˆá‰ áˆ» ድሚ ገጜ á‰ áˆ‹áŠšá‹ áˆ˜áŒáˆˆáŒ« “ዛሬ á‰ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« á‹áˆµáŒ¥ ካሉት áŠ áŠ“áˆ³ ብሔሚ- áˆ°á‰Šá‰œ áŠ¥á‹«áˆµá‰°áŒ‹á‰£áˆáˆ… ይገኛል። ስለሆነም ለዚህ ወገንህና ውድ ልጆቜህ ክቡር ህይወታ቞ውን ለገበሩለት ሉዓላዊ መሬትህ ዘብ
እንድትቆም፣ ካላንተ ሁለገብ ተሳትፎ ዹሚደሹገ ማንኛውም ዚዳር ድንብር ማካለል ሆነ ድርድር ተቀባይነት እንደሌለው
በሚቻለው መንገድ ሁሉ መንግሥትን እንድታስታውቅና እንድታስጠነቅቅ ጥርያቜንን እናቀርባለን።” አለ።Read full story in PDF (ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ)አንዱ á‹šáˆ†áŠá‹ á‹šáŠ¢áˆ®á‰¥ ብሄሚሰብ ወገንህ ለሁለት ተኹፍሎ ህልውናው አደጋ ላይ ዚወደቀበት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ዚድሚሱልኝ ጥሪውን

Dec 21, 2012

(Breaking News/ሰበር ዜና)፡ ሃገር ቀት ባለው ሲኖዶስ ዚሃሳብ ልዩነት ተፈጠሹ






ሐበሻ) ትናንት በሰበር ዜና “ኢትዮጵያ ያለው ሲኖዶስ ፓትርያርክ ለመምሚጥ አስመራጭ ጳጳትን መሹጠ” ዹሚል
ዜና ማስነበባቜን ይታወሳል። ዚሲኖዶሱ ስብሰባ ሳይጠናቀቅ ዹተወሰኑ አባቶቜ በተለይ ውጭ ያለው ሲኖዶስ ጋር
ዹሚደሹገው እርቀ ሰላም ሳይጠናቀቅ ፓትርያርክ እንዳይመሚጥ በመቃወም ስብሰባውን ሹግጠው መውጣታ቞ውንና
አንዳንድ አባቶቜም በስብሰባው ላይ እንዳልተገኙ ዹዘ-ሐበሻ ዚቀተክህነት ታማኝ ምንጮቜ ጠቆሙ።
እነዚሁ ምንጮቜ ፓትርያርክ እንዲሟም በአስመራጭነት ኚተመሚጡት ኹቅ/ሲኖዶስ አባላት፣ ኹመ/ፓ/ጠ/ቀ/ክ
መምሪያ ሓላፊዎቜ፣ ኚገዳማት አበምኔቶቜ፣ ኚሰንበት ት/ቀቶቜ አንድነት፣ ኚመንፈሳውያን ማኅበራት እና ኚታዋቂ
ምእመናን ዚተውጣጡ ናቾው ኚተባሉት 13 ሰዎቜ መካኚል 8ቱ ኚአንድ ብሄር ዚመጡ መሆናቾው ዚጉዳዩን ፖለቲካነት
ዹበለጠ አጉልቶታል ያሉት ምንጮቹ ኹነዚህ አስመራጮቜ መካኚል ኚአንድ ብሄር ኚመጡት 8 ሰዎቜ ውስጥ አቡነ
ጢሞጢዎስ፣ አቡነ እስጢፋኖስ፣ መጋቀ ምስጢር አምደብርሃን፣ ንቡሚ ዕድ እዝራ እንደሚገኙበት አስታውቀዋል።

ለይ አሜሪካ ኹሚገኘው ሲኖዶስ ጋር እርቀ ሰላም ላይ ዚነበሩት አባቶቜ አቡነ ገሪማ፣ አቡነ አትናቲዎስ፣ አቡነ
ቀውስጊስ በዚህ ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚ቎ በተመሚጠበት ስብሰባ ላይ እንዳልተገኙ ዚጠቆሙት እነዚሁ
ምንጮቻቜን አቡነ ኀልሳ እና በውጭ ሃገር ያሉ ጳጳሳት ሁሉ እንዳልተገኙና ድርጊቱን መቃወማቾውን እንዲሁም
በአብዛኛው ፓትርያርክ እንዲሟም በመወትወት ላይ ዚሚገኙት ኚመንግስት አስገዳጅነት ጋር ኚአንድ ብሄር ዚመጡ
አባቶቜ መሆናቾውን ገልጾዋል።
በተለይም አቡነ ሉቃስና አቡነ ቄርሎስ ይህን ዚሲኖዶሱን ስብሰባ ጥለው እንደወጡ ያስታወቁት ምንጮቜ በሲኖዶሱ
ውስት በ6ኛው ፓትርያርክ ሹመት ዙሪያ ዚሃሳብ ልዩነት እንደተፈጠሚ አስታውቀው እንደውም አቡነ አትናቲዎስ
ድርጊቱን አምርሹው መቃወማቾውንና ምርጫውን እንደማይቀበሉት በይፋ መናገራ቞ው ታውቋል።
በመንግስት ኹፍተኛ ጫና 6ኛ ፓትርያርክ በአፋጣኝ ለመሟም ዹሚደሹገው ጥሚት በበርካታ ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ
እምነት ተኚታዮቜ ዘንድ ተቃውሞ እዚገጠመው ይገኛል። ዚሲኖዶሱ ስብሰባ ኹተጠናቀቀ በኋላ ዚሲኖዶሱ ጾሐፊ አቡነ
እዝቅኀል መግለጫ እንዲሰጡ ተጠይቀው ፈቃደኛ ባይሆኑም ስብሰባው ዹተጠናቀቀው በሃሳብ ልዩነት መሆኑን
ምንጮቻቜን ተናግሹዋል።

ሰበር ዜና: ዚግንቊት 7 ሕዝባዊ ኃይል ተመሰሹተ


ዚግንቊት 7 áˆ•ዝባዊ áŠƒá‹­áˆ á‰°áˆ˜áˆ°áˆšá‰°
ህዝባዊ áˆ€á‹­áˆ‰ á‰ á‹ˆáŒ£á‰¶á‰œáŠ“ áˆáˆáˆ«áŠ• á‹šá‰°áˆ˜áˆ°áˆšá‰° áŠá‹ á‰°á‰¥áˆŽáŠ áˆ
ወያኔን á‰ áŠƒá‹­áˆ á‹šáˆ›áˆµá‹ˆáŒˆá‹µ፤ áˆáˆ‰áŠ•áˆ ሀይሎቜ ያሳተፈ áˆ°áˆ‹áˆ›á‹ŠáŠ“ á‹²áˆžáŠ­áˆ«áˆ² á‹šáˆ¥áˆáŒ£áŠ• áˆœáŒáŒáˆ­ á‰ áˆƒáŒˆáˆªá‰± áŠ¥áŠ•á‹²áŠ–áˆ­ áŠ¥áŠ•á‹°áˆšá‰³áŒˆáˆ አስታውቋል
ህዝባዊ ሀይሉ በዶ/ር ብርሀኑ ነጋ ኚሚመራው   á‹šáŒáŠ•á‰Šá‰µ 7 ዚፍትህ ዚነጻነትና ዚዎሞክራሲ ንቅናቄ ጋር ያለው ግንኙነት በግልጜ ዚታወቀ ነገር ዹለም:

ESAT Ethiopia Breaking News 21 12 12

Dec 20, 2012

አራት ዚኢትዮጵያ ጋዜጠኞቜ ዹ 2112 ትን ዓለማቀፍ ዹሄልማን ሜልማት አሾኛፊ ሆኑ


ኢሳት ዜና:-ዹሄልማንን ዚክብር ሜልማት ያሞነፉት ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞቜ፦ በእስር ላይ ዚሚገኙት እስክንድር ነጋ፣ዚአውራምባ ታይምሱ ውብሞት ታዬ፣ዚፍትህ አምደኛዋ ርዕዮት ዓለሙ እና በስደት ዹሚገኘው ዚአዲስ ነገሩ መስፍን ነጋሜ ናቾው።
በሂዩማን ራይትስ ዎቜ አማካይነት ዹሚሰጠውን ይህን ዚክብር ሜልማት ያገኙት አራቱም ጋዜጠኞቜ በኢትዮጵያ መንግስት ዚሜብርተኝነት ክስ ተመስርቶባ቞ዋል።
አጠቃላይ ለዘንድሮው ዹሄልማን ሜልማት ዚበቁት ኹ19 አገራት ዚተውጣጡ 41 ጋዜጠኞቜ ሲሆኑ፤ለሜልማት ዚበቁትም ሀሳብን በነጻነት ዚመግለጜ መብት አስ቞ጋሪ በሆኑባ቞ው አካባቢዎቜ ሙያ቞ውን ለመተግበር መስዋዕትነት በመክፈላቾው እንደሆነ ተመልክቷል።
በሂዩማን ራይትስ ዎቜ አማካይነት ዹሚዘጋጀው  ዹሄልማን ሜልማት ሀሳባ቞ውን  በመግለፃቾው ሳቢያ ዚፖለቲካና ዚሰብዓዊ መብት ጥቃት ለሚፈጞምባ቞ው በዓለም ዙሪያ ላሉ ጋዜጠኞቜና ጞሀፊዎቜ በዚዓመቱ ዚሚሰጥ ነው።

አቶ አንዱአለም አራጌ ላለፉት 15 ወራት በጹለማ ቀት ታስሚዋል


ኢሳት ዜና:-ዚአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊ/መንበርና ዚህዝብ ግንኙነት ሐላፊ ዹሆነው አቶ አንዱዓለም አራጌ በጹለማ ቀት ውስጥ ታስሮ፣ ቀዝቃዛ መሬት ላይ እንዲተኛ መደሹጉ በዚጀናው ላይ ኹፍተኛ ቜግር እዚፈጠሚበት መሆኑን ትናንት ለጠቅላይ ፍርድ ቀት ተናግሯል።
አቶ አንዱዓለም ዚመተንፈሻ ቜግር እንዳለባ቞ው ይሁን እንጅ በጠባብ ክፍል 6 ሆነው በመታጎራ቞ው መታመማ቞ውንና ኚባለቀታ቞ውና ጥቂት ቀተሰባ቞ው ውጪ ሌሎቜ ጓደኞቻ቞ውና ዚስራ ባልደሚቊቻ቞ው እንዳይጠይቁዋ቞ው መደሹጉን ተናግሹዋል፡፡
ዚቀድሞው ዹፓርላማ አባል አቶ አንዷለም አያሌው በበኩላ቞ው ጠበቆቻ቞ው መጥተው ሊያናግሩዋ቞ው እንዳልተፈቀደለቻው ገልጾዋል።ዳኛው አቶ ዳኘ መላኩ ስርአቱን አልጠበክም በሚል ዹመናገር እድል ነፍገውታል፡፡ ዛሬ መንግስት ያቀሚበለት ጠበቃ ቢቀርብም በጊዜ ቀጠሮ ለታህሳስ 28 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲቀርብ ተነግሮታል፡፡
ጠበቃ ደርበው ተመስገን  ይግባኙ እንኳን ሳይጠናቀቅ ኹፍተኛው ፍርድ ቀት  ዚተኚሳሟቜን ንብሚት ለመውሚስ በመጣደፍ ላይ ነው በማለት በቃል ሊያቀርቡ ቢፈልጉም ፍርድ ቀቱ በጜሑፍ ያቅርቡ ሲል አስቁሟ቞ዋል፡፡
ጠበቃ አበበ ጉታ በበኩላ቞ው ደንበኞቻቜን በአንድ ዚክስ መዝገብ ቢኚሰሱም ቃሊቲ እና ቂሊንጩ ተበትነው በመታሰራ቞ው ለጠበቆቜ ጥዚቃ እንዳልተመቻ቞ውና በበቂ መጎብኘትና ማነጋገር አለመቻላ቞ውን ለፍርድ ቀት አሳውቀዋል፡፡
ፍርድ ቀቱ መዝገቡን ለውሳኔ ለጥር 10 ቀን 2005 ዓ.ም በጊዜ ቀጠሮ ያሻገሚ ሲሆን ክርክሩ በጜሑፍ ተገልብጊ እንዲቀርብለት አዟል፡፡
በትናንት ዘገባቜን ዚተኚሳሟቜን ዚመቃወሚያ ሀሳብ ማቅሚባቜን ይታወሳል።

ዚባለስልጣናት ዚሃብት ምዝገባ መሹጃ ኚሕዝብ እንደተደበቀ ነው


ኢሳት ዜና:-በፌዎራል ዚሥነምግባርና ጞሚሙስና ኮሚሜን ሥር ዹሚገኘው ዚባለሥልጣናት ዚመንግስት ዚሥራ ኃላፊዎቜን ሃብትና
ንብሚት ለመመዝገብ ዹተቋቋመው ቢሮ እስካሁን ዹ50ሺ ባለስልጣናትን ሃብት መመዝገቡን ሰሞንን በመንግስት መገናኛ
ብዙሃን ቢገልጜም ዚአንዳ቞ውንም ዚሃብት መሹጃ ለሕዝብ ይፋ እንዳላደሚገ ምንጮቜ አስታወቁ፡፡
በሃብት ማሳወቅና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 668/2002 መሰሚት ዹተቋቋመው ይህው ቢሮ ዚመንግስት ባለስልጣናትና á‰°áˆ¿áˆšá‹Žá‰œáŠ• ሃብትና ንብሚት በመመዝገብና በማደራጀት ለሕዝብ ይፋ ማድሚግና ባለስልጣናቱም ኚገቢያ቞ው በላይ ሃብት áŠ ááˆ­á‰°á‹ ሲገኙ ለፍርድ ማቅሚብ ኚተልዕኮዎቹ መካኚል ይገኙበታል፡፡
ሆኖም ኚአንድ ኣመት በፊት ምዝገባው ሲጀምር ዚባለስልጣናቱን ንብሚትና ሃብት ዝም ብሎ ኚመመዝገብ ባለፈ ኚዚት አመጣህ ብሎ ዹመጠዹቅ ኃላፊነት(ማንዎት) እንደሌለው ማስታወቁ ዚምዝገባውን ፋይዳ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ኚማስገባቱም በላይ፣በሌብነት ዚሚጠሚጠሩ ባለስልጣናት ዚድርሻ቞ውን ኚወሰዱ በኃላ ዚሰሚቁትን ማስመዝገብ እንዲቜሉ አድርገው ሕጉን አወጡ ዹሚል ትቜትን አስኚትሎበታል፡፡
በአዋጁ መሰሚት ዚቀድሞ ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊን ጚምሮ ሚኒስትሮቜ፣አምባሳደሮቜ፣ዹፓርላማ አባላትና ሌሎቜ
ባለስልጣናት ሃብታ቞ውን ያስመዘገቡ ሲሆን ፣ ሰዎቹ ያስመዘገቡት ሃብት ምን ያህል ኚገቢያ቞ው ጋር ዚተመጣጠነ ነው?
ዚሃብት ምንጩስ ምንድነው ዹሚለውን ለሕዝብ ይፋ ማድሚግ ዚነበሚበት ቢሆንም እስካሁን ይፋ ሳያደርግ መቆዚቱ
ዚመዝጋቢውን አካል ነጻነት ጥያቄ ውስጥ ጥሏል፡፡
በአዋጁ ላይ በኮሚሜኑ እጅ ዹሚገኝ ዹማንኛውም ዚተሿሚ፣ዚተመራጭ፣ ወይም ዚመንግስት ሰራተኛ ዚሃብት መሹጃ ምዝገባ ለህዝብ ክፍት እንደሚሆን ቢደነግግም ዚቀተሰብ ሃብትን ዚሚመለኚት መሹጃ በሚስጢር እንደሚያዝ በመደንገጉ ዚምዝገባው አስፈላጊነት ገና ኚጅምሩ ጥያቄ ላይ ዚጣለ ጉዳይ ነበር፡፡ ይህም ሆኖ ዚባለስልጣኑ ዚራሱ ዚምዝገባ መሹጃ እንኳን ለህዝብ ይፋ አለመሆኑ ምዝገባው ዚይስሙላ ነው ዹሚለውን ዚሚያጠናክር መሆኑን ምንጫቜን ጠቅሷል፡፡
በአሁኑ ወቅት ጥቂት ዚማይባሉ ኹፍተኛ ዚመንግስት ባለስልጣናት በራሳ቞ውና በዘመዶቻ቞ው ስም ኹፍተኛ ሃብት ያካበቱ
ሲሆን በሚኒስትር ደሹጃ ዚተቀመጡ ሹማምንት ሳይቀሩ በመንግስት ቀት እዚኖሩ ዹግል መኖሪያ ቀታ቞ውን በኹፍተኛ
ገንዘብ በአደባባይ በማኚራዚት በመነገድ ላይ መሆናቾው ይታወቃል፡፡
ጥቂት ዚማይባሉ ባለስልጣናት ዚገቢ ምንጫ቞ው እንኳን በትክክል በማይታወቅ መንገድ ኹፍተኛ ገቢ ዚሚያገኙና ልጆቻ቞ውን በአገር ውስጥና በውጪ አገር በኹፍተኛ ወጪ ዚሚያስተምሩ መሆናቾው ዚሚታወቅ ነው፡፡
ዚፌዎራል ዚስነምግባርና ጞሚሙስና ኮሚሜን ሃብት እዚመዘገብኩ ነው ቢልም ይህንን ዓይን ያወጣ ሙስናና በስልጣን áˆ˜á‰£áˆˆáŒ ደፍሮ ለማጋለጥ ባለመቻሉ ዛሬም ጥርስ ዹሌለው አንበሳ ዹሚለውን ስሙን ማደስ

ምርጫ ቊርድ ኚኢህአዎግ በላይ ኢህአዎግ ሆኖብናል ሲሉ ተቃዋሚዎቜ ገለጹ


ኢሳት ዜና:-መጪው ዚአካባቢና ዚአዲስ አበባ ምርጫ ፍትሀዊ መሆን አለበት በማለት ፔትሺን ተፈራርመው ያስገቡት 33 ዚፖለቲካ ድርጅቶቜ ዛሬ በመኢአድ ጜህፈት ቀት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ፣ ምርጫ ቊርድ ለጥያቄያ቞ው መልስ አለመስጠቱን ገልጾው፣ በንባብ ዚሰጡዋ቞ውን ምላሜ እንደ አንድ ትልቅ መንግስታዊ ተቋም በደብዳቀ ለመግለጜ እንኳን ፈቃደኛ አልሆኑም ፣ ምርጫ ቊርድ ኚኢህአዎግ በላይ ኢህአዎግ ሆኖብናል ብለዋል።
ዚፓርቲዎቜ ጥምሚት ኮሚ቎ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንዳስታወቀው ምርጫ ቊርድ ለገዢው ፓርቲ በግልጜ ወገናዊነቱን አሳይቷል ብሎአል። ያቀሚቡትን ዚውይይት ሀሳቊቜ ቊርዱ አለመቀበሉን ያሳወቁት ፓርቲዎቜ ፣ ምርጫው ላይ ለመሳተፍ እና ላለመሳተፍ ገና አለመወሰናቾውን ገልጾዋል።
ዚምርጫ ቊርድ ዚህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ወ/ሮ ዚሺ ፈቃደ በምርጫ 1997 ዓም ኢህአዎግን ወክለው ለምርጫ ዚተወዳደሩ ሲሆን ፣ በ80 ድምጜ ብቻ በማግኘት ተሾንፈው ሲወድቁ ዚምርጫ ቊርድ ኀክስፐርት ተብለው በህዝብ ግንኙነት ባለሙያነት ተሹመው ዚፓርቲውን ስራ ያስፈጜማሉ ብለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ዚኢትዮጵያ ብሄራዊ ዚምርጫ ቊርድ ኹ33ቱ ፓርቲዎቜ ዚቀሚበለትን ኚምርጫ በፊት ባሉት ቜግሮቜ ላይ ዚእንወያይ
ጥያቄ “በተጚባጭ መሹጃ ዹተደገፈ አይደለም፣ጥያቄዎቹ ኹ2002 ምርጫ ጋር ዚተያያዙ ናቾው” በሚል ውድቅ
ያደሚገበት አካሄድ ዚቊርዱን ገለልተኛ አለመሆን በተጚባጭ ያሳዚ መሆኑን ኹ33ቱ ፓርቲዎቜ አስተባባሪዎቜ አንዱ
ገለጾዋል፡፡
ይህ አስተያዚት በ33ቱ ፓርቲዎቜ ዚጋራ አቋም ዚተያዘበት ባለመሆኑ ዚሚሰጡት ዹግል ሃሳባ቞ውን መሆኑን ዚተናገሩ
ኹፍተኛ አመራሩ ምርጫ ቊርድ ጥቅምት 15 ቀን 2005 ዓ.ም በአዳማ በጠራው መድሚክ ላይ አንድ አቋም ዚያዙት
33 ፓርቲዎቜ ያቀሚቡትን ዚእንወያይ ጥያቄ ሆን ብሎ ምላሜ ሳይሰጥ ሲያንኚባልል ቆይቶ ኚወራት በኃላ
ሳያነጋግራ቞ው በራሱ ጊዜ በመንግስት መገናኛ ብዙሃን መግለጫ በመስጠት ውድቅ ማድሚጉ ኹዚህ ቀደም በተደጋጋሚ
ዚሚነሳበትን ዚገለልተኝነት ጥያቄ ያሚጋገጠ ነው ሲሉ ኮንነውታል፡፡
ቊርዱ ትክክለኛ ቢሆን ኖሮ ለገዥው ፓርቲ በመወገን ዚፓርቲዎቹን ዚእንወያይ ጥያቄ ውድቅ ወደማድሚግ ኚመሄዱ በፊት
ቢያንስ ባሉት ቜግሮቜ ላይ በመወያዚት፣ኀሳቡንም ለፓርቲዎቹ በማስሚዳት ወደ መግለጫው ቢሄድ ኖሮ ቢያንስ ውጥሚቱንና
አለመተማመኑን በመጠኑ መቅሹፍ በቻለ ነበር ብለዋል፡፡
አያይዘውም ቊርዱ ፓርቲዎቹ ያቀሚቡት ማለትም ዚምርጫ ቊርዱ ኹላይ እስኚታቜ ያሉ መዋቅሮቜ ገለልተኛ ያለመሆን
ጉዳይ፣በነጻነት ዚመንቀሳቀስ፣ደጋፊዎቻ቞ውን ሰብስበው ማነጋገር ያለመቻላ቞ው ጉዳይ፣በዹክልሉ በአባሎቻ቞ውና
ደጋፊዎቻ቞ው ላይ ሕገወጥ እስሮቜ፣ማሳደድና ኚስራ ማሰናበት ዚመኖሩ ጉዳይ፣ዚመንግስት መገናኛ ብዙሃን ፍትሐዊ
አጠቃቀም ጉዳይ፣ዚአንድነት ጋዜጣ በሕገወጥ መንገድ ዕትሙ እንዲቆም መደሹጉና ዚመሳሰሉት ናቾው፡፡
“ቊርዱ ፓርቲዎቹን ጠርቶ ላቀሚባቜሁት አቀቱታ ምን መሹጃ አላቜሁ ብሎ ፓርቲዎቹን ሳይጠይቅ ዹሰጠው ምላሜ
ለፓርቲዎቹ ያለውን ግምት ዚቱን ያህል ዹዘቀጠ መሆኑን ዚሚያሳይና እነዚህ ቜግሮቜ እንደሌሉ ለማሚጋገጥ ያደሚገው
ሙኚራ በመሆኑ ይህ አካል ነጻና ገለልተኛ ምርጫ ያካሂዳል ብሎ ማሰብ እንዎት ይቻላል” ሲሉ ባለስልጣኑ  áŒ á‹­á‰€á‹‹áˆ፡፡
ኹአሁን በኃላ ምን ታደርጋላቜሁ ተብሎ ለቀሹበላቾው ጥያቄ ይህ ውሳኔ በጋራ ዹሚተላለፍ መሆኑን አስታውሰው ነገር ግን
ኹ33ቱ ፓርቲዎቜ አብዛኛዎቹ ሕዝባዊ ተቃውሞ በመስቀል አደባባይ ለመጥራት ፍላጎት እንዳላ቞ው አውቃለሁ ብለዋል፡፡
ምርጫ ቊርድ ዘንድሮ ዚሚያካሂደውን ዚአካባቢና ዚአዲስአበባ አስተዳደር ጊዜያዊ ዹጊዜ ሰሌዳ ላይ ለመምኹር በአዳማ
ኀግዚኪዩቲቭ ሆቮል ጥቅምት 15 ቀን 2005 ዓ.ም በጠራው ስብሰባ ላይ ኹተገኙ 65 ፓርቲዎቜ መካኚል 33 ያህሉ
ኚምርጫ በፊት ውይይት ይቅደም በሚል ዚጋራ አቋም በመያዝ ለቊርዱ ማሳወቃ቞ው ይታወሳል፡፡

ESAT Daily News Amsterdam 20 December 2012 Ethiopia


Ethiopian textile manufacturers preying on export markets.

In the historic town of Adwa in northern Ethiopia (where Ethiopia defeated the Italian invaders thoroughly in 1896) is Almeda Textile (ALTEX), Ethiopia's biggest textile factory.
Textile mill which was completed 10 years ago, employs 3,200 workers of the city's 60,000 residents and is by far the largest employer on the site. The factory is in the midst of a major expansion process where both capacity and workforce planning doubled. Almeda is a subsidiary of the Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFFORT).Ambassador Jens-Petter Kjemprud visited the factory last Saturday.
Almeda currently exports 30% of its production mainly to Italy, Germany, Switzerland and Sudan, but want to increase the export share of production. Almeda thus has just signed an agreement with Starbucks on the production of work for employees in the coffee company's restaurants in the U.S.. Export products are currently mainly work clothes and uniforms, including to health care in Italy in particular (the largest single contract). Also sengeetÞy and curtain fabric is a major export (Almeda previously exported linen to IKEA). The company also supply the uniforms for military and police.Almeda want to promote in Norway on those areas where you have good experiences, or partnership with companies in Norway define new areas and asked the embassy for support to make contacts in Norway. All production is based on Ethiopian short-fiber cotton.
 
Almeda is ISO 9001-2000 certified and produces 16 million meters fabric last year. The company has a prominent role in the ongoing industrialization in Ethiopia and has received numerous awards for production and exports, and price for the best value start a business in Ethiopia. Workers are organized in Tekstiarbeiderforbundet have collective bargaining rights and lÞnnsivÃ¥et well above the Ethiopian minimum wage. Almeda went last year through the Starbucks strict working standards before eskportkontrakten was signed. Salaries are still low compared with the rising wage costs in China and India, and Almeda tries to exploit this competitive advantage, but is under pressure from a variety of Turkish startups in Ethiopia.
For further information, see: almeda@ethionet.et

Etiopiske tekstilprodusenter jakter på eksportmarkeder.



I den historiske byen Adwa i nord-Etiopia (der Etiopia slo den italienske invasjonshÊren grundig i 1896) ligger Almeda Textile (ALTEX), Etiopias stÞrste tekstilfabrikk.
Tekstilfabrikken som sto ferdig for 10 Ã¥r siden, sysselsetter 3200 arbeidere av byens 60.000 innbyggere og er den suverent stÞrste arbeidsplassen pÃ¥ stedet. Fabrikken er midt inne i en stor utvidelsesprosess der bÃ¥de kapasitet og arbeidsstokk planlegges fordoblet. Almeda er et datterselskap til Endowment Fund for Rehabilitation of Tigray (EFFORT). AmbassadÞr Jens-Petter Kjemprud besÞkte fabrikken sist lÞrdag.
Almeda eksporterer i dag 30 % av sin produksjon i hovedsak til Italia, Tyskland, Sveits og Sudan, men Þnsker å Þke eksportandelen av produksjonen. Almeda har således nettopp inngått en avtale med Starbucks om produksjon av arbeidsklÊr til de ansatte i kaffeselskapets restauranter i USA. Eksportproduktene er i dag hovedsaklig arbeidsklÊr og arbeidsuniformer, herunder til helsevesenet i Italia spesielt (stÞrste enkeltavtale). Også sengeetÞy og gardinstoff er en stor eksportvare (Almeda eksporterte tidligere sengetÞy til IKEA). Bedriften levererer dessuten uniformer til militÊre og politi. Almeda Þnsker å markedsfÞre seg i Norge på disse områder der man har gode erfaringer, eller ved samarbeid med selskaper i Norge definere nye områder og anmodet ambassaden om stÞtte til å knytte kontakter i Norge. All produksjon er basert på etiopisk kortfibret bomull.
 
Almeda er ISO 9001-2000-sertifisert og produserer i dag 16 millioner meter tekstilvare Ã¥rlig. Bedriften har en fremtredende rolle i den pÃ¥gÃ¥ende industrialisering i Etiopia og har mottatt en rekke priser for produksjon og eksport samt pris for beste valuta inkomst bedrift i Etiopia. Arbeidstakerne er organisert i Tekstiarbeiderforbundet, har kollektiv forhandlingsrett og lÞnnsivÃ¥et ligger godt over etiopisk minimumslÞnn. Almeda gikk i fjor gjennom Starbucks strenge krav til arbeidsmiljÞstandarder fÞr eskportkontrakten ble undertegnet. LÞnnsnivÃ¥et er allikevel lavt sammenliknet med de Þkende lÞnnkostnadene i Kina og India, og Almeda forsÞker Ã¥ utnytte denne konkurransefordelen, men er under press fra en rekke tyrkiske nyetableringer i Etiopia.
For ytterligere opplysninger, se: almeda@ethionet.et

ዚኢትዮ-ኀርትራን ቜግር ለመፍታት ዚሚሚዱ ነጥቊቜ





ጠቅላይሚኒስትር áˆƒá‹­áˆˆáˆ›áˆ­á‹«áˆ á‹°áˆ³áˆˆáŠ ፣ áŠ áˆµáˆ˜áˆ« ሄደዉ ኚአቶ áŠ¢áˆ³á‹«áˆµ áŠ áˆá‹ˆáˆ­á‰‚ ጋር áˆˆáˆ˜áŠáŒ‹áŒˆáˆ­ á‹áŒáŒ áŠ¥áŠ•á‹°áˆ†áŠ‘ áˆˆáŠ áˆáŒƒá‹šáˆ« áŒˆáˆáŒžá‹‹áˆ።«á‰ áŠ áˆáŒ€áˆ­áˆ±

ስምምነት ተቋቁሞ ዹነበሹው ዚድንበር ኮሚሜን ዹወሰነዉን ዉሳኔ፣ ኢትዮጵያ አክብራ፣ ዚባድመን ኹተማ ጚምሮ
ዚኀርትራ ናቾው ኚተባሉት መሬቶቜ ሁሉ ለቃ እስካልወጣቜ ድሚስ፣ አልነጋገርም» ሲል ዹነበሹዉ ዚኀርትራ መንግስት፣
ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም አስተያዚት ዹሰጠው ኊፌሳላዊ ምላሜ ባይኖርም፣ ፕሬዘዳንት ኢሳያስ ኹዚህ በፊት
ዚነበራ቞ውን አቋም በማለዘብ ኚኢትዮጵያ ጋር ያለዉን ቜግር ለመፍታት ፍቃደኛ እንደሆኑም ዚሚያሳዩ ዘገባዎቜን
እያነበብን ነዉ።
ዚኢትዮጵያ እና ዚኀርትራ ሕዝቊቜ አብሚዉ ዚኖሩ፣ ዚተዋለዱ፣ በባህል በቋንቋ በሃይማኖት ዚተዛመዱ ወንድማማቜ
ሕዝቊቜ ናቾው። ስር ዹሰደደ ዚታሪክ ዝምድና ያላ቞ው፣ አንድ ወቅትም ዚአንድ አገር ሕዝብ ዚነበሩ እንደመሆና቞ው፣
በመካኚላ቞ው ያላ቞ዉን ቜግሮቜ እስኚአሁን መፍታት አለመቻላ቞ው ዚሚያሳዝን ነዉ። በእዉኑ ያሉን ልዩነቶቜ ይሄን
ያህል ዚኚሚሩ ናቾዉን ? አንዱ አሾናፊ ሌላዉ ተሾናፊ ሳይሆን፣ ሁሉም አሾናፊ ዚሚሆነበትን መፍትሄ ማግኘት
ያቅተናልን ? እስኚመቌስ ኀርትራንና ኢትዮጵያን ዚሚያካልለዉ ድንበር፣ ዚልማትና ዚንግድ እንቅስቃሎዎቜ ዚሚታዩበት
አካባቢ መሆኑ ቀርቶ፣ ዹፈንጂና ዚታንክ መናኞሪያ ይሆናል ?
ወደ ኋላ መለስ ብለን ነገሮቜን መመዝን ኹጀመርን ብዙ ልንባባል እንቜላለን። በሁሉም ወገኖቜ ኹዚህ በፊት
ዹተፈጾሙ ብዙ ስህተቶቜ አሉ። በአሥር ሺሆቜ ዚሚቆጠሩ ወንድሞቻቜን ኚሁለቱም ወገኖቻቜን ሹግፈዋል። ያ አካባቢ
በደም ርሷል። አሁን ግን ያለፈዉን ትተን ወደፊት ማዚት ይኖርብናል። ያለፈውን እያነሳን ዚምንወጋገዝበትና
ዚምንካሰስበት ጊዜ አይመስለኝም። ሌሎቜ አገሮቜ ዚትናዚት ደርሰዋል። ለልጆቻቜን እና ልጅ ልጆቻቜን ስንል ፣
ተኚባብሚን፣ ተስማምተን ፣ ይቅር ተባብለንና ተቻቜለን ሁላቜንም በጋራ ዚምናድገበትን ሁኔታ መፍጠር ዚግድ ነዉ።
ለዚህም ነዉ፣ ዹጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማሪያም ለዉይይት ዝግጁነትና ፣ አቶ ኢሳያስ ይዘዋል ተብሎ ዹተዘገበዉን
ዹአቋም መለሳለስ፣ በሰላም ወዳድ ወገን ሁሉ በአዎንታዊነት ሊታይና ሊበሚታታ ዚሚገባ ነዉ ዹምለዉ።

በኀርትራና እና በኢትዮጵያ መካኚል ያለዉን ቜግር ስናይ ዚምናነሳ቞ው በርካታ ጥያቄዎቜ ይኖራሉ። «á‰£á‹µáˆ˜ ለማን
ልትሰጥ ነዉ ? ዚአሰብስ ጉዳይ ? ኚኀርትራ ጋር ነጻ ንግድ ኹተጀመሹ ዚብርና ዹናቅፋ ልዉዉጥ እንዎት ይሆናል ?
ኚኀርትራ ተገንጥለው ኚኢትዮጵያ መቀላቀል ዚሚፈልጉት ዹቀይ ባህር አፋሮቜስ ጉዳይ ? …» ዚመሳሰሉ ጥያቄዎቜን
እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል።
አንድ ነገር ኚወዲሁ በግልጜ ላስቀምጥ። በኢትዮጵያና በኀርትራ መካኚል ያለዉን ቜግር ዚአልጀርሱ ስምምነት፣ ይኾው
ለአሥር አመታት አልፈታዉም። በመሆኑም በዚህ ስምምነት ብዙ ተስፋ ማድሚግ ያለብን አይመስለኝም። እንደዉም
ይሄን ስምምነት እንደሌለ እንቁጠሚዉ።
ኚአልጀርሱ ስምምምነት ዹተለዹ ፣ ቜግሮቜን ለመፍታት ዚሚቜሉ ሃሳቊቜ ይኖራሉ። በዚህ ሚገድ እኔም ይጠቅማሉ
ዹምላቾውን አንዳንድ ዚተጚበጡ ዚእርቅ ሃሳቊቜን በትህትና ለማቅሚብ እሞክራለሁ። እነዚህን ሃሳቊቜ ሳቀርብ
ኢትዮጵያዊ በመሆኔ ለኢትዮጵያ ብቻ አስቀ ሳይሆን፣ አስመራ ዚተማርኩ፣ ለኀርትራ ሕዝብ ፍቅር ያለኝ ፣ በመንፈስም
“ኀርትራዊ ነኝ» ብዬ ዹማምን እንደመሆኔ ፣ ለኀርትራም አስቀ ነዉ።
ኹሁሉም በላይ በዋናነት ዹምደግፈዉና ዹምመኘው ኀርትራ ኚኢትዮጵያ ጋር በፌዎሬሜን እንድትቀላቀል ነዉ። ዚአፍሪካ
ሕብሚት ለማቋቋም እዚተሞኚሚ አይደለም እንዎ ? በአዉሮፓ አንድ ለመሆነ እዚሞኚሩ አይደለም እንዎ ? በመኚባበርና
በፍቅር ላይ ዹተመሰሹተ አንድነት ቢኖር ዹበለጠ ያሳድገናል እንጂ አይጎዳንም። ዚባድመ፣ ዚአሰብ ፣ እንዲሁም
በመካኚላቜን ያሉ ሌሎቜ ቜግሮቜ በሙሉ በአንድ ላይ ተጠቃለው መፍትሄ ያገኙ ነበር። ባድመ ዚኢትዮጵያም
ዚኀርትራም ትሆናለቜ። አሰብም ዚኢትዮጵያም ዚኀርትራ ትሆናለቜ።
ዚዉህደቱ ጥያቄ በሬፌሚንደም እንዲወሰን ማድሚግ ይቻላል። ኹዚህ በፊት ኀርትራዉያን ብቻ ነበሩ ድምጜ ዚሰጡት።
አሁን ግን ዚኀርትራን መቀላቀል ሊቃወሙ ዚሚቜሉ ብዙ ኢትዮጵያዉያን ሊኖሩ ስለሚቜሉ፣ ዚኢትዮጵያ ሕዝብም
ዉህደቱን ማጜደቅ ይኖሚበታል። እርግጠኛ ነኝ አብሮ ዚመስራትን ጥቅም እና ዚታሪክ ትስስራቜን በጥልቀት
መመልኚት እንዲቜሉ ኹተደሹገ፣ ያለፈዉን ዹመተዉን ይቅር ዚመባባል መንፈስ ኹሰፈነ፣ ዚኢትዮጵያ ሕዝብም
ሆነ ዚኀርትራ ወገናቜን ዳግም ለመተቃቀፍ አይኑን ያሻል ብዬ አላስብም። ይሄ ያልተወሳሰበ ዹሰላምና ዚእርቅ
መንገድን፣ እቅድ «áˆ€» ብዬዋለሁ። ፈሚንጆቜ እንደሚሉት ፕላን ኀ (PLAN A)!
ተስፋ ካደሚግነዉና ኚገመትነዉ ዉጭ፣ ወይ ዚኀርትራ ሕዝብ፣ አሊያም ዚኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ወይም ሁለቱም ፈቃደኛ
ሳይሆኑ ቀርቶ፣ ዉህደቱን መፈጾም ካልተቻለ፣ ኀርትራ እንደ አገር እዚቀጠለቜ ፣ ኚጅቡቲ፣ ኚኬንያ በበለጠ ሁኔታ
መልካም ጎሮቀት አገር ሆና እንድትኖር ማድሚግ ዚሚቻልበትን ሁኔታ መፍጠር ያስፈልጋል። ለዚህም ሰጥቶ
በመቀበል መርህ፣ ዹሁሉንም ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ ያሉትን ጥያቄዎቜ መመለስ ይኖርባ቞ዋል። ይሄ ደግሞ
እቅድ «áˆˆ» ወይንም ፕላን ቢ ( PLAN B) ነዉ።
በአሁኑ ጊዜ አሰብና ዹደንኹል በሹሃ፣ ለኀርትራ ይሄን ያህል ጥቅም ዚሚሰጥ መሬት ነዉ ብዬ አላስብም። ኢትዮጵያ
አሰብን መጠቀም ካቆመቜበት ጊዜ ጀመሮ ወደቡ ስራ ላይ ዋለ ማለት ያስ቞ግራል። መቌም ባጜእ (ምጜዋ) እያለቜ
ለአስመራና አብዛኛዉ ዚኀርትራ ግዛት እቃ በአሰብ በኩል ይገባል ማለት ትንሜ ይኚብዳል። አሰብን ለኢትዮጵያ
አኚራይታ ገንዘብ ካላገኘቜበት በስተቀር አሰብ ለኀርትራ አትጠቅማትም።
በቅርበትም ሆነ በጂዮግራፊ አቀማመጥ ካዚን ግን፣ አሰብ ለኢትዮጵያ በጣም ትጠቅማለቜ። ኢትዮጵያ ለጅቢቱ
መንግስት ብቻ በአመት ኹ700 ሚሊዮን ብር ታወጣለቜ። ዚኢኮኖሚ እድገት ዹበለጠ ባደገ ቁጥር ለወደብ
ዹሚኹፈለውም ዋጋ እዚጚመሚ ነዉ ዹሚሄደው። በኢትዮጵያ ወደብ መኖሩ ትልቅ ብሄራዊና አገብጋቢ ጥያቄ ነዉ።
ለኀርትራ ኹሁሉም በላይ ዹሚጠቅመዉና ዹሚበጀው፣ አሰብን ይዞ ኚመቀመጥ፣ ዘለቄታ ያለዉ ሰላም ኚኢትዮጵያ ጋር
መመስሚት ነዉ። ብዙም ዚማይጠቅማትን መሬት ለኢትዮጵያ ሰጥታ፣ ሌሎቜ ዚሚጠቅሟትን ነገሮቜ መቀበል
ዚምትቜልበት ሁኔታ ማመቻ቞ት ዹበለጠ ሊሚዳት ይቜላል። አስተዋይነትም ነዉ። ኢትዮጵያም በበኩሏ አሰብን
ስትቀበል ፣ ለኀርትራን ዚምትሰጠው ሊኖራት ይገባል።
«áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« ዚባህር በር ሊኖራት ይገባል» ዹሚሉ ኃይላት በብዛት እንደመኖራ቞ው፣ ይሄም ጥያቄ ደግሞ ትልቅ አገርዊ
ጥያቄ እንደመሆኑ፣ ኢትዮጵያ ባህር አልባ ሆና አስተማማኝ ሰላም ኚኀርትራ ጋር ማድሚጉ አስ቞ጋሪ ነዉ ዹሚሆነዉ።
ኀርትራ ሁል ጊዜ እንደ ፈራቜና ለጊርነት እንደተዘጋጀቜ ነዉ ዚምትኖሚዉ።
እንግዲህ አሰብን ለኢትዮጵያ መስጠቱ በርግጠኝነት፣ በኀርትራ ሰላምን ለዘለቄታዉ ያሚጋግጣል። ኀርትራዉያን
ኚጊርነት ስጋት ተላቀዉ፣ በሰላም ይኖራሉ። ሰላም ኚማግኘት ዹበለጠ ደግሞ በሚኚት ዚትም አይገኝም። አንድ በሉ።
በአሰብ አካባቢ ዚሚኖሩ አፋሮቜ ኚአስመራ ይልቅ ልባ቞ዉና ታማኝነታ቞ው ለአሳይታና አዲስ አበባ ነዉ። በመሆኑም

ኀርትራ ኚኢትዮጵያ ዚመለዚት መብቷ እንደተሚጋገጠው፣ አፋሮቜም ኚኀርትራ ዚመለዚት መብታ቞ዉ እንዲሚጋገጥ
ይጠይቃሉ። ያም መሰሚታዊ መብታ቞ው ካልተኚበሚ ብሚት ዚማያነሱበት ምክንያት ዹለም። እነርሱን ለመኹላኹልና
በአካባቢዉ ሰላምና መሚጋጋት ለማስፈን አስመራ ብዙ ዉጭ ማዉጣት ትገደዳለቜ። ይህ ደግሞ አነሰም በዛም
ኀርትራን ዚሚጎዳ ነዉ። ሁለት በሉ።
ኀርትራዉያን በታታሪነታ቞ዉና በጠንካራነታ቞ዉ ይታወቃሉ። ኀርትራ ዚኢትዮጵያ አካል በነበሚቜበት ጊዜ በመሃል
አገር ብዙ ዚተሳካላ቞ው፣ ትልቅ ደሹጃ ዚደሚሱ ወገኖቜ ናቾዉ። በልጅነቮ ትዝ ይለኛል አንድ በጣም ዹምንወደው
ብስኩት ነበር። ዹደቀ መሃሪ ብስኩት ! ደቀ መሃሪ ተመርቶ በመላው ኢትዮጵያ ይሞጥ ዹነበሹ ። ነጻ ንግድ፣ ኢትዮጵያ
ዉስጥ ያለገደብ መስራት …. ዚመሳሰሉ ሁኔታዎቜ ቢፈጠሩ ነዉ ዹበለጠ ኀርትራ በኢኮኖሚ ዚምትጠቀመዉ። አስመራ
ዚሚመሚቱ ምርቶቜ በቀላሉ ገዢ ያገኛሉ። ለኀርትራ ባለ ሃብቶቜ 90 ሚሊዮን ዹሚሆን ሕዝብ ደንበኛ ይሆናቾዋል።
ዚኀሌትሪክ ኃይል በቀላል ዋጋ ወደ አስመራ እንዲገባ ማድሚግ ይቻላል። ሶስት በሉ።
በርግጥ በሹጋ መንፈስ፣ ኹሁሉም አቅጣጫ ሁኔታዉን ቢያስቡት፣ ኀርትራዉያን ኹማንም በላይ ዹሚበጃቾው
ኚኢትዮጵያ ጋር መተሳሰር ነዉ።
እንግዲህ ያለፈዉን ሳይሆን ዚወደፊቱን በማዚት፣ ዚሚኚተሉትን ተጚባጭ 7 ዚእርቅ ነጥቊቜ (Road Map of
Ethio-Eritrean Peace) አቀርባለሁ፡
1. ኚጅቡቲ ድንበር እስኚ መርሳ/ፋጥማ ያለዉ፣ አሰብን ዹሚጹምሹዉ፣ ዚኀርትራ ግዛት ለኢትዮጵያ ይሰጥ።
2. በልዋጩ ዚባድመ ኹተማን ጚምሮ ያወዛግቡ ዹሰሜን ኢትዮጵያ መሬቶቜን ወደ ኀርትራ ይጠቃለሉ።
3. ዚኢትዮጵያ ሕገ መንግስት ተሻሜሎ፣ ኀርትራዉያን በኀርትራዊ ዜግነታ቞ው ላይ ደርበዉ፣ ሙሉ
ዚኢትዮጵያዊነት ዜግነት ይሰጣ቞ው። ይሄም በኢትዮጵያ ዉስጥ ያለ አንዳንቜ ገደብ እንዲነግዱ፣ እንዲማሩ፣
እንዲሰሩ፣ እንዲኖሩ ያደርጋል። ኢትዮጵያዉያንም እንደዚሁ በአስመራ ዹመኖር መብታ቞ው ይሚጋገጥ።
4. ኀርትራ ዚኢትዮጵያን ብር እንድትጠቀም ይደሹግ። አሊያም ዚገንዝብ ልዉዉጥን በተመለኹተ ዚጋራ ፖሊሲ
በመንደፍ ሊነሱ ዚሚቜሉ ቜግሮቜ ኚወዲሁ ምላሜ ይሰጣ቞ዉ።
5. አንዱ አገር ሲጠቃ ሌላዉ እንደተጠቃ ዚሚቆጥር ዚዉትድርና ስምምነት ይደሹግ።
6. በሚደሹጉ ስምምነቶቜ፣ አስመራና አዲስ አባባ ያሉ ዚመንግስት ባለስልጣናት በተቻለ አቅም
ዚተቃዋሚዎቻ቞ዉን ድጋፍ ለማግኘት ይሞክሩ። ይህ ዹሰላም መንገድ፣ ዹሁሉም ማህበሚሰብ፣ ዚፖለቲካ
ድርጅቶቜ፣ ሲቪክ ማህበራትን ያሳተፈ ሊሆን ይገባዋል እንጂ አንድ ፓርቲ ብቻ ዚሚወስነው ሊሆን አይገባም።
7. ፕላን ሃ ካልሰራና ዉህደት ማድሚግ አሁን ካልተቻለ፣ ኚጥቂት አመታት በኋላ አይቻልም ማለት አይደልም።
ቁስሎቜ ሲድኑ፣ በሁለቱም ወገኖቜ ዹሚኖሹዉ መቀራሚብ በጹመሹ ቁጥር፣ ዚዉህደት ጥያቄዉ ዹበለጠ
ተቀባይነት ወደፊት ሊያገኝ ይቜላል። በመሆኑ ዚዉህደቱ ጉዳይ ኚአሥር አመታት በኋላ እንደገና እንዲታይ
ይደሹግ።
ዉድ ኢትዮጵያዊያን እና ኀርትራዉያን ወገኖቌ፡
ሰላም ይበጀናል። መሚዳዳቱና መደጋገፉ ይሻለናል። ይህ አይነቱን ስምምነት ማድሚግ ካልቻልን አማራጩ ዹኹፋ ነዉ
ዚሚሆንብን። ጊርነት ባልታሰበ ሰዓትና ጊዜ ይቀሰቀሳል። ዛሬ ያሉ መንግስታት ቢስማሙም፣ ነገ ዚሚመጡ
መንግስታት መካኚል ጠብ ሊፈጠር ይቜላል። ካለፈው መማር አለብን። ኚባድመ ጊርነት በፊት በነበሩት 8 አመታት
አስመራና አዲስ አበባ መልካም ግንኙነት ነበራ቞ው። ሳይታሰብ ነዉ ድንገት ወዳጅ ዚነበሩ መንግስታት፣ ጩር
ዚተማዘዙት። አስተማማኝ ሰላም ዹሚገኘዉ ፣ ያልተሞፋፈነ፣ በቅንነት ላይ ዹተመሰሹተ፣ መሰሚታዊ ጥያቄዎቜን
ዚሚመለስ ስምምነት ሲደሚግ እና ሁሉም ሰጥቶ በመቀበል መርህ አሾናፊ ሆኖ ሲወጣ ብቻ ነዉ። እንግዲህ በሁሉቱም
ወገን ላሉ መሪዎቜ እግዚአብሄር ልቩና ይስጣ቞ው እላለሁ።

Breaking News (ሰበር ዜና): ኢትዮጵያ ያለው ሲኖዶስ ፓትርያርክ ለመምሚጥ አስመራጭ ጳጳትን መሹጠ


ኹማህበሹ ቅዱሳንም አስመራጭ ተወክሏል
ሐበሻ) በዳላስ ዹተደሹገው ዚሁለቱ ሲኖዶሶቜ ድርድር ዹተጠናቀቀው በቀጣይ ጥር 16 ቀን 2005 ዓ.ም ቀጣዩ
እርቅ እስኚሚደሚግ ድሚስ እርቀ ሰላሙን ዚሚያሰናክሉ ነገሮቜን ኚማድሚግ እንዲቆጠቡ ዹሚል ድርድር ደርሰው ነበር –
ኚሁለቱም ወገኖቜ ያሉት አባቶቜ። ሆኖም ግን አሁን በሰበር ዜና ለዘ-ሐበሻ በደሹሰው ዜና ኢትዮጵያ ያለው ሲኖዶስ
ስምምነቱን በመጣስ ፓትርያርክ ለመምሚጥ አስመራጭ ጳጳሳትን መምሚጡን ታማኝ ምንጮቻቜን ገለጹ።
ቀተክህነት አካባቢ ያሉት ዹዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮቻቜን ገለጻ 4 ጳጳሳትና ሌሎቜ አራት ሰዎቜ ለፓትርያርክ
አስመራጭ ኮሚ቎ነት ተመርጠዋል።
ለፓትርያርክ አስመራጭነት ኮሚ቎ ዚተመሚጡት ጳጳሳት፦
1ኛ. አቡነ ጢሞጢዎስ
2ኛ. አቡነ ቄርሎስ
3ኛ. አቡነ እስጢፋኖስ
4ኛ. አቡነ ቀሌምንጊስ ሲሆኑ
ሌሎቹ 4ቱ ደግሞ፦
1ኛ. ሊቀትጉሃን ሃይለጊዮርጊስ ዳኜ
2ኛ. ሊቀማህምራን ፋንታሁን ሙጬ
3ኛ. አቶ ባያብል ሙላቮ ኹማህበሹ ቅዱሳን
4ኛ. አቶ ዓለማዹሁ ተስፋዬ ኚኢዚሩሳሌም መታሰቢያ ድርጅት ናቾው።
ዹዘ-ሐበሻ ታማኝ ዚቀተክህነት ምንጮቜ ጹምሹውም ስምንት ጳጳስት ቀተመንግስት ድሚስ እዚተጠሩ እንደሚሄዱና
ዚፓትርያርክ ምርጫ በአስ቞ኳይ እንዲፈጞም እንዲጎተጉቱና እንዲያስፈጜሙ ዹተደሹገ ሲሆን ኹነዚህ ስምንቱ ጳጳስት
ውስጥ፦
1ኛ.አቡነ ጎርጎዮስ
2ኛ. አቡነ ሳሙኀል
3ኛ. አቡነ ቄሌንጊስ
4ኛ. አቡነ ሳዊሮስ እንደሚገኙበት ታውቋል።
ተጚማሪ መሚጃዎቜን ይዘን እንመጣለን።
በርኚት ያሉ ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተኚታዮቜ ሁለቱ ሲኖዶሶቜ ወደ አንድነት እንዲመጡ ሲጞልዩ ዹኹሹመ
ቢሆንም ኢትዮጵያ ያለው ሲኖዶስ በመንግስት ጫና መንግስት ዹሚፈልገውን ፓትርያርክ ለመምሚጥ መዘጋጀታ቞ው
ዚአንድነት ተስፋውን እንዳጚለመባ቞ው ኚሚሰጡት አስተያዚት መሚዳት ይቻላል።
ዘ-ሐበሻን ለፈጣን መሹጃ ሁሌም ያንብቡ።

Dec 19, 2012

ዚአቶ በሚኚት ስምዖን ሠራተኞቜ ብሶታ቞ውን በደብዳቀ ጻፉ

ይድሚስ ለክቡር አቶ በሚኚት ስምዖን


ዚኢ.ፌ.ዲ.ሪ ዚመንግሥት ኮሙዩኒኬሜን
ጉዳዮቜ ጜ/ቀት ኃላፊ (ሚኒስትር)



ኚእንጀራ ልጆቜዎ



ክቡር ሚኒስትር አቶ በሚኚት ሆይ
ልብ ብለው ይስሙን፡፡ እባክዎትን አንድ ጊዜ
ጆሮዎትን ያውሱን፡፡ ምነው ልብዎት በእኛ
ጚኚነሳ? ይህ ዚእንጀራ ልጅን ዹማግለል ሥራ
ውጀቱ ጥሩ ዹሚሆን ይመስልዎታልን? እንዎት
ነው ነገሩ?
ክቡር አቶ በሚኚት፡- እኛ ለእርስዎ ልዩ ክብርና አድናቆት አለን፡፡ ዚኮሙዩኒኬሜን ድ/ቀትን መምራት ኚጀመሩበት
ጊዜ ጀምሮ በዋናነት በእርስዎ አመንጭነትና አስፈፃሚነት ዚተወሰዱ ዚተለያዩ እርምጃዎቜ በአገራቜን ለዘመናት
ዹነበሹውን ዚኮሙዩኒኬሜንና ሕዝብ ግንኙነት ሥራ ለማሻሻል ጥሩና አበሚታቜ ጅምር ያሳዩ ናቾው፡፡ ይህን
እናምናለን፡፡ በእርስዎ አንቀሳቃሜነት እዚመጡ ያሉ መሠሚታዊ ለውጊቜን ሁላቜን በዚመስሪያ ቀታቜን እያዚንና
እዚተደሰትን ነው፡፡ ድካምዎት ሁሉ ለአገራቜን ሁለንተናዊ ለውጥ ዚኮሙዩኒኬሜን ሥራ ታላቅ አስተዋጜኊ
እንዳለው በመገንዘብና ለአገራቜን መልካም ገጜታ መገንባት ኚልብ በማሰብ ነው ብለንም እናምናለን፡፡
እርስዎ በጜ/ቀትዎት እያመጡት ካለው ለውጥ ውስጥ በዋናነት ዹሚጠቀሰውም በዹጊዜው ዹሚሰጠው ዹአቅም
ግንባታ ሥልጠና ነው፡፡ ልዩ ዚኮሙዩኒኬሜን ሥልጠናው፡፡ በተለይም በደንብ በተጠናና ተኚታታይነት ባለው
መልኩ ቢሆን ኖሮ፡፡ ዚኮሙዩኒኬሜን ሥልጠናው ዚተሰጠበት መንገድ ማለትም ዚሠልጣኞቜ አመላመል ቜግር
እንደተጠበቀ ሆኖ፡፡ ለኮሙዩኒኬተርነት ዹማይበቁ ብዙ ኮሙዩኒኬተሮቜ ሥልጠናውን ቢወስዱም ኮሙዩኒኬተር
መሆን እንዳልቻሉ እርስዎም እያዩት ይመስለናል፡፡ ዹዚህ ቜግር ዋናው መነሻ ደግሞ ዚኮሙዩኒኬተሮቜ አመላመል
ነበር፡፡ ዚተፈጥሮ ሳይንስ ምሩቃን፣ ዚሒሳብና ፊዚክስ መምህራን ኮሙዩኒኬተር ሁኑ ሲባሉ ቜግር ባይገጥም ነበር
ዹሚገርመው፡፡
ዹሆነው ሆኖ ግን እስኚመሠሚታዊ ቜግሮቹም ቢሆን ኮሙዩኒኬተሮቜን በአቅም ለመገንባት ዚተሰጡ ሥልጠናዎቜ
አበሚታቜ ለውጥ እያሳዩ ነው ማለት ይቻላል፡፡ በዚፌዎራል መስሪያ ቀቱ ኮሙዩኒኬተር መኖሩ በራሱ ጥሩ ነገር
ነው፡፡ ይህ ግን ብቻውን ትርጉም ያለው ለውጥ አያመጣም፡፡ በተለይ በድ/ቀትዎ በኩል በአሁኑ ሰዓት
ለኮሙዩኒኬተሮቜ እዚተሰጠ ያለው ዚትኩሚት ማነስና አድሎ ዚተሞላበት መኹፋፈል ኚፊት ለፊቱ ትልቅ ስጋትን
ደቅኗል፡፡ በዚፌደራል መስሪያ ቀቱ ዹተገለልን ዚሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎቜ ጉዳይ በአስ቞ኳይ መፍትሔ
ካልተሰጠው ወደ ኹፋና አስቀያሚ ቜግር ያመራል፡፡ አይጠራጠሩ፡፡
ይህን ዚምንልዎት ኚመሬት ተነስተን አይደለም፡፡ እጅግ ተጚባጭ ማስሚጃዎቜና ማሳያዎቜ አሉን ምን አልባት
አይደርስዎት እንደሆነ እንጅ ዚጜ/ቀትዎ ኮሙዩኒኬተሮቜ/አስተባባሪዎቜ በተለይ/ በዚመስሪያ ቀታቜን መጥተው

ቜግሩን በመሹጃ አስሚድተና቞ው አምነውበታል፡፡ ፊርማ አሰባሰበን ማመልኚቻም አስገብተናል፡፡ በተለያዩ
ጊዜያትም ቜግሩ መፍትሔ እንደሚሰጠው ተዋሜቶልናል፡፡ ሁል ጊዜ ውሞትና ዹማይፈፀም ቃል ግን ይሰለቻል፡፡
ለማንኛውም ዚጜ/ቀትዎን ቜግር ወይም ዚእርስዎን ክፍተት ለዛሬ ጥቂቶቹን ብቻ እናንሳ፡፡
1ኛ/ ዹአቅም ግንባታ ቜግር፡- ይህ ጉዳይ ስትራ቎ጅካዊ ቜግር ነው፡፡ አሁን በዚፌዎራል መስሪያ ቀቶቜ ያለን
ኮሙዩኒኬተሮቜ ኹፍተኛ ዹሆነ ዹአቅም ክፍተት አለብን፡፡ ካሁን በፊት ዚተሰጡ ዹአቅም ግንባታ ሥልጠናዎቜ
ለተወሰኑ ኮሙዩኒኬተሮቜ ብቻ ነበር፡፡ ዚተወሰኑት ለ2ኛና 3ኛ ዙር በተደጋጋሚ ሲስለጥኑ ሌሎቻቜን ግን
ሥልጠናው አይመለኚታቜሁም ተብለናል፡፡ ዚአብዛኞቻቜን ዹአቅም ክፍተት መንጩ ይኜው አድሎአዊና ዹተወሰኑ
ግለሰቊቜን ብቻ መሠሚት ያደሚገ ሥልጠና አሠጣጥ ነው፡፡ ግን ለምን? እኛ ኢትዮጵያዊያን አይደለንም?
ዚአገራቜን ለውጥ እኛን አይመለኹተንም? ሥልጠናውን ለማግኘት ምን መስፈርት ነው ማሟላት ያለብን?
ኹ50% በላይ ዹምንሆን ባለሙያዎቜ እኮ ሥልጠና አልወሰድንም፡፡
ብዙ ጊዜ ዚኮሙዩኒኬሜን ሥልጠና ዹሚሰጠው ለኢህአዎግ ታማኝ አባላት ነው ዹሚል ግምት ነበሹን፡፡
በተጚባጭ ኚዚመስሪያ ቀቱ ያለን ዚእንጀራ ልጅ ዚሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎቜ በግል ተሰባስበን ስንነጋገር ግን
ይህ አይደለም እውነቱ፡፡ እንዲያውም እንዳንድ ፀሹ ዎሞክራሲያዊና ፀሹ ልማታዊ ዹሆኑ በሥልጠናው ሲጠቀሙ
እጅግ ጠንካራ ዚድርጅቱ ልጆቜ ግን እስካሁን ተገለዋል፡፡ በጣም ዹሚገርመው በአብዛኛው ፌደራል መስሪያ
ቀቶቜ ያሉና ሥልጠናውን ዚወሰዱ ኮሙዩኒኬተሮቜ ዚነበራ቞ው ዚትምህርት ዝግጅት ዚተፈጥሮ ሳይንስ በመሆኑና
አሁንም ለመለወጥ ዝግጁ ስላይደሉ ሥልጠናውን ደጋግመው ቢወስዱም እንኳን በስም እንጅ በግብር
ኮሙዩኒኬተር መሆን አልቻሉም፡፡ በአንፃሩ ግን በፖለቲካል ሳይንስ፣ በቋንቋ፣ በደርናሊዝምና ኮሙዩኒኬሜን
ተመርቀን ሥራውን በአግባቡ እዚሰራን ያለን ባለሙያዎቜ ሥልጠናውም አልተሰጠንም፣ ዚኮሙዩኒኬተርነት
ማዕሹግም ዹለንም፡፡
ዚስልጠና መስፈርቱ ምን ይሆን? ለምንስ ዹአቅም ግንባታ ሥልጠናው ቆመ? “ዚክቡር አቶ በሚኚት መልካም
ፈቃድ ስለሚያስፈልግ ነው” ዹሚለው ዚእርስዎ ባለሙያዎቜ መልስ እውነት ነው? እውነት ኹሆነ እኛ ምን
አጥፍተን ነው ዚእርስዎን መልካም ፈቃድ ማግኘት ያልቻልነው? ሥልጠናውን ብንወስድ ምን ይጎዳዎታል?
እባክዎትን ያስቡበት፡፡ ይህ ማግለል አገርን ይጎዳል ለሥራዎም እንቅፋት ይፈጥራል፡፡ እኛም በኢትዮጵያ ጉዳይ
ያገባናል፡፡ በሥልጠናው አቅማቜንን ገንብተን ለአገራቜን ሕዳሎ ዚራሳቜንን ድርሻ መወጣት እንፈልጋለን፡፡
እባክዎትን ያሰልጥኑን! ዹሰለጠነ አይጎዳም- ይጠቅማል አንጅ!
2ኛ/ዚቡድንተኝነት መንፈስ፡-
ይህ መጥፎ ዹሆነ ዚቡድንተኝነት መንፈስ በአብዛኞቹ ፌደራል መስሪያ ቀት ኮሙዩኒኬተሮቜ ዘንድ በግልፅ
ይታያል፡፡ ዚእንጀራ ልጅ ዚሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎቜ ኚዚመስሪያ ቀቱ በግል ተሰባስበን በተወያዚንበት ወቅት
በግልፅ እንደተሚዳነው ይህ ዚቡድንተኝነት መንፈስ በሥራ ላይ ኹፍተኛ ጫና እያሳደሚ ይገኛል፡፡ ይህ ቜግር ደግሞ
ኚዚመስሪያ ቀቱ ወጥቶ ይሄው ሀገራዊ እዚሆነ ነው፡፡ ሥልጠናውን ዚወሰዱና ዚኮሙዩኒኬተርነት ማዕሹግ
ዚተሰጣ቞ው ሥልጠና ያልወሰድን ባለሙያዎቜን እያገለገሉን ነው፡፡ በሆነ ባልሆነው ኮሙዩኒኬተር
አለመሆናቜንንና ኚሕዝብ ግንኙነት ሥራም ልንባሚር እንደምንቜል ይነገሹናል፡፡ ይህ ሁሉ ዛቻና ማግለል ኹፍተኛ
ዹሆነ ዚሞራል ውድቀት እያስኚተለብን ነው፡፡ እስኚመቌ እንደዚህ ሆነን እንኖራለን? በፌዎራል መስሪያ ቀቶቜ
እኮ ኹ5ዐ% በላይ ዚሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎቜ ሥልጠና አልወሰድንም፡፡ ታዲያ ይህን ክፍል ያገለለ ሥራ
ውጀታማ ይሆናል ብለው ያስባሉ?
በጣም በሚገርመው በሁለቱ ቡድኖቜ ማለትም በሠለጠኑ እና ባለሠለጠኑ ኮሙዩኒኬተሮቜ መካኚል መሹጃ
ዚመደባበቅ ሁኔታው ኹፍተኛ መሆኑ ነው፡፡ በተለይ ዹሠለጠኑ ኮሙዩኒኬተሮቜ ኚመንግሥት ኮሙዩኒኬሜን ጜ/
ቀትም ሆነ ኹሌላ ዚሚደርሳ቞ውን መሹጃ ለራሳ቞ው ብቻ ይጠቀሙበታል፡፡ ለነገሩ ዚመንግስት ኮሙዩኒኬሜን ጜ/
ቀትም ቢሆን መሹጃ ዹሚልኹው ለሠለጠኑትብቻ ነው፡፡ እርስዎም ይህን ያውቃሉ ብለን እናምናለን፡፡ ዚእኛን ኢ-
ሜይል /E-mail/ አድራሻ እኮ ጜ/ቀትዎ አያውቀውም፡፡ምንም መሹጃም ደርሶን አያውቅም፡፡ ምክንያቱም
ዚእንጀራ ልጆቜ ነና፡፡ ይህ ግን ዚአገሪቱን ዚሕዝብ ግንኙነት ሥራ ምን ያህል እንደሚጎዳ ታስቊበት ነው እንዲህ
ዹሚደሹገው? እርስዎ ያሰቡትን ያህል ለውጥ እዚመጣ ያልሆነው እኮ በዚህ ምክንያትም ነው፡፡ እርግጠኞቜ ነን
መሚጃዎቹ ምሥጢራዊ አይደሉም፡፡ እኛ እንዳናውቅ ዚምንደሚግበት ምክንያት ግን ግልፅ አይደለም፡፡ እባክዎትን
ይህ ጉዳይ አገር ይገድላልና ያስቡበት፡፡
3ኛ/ኹፍተኛ ዹሆነ ዹደመወዝና ዚጥቅማጥቅም ልዩነት፡-
ክቡር ሚኒስትር አቶ በሚኚት፡- ይህ መቌም ኚእርስዎ ዹተደበቀ አይደለም፡፡ እያወቁ ለምን እንዲህ እንዲሆን
እንደፈቀዱ ግን ለማንም ግልፅ አይደለም፡፡ በደመወዝ እንጀምር፡፡ አንድ ልዩ ሥልጠና ወስዶ (ዹ15 ቀናት

ሥልጠና) ዚእርስዎ ክቡር ፊርማ ያሚፈበት ዚመንግስት ኮሙዩኒኬተር ዹሚል ስርተፊኬት ያለው ዚሒሳብና ፊዚክስ
ምሩቅ ጀማሪ ኮሙዩኒኬተር መነሻ ደመወዝ 3,348.00ብር ነው፡፡ ነገር ግን በቋንቋ፣ በጆርናሊዝምና
ኮሙዩኒኬሜን 3 ዓመት ሰልጥነን ዚመጀመሪያ ዲግሪ ያለን ነገር ግን ልዩ ሥልጠናውን ያልወሰድን ዚሕዝብ
ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሜን ባለሙያዎቜ መነሻ ደመወዛቜን 1,499.00ብር ነው፡፡ በተመሳሳይ መደብ ላይ
ተመሳሳይ ሥራ እዚሠራን ይህን ያህል ዹደመወዝ ልዩነት ለምን? እውነታው እኮ ያማል፡፡ ኹፍተኛ ዹሆነ ዚሞራል
ውድቀትም አስኚትሎብናል፡፡ በምን መስፈርት ነው ተመሳሳይ ሥራ እዚሠራን በ1,849.00ብር ወርሀዊ ደሞዝ
ዚሚበልጡን? አንዳንዶቻቜን 8 እና 7 ዓመታት በሕዝብ ግንኙነት ሥራ ቆይተን ደመወዛቜን ግን
ኚሠለጠኑጀማሪ ኮሙዩኒኬተሮቜ እጅግ ያንሳል፡፡ ለምን? በጣም ዚሚያሳዝነው ደግሞ ሥልጠናውን ወስደውም
ግን በተለያዚ ምክንያት ደሞዛቾው ያልተስተካኚለላ቞ው ኮሙዩኒኬተሮቜ መኖራ቞ው ነው፡፡ ምክንያቱ ግልፅ
አይደለም፡፡ ብዙዎቹም ተስፋ በመቁሚጥ ሥራ እዚለቀቁ ነው፡፡ ለጜ/ቀትዎ ተፈራርመው ያስገቡት ማመልኚቻም
መልስ አላገኘም፡፡
ሌላው ጉዳይ ደግሞ ጥቅማጥቅም ነው፡፡ በተለይ በእርስዎ ልዩ ትዕዛዝ ኹዹክልሉ ተሰባስበውና ዹ3 ወር ሥልጠና
ተሰጥቷ቞ው ኮሙዩኒኬተር ዹሆኑ (አብዛኞቹ በዹክልሉ ዚተፈጥሮ ሳይንስ መምህራን ዚነበሩና በፖለቲካዊ
አቋማቾው ዹተመለመሉ) በርካታ ዚሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎቜ ቀት ተሰጥቷ቞ዋል፡፡ ለእነርሱ ለምን ተሰጣ቞ው
ዹሚል ተቃውሞ ዹለንም፡፡ ነገር ግን ለሌሎቻቜን ቢያንስ ደመወዝ እንኳን ለምን አይስተካኚልልንም? ዚእንጀራ
ልጅ ስለሆንን? በዚህ መልኩ እኮ እርስዎ ዚሚደክሙለት ዚኮሙዩኒኬሜን ሥራ ሊሻሻል አይቜልም፡፡ ብዙ ጥሩ
ባለሙያዎቜን በማሾማቀቅና ሞራላ቞ውን በመግደል ዚሚመጣ ለውጥ ያለ አይመስለንም፡፡ ለፌደራል መስሪያ
ቀቶቜ ዚሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሜን ባለሙያዎቜ ዹተፈቀደው ደመወዝ እኛን ዚማይመለኚት፣ ነገር ግን
ሥራው ዹሚመለኹተን ኹሆነ ትንሜ ይኚብዳል፡፡
እናም ክቡር አቶ በሚኚት፡- እስኚመቌ ነው እኛ ዚእርስዎ ዚእንጀራ ልጆቜ ሆነን ዚምንቀጥለው? እባክዎትን ደግ
አባት ይሁኑልን፡፡ አባት በልጆቹ መካኚል ልዩነት መፍጠሩ ጥሩ አይደለም፡፡ እርስዎ ዚአባትነት ድርሻዎን
ካልተወጡና እኛን ካገለሉን እኛም ተጹቋኝ ዚእንጀራ ልጆቜ ሆነን ዚምንቀጥል አይመስለንም፡፡ ለቀጣይ ሌሎቜ
ቜግሮቜን ይዘን እንመጣለን፡፡ እባክዎትን ያስቡን፡፡”ኹልጅ ልጅ ቢለዩ ዓመትም አይቆዩ” ሲባል አልሰሙ ይሆን?
ልዩ ማሳሰቢያ፡-
በአሁኑ ሰዓት ዚተበዳይ ኮሙዩኒኬተሮቜ ቁጥር በኹፍተኛ ደሹጃ እዚጚመሚ ሲሆን በኮሙዩኒኬሜን ጜ/ቀትም ሆነ
በሌሎቜ መስሪያ ቀቶቜና ባለስልጣናት ገመና ዙሪያ መሚጃዎቜን በማሰባሰብ ላይ እንገኛለን፡፡ ክቡር አቶ
በሚኚትም በተለመደ ንቀታ቞ውና ዝምታ቞ው ዚሚቀጥሉ ኹሆነና እነደማነኛውም ኮሙዩኒኬተር ዹደመወዝና
ሌሎቜ ጥቅማጥቅሞቜ ዚማይስተካኚሉልን ኹሆነ ወይም በተለመደ ዚማታለል ስልታ቞ው (በሚቀጥለው ወር
ትሰለጥናላቜሁ በሚል ፈሊጣ቞ው) ዚሚቀጥሉ ኹሆነ በምስልና በድምጜ ዚተቀነባበሩ መሚጃዎቜን ለተለያዩ
ዹውጭና ዹሀገር ውስጥ ሚዲያዎቜ በመስጠትና ለሕብሚተሰቡ በማድሚስ ዚምንቀጥል መሆኑን እናሳስባለን፡፡
እስኚሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት መልስ ዹማይሰጠን ኹሆን ወደ ቀጣዩ ዹኹፋ እርምጃ ለሄድ እንገደዳለን፡፡ ሲሆን
ለዓመታት እዚተበደልን ላገለገልንበት ካሳ እንዲኚፈለን ባይሆን ግን በመመሪያው መሰሚት እንዲኚፈለን
ካልተደሚገ በስተቀር በቀጣይ በተኚታታይ ዚምንወስዳ቞ው እርምጃዎቜ እጅግ ዹኹፉና እኛንም ሆነ መንግስትን
ውድ ዋጋ ዚሚያስኚፍሉ ይሆናሉ፡፡ በእኛ በኩል እስኚሞት ዋጋ ለመክፈል ተዘጋጅተናል፡፡ አንድ ቀን
ምንአልባትም በሳምንታት ውስጥ በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ሥራ ዹማቆምና ኚሥራ ዹመልቀቅ አድማ ለማድሚግም
ተስማምተናል፡፡ ኹዛም ስለቀጣይ ጉዟቜን ኚተለያዩ አካላት ጋር እዚተመካኚርን ሲሆን ጥገኝነት ለመጠዹቅ
ኢምባሲዎቜን እያነጋገርንና ባንዳንዶቜ ዘንድ በጎ ምላሜ እያገኘን ነው፡፡ ነገሮቹ ሁሉ ወደ ኹፋ ደሹጃ
ኚመድሚሳ቞ው በፊት ግን ቢታሰብበት መልካም ነው እንላለን፡፡ ለአገራቜን ሁላቜንም ያገባናል፡፡
መብታቜንን ለማስኚበር ዹሚኹፈለውን ዋጋ ሁሉ እንኚፍላለን!
በእርግጠኝነት እናደርገዋለን!
ምንም ዚሚያስፈራን ነገር ዹለም፤ ሞትም ቢሆን!
ዚተበዳይ ኮሙዩኒኬተሮቜ ሕብሚት አንድነት ጉባኀ
አዲስ አበባ

አርቲስት ታማኝ በዹነ ቀተሰቊቜ በተለይም እህቱ ታስራ ተፈታቜ


ዚአርቲስት á‰³áˆ›áŠ በዚነቀተሰቊቜ á‰ á‰°áˆˆá‹­áˆ áŠ¥áˆ…á‰± ታስራ á‰°áˆá‰³á‰œ።ዝርዝሩን áŠšáŠ¢áˆ³á‰µ áˆ«á‹µá‹®  áŠ¥áŠáˆ†
ያድምጡት።

Total Pageviews

Translate