Pages

May 17, 2013

ወገኖቼ እባካችሁ ለጥያቄዬ መልስ ስጡኝ (ተሾመ ደባልቄ)

ሾመ ደባልቄ

ዲሞክራሲና ትግል
ዲሞክራሲ አገሮች የሚኖሩ የወያኔ ጉጅሌዎች የሚወዱትን መሪ መርጠው ለኢትዮጵያ ህዘብ ግን ወያኔ ይበቃዋል ማለታቸው ማሞ ቂሎ መሆናቸውን ያቁታል?
ለህዝብ ነፃነት እታገላለሁ የሚል የግለሰብም ሆነ የቡድን ልዩነት የሚመጣው ከህዘብ ይልቅ እራሴን ላስቀድም የሚል ስግብግብነት ነው ቢባል ዕውን አይሆንም?
ነጻነትና ዲሞክራሲ ሲባል ሆዱን የሚቆርጠውና የሚያስለፈልፈው ዜጋ የሌባ እንጀራ የበላ ብቻ ይሆን?
ወያኔስ በድንቢጥ ምስክሮቹ 99.6 በመቶ ህዝብ መረጠኝ ብሎ መንግስት ነኝ ሲል ደጋፊዎቹን ቆረቆሮ ራስ ደንቆሮዎች እያለ የሚፌዝባቸው ምን ያህል ቢንቃቸው ነው?
ይህ አቢዩታዊ ዲሞክራሲ የሚሉት የወያኔ ሥርዓት ፓርላማ መግባት እንጂ መውጣት አያቅም ማለት ነው? አብዮት ነፍስ ለመብላት ዲሞክራሲ ደግሞ ለማጭበርበር ቢባልስ ያስወነጅላል?
ወያኔ የትግራይ ሪፐብሊክ የሚለውን ክልል ከኢትዮጵያ ነፃ አወጣሁ ካለ ከርሟል መቼ ነው ክልሉን ከወያኔ ሌቦች ነፃ የሚያወጣው? ሽብር አትፍጠሩ ክልሉ በኮንስትቱሹኑ የብሄር ሌቦች ምሽግ ነው የሚለን?
የምርጫ ቦርድ የሞሉት ሙህሮች ከቀኝ ወደግራ እንዲቆጥሩ ያስተማራቸው የሕዋዕት ካድሬ ነው ወይስ መምህር?
ልማትና ኢኮኖሚ
ኑሮ የተወደደው ኢኮኖሚው በፈጣን ስላደገ ነው የሚሉ ሙሁራን አጥንተው ነው ወይስ ወያኔ አስጠንቷቸው?
ሌብነትን ልማት ነው የሚሉን የወያኔ ጉጅሌዎች ባቋራጭ ሌቦችን ከንጹህ ዜጋ  እኩል ለማደረግ ይሆን?
የውጭ እንቭሰተሮች ወያኔ ላይ ነው ወይስ ሀገር ላይ እንቬሰት የሚያደርጉት?
አላሙዲ የሚባለው ኢንቨስተር ክልልም ገደብም የለውም ማለት ነው? ኮንስትትሹኑ ዶላር ያለውና ወያኔ ኢትዮጵያዊ ሌላው ደግሞ ብሄርና ብሄረሰቦች ናቸው የሚል ተጽፏል ማለት ነው? ታዲያ ወያኔ የትግሬ ነፃ አውጭ ነኝ ከሚል የሌቦች ነፃ አውጪ ነኝ ቢል አይቀልም?
አዲሱ የወያኔ የውጭ ጉዳይ ሚንስተር የአባይ ግድብን የሚቃወሙ ሀገራቸው እንዳያድግ የሚፈልጉ ናቸው እያለ የሚለፍፈው ወያኔ ወገንን ሽብርተኞች ማለት አልሰራ ስላለ ይሆን?
የትግራይ ልማት የሚባለው የልመና ድርጅት ትግራይን ሊያለማ ወይስ ኢትዮጵያን ሊያደማ የተቋቋመው? ካልሆነ ለምን በኢትዮጵያ ሥም ለምኖ በትግራይ ክልል ስም ይቸረችራል?
ልማት ተፋጥኗል የሚሉ ምሁሮች ኪሳቸውን እየዳበሱ ነው ወይስ ጥናት እያጠኑ?
በልመና እድገት አመጣለሁ የሚለው የወያኔ ሥርዓት ድህነትን ማስፋፋትን ለልመና ያመቻል ብሎ ይሆን? ድህነት ባይኖር በምን ሊኖር ነው፤ በማጅራት መች?
ሰባዊ መብት
የወያኔ የሰባዊ መብት ኮምሽን ሥራ የሚቀጠር ግለሰብ የራሱን መብት የማያውቅ ብቻ ይሆን?
የአለም መንግሥታትና ድርጅቶች ወያኔ ሰባዊ መብት ይጥሳል ሲሉ ጉጅሌዎቹ የስድብ ናዳ የሚያወርዱባቸው አንጥስም ወይስ ሰባዊ መብት አልገባንም ማለቱ ነው?
ፖሎቲካ
እኔ ፖሎቲካ አልወድም የሚሉ ግለሰቦች በአዙርኝ ወያኔ ተመችቶናል እንብላበት ተዉን ማለት አይሆንም?
የፖሎቲካ ፓርቲ ነኝ ማለት እራሴን ነፃ ላውጣና እንደወያኔን ልሁን ነው እንዴ?
ፖሎቲካ ምን ያደርጋል ልማት ነው ጥሩ የሚሉ፤ ሰርቄ ወድያለሁ ተወንጅዬ እስር ቤት መግባት አልፈልግም ማለታቸው ይሆን?
ወያኔ የዲያስፖራ ወገኖችን አክራሪ ፖለቲከኞች እያለ የሚዘፍነው ማሰርና መግደል ስላቃተኝ ሌላ ምርጫ የለኝም ማለቱ ይሆን?
ወያኔ ወገኖችን ተቀዋሚ ፖሎቲካ አትግቡ እያለ በካድሬዎቹ የሚያስፈራራው የውሸት መንግስት መሆኔን ይታወቅብኛል ማለቱ ነው?
ሙሥናና ሌብነት
የወያኔ ጉጅሌዎች ጆሮዋቸውን የደፈነው ከሌብነት እንጀራ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? ዘረኛነት?
ሌባ…ሌባ ተብለው የተባረሩት የወያኔ ዲፕሎማቶች ወዴት፤ እስር ቤት ወይ ሹመት ?
የወያኔ መሪዎች እነደሙጫ ያጣበቃቸው ሌብነቱ ወይስ አቢዎታዊው ዲሞክራሲው?
ድሕነትን ሐጥያት ፣ ነፃነትን ወንጀል፣  ሌብነትን ልማት ያደረጉ የዘንድሮ ሙሁሮች  የዕውቀት ድክመት ወይስ የሌብነት ቁረኛ?
ብሔርና ብሔረሰብ
ወያኔ የብሄርና ብሄረሰቦች ፌደራሊዝም እያለ በራሱ ‘ብሄር’ ላይ ከማፌዝ በላይ ያተረፈው ዘረፋ ብቻ ነው ቢባል  አሸባሪዎች የሚላቸው ወገኖች አብረውት ዘረኛ፣ አሸባሪና ዘርፊ ያለሆኑቱን ማለቱ ይሆን?
በብሄሩ አንድን ሥርዓት የሚደግፍ ግለሰብ ወይ ቡድን ሌላ ባህሪ የሌለኝ ለሆጌ የምኖረ ዘረኛ ነኝ ማለቱ ይሆናል?
ብሄርና ብሄረሰቦች ብሎ ኢትዮጰያውያንን ለፖሎቲካ ጥቅም የሚቸረችር ሥርዓት ሆነ ቡድን ብሄሩንም ማንነቱንም የማያውቅ እኔ ከሞትኩኝ ሰርዶ አይብቀል ያለ ጠፍቼ አጠፋለሁ ያለ ሽብርተኛ ነው ቢባል በወያኔ ፍትህ በዘር ማጥፋት ያስወነጀል ይሆን?
የወያኔ የክልል ሥርዓት ቀስ በቀስ የቻይና የህንድና የአረብ ብሄረሰቦች ክልል ያስፍጋል ብሎ በአንቀፅ 39 መሠረት መገንጠል መብታቸው ነው ማለቱ ይቀራል?
አንድ ዜጋ ወያኔን የሚደግፈው በዘሩ ከሆነ ዘረኛ በስራው ከሆነ ቀማኛ ቢባል ትክክክ አይደለም?
አማራ እያጠቁ በአማራናቱ ኦሮሞን ባኦሮሞነቱ…ወዘተ ይደራጅ የሚሉ ጉጅሌዎች የወያኔን ኢትዮጰያኖችን ከፋፍል ሴራ ፍጻሜ ግብ አድርሱ የተባሉ አይመስሉም?
ትግሬ ነን የሚሉ የወያኔ ጉጅሌዎች ለምን በትግሬ ሥም ሀገርን ህዘብን መዝረፍና ማጥፋት መረጡ ብል ትግሬን  ወይስ ሌባንና አጥፊን ጠላሁ ማለት ነው ?
ፍትህና ሕግ
ንጹህ ዜጋን አሸባሪ ብሎ መወነጀል  የፈሪ በትር አይሆንም? ፍርሀት ደግሞ የሚመጣው በሰሩት ወንጀል ተሸብረው ንጹሃንን በማሸበር የሚሽሩ የሚመስላቸው ሰዎች ናቸው ቢባል ሀሰት ይሆን?
በሀሰት ንጹሀን ላይ የሚመሰክሩ ግለሰቦች በቁም ሞተው በቁሙ ለሞተ ሥርዓት ያጎበደዱ ብቻ ናቸው ማለት አይቻላልም?
ሚሚ ስብሃቱ የተባለች የወያኔ ታናሻ የአፈ ጉባዬ ጉጅሊት (የበረከት ታናሽ) ‘ህግ ወጥ ሰፋሪ’ ያለቻቸው ዜጎች ከሬዲዎ ፈቃድ ሌላ የራሷን ህግ እንድታወጣ ፈቃድ የፍትህ ሚኒስተር ሰጥተዋት ይሆን? በወያኔ ሥርዓት ስንት ህግ አውጭ ነው ያለው?
ፍርድ ቤት የተጎለቱት ዳኞች እስር ቤት የላኳቸውን ዳኛ እነሱ ደግሞ እስር ቤት ቢወርዱ ፍትህና ነጻነት መጣ ማለት አይቻልም?
ወገንና ሀገር አጥፊዎች
የሀገሩን ህዝብ እነደጠላት የሚያይ ግለሰብ ሆነ ቡድን ሀገርም ዘርም ህሊናም ሀይማኖትም የሌለው ቅጥረኛ ነው ቢባል በወያኔ ሥርዓት ሽብርተኛ ወይ ትምከተኛ ያስብል ይሆን?
ወያኔ ጉጅሌዎች ለቅሶ የተቀመጡት ለሟቹ መሪያቸው ወይ እየተጋለጠ ላለው ወነጀላቸው?
ዘንድሮ ወያኔ ነኝ የሚል ግለሰብ ወንጀለኛ ነኝ ቢል በቶሎ ነጻ አይወጣም?
የኢትዮጵያን ኮንስትትሹን ያረቀቁት የወያኔ ጉጅሌ ሙህሮች እኒቨሰተርስ ወይ የውጭ ዜጎች ካልሆኑ በቀር እንዴት የሕዋዕት ማኒፈስቶ ሊመስል ቻለ?
የወያኔ ሙህሮች ከሥርሃቱ ጋር ሊሞቱ ካልቆረጡ በቀር እደመሀይም ለምን ደጅ ይጠናሉ?
አዲሱ ጠቅላይ ሚንስተር ከወያኔ ባርነት ነጻ ልውጣ ብለው ከተቀዋሚውን ጎራ ቢቀላቀሉ ከአሻንጉሊነት ይድናሉ ማለት በስም ማጥፋት ያስወነጅል ይሆን?
በረከት ስሞን ምን ነካቸው ብሄራቸው ያልሆነውን ህዝብ እወክላለው ብለው ልባችንን በፕሮፖጋነዳ ከሚያደርቁን ያአማራ ፍቅር ነው ወይሰ ክልሉ ወያኔና ሻቢያ ክልልና ሀገር የነፈገው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ክልል ነው?
የቀድመው የወያኔ እመቤት የባለቤታቸው ለቅሶ አብቅቶ ላጠቁት የኢትዮጵያ ህዘብ ቢያለቅሱ እድገትና ትራነሰፎረሜሽን በፍጥነት ይመጣል ማለት ይቻላል?
ወያኔና ጉጅሌዎቹ ኢትዮጵያና አማራ ጠላት ነው ባንዲራም ጨርቅ ነው እያሉ ሲለፍፉ፣ ሲገሉ፡፣ ሲገፉ፣ ሲዘርፉና ሲዘፍኑ ከርመውና ሰንብተው ምነው ከአለማቸው ሽሽት መረጡ?
ዘር የማጥራት ወንጀል የሚፈጽሙ የወያኔ ባልስጣኖች ዘራቸውን ያውቃሉ ወይስ ወያኔ ነው የሚያድላቸው?
የመለሰ ፋውንዴሽንን የሚሉት አቋም ቻይና ወይ ህንድ አልያ ሳዓውዲ ሀገር ውስጥ ቢገነባ አይሻልም?
አስተዳደደር
ነፃ አውጭ ነኝ በሚል ስም የሚነግደው የገዠው ቡድን እንኳን ትግራይን ነፃ ሊያወጣ እራሱን ከሌብነት ነጻ ማውጣጥ ችሎታ የለውም ብል የግንቦት 7 ‘አሸባሪ’ ቡድን አባል ነህ ተብዬ በአሸባሪነት ልወነጀል እችል ይሆን?
ሠራዊቱ ተብዩ ለወያኔ ከህዘብ ዘበኛ ወይስ ህዘብን ከወያኔ ተከላካይ?
የመንግስት ሰራተኞች ሲባል ደሞዝ የሚከፍላቸው ህዘብ ወይስ ወያኔ?
በብሄር ሥልጣን የያዘ ሰው ማንን ነው የሚያስተዳድረው? እራሱን?
የኢትዮጵያን ኤምባሲ የሞሉት ዲፕሎማቶች ዜጋቸውን ወይስ ብሄረቸውን  የሚወክሉት? አልያ ለምን ወያኔ ኤንባሲ አይሉትም?
ሐይማኖት
ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች በሀይማኖት ስም ዳግም ተወለድኩኝ የሚሉ ባጠፉትን ወንጀል እንዳይጠየቁ ምሸግ ያገኙ መሰላቸው ወይስ ተጸጽተው? አይዣቹህ የሚላቸውስ የሃይማኖት ሥርዓት ወንጀል የፈጸመ  ሁሉ ዳግም ከተወልዶ ነፃ መውጣት ትችላላቹህ ነው የሚሉት?
የዘመኑ ፓስተሮች የኢየሱስን ወይስ የወያኔን ቃል የሚሰብኩት?
ወያኔ የሾማቸው የሀይማኖት መሪዎች ሀይማኖትን ከሚያረክሱ ከመስቀል ይልቅ ጠመንጃ ታጥቀው ባለ ሀብት ነኝ ቢሉ አያምርባቸውም?
አቦይ ሰብሃት የሚባሉ የሽማግሌ ቅሌታም ንሳሃ እንዳይገቡ የነፍስ አባት የላቸው፣ እንዳይመኖክሱ ገዳሞች  አፍርሰዋል፣ እዳያስቀድሱ ቤተ ክርስትያና እንደሕዋዓት ቢሮ የካድሬ መዋያ ሆነዋል፤ አንደኛውን ዳግም ተወለድኩ ብለው የየሱስ በግ ነኝ እያሉ እንደ ቀድሞው ጠ/ሚንስተር ቢሰብኩ አይሻልም? ለመሆኑ የኢየሱስ በግ መሆን ሌባንም ያድናል እንዴ?
ኢትዮጵያዊያን የእስላም ሀይማኖት ተከታይ ወገኖቻችን ሀገራችን ሀይማኖታችን ወገናችን ወይ ሞት ሲሉ እሰየው ከማለት ምን አስደነገጠው ወያኔ?
የኦርቶዶክስ ሀይማኖት የአማራ መመሸጊያ ነው ስሉ ወያኔዎች ለትግሬ ወገኖች ምንድነች ነው የሚሉት?
በዲያስፖራ ያሉ ቤተ ክርስቲያናት ገለልተኛ ነን ሲሉ ከማን ነው የሚገለሉት? ከሀይማኖት ወይስ ከወያኔ?
ያልሀበሽ የሚሉት ወያኔ ያመጣብን አዲሱ ሞዴል ሀይማኖት ከኢኮኖሚ እደገትና ትራንስፎርሜሽን ጋር አብሮ የሚሄድና ባቋራጭ አላህ ጋር እንዲያገናኘን ነው ወይስ ወያኔ አላህ ነው እንድንል?
ጋዜጠኞችና ብዙሃነ መገናኛ (ሚዲያ)
ወያኔ ከኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ጋር እሳትና ጭድ የሆነው በውሸት ህዝብና አገር ሲያቃጥል ሰንብቶ የእውነት እሳተ ሰደዶ ስለመጣበት እንጂ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?
የበረሀ የጦረኛ ጀግናዎች ነን የሚሉ ወያኔዎች ኢሳት ቴሌቪዝን ፈርተው የተሸሸጉት የውሸት ጀግኖች ወይስ እውነቱ ፈሪዎች?
ሀገር ውስጥ የብዙሃን መገናኛ (ሚዲያ) አለን የሚሉ ግለሰቦች ወይ እውነቱን ተናግረው ወያኔ እሥር ቤት ቢገቡ አልያ እግራቸተውን ሰብስበው እቤታቸው ቢቀመጡ ከውሸት ጛደኝነት አይመረጥም?
ብሄር የሌላቸው በረከት ስምዖን የሚሏቸው የወያኔ የብሔር ብሔረሰብ ፌደራል ባልስልጣን የቡዙሀኑን መገናኛ ለ 22 አመት ሙጥኝ የሉት፤  ብሄር ስለሌላቸው ወያኔ ገለልተኛል ማስረጃ ያቀርባሉ ብሎ ወይስ የውሸት ባለሞያ ስለሆኑ?
ሚሚ ስህባቱ የሚባሉ በነጻ ሚዲያ ስም ወያኔ ብቸኛ ‘የግል’ ሬዲዎ ጣቢያ የለገሳቸው ግለሰብ ድሮ የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ጋዜጠኛ፣ ብሄራቸው ትግሬና ዜግነታቸው አሜሪካ ሆኖ የአማርኛ ሬዲዎ የከፈቱት ብሄራቸውንም ዜግነታቸውንም ለውጠው ነው ማለት ነው? የወያኔ ሥርዓት ብሄር መለወጥ ይቸሃላል እነዴ? የሁሉም ብሄር ያካተቱ የሚል ኢትዮጰያዊ ብሄር መታወቂያ አለ እንዴ?
ኢትዮጵያን ጋዜጠኞች በእስር ቤትና በስደት አልቀዋል የቀሩት ምንድናቸው ማለት ነው?  የማስታወቂያ ሥራ ድርጅቶች?
ኢቲቪ የሚሉት የብዙሃን መገናኛ ከወያኔ ነፃ ቢወጣ ሥርዓቱ ሁለት ቀን ማደር ይችላል?
ያ ወፍራሙ ወያኔ ሬዲዎ ጣቢያ የከፈተለት ዘፋኙን ጋዜጠኛን የሚያዳምጡ ወገኖች በድምጹ ወይስ በዕውቀቱ ተማረከው? አብሮት የሚያጓራ ዶክተር ነኝ የሚል ግለሰብስ የውነት ዶክተር ነው ወይስ የእንድርያስ እሸቴ ጓደኛ?
በዲያስፖራ ያሉ አንዳንድ ድህረ ገጾች ስለ አሜሪካ ዲሞክራሲና ምርጫ ሲዘግቡ ደስ ይላሉ ግን የሀገር ድሞክራሲና ምርጫ ጉዳይ ሲሆን ቻይና እንዳሉ ጋዜጠኞች አይተነፍሱም፤ ፈሪ ከሆኑ ምን አስፈራቸው ወያኔስ ከሆኑስ ምን አስደበቃቸው ብሎ የሚጠይቃቸው እንዴት ጠፋ?
ታጋይ
ይሄ ታማኝ በየነ የሚባል ወገን ጦብያ ሀገራች ለዘላልም ትኑር እያለ የወያኔ ጉጅሌዎችን የሚያቃጥላቸው ለምን ደፈጣ ውጊያችሁን ተውና በህዝብ ፊት ኢሳት ላይ ግጠሙኝ አይላቸውም? ወገኖቼ እነዳይዋረዱ ብሎ አዝኖላቸው ይሆን?
ሕውዓቶች ጀግና ነን  ተራራውን አመስነው እያሉ ባዶ ሜዳ ላይ የሚፎክሩትና ዳንኪራ የሚረግጡት  እንዴት አንድ ኢትዮጵያዊ አርቲሲት ባዶ እጁን ፈረተው፣ ሸሸተውና እንቅልፍ አጥተው ሊደናበሩ ቻሉ?
ለምንድነው ወያኔ አገራቸውንና ህዝባቸውን በጣም የሚወዱ ኢትዮጵያኖችን ታጋዮች መርጦ መርጦ አሸባሪ የሚያላቸው?
ኦባንግ ሜቶ የሚሉት ኢትዮጵያዊው ቡልዶዘር ወያኔ የሚገነባውን የክልል ግንብ እያፈረሰ አንድ ህዝብ አንድ ሀገር ስላለ አሸባሪ ስም ያሸከሙት ወያኔን ወይስ ወገኑን ስላሸበረ ነው?
ዶ/ር ብርሃኑ የሚባሉት የግንቦት 7 መሪና ወገን በወያኔ አሸባሪ ተብለው የተፈረጀባቸው በግንቦት 7 ህዝብ ስለመረጣቸው ወይንስ ወያኔን ከግንቦት 7 ጀምረው ሽብር ስለጨመሩት?
ወገን በዲያስፖራ
በውጭ ያሉ የወያኔ ደጋፊ ኢትዮጵያውያን ከወያኔ በሓላ ሀገር አትኖርም ብለው ሀገር ሊከዱ አስበዋል እንዴ?
ዲያስፖራውን ፈሪ ያደረገው ወያኔ የሰጠውን መሬት ይወስድብኛል ብሎ ይሆን?
የሕዋት ካድሬዎች ስንት ብሄር ነው ያለቸው? አንደኛውን ኢትዮጽያ ነው ብሄሬ ቢሉ አይሻልም?
በውጭ ሀገር ለህዳሴ ግንባታ ገንዘብ ለማሰባሰብ የሚመጡ የወያኔ ጉጅሌዎች ኢትዮጵያንን ሁሉ ሲጋብዙ አባይ ክልል የለውም ማለት ነው? ለምን የትግራይ ክልል ግንባታ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ አይጋበዙም?
ዲያስፖራ ያሉ የሕዋዓት አባሎች ዜግነታቸው ሕዋዓት ነው ወይስ ኢትዮጵያዊ?
ለምንድነው የወያኔ ጉጅሌዎች በዲያስፖራ ስማቸውንና ተግባራቸውን ደብቀው ድፍጢያ ውጊያ የያዙት፤ ስራቸው ወንጀል መሆኑን ያውቃሉ ማለት ነው?
ጥያቄው ይቀጥላል…

When the truth punches the desperate Ethiopian regime in the face?

Like it or not Ethiopians are coming together to end Woyane rule. What is left for regime and its stooges is to continue pocking hole on Ethiopiawinet; pandering and instigating ethnic and religious divisions and conflicts to divert the issue of illegitimacy. As my uncle use to say, ‘ወያኔ ፈረስ ከገብስ ያጣላል’ In its desperate attempt to cover up the truth and avoid responsibility diversion became the only option left. የቸገረው እርጉዝ ያገባል?

Like it or not Ethiopians are coming together to end Woyane rule
by Teshome Debalke
Recent news the regime ruling Ethiopia detained some of its corrupt officials after it use and abuse them for two decade to accomplish its grand corruption is another hide-and-seek game of the illegitimate regime plays. It sounds more of the same face saving scum of TPLF to preserve its draconian rule and corruption by all means necessary. TPLF’s apologist and the badmouth Medias running wild and swinging wide to preserve the rotten regime.
The so called Federal Ethics and Corruption Commission spontaneous andunexpected move like its sister agencies TPLF set up isn’t different to rescue the self declared and illegitimate ethnic minority regime. Like the Election Board, the Human Right Commission, the Federal Courts, the Prosecutor Office, Communication Affair Minster… and the rest that are notorious to put up dramas to show there is a resemblance of a functioning government in Ethiopia is in full gear.
The infamous Federal Court is exceptionally notorious in putting up shows; thwarting real justice to send the innocent to jail to protect TPLF’s felons running loss in cover  of Justice. Likewise, FECC was set up as instrument of eliminating TPLF’s economic treats as well as its political opponents with tramp up charges in the name of fighting corruption.
This time around TPLF activated FECC on its own cadres and found fall guys to divert the many accusations coming its way, particularly the charge of ethnic cleansing. The hapless TPLF’s stooges are also throwing all kinds of diversion at us to protect the grand villains and their machinery of corruption and atrocity.   It is the same old ritual small time tyrants use to ‘eat’ their own offspring to show there is resemblance of normalcy in the ‘government’ they run; mostly for international consumption.
The last and only time FECC was used on TPLF members before was on Siye Abrha and family. The former TPLF executive member and the ‘Defense Minster’ of Ethiopia that spent six years in jail convicted of corruption; something common among TPLF members when they ransacked the public resources since Woyane took power. It was TPLF’s way of telling the rest of its members, if you mess up with the grand plan of Woyan you will bit the dust even if you are Siye’s stature.
Ever since, the stooges are scared to rock the boat; quietly robbing Ethiopians with impunity until the new round of arrest began unexpectedly. The motive behind the new wave of arrest for sure wasn’t corruption until the news broke out TPLF security agency is behind the whole thing. Like always, it turns out to be another diversion to protect the big fishes and the establishment; striped necked of conspiracy in committing heinous crimes of all kinds against the people of Ethiopia.
Speaking of Siye, it would be brave of him to tell the truth and nothing but the truth what he knew, when he knew it and how TPLF conspired to commit the heinous crime of ethnic cleansing and economic alienation of one group of Ethiopians or another to divide the people and rule. The last time he addressed the Diaspora in the US as a leader of the opposition we heard people didn’t appreciate for failing to come clean; acting as firefighter after he was member of the arsonist club most of his adult life. It doesn’t seem he fully comprehend the enormity of TPLF’s conspiracy of ethnic cleansing and economic annihilation of the people of Ethiopia.
Therefore, the recent bogus arrest of Woyane officials shouldn’t distract people from the real issue of the regime’s crime against humanity and massive corruption of TPLF and the unfinished business of freedom and democracy the people demand from the self declared minority ethnic junta.
Frankly it would have been appropriate if FECC arrested the ringleaders of TPLF’s corruption and ethnic cleansing like Azeb Mesfin, Berkit Simon, Sebhat Nega, Syoum Mesfin, Berhane G. Kirstos… to mention a few. But, the Commission picked foot soldiers that are feeding the grand corruption as ordered; reviling it is another diversion like many before it.  The Commission should also arrest Al-amudi, the Saudi investor that allegedly known to bribe many government officials to advance his economic interest. In fact, he in many occasions admitted in public advancing benefits to his close associates in the Woyane regime that landed him an exclusive right to the gold mines and land grabbing at will. If that isn’t grand corruption to charge him we don’t know why FECC is chasing small fishes.
Likewise, the Election Board members should also be arrested for conspiracy to steal the public’s votes to justify Woyane rule. Corruption doesn’t means monitory theft alone. It comes in all form; colluding with the political power against the people. The recent election that made Woyane the only party to win 100% of the vote makes all the Election Board members conspirators against the people of Ethiopia.
Most importantly, if there was a government worth its name the so called ‘Federal Police’ would have arrested the ring leaders of TPLF’s ethnic cleansing  for driving out Ethiopians off their land while harassing, threatening and jailing innocent Ethiopians in cover of fighting terrorism. The latest fall guys for crime of ethnic cleansing turn out to be low level regional officials in Beni-Shangule Region, according the Prime Minster.
The fact the truth coming out due to the expansion of independent Media like ESAT and social Media is making the regime scramble to find fall guys to cover up the grand crime.
The TPLF security agency and the so called Federal Police that boost to find an e-mail communication between Ethiopians as ‘terrorists’ plot simply missed the crime of TPLF forcing out 1000s of Ethiopians from their farms and homes in broad daylight and transported 100 of miles away. The sorry Prime Minster, instead of going to the people in person to see first hand the condition of their displacement by TPLF goons he blame low level regional officials in a staged address in the Parliament while TPLF run Media and surrogates are no where to be found or blame the victims like the witch of Media Mimi Sebhatu did. Where is the fast moving Binyam Kebede of EthiopiaFirst that crisscross continents to cover up for Woyane when real journalism is needed uncovering ethnic cleansing of Ethiopians by his beloved regime? He might as well change his slogan as WoyaneFirst and live in shame.
The bucks stop on the top ringleaders of TPLF and associates.  Ethiopians must be prepared to take TPLF ringleaders and accomplices in international venue for grand corruption, atrocity and heinous human right violation including ethnic cleansing. The Woyane establishments and their corrupt associates around the world haven’t seen real challenge yet.  People must realize better organization and identification the sources and the methods of the crimes is needed to zero-in on the real villains than the small time stooges that are the scapegoat of TPLF.
TPLF sympathizers would also be advised to stick with their people than attempting to cover up the illegitimacy and the crime of Woyane. The rights of the people to be free to elect their leaders and ruled by their own government is not rocket science to understand. Splitting hair and coming up with all kinds of bizarre imagination to preserve Woyane’s is not going to save the regime.  Instead, it would incriminate those willing to conspire in the cover up of the crime.
In my opinion the recent article by Professor Tecola Hagos titled ‘Breaking Political Barriers and Political Taboos is an example of diversion at its best. It would have been the right message if only the title matches the continent of the article. Unfortunately, the good Professor is dancing around with TPLF mantra; fixated with ethnic Federalism than addressing the burning issue of illegitimacy and the crimes of the regime. Though he have all the rights to rap his ethnic identity to define his Ethiopiawinet most Ethiopians can’t be defined by TPLF’s manufactured Ethnic Federalism or the parties it brought with it, including SEPDM he claim to admire. He states:
I believe what we have now in SEPDM is a game-changer political organization that is also the best miniature representative of Ethiopia due to the fact that it is a multi-ethnic organization. Moreover, there seems to be no other agenda in the politicks or the ethos of that multi-ethnic aggregation other than the fact of “Ethiopiawinet”. I am much more comfortable in the leadership of such organization leaders due to the fact that they are already functioning quite well in a multi-ethnic oriented structure fully aware of the reality of Ethiopia’s historic constituents. The former APDM (the current ANDM) would have evolved in that same dynamic change had it not been forced to adopt an ethnic identity by Meles Zenawi and his TPLF supporters when it associated itself with the TPLF by breaking away from the EPRP. You can still see some of its lost features in its Central Committee members, such as Bereket Simon who is born of an Eritrean family who chose to fight for Ethiopia as a whole as a member of the EPRP when he could have easily joined the EPLF. In fact, that is why I still have grudging respect for that political choice he made at such a young age in the 1970s. Nevertheless, almost all of the people of Ethiopia, with very few exceptions do understand the destructiveness ethnic based politics.
The entire article and the timing speak for itself. But, the good Professor seems to miss TPLF’s instigated Ethnic Federalism is a hoax its time has passed and buried and there is no back door to it. We expect more from a supposedly high caliber Professor than from an average Joe to teach us there is more to Federalism and development than what fits TPLF’s ethnic agenda and pocket book. To the minimum, the good Professor should join the opposition publicly to demand TPLF to get out of the massive corruption businesses on the back of Ethiopians and surrender its holding. He should call for FECC to arrest the ringleaders of TPLF’s grand theft of the nation. He should demand independent international body and Media to investigate ethnic cleansing and atrocity led by TPLF’s special security agency.
Instead, he skirted the issue of representation as ‘multi-ethnic aggregation’ as if Ethiopians are different species of sheep and as he did with corruption in his previous article “Behind the Facade of Corruption in Ethiopia and what the Government ought to do” claiming corruption is not an exception in Ethiopia, as if the ruling TPLF regime is only engage in a typical corruption of similar regime elsewhere.
Whether he is insulting our intelligence to cover up the scope of TPLF crimes or he is simply ignorant of the facts like most people are is hard to say. But, the fact he as a professional refused to call for transparency and dig deeper to find out the enormity of TPLF’s crime that would disqualify it to govern says a lot.
Also, the professor’s romance with one of the three TPLF surrogate parties is too convenient to convince me; claiming ‘SEPDM is a game-changer’…and that he is ‘much more comfortable’ with a surrogate party of TPLF’ security agency. He further goes to tell us his admiration of the notorious propaganda Minster ‘Berket Simon who is born of an Eritrean family choice to fight as Ethiopian’ ignoring his fraudulent representation of the Amhara Region where he doesn’t belong in violation of TPLF’s instigate Ethic Federalism the Professor seems to admire. What does Berket’s love for Ethiopia have to do with what he does?

I highly recommend the Professor and all Ethiopians to learn from an extraordinarily brave and bright young EthiopianBrave and bright young Ethiopian from Jijiga by the name Abdulahi Hussein. from Jijiga by the name Abdulahi Hussein. His farsightedness to see the danger of TPLF and its hand picked President of the ‘Somalia Region’ with no formal education raising havoc on our people. Abdulahi not only teaches us bravery at its best to defend our people and country but, show us his moral superiority. How is it a young Ethiopian see the best in Ethiopiawinet when Woyane apologists see gloom and doom in our unity and willing to preserve it? Truly, here is one Ethiopian gentleman we should be proud and role model for the generation to come for bright future to come. Frankly, he is the one that deserves a Foundation for leadership not Melse Zenawi.
In contrast, apologists of the fake Ethnic Federalism of the regime want to have their cake and eat it too. Either they are as confused as the regime itself or conspiring with the regime’s bigger mission to fit every thing to the Woyane dream of colonizing Ethiopians. Both ways, they are losers; as individuals, as citizens, as professionals, as Ethiopians and as human beings.
To his credit, the Professor doesn’t deny the many flaws of the TPLF regime. But, it is not clear whether he is teasing us in things that don’t matter to cover up the bigger issue or he is genuinely ignorant to see only the flaws he knows and considers to be important in his eyes. Regardless, he seems convinced the regime is legitimate enough and crimes free enough not to vacate power but only requires cosmetic change. The problem with that argument is the law maker, the judge and the prosecutor and the informer of the national affair happens to be only TPLF itself. Under such scenario, any one can understand if the argument came from an average Joe. But, coming from a ‘high caliber’ Professor not only neglects professional duty but, it is in bad taste.
The question is, are our learned men and women going to elevate us to the higher ground or keep us down; pandering for one form of tyranny or another (ethnic or otherwise) to indulge themselves with what their chosen tyranny offers in defiance with the rule of law, democracy and the rights of our people to be free?
Consciences are building among average Ethiopians the atrociously corrupt and self declared illegitimate minority regime isn’t going to decide the fate of our people, period.  By choice or by force Woyane will surrender for the will of the people and accept its faith. The sooner that reality sinks in the head of the Professor or all of us the better everyone will be. Therefore, what is ‘comfortable’ to the Professor or any other that believes cosmetic change to the rotten TPLF’s Ethnic Federalism would preserve the self declared minority tyranny and mitigate the illegitimacy and the crimes of the regime against the people of Ethiopia is pipedream.
The best the Professor and his elk should ask for is how to live with democracy in their chosen ethnic region if they believe their ethnicity defines their Ethiopiawient. But, what they can’t do is recruit worthless individuals from one ethnic group or another of their liking to undermine Ethiopians that rightly consider the regime illegitimate or attempt to define Ethiopians by our ethnicity to suite Woyane under fake Ethnic Federalism. Moreover, as one of the drafter of the failed TPLF/EPDRF Ethnic Federal constitution, the Professor should be the last person to argue ‘breaking political barrier and taboos’ and attempt to salvage the regime. It is better left to other Ethiopians that have noting to do with TPLF or any other party that caused havoc on the people of Ethiopia. After all, we hope the Professor is aware of the concept of Conflict of Interest. We can’t be the judge, the jury and the prosecutor of what we do and expect to have creditability.
Only delusional individuals and groups believe their own illusion to make something out of nothing. The falsification of history to undermine Ethiopiawinet might have served the short term political and economical end of TPLF and its associates but, it would be wise to tell the truth now or never. The more one skirt the truth to cover up for TPLF and its deviant agenda the more s/he will be responsible for the crimes against the people of Ethiopia.
In conclusion, Ethiopians showed our extreme tolerance for the most egregious crime against our people and nation by Woyane and associates. What Woyane and its apologist doesn’t seem to understand is Ethiopians survived Woyane’s onslaught with honor. Can Woyane survive Ethiopians unity and our demand for democracy?
Instigating conflicts among Ethiopians may have worked to get Woyane where it is now or to prolong its rule but, it wouldn’t stop Ethiopians from coming together after Woyane. If Ethiopians from all walks of life coming together as one people and one nation frightens Woyane and its stooges they might as well renounce their nationality and look for a place that accommodate their deviant behavior. After all, historically Ethiopians always came together when their survival is in question by foreign enemy. Woyane would be the first domestic enemy to find out our survival doesn’t distinguish domestic from foreign enemy.
As the brave Ethiopian journalist Esknder Nega said the truth will prevails, so Ethiopia

May 16, 2013

ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል

ህወሃት በእሱና በራሱ ጉጅሌ አባላቶቹና ሚዲያዎቹ “በአገራችን ታሪክ ያልታየ ክስሰት በዋናነት ዜጎች በአንድነት፣ ከድህነት በማውጣት በደስታ የተሞላ ህይወትን ለማምጣት የኢኮኖሚ እድገታችን እያደገ ነው ይለናል” ይህ በሬዲዮ አዲስ አበባ፣ በሬዲዮ ኢትዮጵያ እና በሬዲዮ ፋና ብቻ ነው። ይህ ውሸት እንደተጠበቀ ሆኖ አዲሱ የለውጥ ምእራፍ ደግሞ የወያኔ ቡችሎች በየጊዜው ከህወሃት መጋረጃ በስተጀርባ ያለውን የተደበቀውን እውነት ወይም ግንቦት 7 ሲል የነበረውን የሚያረጋግጡ መረጃዎችን መስማት መጀመራችን ነው።
ህወሃታዊ መነቃቃትን ለማምጣት ደካሞችንና ለሆዳቸው ያደሩ ባለስልጣናቱን ሰብስቦ ስለ እድገት ጎዳናና ኃይል የሚያመረቁ ትሩፋቶችን በሚዲያዎቹ ያስነግራል። የዜጎችን የስነ ልቦና ውድቀት በከፍተኛ ደረጃ የሚፈልገው ህወሃት ባሪያዎቹንና አገልጋዮቹን በጥቅማጥቅም በማሸነፍ እውነትን ይደብቁለት ዘንድ ሁሌም ሙከራ ያደርጋል። አንዱም ተሳክቶለት አያውቅም እንጅ።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት የሆነው ህወሃትና የእነሱ ተላላኪ ወያኔዎች ጦር ሰብቀው፣ መሣሪያ ወድረውና በከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲያቸው ተጠቅመው ሀገሪቷን እና ህዝቡን ከፋፍለው በዘር ካርድ ተጫውተው የስልጣን እድሜያቸውን ማራዘም ተቀዳሚ አጀንዳቸው እንጂ መቼም ስለ ኢትዮጵያ አንድነትና እድገት አስበውም አልመውትም አይውቁም፡፡ የሶማሊያው ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ሙሃመድ የተናገረውም ይህንኑ ነው ተደጋገመ እንጂ።
የከፋፍለህ ግዛ የጫካ ፖሊሲያቸውን ተጠቅመው ሀገሪቷን እንደተቆጣጠሩ ለመዝለቅ በማስብ የግል የሥልጣን እርካታቸውን ለመጠበቅ ብቸኛ ስልት ሆኖ ያገኙት የሶማሊያ ፕሬዝዳንቱ እንደሚሉት ለሶማሊያው “አማራው፣ ኦሮሞው፣ ጉራጌው፣ አፋሩ ከተባበሩ ለሶማሊያ አይመቹም። ስለዚህ ህወሃትን ደግፉና እነሱን ውጉ፤ አማራውና ኦሮሞው መቼም አይስማሙም።” በዚሁ ያልተገራ አንደበታቸው ደግሞ የህወሃቶቹ የአማራ ጎጅሌ ተላላኪ ባለስልጣናት አማራ ክልል ይሄዱና “የሶማሊያና የኦሮሞው ሰርቶ አደር ህዝብ የእንገንጠል ጥያቄ ሊያቀርቡብህ ነው” ይላሉ፤ ለባለታሪኩ የኦሮሞ ህዝብም ሄደው “አማራ ሊገዛችሁ ነው” የሚል ቆሻሻ የዘርን ክፍፍል መሰረት ያደረገ ፖለቲካዊ፣ ያልበሰለ ራእያቸውን ለማስፈጸም ሺ ምላስ ይሆናሉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ በረዥም የታሪክ ዘመኑ ውስጥ በተደጋጋሚ የሚፈታተኑትን ጠላቶቹንና ተላላኪዎቹን የተንኮል አጀንዳ ቀድሞ ስለሚያውቅ ልዩነቱን አስወግዶና ቅድሚያ ለሀገሩ፣ ለአንድነቱ ሰጥቶ መሰሪ ጥቃታቸውን በማክሸፍና በማኮላሸት ረገድ ከፍተኛ ሚና ያለው ህዝብ፣ በእነዚህ የህወሃት/ኢህአዴግ የዘር ድብቅ አጀንዳ አይንበረከክም አይከፋፈልም። አማራውም፣ አሮሞውም፣ ጉራጌውም፣ ትግሬውም፣ ቤንሻንጉሉም፣ ደቡቡ አንድ ነው። ተከባብሮ ያለ እና የሚኖር ታላቅ ህዝብ በመሆኑ ከጠላቶቹ ህወሃት ከሀገር አጥፊ ዘረኞች የሚመጣበትን ቀድሞውንም ጠንቅቆ ያውቀዋልና አይገርመንም፡፡
ባለ ብዙ ምላሱ የወያኔ መንግስት መርዶ ነጋሪ እየሆኑ ያስቸገሩት ግለገል ፍየሎች የዚሁ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ በሽታ ተጠቂ (victim) ናቸው። ብቻቸውን በተለቀቁ፣ ተንፍሱ በተባሉ ጊዜ በጀሮዎቻቸው የሚሰማቸው የተደበቀውን የእውነት ያለህ ጩኸት ነው የሚናገሩት። የህዝባቸውን በደል፣ ሰቆቃ እና የወያኔን እውነተኛ ገፅታና ያለበትን ተጨባጭ የዕድገትና የልማት ሁኔታ ያወጣሉ፣ ይናገራሉ።
ፕሬዚዳንቱ እፎይ ብሎ አዩኝ አላዩኝ ሳይል ያደረገው ንግግርም “ እኛ እንዳደግን ፣ ጥሩ ደረጃ ላይ እንደደረስን ተደርጎ በየጊዜው የሚቀርበው ሪፖርት ፍጹም ትክክል ያልሆነ ውሸት ነው። አሁን በእጄ የያዝኩት ሪፖርት እውነት ስለመሆኑ እርግጠኞች አይደለንም፤ ከአሁን በፊት ይቀርቡ የነበሩ ሪፖርቶችም እንዲሁ ናቸው። ግምገማ ለማለፍ ተብሎ በውሸት የተሞሉ በቁጥር የታጀቡ የውሸት ሪፖርቶች ናቸው የሚቀርቡት እንጅ እኛ በድህነት አረንቋ ውስጥ ነን ” ብሏል። የሚገርመው ፕሬዝዳንቱ ይህንን ውሸት ህዝብ የሚያውቀው አልመሰለውም፤ ለሁሉም በርታ አይዞህ ሆድ አይባስህ እኛም እያልን ያለነው ይህኑን አይን ያወጣ ውሸት እንታገለው ነው የምንለው።
አቶ አብዲና ሌሎችም ለሆዳችሁ ያደራችሁ ባለሰልጣናት ራሳችሁን ቀይሩ ውስጣችሁን አውሩ በታሪክ ተጠያቂ አትሁኑ፣ ህሊናችሁን አዳምጡ እንጂ ለህዝብ ጠላት ለሆነው የህዝብ ድጋፍ ከሌለው ለህወሃት ፍርፋሪ በማደር ሀገራችን ለማጥፋት ሁሌ ከሚያስቡ ከህወሃት ቡድኖች ጋር አብራችሁ ወገንን ማታለልና በዘር ካርድ መጫዎት ይብቃችሁ። የዲሞክራሲ ሃይሉን ጎራ ተቀላቀሉ፣ መረጃ አቃብሉ።
የወያኔ እውነተኛ ገፅታ ራሳቸውም እንደሚያረጋግጡት ይህ በመሆኑ፣ በየቦታው ዜጋን በማፈናቀል ህዝብ በሀገሩ ስደተኛ እንዲሆን ፊትም የጀመረውን ድብቅ ሥራ አማራውን በማሰደድ ያላቸውን ጥላቻ በእጥፍ በማሳደግ በርካታ አባዎራዎችን በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ህይዎታቸው ጉስቁል እንዲሆን እያደረጉ ነው። ታዲያ ይህን እውነት እየሰማን እሰከ መቼ እንተኛ ይሆን? ግንቦት 7 ንቅናቄ ተነሱ ኑ! ተቀላቀሉን ብለናል።
ወያኔን ማስወገድ የሁሉም ብሄሮች ጥቅም ነው። ሁሉም ህዝብም፣ ሁሉም ፓርቲ በወያኔ መወገድ ይስማማል። ታዲያ ማን ያስወግደው? ከጥንት ጀምሮ ብዙ ትውልድ ሀገሩን ከውስጥና ከውጭ ወራሪ ለመታደግ በዚህች የኢትዮጵያ ምድር ላይ መሰዋእት ከፍሏል፡፡ ወጥቷል፣ ወርዷል አልፏል፡፡ የሰው ልጅ ተፈጥሮ የለገሰችውን የቅብብሎሽ ህግ ተቀብሎ ለነጻነቱ፣ ለማንነቱ መከበር እምቢተኝነትን ሲቀባበል፣ ሲተካካ ኖሯል፡፡ ወደፊትም ይኖራል፡፡ በዚህ የአሁኑ ሂደት ደግሞ እኛ ባለተራዎች ነን እማማ ኢትዮጵያን ከህወሃት መንጋዎች መንጋጋ ፈልቅቆ የማውጣት! ስለዚህ ለነጻነታችን ከሰማይ የሚወርድ ምንም አይነት መና የለም። እኛው ለእኛው ለራሳችን መሰዋእት ከፍለን ወያኔን እናስወገድ ዘንድ ትግሉ፣ ወቅቱ አሁን ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

5 ሰዓታትን በቀድሞ ማዕከላዊ ፖሊስ (ፍሬው አበበ በአዜብ መስፍን ክስ ከተመረመረ በኋላ የፃፈው)

ሰኞ ዕለት ከሰዓት በኋላ የተንቀሳቃሽ ስልኬ አንጫረረ፡፡ ሳነሳው ለስላሳ የሴት ድምጽ ፍሬው መሆኔን ማረጋገጫ ጠይቃኝ ስታበቃ
የቀድሞ ማዕከላዊ ስለምፈለግ ደረስ ብዬ መምጣት እችል እንደሆን በፍጹም ትህትና ጠየቀቺኝ፡፡ በዕለቱ እንደማይመቸኝ፤ ዕረቡ
ጠዋት ግን መገኘት እንደምችል ለደዋዬ ነግሬ ሰልኩን ዘጋሁ፡፡ እንግዲህ በፕሬስ ክስ ጉዳይ ለፖሊስ ቃሌን ስሰጥ ይኸኛው
ለአራተኛ ጊዜ መሆኑ ነው፡፡ ከቀድሞዎቹ ሶስት ክሶች አንዱ የስም ማጥፋት ሲሆኑ ሌላኛው በተሰረዘ ፈቃድ ሰርታችሃል፣ ሌላው

ደግሞ ያለፈቃድ ጋዜጣ ታትማላችሁ የሚል ነበር፡፡ በአጋጣሚ ሁለቱ የቀድሞ ክሶች ከፖሊስ ያላለፉ ሲሆን አንደኛው ማለትም
የኒቲ የኒቨርሲቲ ያሳትመው የነበረው “ኤቢቢአይ ዊክሊ” የተባለው ጋዜጣ በተሰረዘ ፈቃድ ሰርታችሃል በሚል ክስ
ከተመሰረተባቸው 14 ያህል ሰራተኞች አንዱ ሆኜ አንድ ዓመት ተኩል ጊዜያት ያህል ፍ/ቤት ከተመላለስኩ በኋላ እኔን ጨምሮ
13 ተከሳሾችን ፍ/ቤቱ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ይሰናበቱ ሲል ውሳኔ በመስጠቱ ነጻ መሆን ችያለሁ፡፡ (እዚህ ምድብ
ውስጥ የአዲስ ነገሩ አብርሃም በጊዜው ይገኝበት ነበር)
ዛሬ ረቡዕ በጠዋት ማልጄ በመነሳት ቁርስ ቀማምሼ ወደተጠራሁበት የቀድሞ ማዕከላዊ ፖሊስ 3፡15 ሰዓት ላይ ደረስኩ፡፡ ማልጄ
መነሳቴ ወድጄ አልነበረም፤የሄድኩበትን የምርመራ ጣጣ ከምሳ በፊት ባጠናቅቅ በሚል ጉጉት ነበር ፤አልሆነም እንጂ፡፡ መርማሪዬ
ትሁት ሴት ፖሊስ መሆኑዋ ጭንቀቴን ለጊዜውም ቢሆን እንድረሳ ረድቶኛል፡፡ ያው የተለመደውን አሰልቺ ቅጽ መሙላት ግን
የግድ ነበር፡፡ ሙሉ ስም፣አድራሻ፣የእናት ሙሉ ስም፣የአባት ሙሉ ስም፣የትውልድ ቦታ፣ የትውልድ ቦታ አድራሻ፣ብሔር፣የባለቤቴ
ስም፣አድራሻ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ስም፣የት/ቤቱ አድራሻ፣የተማርኩበት ጊዜ፤የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ስም፣አድራሻ፣
የተማርኩበት ጊዜ፣ የከፍተኛ ትምህርት የተማርኩበት ዩኒቨርሲቲ ስም፣አድራሻ፣የተማርኩበት ጊዜ፣የቀድሞ መ/ቤት ስም፣የነበረኝ
ኃላፊነት፣የነበረኝ ደመወዝ መጠን፣ የአሁን መ/ቤት ስም፣ያለኝ ኃላፊነት፣ያለኝ የደመወዝ መጠን፣ የጋብቻ ሁኔታ፣የልጆች
ብዛት፣ዕድሜያቸው፣አጠቃላይ ክሱ እና በክሱ ላይ ያለኝ ምላሽ፣ የተጠረጠርኩበትን መፈጸም አለመፈጸሜን (የእምነት ክህደት
ቃል) ወዘተ….እጅግ አድካሚ ዶሴ ተሞላና ጨረስኩ ስል አሻራና ፎቶግራፍ መነሳት የግድ ነው ተባልኩ፡፡ ከዚህ ቀደም
በተደጋጋሚ ሰጥቻለሁ ብልም ሰሚ አልነበረም፡፡ እዚያም የእያንዳንዱ ጣት አሻራ(የግራ የቀኝ) ፣ ፎቶ ፊትፊት በግራና ቀኝ መነሳት
ግድ ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ግን በፕሬስ ተፈጸመ ተብሎ በአንድ ሰው በቀረበ አቤቱታ መነሻነት ገና ለገና ተጠርጣሪ ነው የተባለው ፕሬስ
ዋናአዘጋጅ የመጀመሪያዋ ቀላል ፈተና መሆኑ ነው፡፡
ፖሊስ ቃል ከመስጠቴ በፊት ሁለት ጥያቄዎች እንዲመለሱልኝ ለመርማሪዬ ጥያቄ አቀረብኩኝ፡፡ አንዱ የተከሰስኩበት ጉዳይ እና
ከሳሼ ማን እንደሆነ ነበር፡፡ የተከሰስኩበት ጉዳይ በቀድሞው ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን
ከቤተመንግስት አለመውጣታቸውን ጠቅሰህ ጽፈሃል፣በዚህ ስም አጥፍተሃል የሚል ይዘት ያለው መሆኑ ተነገረኝ፡፡ ዜናው
የተሰራው በአበሻ አቆጣጠር መስከረም 30 ቀን 2005 ዓ.ም ሲሆን በጠቅላው ወደስምንት ወር ገደማ ሆኖታል፡፡

የዜናው ይዘትም በአጭሩ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከቤተመንግስት አለመውጣታቸውን በአንድ በኩል በሌላ በኩል በወቅቱ ከተሾሙ
19 ቀናት የሞላቸው ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ መኖሪያ ቤታቸው ከሚገኝበት ሳር ቤት አካባቢ በየዕለቱ ትራፊክ እያዘጉ
በመውጣትና በመግባት ላይ መሆናቸው፣ የአካባቢውን ህብረተሰብ የመንቀሳቀስ ነጻነት ላይ ችግር መፍጠሩን፣ለደህንነታቸውም
ቢሆን አስጊ መሆኑን፣ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ቤተመንግስቱን እንዲለቁ በተደጋጋሚ ተጠይቀው ባልታወቀ ምክንያት ፍቃደኛ
አለመሆናቸውን የሚያትት ነበር፡፡ ዜናውን ስንሰራው በትልቁ ታሳቢ ያደረግነውና እንደጋዜጠኛ ሙያዊ ነጻነታችን ተወጥተኛል
ብለን የምናስበው የጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ስራቸውን ማከናወን በምንም መልኩ ተቀባይነት
ያልነበረውና ደህንነታቸውንም በእጅጉ ለአደጋ ያጋለጠ የመሆኑ ጉዳይ ነበር፡፡ የዚህ ዜና መውጣት በአገር ውስጥና በውጪ
መነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ ሆኖ በመቆየቱ ወ/ሮ አዜብ በክብር ወደተዘጋጀላቸው ቦታ እንዲዛወሩ፣አቶ ኃ/ማርያምም
ወደቤተመንግስት እንዲገቡ በማድረግ ረገድ ሁለቱንም ወገኖችን የጠቀመ ውጤት አስገኝቷል ብለን እናምናለን፡፡ በዚህ ዜና
መሸለም እንጂ መጉላላትና ክስ ይቀርብብናል ብለን አስበንም አናውቅም፡፡
ሌላው መርማሪዬን የጠየኳት ጉዳይ ከሳሼ ማን ነው የሚል ነበር፡፡ ይህን ጥያቄ በቀጥታ ለመመለስ አልፈለገችም፡፡ምናልባትም
አለቆችዋ እንዳትነግር አስጠንቅቀዋት ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ ግን እንደተከሳሽ ቃሌን ለመስጠት ቢያንስ ከሳሼ ማን እንደሆነ የማወቅ
መብቴ ሳይከበርልኝ ቀርቷል፡፡ በድፍኑ “ከሳሽ ፖሊስም ሊሆን ይችላል” ተብዬአለሁ፡፡ በስም ማጥፋት ክስ ጉዳይ ግለሰብ ከሆነ
ራሱ በሚያቀርበው አቤቱታ፣የመንግስት ሹመኛ ከሆነ በዓቃቤ ሕግ በኩል ክስ ሊቀርብ እንደሚችል ያለውን ድንጋጌ አንስቶ
መከራከር እዚህ ቦታ ላይ ዋጋ አልነበረውም፡፡ ያም ሆነ ይህ ከሳሼን የማወቅ መብቴ ተከልክዬ እነሆ ቃሌን ለመስጠት በቃሁ፡፡
በዚህ ሁኔታ ጠዋት 3፡15 ገደማ የቀድሞ ማዕካዊ የገባሁ የአምስት ሺ ብር ዋስ እስካቀርብ ድረስ የቁም አስረኛ ሆኜ ከቀኑ 8፡30
ሰዓት ገደማ ግቢውን ለቅቄ ወጥቻለሁ፡፡
ፍሬው አበበ
የሰንደቅ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ

Etiopiske redaktør avhørt i løpet historien om Meles 'enke


CPJ) New York, 15 mai 2013-etiopiske politiet i Addis
Abeba avhørt en redaktør i flere timer i dag i forbindelse med
en historie publisert i oktober om enken til den avdøde
etiopiske lederen Meles Zenawi, ifølge nyhetsrapporter.
Offiserer i den etiopiske føderale politiet Crime Investigation
Department avhørt Ferew Abebe, tidligere redaktør-in-chief
av privat amharisk-språk ukentlig Sendek , om hans kilder for
den 10 oktober 2012, historien som sa Azeb Mesfin, Meles
'enke, hadde nektet å forlate den etiopiske nasjonale sted
nesten to måneder etter at statsministerens død , sa lokale
journalister. Historien, som ble mye dekket i lokale og internasjonale presse, sitert
offentlige kilder som sier at Meles 'etterfølger, Hailemarian Desalegn, var ikke i stand til å
leve i palasset.
Ferew nektet å identifisere sine kilder og sitert etiopiske lover som garantert rettighetene
til en journalist å holde kilder hemmelig, sa lokale journalister. Ifølge den etiopiske
straffeloven , kan en domstol tvinge journalister til å avsløre sine kilder hvis en forbrytelse
har blitt begått mot den konstitusjonelle orden, nasjonale forsvar, eller sikkerheten til
staten, som utgjør klar og overhengende fare.
Politiet utgitt Ferew på en obligasjon på 5000 birrs (US $ 265) i påvente av videre
etterforskning, ifølge de samme kildene.
På mandag politiet også innkalt en nestleder redaktør for Sendek å spørre ham ut om den
samme historien, sa lokale journalister. Han ble løslatt uten tiltale.
"Etiopisk politiets krav om at Ferew Abebe avsløre sine kilder for en historie publisert syv
måneder siden, er trusler og tramper på den beskyttelse som gis til journalister i henhold
etiopisk lov," sier CPJ-Afrika Advocacy koordinator Mohamed Keita. "Vi oppfordrer
myndighetene til å forlate sine langvarige mønster av vindicative forfølgelse av journalister
som stiller spørsmål om saker av offentlig interesse, for eksempel okkupasjonen av en
offentlig bygning av den tidligere førstedame."
Minst sju journalister er bak gitter i Etiopia, noe som gjør landet den nest største
fangevokteren av journalister i Afrika, ifølge CPJ forskning. Etiopia stier bare Eritrea blant
Afrikas verste fangevokterne av journalister, viser CPJ forskning.

May 15, 2013

የባህርዳሩ ጭፍጨፋና የዜናው አዘጋገብ


ECADF – በባህርዳር ከተማ አንድ የፌደራል ፖሊስ (ወያኔ) ንጹሃን ዜጎችን እንደጨፈጨፈ የሀገሬው ነዋሪዎች እየተናገሩ ነው። ማንኛውም ጋዜጠኛ ይህንን ለማጣራት የሚከብደው አይደለም። በርካታ መረጃዎች ድርጊቱ ከተፈጸመበት ምሽት ጀምሮ ሲደርሱን ቆይተዋል። የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) አሳቃቂውን ጭፍጨፋ በተመለከተ በቀጥታ የሀገሬውን ነዋሪዎች ማነጋገር ችሏል።
Bahirdar, Ethiopia tragedy
በጭፍጨፋው ለተገደሉ የባህርዳር ነዋሪዎች የፍትሀት ጸሎት ሲደረግ
ይህ በዚህ እንዳለ አንጋፋው የኢትዮ-ሚድያ ድረ-ገጽ ግድያውን የፈጸመው “Ethiopian Unity and Freedom Force (EUFF)” (የኢትዮጵያ አንድነትና የነጻነት ሀይል) በመባል የሚጠራ የሽምቅ ተዋጊዎች ቡድን ነው በማለት ዘግቧል። ድረ-ገጹ ዘግይቶ እንዳደሰው ዜና ከሆነ ደግሞ ከሟቾቹ መካከል ሁለት ከፍተኛ ባለስልጣናት ይገኙበታል (የተባሉት ባለስልጣናት በስም አልተጠቀሱም) ኢትዮ-ሚድያ የመረጃውን ምንጭ ያደረገው ይህንኑ ግድያውን እንደፈጸመና ሀላፊነቱንም ወስጃለው ያለውን ቡድን ነው። ዘገባው በከፊል እንዲህ ይነበባል፣
The Ethiopian Unity and Freedom Force (EUFF), a rebel group that has been targetting the ruling EPRDF party officials and their businesses, claimed responsibility for the deadly attack. EUFF said the names of the officials killed and wounded would be released soon.
ለመሆኑ “EUFF” በመባል የሚታወቀው የአርበኞች ቡድን ማን ነው? ተዋጊዎቹስ እነማን ናቸው? የቡድኑን ቃል-አቀባይ መድረስ ይቻል ይሆን? ይህ ቡድን የራሱ የሆነ ልሳን አለው? ድረ-ገጽ ይኖረው ይሆን? በርካታ ጥያቄዎችን ማንሳት የሚቻል ቢሆንም ማን መልሱን እንደሚመልስ ማወቅ ግን አስቸጋሪ ነው።
በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው እስካሁን ከ16 በላይ ሰዎች ከወያኔው ታጣቂ በተተኮሰ ጥይት ተገድለዋል። ምናልባትም ቆስለው ከተረፉት መካከል የሚሸነፉ ካሉ ደግሞ የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ ይችላል።
Bahirdar Ethiopia 18 killed
ወንዝ ዉስጥ ገባ፣ ከዚያም ደግሞ ተያዘ የተባለው ገዳይ
የወያኔ/ኢህአዴግ ባለስልጣናትና በቁጥጥራቸው ስር ያሉ የመገናኛ ብዙሃን ጉዳዩን አስመልክቶ የሚያሰራጯቸው መረጃዎችም እንዲሁ ግራ የተጋቡና ወይንም ደግሞ ሆን ብለው ግራ ለማጋባት የሚመስሉ አይነት ናቸው።
አያሌው ጎበዜ የክልሉ ፕሬዝዳንት (አብዛኛው ህዝብ ስልጣኑ ከተላላኪነት ያለፈ አይደለም ብሎ ያምናል) ሰላማዊ ሰዎችን የጨፈጨፈው የመንግስታቸው አንጋች እንዳልተያዘና በጸጥታ ሀይሎች እየታደነ መሆኑን ሲገልጹ፣ ሌላኛው ሹም ደግሞ ቀበል አድርጎ “ገዳዩ ሊያዝ ሲል ዘሎ አባይ ወንዝ ውስጥ ገባ” ይላል። እንዲህ እንዲህ ሲሉ አረፋፍደው በመጨረሻ ፊቱ በደም የተበከለና የፌደራል ፖሊስ ዩኒፎርም የለበሰ አስክሬን ቃሬዛላይ አድርገው “ይሄው ገዳዩ አሁን ተገኘ” በማለት ደመደሙት።
ይህ ሁሉ መዘባረቅ እና ማዘበራረቅ ለምን አስፈለገ? እወነተኛ የህዝብ ወገን ጋዜጠኞች ሰላማዊ ዜጎች በቄያቸው ለምን እና በማን እንደተጨፈጨፉ ያሳውቃሉ ብለን እናምናልን።

ዱላ መመከት ያቃተው አማራ (ይኸነው አንተሁነኝ)


ግንቦት 14 2013
ሕወሃት ሀገራችንን በገልበቱ መግዛት ከጀመረበት ግንቦት 1983 ዓ/ም ጀምሮ ለቁጥር የሚያታክቱ ለመስማት የሚያስጨንቁ ብዙ ቁም ስቅሎችን ፈጽሟል። የራሱን የሕወሃትን ፓርላማ አንቀጽ 39ን በመመርኮዝ ራስን የመቻል ጥያቄ አቅርባችሗል ወይም ልታቀርቡ አስባችሗል በሚል ሰበብ ሰፊው የኦሮሞ ሕዝብ የስቃይ ዘመናትን አሳልፏል። ከእኛ ጋር አልተባበራችሁም ሁሌ ትወጉናላችሁ እየተባሉ ያለቁት የኦጋዴን ህዝቦች የትየለሌ ናቸው። በጥቅሉ  የልማት እቅዳችንን ትቃወማላችሁ፣ እኛን እንደ መንግስት አልተቀበላችሁንም፤ የምንላችሁን ለመፈጸም ዝግጁነት ይጎድላችሗል፤ ታሪካችንን የኢትዮጵያ ታሪክ ለማድረግ በምናደርገው ጉዞ መሰናክል እየሆናችሁብን ነው በሚሉና በሌሎችም ምክንያቶች በመላ ሀገሪቱ በሁሉም አቅጣጫ ሊባል በሚችል መልኩ ሕወሃት ሰቆቃዎችን ፈጽሟል።
በተለይ ከሁሉም በለይ ሕወሃት ለያዘው የመከፋፈልና ሀገር የማጥፋት እንቅስቃሴ በተቃራኒው በመቆም፣ ስለ አንድነት በመስበክና ለዚህም በጽናት በመታገል ችግር ፈጥሯል በማለት ወደ ስልጣን ከመምጣቱ በፊት ጀምሮ የፈረጀውን አማራውን ባጠቃላይ ከጫወታ ውጭ ለማድረግ ወይም አማራው አቋሙን ቀይሮ ሕወሃት ባሰመረው መስመር ገብቶ እንዲጓዝ ለማስገደድ ወያኔ ሕወሃት በዙ ስቃዮችን በአማራው ላይ በመፈጸም ላይ ነው። ምንም እንኳ ሕወሃት ዋናዎቹን ሁለቱን የእምነት ተቋማት የኦርቶዶክስ ተወህዶ ክርስትናንና የእስልምናን ተከታዮች ያለ ርህራሄ ያጠቃ ቢሆንም በተለይ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እየደረሰባት ያለው መጎሳቆል የአማራው መሸሸጊያ ዋሻ በሚል መሆኑ ሲታወስ ወያኔ ሕወሃት አማራውን ከሁሉም አቅጣጫ ለመመንጠር ምን ያህል እንደተዘጋጀና እየተገበረው መሆኑን ያሳያል።
ገና ወያኔ ስልጣን በያዘ ማግስት፤ በተለይ በአማራው ለይ የተፈጸመው የአርባ ጉጉና የበደኖ ጭፍጨፋ አንገብግቧቸው ጥያቄ ያነሱትና በሗላም የአማራው ድምጽ እንዲሰማ የፖለቲካ ድርጅት በማቋቋም አንቱ የሚያስብል ስራ የሰሩት እውቁ የህክምና ባለሙያ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ፤ ለሌላው ኢትዮጵያዊ ያለ አድሎ ሲሰጡት የነበረውን የህክምና አገልግሎት እሳቸው እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ባስፈለጋቸው ጊዜ በሕወሃት እንዳያገኙ ተነፍጓቸው የሞቱት ከአማራነታቸው በቀር ምን ምክንያት ሊሰጠው ይችላል።
ትምክህተኛና ነፍጠኛ የሚባሉ ቃላትን ከአማራው ሕዝብ ጋር በማያያዝ አማራው ለሚያቀርባቸው የመብት ጥያቄዎች ይህ የትምክህተኞች አመለካከት ነው። ወይም ደግሞ ነፍጠኛነት ነው በማለት ወያኔ ሕወሃት ቁጥራቸው የበዛ አማራዎችን መቷል አሳዷል የማሸማቀቅ ተስፋ የማስቆረጥና የተነገረውን ብቻ እንዲፈጽም የማስገደድ ከፍተኛ በደልም ሲፈጽም ቆይቷል።
የ1993ቱን የሕወሃት መሰንጠቅ ተከትሎ በወናነት ኢኮኖሚውን በመቆጣጠር ሂደት ስጋቶቼ ናቸው፤ የስኬት መንገዶቻቸውንም ለሌሎች አማሮች ያሰለጥናሉ ያላቸውን ቱጃር ቱጃር አማሮች በሙስናና የዚህ ወያም የዚያ ደጋፊ በሚል ሰንካላ ምክንያት ከሶና ወህኒ አውርዶ ከጫወታ ውጭ ማድረጉ ሲታወስ ሕወሃት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣተር አማራውን ከዚህ የስራ ዘርፍ ማስወጣት ቀዳሚው መሆኑን በመገንዘብ መሆኑ አሌ ሊባል አይችልም። ይህ ስቃይ የደረሰባቸው ነጋዴዎችም ቢሆኑ አማራነታቸው ካልሆነ በቀር ሙስና የተባለው በሙሉ ሕወሃት ሲከወን የቆየ በመሆኑ እነሱ ብቻ ሊወነጀሉ ባልቻሉም ነበር። ላለፉት ሁለት አመታት ሳይቋርጥ የቀጠለው በጉራ ፈርዳ የሚኖሩ አማራ ገበሬዎችን ከኢኮኖሚ ይዞታቸው የማፈናቀል ሂደት ሳይቀዘቅዝ፤ በቤኒሻንጉል ክልል የሚኖረውን አማራ ገበሬ የማፈናቀሉ ሂደት በተመሳሳይ ልክ እንደ ከዚህ ቀደሙ  ደን በማቃጠል ሰበብ በወያኔ ሹመኞች በስፋትና በተደራጀ መልኩ መቀጠሉ፤ የሕወሃት የማጣሪያ ወንፊት አማራውን ከየትኛውም የኢኮኖሚ ዘርፍ ለማስወጣትና ጥገኛ እንዲሆን ለማድረግ በተለይ ለአማራው ብቻ በልኩ የተሰራ ለመሆኑ ማረጋገጫ ነው።
የ1997ቱን ምርጫ ተከትሎ ከመጣው መተረማመስ ጋር በተያያዘ የወያኔን ጦር ሰራዊት ጨምሮ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎችና በየትኛውም ምስሪያ ቤት ቅንጅትን ምክንያት በማድረግ ማሰጠንቀቂያ የደረሳቸው፣ ከስራ የተባረሩት፣ የታሰሩትና የተሳደዱት በሙሉ ለማለት በሚያስደፍር መልኩ አማራነታቸው ያመጣባቸው ጣጣ እንጂ ሌላ ምንም አልነበረም።
አማራው በልማት ከሌላውም የኢትኦጵያ ክልል  በከፋ ሁኔታ ላይ ያለ መሆኑ እየታወቀ ወያኔ ሕወሃት ግን በልማት ወደ ሗላ የቀሩና በጦርነት የተጎዱ በሚሉ ምክንያቶች አማራውን በማስወገድ አድሏዊ የእርዳታና በጀት ፍሰት ሲያከናውን መቆየቱ። ከዚህም በከፋ መልኩ ወያኔ በግል ፓርላማው አማካኝነት ለአማራው የሚመድበውን በጀት ለመቀነስ በማሰብ ባለፈው ሀገራዊ የሕዝብ ቆጠራ ወቅት በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማራዎች ሳይጠፉ ሆን ተብሎ እንዲተፉ ማድረጉ አማራውን ከምንም ጥቅማጥቅም በማስወጣት በአማራነቱ እንዲያፍርና እንዲሸማቀቅ ለማድረግ ካልሆነ ምን ሊሆን ይችላል።
ከአራት ዓመታት በፊት ለሀገራችን ብርቅየ የተባሉ አማራ ጀነራሎችንና ባለሌላ መእረግ ወታደሮችን ጨምሮ፤ ብዙ የአማራ ምሁራንን ከግንቦት ሰባት የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ መመስረትና መንቀሳቀስ ጋር በማያያዝ፤ በአባልነትና በመንግስት ግልበጣ ያለ ማስረጃ ከሶ እስከ እድሜ ልክ እስራት በማስፈረድ የቀጣው በአማራነታቸው ስለመሆኑ ዘራቸው እየተጠቀሰ ሲሰደቡና ሲንቋሸሹ እንደነበር በወያኔው ፍርድ ቤት የተገኙት ፍርደኞች በሕዝብ ፊት የተናገሩት ጉዳይ ነበር። ይህ ሁሉ ሲፈጸም ታዲያ ግፉ እየወረደበት ያለው አማራውም ሆነ ሌለው ሰቆቃ ቀማሽ የሀገራችን ሕዝብ ገና ከጥልቅ እንቅልፉ አልነቃም የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም። ይህስ ካልሆነ የፍርሃት መንገዱ እስከ ምን ድረስ ነው? ብለው የሚጠይቁም ብዙዎች ናቸው።
የተለያዩ ምክንያቶችን በመጠቀም አማራው ከስልጣን፣ ከእርሻና ከንግድ ቦታው፣ ከስራና ከመኖሪያ ቤቱ፣ ከትምህርትና ከተለያዩ የአመራር ቦታዎች ገለል እንዲል የማድረጉ ሂደት ሰሞኑንም በወያኔ መንደር በስፋት እየተተገበረ ነው። በመሰረቱ አሁን ባለው የህወሃት አገዛዝ አንድን ባለስልጣን በሙስና መክሰስ ላፍ ካልሆነ በቀር ውሃ የሚቋጥር አይደለም። ምክንያቱም ትልልቅ የህወሃት ጀነራሎችና ዋና ዋናዎቹ ባለስልጣናት የእለት ከእለት ስራቸው ሙስና መከወን ነውና። ስለሆነም ሰሞኑን በሙስና ሰበብ ከስራ የተባረሩትም ሆኑ የታሰሩት የወያኔ ባለስልጣናት አንዳንድ አሯሯጮች ከተጨመረላቸው በቀር በአማራነታቸው ምክንያት የራሳቸው ድርጅት የበላቸው አማራ ወያኔዎች ናቸው።
ይህን ሁሉ ግፍ እየተቀበለ ያለው አማራ ታዲያ ሕወሃት በልኩ የሰራለትን የማጣሪያ ወንፊት የሚበጣጥሰው መቼ ይሆን? ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብስ ከወያኔ የተንኮል ወጥመድ ወጥቶ፣ እርስ ለርስ ከመወነጃጀልና ከመበላላት ጸድቶ ከከሕወሃት በተቃራኒ በመቆም የሀገር ተስፋነቱን ለመቼ ይቆጥበዋል? ሕወሃት እንደሁ የጥፋት እጁን አስረዘመ እንጅ አልመለሰም፣ ማስፈራራትና ድንፋታውን ቀጠለበት እንጅ አልበረደም፣ ጫካ እያለ በቀየሰው የእልቂት መልገድ ቀጠለ እንጅ የሕዝብ ጥያቄም ሆነ የሀገርና የዓለም ነባራዊ ሁኔታ እቅዱን እንደገና እንዲፈትሽ አላስገደዱትም። ስለሆነም አሁን በሀገራችን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ከቀጠልንና  አንዱ ሲጠቃ ሌላው ካልረዳ፤ በእኛ ጩኸት ወቅት ከጎናችን የሚቆም እንዳናጣ ያሰጋል። ከመቼውም ጊዜ በባሰ መልኩ ወቅቱ መተባበርንና አንድ ሆኖ መቆምን የሚጠይቅበት ወቅት ነውና በአንድነት እንነሳ።

May 11, 2013

ሠማያዊ ፓርቲና የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪው

SOURCE: ADDIS ADMAS

Saturday, 11 May 2013 11:37
ሠማያዊ ፓርቲና የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪው
Written by ናፍቆት ዮሴፍ

ሰማያዊ ፓርቲ ሠሞኑን በሠጠው መግለጫ፤ ከግንቦት 17 ጀምሮ መንግስት አልመለሳቸውም ባላቸው አራት ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ሠላማዊ ሠልፍ እንደሚያካሂድ አስታውቋል፡፡ ሠልፉ የሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት 50ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓል በሚካሄድበት ጊዜና ቦታ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በተጠራው ሠላማዊ ሠልፍና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ ከሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ከአቶ ይልቃል ጌትነት ጋር ያደረገችው ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ ሠላማዊ ሠልፍ ማድረግ መብት ቢሆንም እስከዛሬ እየተጠሩ ሳይካሄዱ የቀሩ ሠልፎች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ በቅርቡም ከግራዚያኒ ሀውልት መቆም ጋር ተያይዞ ያደረጋችሁት የተቃውሞ ሰልፍ አልተሳካም፡፡ እንደውም የሰልፉ መሪዎች ታስረው ነበር፡፡ አሁንስ የሚሳካላችሁ ይመስላችኋል? እንግዲህ እኛ ትግል ሥናደርግ መሠረታዊ መነሻችን መርሁ ነው፡፡ ሁለተኛ ህጉ ነው። በእነዚህ ሁለት ነገሮች ነው የምንመራው።

በሌላ በኩል ሠው በመሆናችን መሠረታዊ መብት አለን። ሀሣባችንን በነፃነት የመግለፅ መብታችንም በህጉ ተደንግጓል፡፡ ሥለዚህ ህገ-ወጦች የሚያደርጉትን ማስፈራራትና ዛቻ አይተን መብታችንን ከመጠየቅ ወደ ኋላ አንልም፡፡ ወደ ፖለቲካ ትግል የገባንበት ዋናው ነገር፣ ህገ ወጥ አሠራርን በመንቀፍና በመቃወም ህጋዊ ስርዓት እንዲመጣ ህዝብን እየመራን ለመታገል ነው፤ አላማችንም ይሄው ነው፡፡ ስለዚህ ኢህአዴግ ህገ-ወጥ ነገር ሲያደርግ ያንን ታግለን መቀየር እንጂ እሱ ስለማይፈቅድ ብለን መብታችንን አሣልፈን መስጠት የለብንም፡፡ እንደውም አለመፍቀዱ ነው የበለጠ እንድንታገል የሚያነሣሣን፡፡ ኢህአዴግ የሚሰራውን ህገ ወጥ ድርጊት በመታገል ህጋዊ አሠራር ለማስፈን እንጥራለን፡፡ ኢትዮጵያ የታሪክ፣ የነፃነት ተምሣሌት የሆነ፣ መንግስት የነበራት አገር እንደመሆኗ፤ እንዲህ አይነቱን ችግር በዚህ ጊዜና ዘመን ማስተናገድ እጅግ ነውር ስለሆነ ይህን ለማስተካከል ነው እንደ አማራጭ ሀይል ተደራጅተን ትግል የጀመርነው፡፡

ስለዚህ ምንም ጥርጥር የለውም እናደርገዋለን፡፡ እንደባለፈው አይነት እስርና መስተጓጐል አይገጥመን ብላችሁ ታስባላችሁ?

እኛ እንግዲህ እሱን አናውቅም፡፡ እኛ መብታችን ነው፤ ኢህአዴግ ወንበዴ ሆኖ ካሠረን ግን አንቺም መጠየቅ ያለብሽ እሱን ነው፡፡ እኔን መጠየቅ ያለብሽ ህገ-ወጥ ናችሁ ካልሽ ብቻ ነው፡፡ እኔ ህጋዊ ከሆንኩና የምጠይቀውም መብቴን ከሆነ፣ ያንን ህግ የሚጥሠውንና የህዝብን ሥልጣን ይዞ ያለአግባብ ሌላውን የሚበድለውን አካል ነው “ለምን እንዲህ ታደርጋለህ” ብለሽ መጠየቅ ያለብሽ፡፡ እኔ የሚገርመኝ ሚዲያዎች ለምን እንዲህ ዓይነት ጥያቄ እንደምትጠይቁን ነው፡፡ ምክንያቱም መብታችን እንደሆነ ታውቃላችሁ። ነገር ግን ለኢህአዴግ ጉልበተኝነት መብት ሠጥታችሁታል፡፡ ጥያቄዬን ግልፅ ላድርግልዎት፣ መብት የላችሁም ማድረግ አትችሉም እያልኩ አይደለም፤ ነገር ግን በቅርቡ የጠራችሁት ሠላማዊ ሠልፍ ተበትኗል፤ እናንተም ታስራችሁ ነበር፡፡

አሁንስ ከዚያ የተለየ በምን መልክ ልታካሂዱት አስባችኋል ማለቴ ነው…? እኔ እነዚህ ነገሮች የሚፈቱት በትግል ነው ባይ ነኝ፡፡ አንድ አምባገነን ፈቅዶ የሚሠጠው መብት አለ ብዬ አላስብም፡፡ በአለምም ታሪክ አምባገነን ለዜጐች ዴሞክራሲን ወዶና ፈቅዶ ሠጥቶ አያውቅም፡፡ ህዝብ በታሪኩ ለዘላለም ተሸንፎ የቀረበት አጋጣሚ የለም፡፡ ነገር ግን ይህ የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ የተከለከሉ መብቶቻችንን ማረጋገጥ የምንችለው በትግል ነው፡፡ መብታችንን ማስከበር የምንችለው ትግሉን አጠንክረን ስንቀጥል እንጂ እጅ አጣጥፈን በመቀመጥ አይደለም፡፡ ለሠላማዊ ሠልፉ መነሻ ያደረጋችኋቸው አራት ነጥቦች የቆዩ ናቸው፡፡ ከዚህ አንፃር ሠልፉን ከአፍሪካ ህብረት 50ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አከባበር ጋር ያደረጋችሁበት ምክንያት ምንድን ነው? ቀኑን ለምን መረጣችሁት?

ይህን የበዓል አከባበር የመረጥንበት ዋናው ነገር ወቅቱ ዓለም በሙሉ ወደ ኢትዮጵያ የሚያይበት ስለሆነ ነው፡፡ ያኔ የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ ሚዲያዎች ለጉዳዩ ትኩረት የሚሠጡበት በመሆኑ እኛም በዚህን ወቅት ሠላማዊ ሠልፍ ማድረጋችን ድምፃችን ጐልቶና ከፍ ብሎ እንዲሠማልን ለማድረግ ብለን ነው፡፡ ይሄ ደግሞ የተለመደ ነው፡፡ በሌላውም ዓለም ትላልቅ ሥብሠባዎች በሚካሄዱበት ጊዜ እንዲሁ ድምፃቸውን ለማሰማት ሠልፍ ያደርጋሉ፡፡ ትኩረት ለመሣብ ነው? አቴንሽን ለመሣብ አይደለም (በቁጣ) ድምፅ ለማግኘት ነው፡፡ ትኩረት ለመሣብ የሚለው ቃል የእኛን ሀሣብ ያዛባዋል፡፡ ሠላማዊ ሠልፍ እንዳልኩሽ መብታችን ነው፡፡ ይሄንን መብታችንን ከህዝብ የምንጋራበትና ውጤታማ የምንሆንበት ጊዜ ነው፡፡ ለምሣሌ ኤርትራዊያን ኢትዮጵያ ውስጥ ሠላማዊ ሠልፍ ያደርጋሉ፤ የተለያዩ ስብሠባዎች በሚካሄዱበት ወቅት፡፡ የመንግስት ሚዲያም ለጉዳዩ ሽፋን ይሠጣል፡፡ ይሄ መንግስት ለኤርትራውያን ሠልፍ ከፈቀደና፣ ግብር ከፋይ ለሆኑት ኢትዮጵያዊያንና በህጋዊ መንገድ እውቅና ለተሠጠን ፓርቲዎች የማይፈቅድ ከሆነ፣ ከኢትዮጵያዊያን በላይ ለኤርትራዊያን ይጨነቃል ያዳላል ማለት ነው፡፡ ሠላማዊ ሠልፉ የተጠራባቸው የኑሮ ውድነት፣ መፈናቀል፣ እስራትና የሀይማኖት ጉዳዮች የኢትዮጵያን መንግስት የሚመለከቱ ናቸው፡፡ ለአፍሪካ ህብረት ተሠብሣቢዎች መናገሩ ለምን አስፈለገ? የሚሉ ወገኖች አሉ፡፡ በተጨማሪም ሠማያዊ ፓርቲ አዲስ እንደመሆኑ በዚህ አጋጣሚ ራሱን ፕሮሞት ለማድረግ ሥለፈለገ እንጂ ሠላማዊ ሠልፉ ይሳካልኛል ብሎ አይደለም ይባላል፡፡

የእርስዎ ምላሽ ምንድነው? በመሠረቱ አስተያየት መስጠት መብት ነው፡፡ በምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎችና ስራዎች ሠዎች አስተያየት መስጠት፣ መተቸት መብታቸው ነው፡፡ በዚህ ተቃውሞ የለኝም። ነገር ግን ፓርቲው ራሱን ለማስተዋወቅ ነው የሚለውን አልቀበልም፡፡ ምክንያቱም እስካሁን በአገሪቱ ውስጥም ሆነ በአለም ላይ ስለ ሠማያዊ ፓርቲ ያልዘገበ የለም፡፡ ሠማያዊ ፓርቲ፤ በዚህ አስቸጋሪና የፖለቲካ ደብዛው በጠፋበት ጊዜ መጥቶ፣ በዓለም አቀፍ ማህበረሠብም ሆነ በኢትዮጵያዊያን ዘንድ አንድ የፖለቲካ ሀይል ሆኖ በመውጣት በኩል የተሣካለት ፓርቲ ነው፡፡ ራስን ለማስተዋወቅ የሠላማዊ ሠልፍን ስልት አንጠቀምም፡፡ ምክንያቱም ከበቂ በላይ የታወቅን ፓርቲ ነን፡፡ አሁን ጐግል ውስጥ ገብተሽ ሠማያዊ ፓርቲ ብትይ ታገኝናለሽ፡፡ እኛ ከምንለውም በላይ የታወቀ ፓርቲ ነው፡፡ ታወቅን የምትሉበት ምክንያት ምንድን ነው? ስለ ሠራን ይመስለኛል፡፡ ፖለቲካ ማለት የመርህ ትንተና ማለት አይደለም፡፡

አካዳሚ ስራም አይደለም፡፡ ለተጨባጭ ችግሮች ተጨባጭ መፍትሄ ማምጣት ነው፡፡ ስለዚህ ሠማያዊ ፓርቲ በአደረጃጀቱም በአመራር ብቃት፣ የህዝብ አጀንዳዎች ይዞ በመነሣት በኩል ያለው ተሠሚነትም ለትግሉ ያለውን ቆራጥነት የሚያሣይ ነው፡፡ ጉዳዩ የመንግስት ነው፤ በአፍሪካ ህብረት የስብሰባ ቀን ለምን ለተባለው እስከዛሬ የመንግስት ጉዳይ ነው ብለን ችግሮቹ እንዲስተካከሉ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ምላሽ አልተገኘም። አሁንም የኑሮ ውድነት አለ፣ አሁንም ዜጐች ይፈናቀላሉ፡፡ አሁንም ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች በሽብርተኝነት ስም ወህኒ ነው ያሉት፣ አሁን መንግስት በሀይማኖት ጣልቃ ገብነት የሀይማኖት ሥርዓታችን ይከበር ባሉት ሙስሊሞች ላይ እስርና እንግልቱን አላቆመም፡፡ ስለዚህ በህብረቱ በኩል ጫና ለመፍጠርና ችግሮች የሚፈቱበትን መንገድ ለማፈላለግ ነው ሠልፉ ከህብረቱ 50ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አከባበር ጋር እንዲገናኝ ያደረግንበት ምክንያት፡፡ ሠልፉ ተፈቀደና ተሣካ እንበል፡፡ ከዚያም የታሣሪ ቤተሠብ አለ፣ የሀይማኖቱ፣ የመፈናቀሉ፣ እንዲሁም የኑሮ ውድነቱ አንገፍግፎኛል የሚል ህዝብ ግልብጥ ብሎ ወጥቶ አገሩን ቢያጥለቀልቅ ሀላፊነቱን ትወስዳላችሁ፣ በምንስ ነው የምትቆጣጠሩት? የእኛ ፍላጐት ከላይ አንቺ እንደ ስጋት ያነሣሽው ነገር እንዲከሠትና ህዝቡ ግልብጥ ብሎ እንዲወጣ ነው የምንፈልገው፡፡

ህዝቡ ግልብጥ ብሎ ሲወጣ ደግሞ ይህንን የሚያረጋጋ ደሞዝ የሚከፈለው ደህንነትና ፖሊስ አለ። መጨረሻ ላይ ሠልፍ ልናካሂድ እንደሆነ ለሚመለከተው አካል የምናሣውቀው እኮ ይሄንን ነገር ጠብቆ ዝግጅት እንዲያደርግ ነው፡፡ ደሞዝ የሚከፈለው የፖሊስ ተቋም ዋናው ሥራው ከቁጥጥር ውጭ የሆኑና ያልተገቡ ነገሮች በግብር ከፋዩ ህዝብ ላይ እንዳፈፀም ነው፡፡ ሠላማዊ ሠልፍ እኮ መብት ነው፡፡ እኛም ለመንግስት አካል የምናሣውቀው በሠልፉ ጊዜ አላግባብ የሆነ አመፅና ሁከት የሚፈጥር ሠው ቢኖር ያንን ለይቶ ሥርዓት የሚያሲዝ እንዲመደብ ነው፡፡ ይሄ የመንግስት ግዴታ እንጂ የሠማያዊ ፓርቲ አይደለም፡፡ አሁን እናንተ ለሚመለከተው አካል አሳውቃችኋል? ማዘጋጃ ቤት ውስጥ የሚገኝ አንድ ቢሮ አለ፤ እንዲያውቀው የሚደረገው ሠልፉ ከመካሄዱ ከ48 ሠዓት በፊት ነው፤ እኛም ጊዜው ሲደርስ ግንቦት 15 አካባቢ እናሣውቃለን፡፡ አሁን ትኩረት ያደረግነው ለህዝቡ በስፋት የማስተዋወቅ የህዝብ ግንኙነት ሥራ ላይ ነው፡፡ ከሠልፉ ምን ትጠብቃላችሁ? ሠልፈኛው ጥቁር እንዲለብስ የፈለጋችሁበት ምክንያት ምንድነው? ቀደም ብዬ እንደነገርኩሽ የሠልፉ አላማ መንግስትን በተደጋጋሚ የጠየቅነው ነገሮች ነበሩ።

በመግለጫው ላይ እንዳመለከትነውም ችግሮቹ ዛሬ የተፈጠሩ አይደሉም፣ በተደጋጋሚ በግልጽ ደብዳቤ ጠይቀናል፣ አቋም ወስደንም በመግለጫ አውጥተናል፡፡ ነገር ግን መንግስት እኛን ከማጥላላት፣ ከማንኳሰስና ጆሮ ዳባ ልበስ ከማለት ውጭ መልስ አልሰጠም፡፡ ስለዚህ አሁንም አላማችን ጥያቄዎቻችን ጆሮ አግኝተው መፍትሔ እንዲሰጥ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት የስራ አጡ ቁጥር የትየለሌ ነው፣ ኑሮ ውድነቱ አላፈናፍን ብሏል፣ ሙስና ተቋማዊ ሆኗል፣ ጋዜጠኞች እስር ቤት ናቸው፣ የሃይማኖት ጥያቄ የጠየቁ ሰዎች እስር ቤት ናቸው፤ መፈናቀሉን አሁንም አልቆመም፡፡ “ይህን ሁሉ ነገር መልክ አስይዝ” ነው የምንለው፡፡ ምክንያቱም መንግስት ግዴታ አለበት፡፡ ይህን እስኪመልስ አሁንም ግፊታችን ይቀጥላል፡፡ ሠላማዊ ሰልፉ የግፊቱ አንድ አካል ነው፡፡ ህዝቡ ግብር የሚከፍለው መንግስትም የህዝብን ስልጣን የያዘው እነዚህ ችግሮች እንዲፈቱ እኮ ነው፡፡ ይህንን ካላደረገ የማንን ጐፈሬ ሊያበጥር ነው፡፡ ስለዚህ “እባክህ ስማን” ነው እያልን ያለነው። መቼም ሟርት አይደለም፤ ግን ሠላማዊ ሰልፉ እንደከዚህ በቀደሙ ቢከለከል ምን ታደርጋላችሁ? እኔ አሁን ስለመከልከሉ አላስብም፡፡ መብቴ ስለሆነ ሰልፉ ይካሄዳል የሚል እምነት ነው ያለኝ፡፡ የእስከዛሬው የተከለከለው መብታችሁ ስላልሆነ ነው እንዴ? እንደሱ ማለት ሳይሆን ያንን አደረጉት ራሱ መንግስት ይወቀስበታል፡፡ ነገር ግን ገና ለገና እንከለከላለን እያልን እጃችንን አጣጥፈን አንቀመጥም፡፡ እንደባለፈው መታሰር ቢመጣስ ለዚያ ዝግጁ ናችሁ? ያንን እነሱ ናቸው የሚያውቁት፡፡ ይሠሩን፣ ይግደሉን፣ ወይም ከዚህ የተለየ ነገር ያድርጉ፤ ህገ-ወጥ ስለሆነ፣ በቃ ህገ-ወጥ ድርጊት ነው፡፡

ለምሣሌ አንቺ ሠላማዊ ሰው ነሽ፤ ከዚህ ስትወጪ ማጅራት መቼ ቢያገኝሽ ምን ትያለሽ? አንቺ መብት ያለሽ ዜጋ መሆንሽን በሠላም ወጥተሽ መግባት መብትሽ እንደሆነ ነው የምታምኚው፡፡ ነገር ግን እኔ ህጋዊ ስለሆንኩ ሠላማዊ ሰልፍ ማድረግ መብቴ እንደሆነ እኔ ብቻ ሳልሆን እናንተ ጋዜጠኞችም ታውቃላችሁ፤ ስለዚህ እኔ ህጋዊ መሆኔን እንጂ ህገ-ወጦች ስለሚሠሩት ላውቅ አልችልም። እኔ የማውቀው የተፈቀደውን እና ህጋዊውን እንጂ በህገ-ወጥና በውንብድና የሚደረገውን አላውቀውም፡፡ ሠማያዊ ፓርቲን ያፍርሰው፣ ሰብስቦ አመራሩን ይሰረው፣ እንደተለመደው ሌላ አይነት ፋይል ያዘጋጅ፤ ያ የእርሱ ፋንታ ነው፡፡ እንደተለመደው ሌላ አይነት ፋይል ያዘጋጅ ሲሉ ምን ማለትዎት ነው? ጓደኞቻችን ሽብርተኛ ተብለው በየእስር ቤቱ አይደለም እንዴ ያሉት! ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች ማለቴ ነው፡፡ ለምሣሌ እነ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ የቅርብ ጓደኞቼ ናቸው፤ እስር ቤት እንዳሉ ታውቂያለሽ፤ የሽብርተኝነት ፋይል ተዘጋጅቶላቸው አይደለም እንዴ? እና እንዲህ ያለው ነገር ለኢትዮጵያ አዲስ አይደለም። ነገር ግን ይህ እንዲለወጥ ነው ትግላችን፡፡ በሠላማዊ ሠልፉ ላይ ጥቁር ስለመልበስ ጠይቀሽኝ ነበር፡፡ ችግራችንን ሀዘናችንን፣ ያለንበትን አስቸጋሪ ሁኔታ ለማመልከት ነው ጥቁር እንዲለበስ ያስፈለገው፡፡ ከአፍሪካ ህብረት 50ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ጋር አስታካችሁ ሠልፉን መጥራታችሁ ክብረ በዓሉን አይረብሽም ትላላችሁ? በምንም መንገድ አይገናኝም፡፡

ቀደም ብዬ እንደነገርኩሽ አንቺም እንደምታውቂው ይህ አይነቱ ብሶትን የማሰማት አሰራር በትላልቅ ስብሰባና ኮንፈረንሶች ላይ ይደረጋል፤ በአለም አቀፍ ደረጃ የተለመደ ነው፡፡ ስለዚህ ሰላማዊ ሠልፉ ስብሰባውን ይረብሻል የሚለው ፍፁም የማይገናኝ ነገር ነው፡፡ ፓርቲው ራሱን ለማስተዋወቅ ሠላማዊ ሠልፍ አይጠራም፣ በሠራቸው ሥራዎች በአገር አቀፍም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ ታውቋል ብለዋል፡፡ እስቲ በዚህ አንድ አመት ውስጥ ምን ምን እንደሠራችሁ ይንገሩኝ…? እንግዲህ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ለመንግስት የአሠራር አቅጣጫ ነድፎ አይሰጥም። ሊያደርግ የሚችለው ፖሊሲውንና ፕሮግራሙን ለህዝብ ማስተዋወቅ፣ ድርጅታዊ ጥንካሬውን መፍጠር፣ አማራጭ ሀይል ሊሆን እንደሚችል ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ፣ ለሲቪክ ማህበረሰቡና ለሌሎች ቡድኖች ማሳወቅ፣ ፓርቲው አመራር መቀበል የሚችል አቅም ያለውና የኢትዮጵያን ችግሮች ሊፈታ የሚችል መሆኑን፣ በአሠራርም በአደረጃጀትም ሆነ በፖሊሲ ደረጃ ከአንድ ተቃዋሚ የሚጠበቀውን በማድረግ ረገድ ፓርቲው ከሚገባው በላይ ከፍተኛ ሥራ ሰርቷል። በተለያዩ አገራዊ አጀንዳዎች ላይ የተለያዩ ውይይቶችን በቢሮው አድርጓል፡፡ ወሳኝ የሆኑ አገራዊ ጥያቄዎችን ይዞ ወደ ህዝብ ወጥቷል። ስለዚህ በእኔ እምነት እንደ አንድ ተቃዋሚና ስልጣን ያልያዘ ፓርቲ የምንችለውን ሁሉ ሠርተናል ብዬ ነው የማምነው፡፡ አዲስ እንደመሆናችሁ ከሌሎች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ያላችሁ ግንኙነት ምን ይመስላል? በጣም ጥሩ ግንኙነት አለን፡፡ በተለያዩ ፓርቲዎች ያሉ ሰዎችንም እናውቃቸዋለን።

አብረናቸው ስንሰራም ነበር፡፡ ለምሣሌ የ33ቱ ፓርቲዎች ውስጥ አለንበት፡፡ ባለፈው ለሁለተኛ ጊዜ የመግባቢያ ሰነድ ከተፈራረምን በኋላ የመጀመሪያውን አብይ ኮሚቴው ስብሰባ ሲያደርግ በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ውስጥ ነበር፡፡ በአብይ ኮሚቴው በምክትል ፀሐፊነት የሚሠራው የፓርቲያችን ምክትል ሊቀመንበር ነው፡፡ ከአንድነትም ሆነ ከመኢአዶች ጋር መልካም ግንኙነት ነው ያለን፡፡ አሉ ከሚባሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር አብረን እየሠራን ነው፡፡ በመጨረሻ የሚሉት ነገር ካለ …? እንግዲህ ሰልፉ እንደስሙ ሠላማዊ መሆኑን ደጋግመን ገልፀናል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ ሥራ ሃሳብ አመንጭቶ ስትራቴጂ ነድፎ ህዝቡን መምራት ነው፡፡ አንደበቱ ሚዲያ ሲሆን ጉልበቱ ህዝብ ነው፡፡ ውጤት እንዲመጣ ከተፈለገ ከላይ የተጠቀሱት ሶስት ነገሮች መተሳሰር መቻል አለባቸው፡፡ ሚዲያ አንደበት ነው፣ ፓርቲ አዕምሮና መሪ ነው፣ ህዝብ ጉልበት ነው፡፡

ይዘን የተነሳነው የህዝብ ጥያቄ ነው፡፡ እኔ የግል ጥያቄ የለኝም ወይም ሰማያዊ የተለየ ጥያቄ የለውም፡፡ ነገር ግን የዚህ አገር ችግር የህዝብ ችግር ነው፡፡ ጥያቄውን ይዘን መጥተናል፤ ወደ ውጤት የምንመጣው በህዝብ ተሳትፎ ነው፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የኢህአዴግ አባላትን ጨምሮ ሁሉም በኑሮ ውድነት ውስጥ ነው፡፡ የተለየ ጥቅም የሚያገኙና ባለስልጣናት ካልሆኑ በስተቀር የኢህአዴግም አባል ሆኖ ብዙ የተቸገረ ሰው እንዳለ እናውቃለን፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ ይመለከተናል የሚሉ ሁሉ በሰልፉ ተሣታፊ እንዲሆኑ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

Total Pageviews

Translate