Pages

May 29, 2013

ኚሙስና ተጠርጣሪዎቜ እሥር በኋላ ዚጥቆማ ቁጥር በእጥፍ ጹመሹ፤ ሕጉ ይሻሻላል ተባለ


                                                     áŠ á‰¶ ገብሚዋህድ ወ/ጊዮርጊስ
ኚሙስና ተጠርጣሪዎቜ እሥር በኋላ ዚጥቆማ ቁጥር በእጥፍ ጚመሚበጋዜጣው ሪፖርተርዚፌዎራል ዚሥነ ምግባርና ዹፀሹ-ሙስና ኮሚሜን በገቢዎቜና ጉምሩክ ባለስልጣን ኹፍተኛ ዚሥራ ኃላፊዎቜና ሌሎቜ ተጠርጣሪግለሰቊቜ በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ ኚያዘ በኋላ ለኮሚሜኑ ዹሚደርሰው ዚሙስና ጥቆማ ቁጥር መጚመሩ ታወቀ።ኮሚሜኑ በድሚገፁ ይፋ እንዳደሚገው በተለይ ኚግንቊት 2 ቀን 2005 ዓ.ም በኋላ ባሉት አስር ቀናት ብቻ ኹዚህ ቀደም ኹነበሹውጋር ሲነፃፀር ዚጥቆማ ቁጥር በእጥፍ በልጩ መመዝገቡን ገልጿል።ኀብሚተሰቡ ሙስና አስኚፊ ድርጊት መሆኑን ተገንዝቩ ለማጋለጥና ሙስናን ለመዋጋት እያሳዚ ላለው ጥሚት ኮሚሜኑ ምሥጋናአቅርቧል። ሆኖም ምን ያህል ጥቆማ እንደቀሚበለት በቁጥር ኹመግለፅ ተቆጥቧል።ዚፌዎራሉ ዚሥነ ምግባርና ዹፀሹ ሙስና ኮሚሜን በ2005 በጀት ዓመት አስር ወራት ዚድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጜ/ቀትን ጚምሮ3001 ጥቆማዎቜና አቀቱታዎቜን መቀበሉን ኹነዚህ ውስጥ በኮሚሜኑ ዚሥልጣን ክልል ሥር ዚሚወድቁት 1ሺ 335 ወይም 44በመቶ ያህሉ ሲሆን ዚተቀሩት 56 በመቶ ኚሥልጣኑ ክልል ውጪ መሆናቾውን ኮሚሜነር ዓሊ ሱሌይማን ኚሳምንት በፊትለሕዝብ ተወካዮቜ ም/ቀት መግለፃቾው ይታወሳል።nበሌላ ዜና                                                                ዹፀሹ-ሙስና ሕግ ሊሻሻል ነው                                    · ዚአክሲዮን ማኅበራት፣ ባንኮቜ፣ ኢንሹራንሶቜና ዚልማት ማኅበራት                                                        በአዲሱ ዚሙስና ሕግ ይካተታሉበዘሪሁን ሙሉጌታዚፌዎራል ዚስነ-ምግባርና ዹፀሹ-ሙስና ኮሚሜን ሕግ በወንጀል ሕጉ ዹተደነገጉ ዚሙስናወንጀሎቜ እንደገና ዹሚደነግግ አዋጅ በማዘጋጀት አሁን እያስቀጣበት ያለውን ሕጋዊ ወሰንበማስፋት አዋጁን ሊያሻሜል ነው።አዲስ እዚተዘጋጀ ባለው ሹቂቅ ሕግ በዋናነት ዹግል ዘርፍ አካላትን በሙስና ወንጀል ተጠያቂዚሚያደርግ እንደሆነ ለማወቅ ተቜሏል። በተለይም በመቶ ሚሊዮኖቜ ገንዘብ ዚሚገመት ሀብትእያንቀሳቀሱ ያሉ፣ ዚሕዝብ ሀብት ዚሚያስተዳድሩ ዹግል ዘርፍ አካላት ላይ ሹቂቅ ሕጉአተኩሯል። እነዚህ አካላት በማንኛውም አግባብ ኚአባላቶቻ቞ው ወይም ኚሕዝብ ዹተሰበሰበወይም ለሕዝባዊ አገልግሎት እንዲውል ዹተሰበሰበ ገንዘብ፤ ንብሚት ወይም ሌላ ሀብትንዚሚያስተዳድሩ ወይም ዚሚያንቀሳቅሱ አክሲዮን ማኅበራት በማኑፋክ቞ሪንግ፣ በእርሻ፣በንግድ፣ በኮንስትራክሜን፣ በትራንስፖርት፣ በፋይናንስ እንዲሁም ዚፋይናንስ ተቋማትመካኚል በአክሲዮን ዹተቋቋሙ ባንኮቜ፣ ዚኢንሹራንስ ኩባንያዎቜ ዹሐዋላ ተቋማት ዚሙያና ዚብዙሃን ማኅበራት ፌዎሬሜኖቜናኮንፌዎሬሜኖቜ፣ ዚኅብሚት ሥራ ማኅበራትና ዩኒዚኖቜ፣ ኢንዶውመንቶቜና ዚልማት ማኅበራት (ለምሳሌ አልማ፣ ኩልማ፣ ወዘተን)ያካትታል።ሕጉን እንደገና ለማሻሻል ያስፈለገው ሙስናን ዹሚፀዹፍ ኅብሚተሰብ እንዲፈጠር ዹሚደሹገውን ጥሚት ለማጠናኹር፣ በዓለም አቀፍደሹጃም፤ በግል ዘርፍ ዹሚፈፀም ጉቊኝነትና ምዝበራ በሙስና ወንጀል ዚሚያስቀጣ በመሆኑ ሲሆን፤ አዲሱ ሹቂቅ ሕግምኚሲንጋፖር፣ ኚስዊዲንና ኚደቡብ አፍሪካ ተመሳሳይ ሕጎቜ በመቀመር መዘጋጀቱም ታውቋል።በአዲሱ ሕግ መሠሚት ለሕዝብ ተብሎ ዹተሰበሰበ ሀብት ዚሚያንቀሳቅሱ እና ዚሚያስተዳድሩ ዹበጎ አድራጎት ድርጅቶቜ፣ ዚፖለቲካድርጅቶቜና ዹዓለም አቀፍ ድርጅቶቜን በሙስና ወንጀል እንዲጠዚቁ ማድሚጉ ኚጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ስለሚያመዝን በሕጉያልተካተቱ ሲሆን፤ ሌሎቜ ዚሕዝብን ገንዘብና ሀብት ዚሚያስተዳድሩ ጥቃቅን እና አነስተኛ ተቋማት፣ እድር እና ተመሳሳይ ባህላዊወይም ሃይማኖታዊ ይዘት ያላ቞ው ማኅበራት አባላቱ እርስ በርስ ዹሚተማመኑና ለሙስና ዚመጋለጥ ዕድላ቞ው ዝቅተኛ በመሆኑ፣በሙስናውም ቀጥተኛ ተጠቂ ዹሚሆኑ ዚኅብሚተሰብ ክፍሎቜ ጥቂቶቜ በመሆናቾውና ኚሚያንቀሳቅሱት ሀብት አነስተኛነት ዚተነሳበሙስና ተጠያቂ በማድሚግ ኚሚድነው ሀብት ይልቅ ተጠያቂ ለማድሚግ ዚሚባክነው ሀብት ኹፍተኛ በመሆኑ ኹሕጉ ውጪተደርገዋል።በአዲሱ ዚሙስና ወንጀል ሹቂቅ ሕግ በግለሰብ ባለሀብት ወይም ባለሀብቶቜ ዹተቋቋመ ኃላፊነቱ ዹተወሰነ ዹግል ኩባንያ በሙስናወንጀል አይጠዹቅም።¾á‰ áˆŒáˆ‹ ዚሙስና ዜናበእነ ገብሚዋህድ ወ/ጊዮርጊስ መዝገብ ስር ዚተዘሚዘሩት 12 ተጠርጣሪዎቜ ተጚማሪ ዹጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባ቞ው- በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ያሉ ተጠርጣሪዎቜ ጉዳይ ዛሬ ይታያል- አቶ ነጋ ገ/እግዚአብሔር ድብደባ ተፈፅሞብኛል አሉበአሾናፊ ደምሎዚፌዎራሉ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት 2ኛ ወንጀል ቜሎት በሙስና ወንጀል ተጠርጥሚውበሥነ-ምግባርና ፀሹ-ሙስና ኮሚሜን ዚምርመራ ቡድን ተጚማሪ ጊዜበተጠዚቀባ቞ው በእነ ገብሚዋህድ ወ/ጊዮርጊስ መዝገብ ስር ዹሚገኙ አስራሁለትተጠርጣሪዎቜ ላይ ዹ14 ቀኑ ጊዜ ቀጠሮ ሲፀናባ቞ው፤ ዚገቢዎቜና ጉምሩክባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታን ጚምሮ በሊስት ዚተለያዩመዝገቊቜ ዚተዘሚዘሩትን 22 ተጠርጣሪዎቜ ጉዳይ ለመመርመር ደግሞ ዛሬንጚምሮ ሐሙስና አርብ ተለዋጭ ቀጠሮዎቜን ሰጥቷል።ቜሎቱ በዕለቱ ሲሰዚም ኮሚሜኑ ዚደሚሰበትን ዚምርመራ ውጀት ለመስማትእንደሆነ ፍርድ ቀቱ አስታውሶ፤ ለፌዎራሉ ስነምግባርና ፀሹ ሙስና ኮሚሜንዚምርመራ ቡድን ተወካዮቜ ሀሳባ቞ውን እንዲያስሚዱ ዕድል በመስጠት ጀምሯል።በቜሎቱ ዚተገኙት ዚመርማሪ ቡድኑ ተወካይም ቡድኑ ያሳካ቞ውንና ያላሳካ቞ውንዚምርመራ ውጀቶቜ በሁለት ኹፍለው ለፍርድ ቀቱ አሰምተዋል። በዚህም በዘጠኝተጠርጣሪዎቜ መኖሪያ ቀት በመድሚስ ዚኀሌክትሮኒስ መሳሪያዎቜን፣ ዚተደበቁሰነዶቜንና በህገወጥ መንገድ ዹተገኙ ገንዘቊቜን (መኒ ላውንደሪ) መሰብሰቡንጭምር ገልጿል። አክሎም ዹ28 ተጠርጣሪዎቜ ክስ መቋሚጡን ዚሚያስሚዱሰነዶቜን፣ ስምንት በቫት ማጭበርበር ተጀምሹው ዚተቋሚጡ ክሶቜን፣ ኊዲትያልተደሚጉ ሰነዶቜን እና ዹ15 ምስክሮቜን ቃል ስለመቀበሉ ካጠናቀቃ቞ውውጀቶቜ አንኳሮቹ ናቾው ሲል አስሚድቷል።በአንፃሩ ደግሞ ዚኮሚሜኑ ዚምርመራ ቡድን አላጠናቀኳ቞ውምና ተጚማሪ ዚምርመራ ጊዜ ይሰጠኝ ሲል ጥያቄ ያቀሚበባ቞ውጉዳዮቜ መካኚል፤ ተጚማሪ ዚሙስና ወንጀሎቜ ዚታገዱባ቞ው ሰነዶቜ፣ ዚታገዱ ንብሚቶቜን ማጣራት፣ ኚአራጣ ብድር ጋርዚተያያዙ ጉዳዮቜን ማጥራት፣ ዚምርመራ ስራው ኚአዲስ አበባ ውጪ ባሉ ቊታዎቜ ዚሚካሄድም ጭምር መሆኑን እና በምርመራቡድኑ አማካኝነት ዹተገኙ ሰነዶቜን መርምሮ ኚክስ መዝገቡ ጋር እንዲያያዙ ለማድሚግ ይሚዳ ዘንድ ተጚማሪ 14 ቀናትን ፍርድቀቱ እንዲፈቅድ ጠይቀዋል።ሰኞ ኚሰዓት በኋላ በፌዎራሉ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት 2ኛ ወንጀል ቜሎት በቀዳሚነት ጉዳያ቞ው በቜሎቱ መሰማት ዹጀመሹውበሁለተኛ ዚክስ መዝገብ ስር ዚተዘሚዘሩት 12 ተጠርጣሪዎቜ ሲሆን፤ በዚህም ስር ዚገቢዎቜና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዋናዳይሬክተር አቶ ገብሚዋህድ ወ/ጊዮርጊስ ጚምሮ ሌሎቜም ባለስልጣናት እና ነጋዎዎቜ በሙስና ወንጀሉ ተሳታፊ ሆነዋል ዚተባሉቀተሰቊቜ በቜሎት ቀርበው በጠበቆቻ቞ው በኩል ጉዳያ቞ውን አስሚድተዋል።አብዛኞቹ ተጠርጣሪዎቜ በጠበቆቻ቞ው በኩል ለፍርድ ቀቱ ባቀሚቡት ጥያቄና አቀቱታ መሠሚት፣ መርማሪ ቡድኑ በቂማስሚጃዎቜን ሰብስቀያለሁ ያለ መሆኑን በመጥቀስ፤ አንዳንድ ተጠርጣሪዎቜም አሁን ድሚስ ዚተጠሚጠሩበትን ወንጀል ክስአለማወቃ቞ውን እና በጀናና በቀተሰብ ጉዳይ ላይ ተንተርሶ ዚዋስትና መብታ቞ው እንዲኚብር ጥያቄ አቅርበዋል።ዚገቢዎቜና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዚሆኑት አቶ ገብሚዋህድ ወ/ጊዮርጊስ በጠበቃቾው አማካኝነት ዚምርመራቡድኑ አገኘሁት ያለው መሹጃ በቂ ሆኖ ሳለ ሁለት ህፃናት ልጆቌ በቜግር ላይ ስለሚገኙ ዚዋስ መብ቎ ተጠብቆ ኚእስር ልለቀቅይገባል ዹሚል ሀሳብ አቅርበዋል።አቶ ገብሚዋህድ አክለውም፤ ሁለት ህፃናት ልጆቌ ዚሚንኚባኚባ቞ው በሌለበት መልኩ እንዲኖሩ ተገደዋል። ባለቀ቎ም ሆነቜ እህቷዚተመሠሚተባ቞ው ክስ ሰነድ መደበቅ ቢሆንም ተደብቋል ዚተባለው ሰነድ ግን ቀድሞም በኮሚሜኑ እጅ ዚገባ መሆኑን በማስታወስ፤ኚገቢዎቜና ጉምሩክ ባለስልጣን መስሪያ ቀት ጋር ምንም ግንኙነት ዹሌላቾው ሰዎቜ በዚህ ክስ ስር መጠቃለላቾው አግባብአይደለም ብለዋል። ይህም በመሆኑ ፍ/ቀቱ ሁለቱን ዚቀተሰብ አባላት በዋስ መብታ቞ው ተጠቅሞ እንዲያሰናብታ቞ውጠይቀዋል።በሌላም በኩል በተለይም በሁለተኛው ዚክስ መዝገብ ስር 5ኛ ተኚሳሜ ሆነው ዚቀሚቡት ዹነፃ ትሬዲንግ ባለቀት አቶ ነጋ ገ/እግዚአብሔር በምርመራ ወቅት ኹፍተኛ ድበደባ እንደተፈፀመባ቞ውና ለሁለት ጊዜያት ያክል ራሳ቞ውን ስተው እንደነበርበማስታወስ፤ “በእስር ቆይታዬ አገሬ ምን እንደምትመስል አውቄያለሁ” ሲሉ ለፍርድ ቀቱ አስሚድተዋል። አቶ ነጋ ገ/እግዚአብሔር ዚልብ፣ ዹደምና ዚስኳር ህመምተኛ መሆናቾውን ጭምር በማስሚዳት ዚዋስትና መብት ጠይቀዋል። በዚሁ መዝገብ 3ኛተጠርጣሪ ሆነው ዚቀሚቡት አቶ ጥሩነህ ባልቻ በበኩላ቞ው ሕገመንግስቱንና ሰብዓዊ መብትን በሚቃሹን መልኩ በዱላ ዚታገዘምርመራ ተፈፅሞብኛል ሲሉ ቅሬታ቞ውን ለፍርድ ቀቱ አሰምተዋል።በመዝገቡ ስር ሁለተኛ ተጠርጣሪ ሆነው ዚቀሚቡት ዚገቢዎቜና ጉምሩክ ባለስልጣና ዋና ኊዲተር አቶ በላቾው በዹነ፤ በጠበቃ቞ውአማካኝነት በቂ ማስሚጃና ኀግዚቢት ይዘናል፤ ሠነድ ሰብስበናል ካሉ በኋላ ዚደንበኛዬን ዚዋስትና መብት በመገደብ ተጚማሪ ዹ14ቀናት ቀጠሮ ሊጠይቅ አይገባም ሲሉ ተኚራክሚዋል። ለ27 ዓመታት በመንግስት መስሪያ ቀት ማገልገላቾውን ያስሚዱትተጠርጣሪው፤ እኔ ዚምተዳደሚው በወርሐዊ ደመወዜ ነው ሲሉ በእርሳ቞ው መታሰር ምክንያት ቀተሰባ቞ው ቜግር እንደገጠመውበመጥቀስ ፍርድ ቀቱን ዚዋስትና መብት ይኹበርልኝ ሲሉ ጠይቀዋል።በድምሩም በቜሎቱ ለመርማሪ ቡድኑ ኚቀሚቡት ጥያቄዎቜ መካኚል ፍርድ ቀቱ አፅንኊት ዚሰጡባ቞ው ሊስት አበይት ጉዳዮቜሲኖሩ፤ ይኾውም ቡድኑ ተጚማሪ ዚምርመራ ጊዜን ሲጠይቅ ምንን እንደሚጠይቅ ቢታወቅም ማንን እንደሚጠይቅ በግልፅአለመቀመጡን፣ ዚሚሰሙት ምስክሮቜ በማን ላይ ምስክርነታ቞ውን ዚሚሰጡ ስለመሆና቞ውና ዚትኛው ተኚሳሜ በዚትኛው ክስ ስርተጠያቂ እንደሆነ በግልፅ አለመስፈሩ ተጠቁሟል።ዚምርመራ ቡድኑ ተወካዮቜ በበኩላ቞ው ለፍርድ ቀቱ ሲያስሚዱ፤ ተጚማሪ ዚምርመራ ጊዜ ዹተጠዹቀው ወንጀሉ እጅግውስብስብና ሰንሰለታማ መሆኑን በመጥቀስ፤ ተጠርጣሪዎቹ ባለስልጣናትና ባለሃብቶቜ ኹመሆናቾው አንፃር ኚእስር በዋስ ቢለቀቁማስሚጃዎቜን ኚማጥፋትም በላይ ምስክሮቜን ሊያሞማቅቁ አሊያም ሊያግባቡ ዚሚቜሉ ናቾው ሲል አስሚድቷል።በምርመራ ሂደት ውስጥ ተፈፅሟል ለተባለው ሕገ-መንግስቱን ዚጣሰ ዚሰብዓዊ መብት ቜግር አስመልክቶ በሰጡት ምላሜ፣ ጉዳዩለፍርድ ቀት ሲደርስ ተጠርጣሪዎቹ ማስሚጃ ማቅሚብ ይኖርባ቞ዋል። ነገር ግን እንደኚዚህ ቀደሙ ሁሉ ቜግሮቜ ካሉ እናርማለንዚሚል ምላሜ ሰጥተዋል።ዹህክምናና ዚቀተሰብ ጉዳዮቜን አስመልክቶ ለተነሱት ጥያቄዎቜ መልስ ሲሰጡም፤ ታማሚዎቜ ካሉ ማሚሚያ ቀቱ ዚራሱ ዹሆነክሊኒክ መኖሩን በመጥቀስ ኚክሊኒኩ በላይ ለሆኑ ህመሞቜ በሪፈራል ደሹጃና ኚዚያም በላይ ለማሳኚም ዚሚያስቜል አቅም መኖሩንጠቅሰዋል። ቀተሰብን በተመለኹተ በተለይም 1ኛ ተጠርጣሪ በሰጡት አስተያዚት ላይ ተመርኩዘው ሲያስሚዱ ኚቀተሰቡ ዚተገኘውሰነድ እንዳለ ሆኖ መርማሪ ቡድኑ ዹሚፈልጋቾው ሌሎቜ ሰነዶቜም ስለመኖራ቞ው በመግለፅ ተጠርጣሪዎቹ በዋስ መብት ኚእስርቢለቀቁ አስ቞ጋሪ ይሆንብናል ብለዋል።በጥቅሉም ለተጠርጣሪዎቹ ዚዋስትና መብት መስጠትን በሚመለኚት በወንጀለኛ ሕጉ ላይ፤ ዹተፈፀመው ወንጀል በሀገር ሀብት ላይኹሆነና ኹ10 ዓመት በላይ ሊያስቀጣ ዚሚቜል መሆኑ ኚግምት ኚገባ ዋስትና እንደማይሰጥ ይደነግጋል ሲሉ ለፍርድ ቀቱአስሚድተዋል።ዚግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው ቜሎቱም፤ ተኚሳሟቹ ዚተጠሚጠሩበት ወንጀል ኚባድና ውስብስብ መሆኑን በመጠቆም ዚዋስትናመብታ቞ውን ውድቅ አድርጐ ለመርማሪ ቡድኑ ተጚማሪ ዹ14 ቀናትን ዹጊዜ ቀጠሮ ፈቅዷል። አያይዞም በሰጠው ትዕዛዝ፤ዚተጠርጣሪዎቜን ሰብዓዊ መብት በሚመለኚት ጥንቃቄ መደሹግ እንደሚገባው አሳስቊ ዚምርመራ ሂደቱም ግልፅ ይሁን ሲል ትዕዛዝበመስጠት ለሰኔ 3 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።በተያያዘ ዜና በሙስና ወንጀል ዚተጠርጣሪዎቹን ቁጥር ወደ 54፤ ዚክስ መዝገቡን ደግሞ ወደ ሰባት ያደሚሰው ዚእነመልካሙእንድርያስ ጉዳይ በመርማሪ ቡድኑ ዚተጚማሪ ቀነ ቀጠሮ በመጠዹቁ ለግንቊት 23 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል። በዚህመዝገብ ዚተዘሚዘሩት ግለሰቊቜ መልካሙ እንድርያስ ዚናዝሬት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ሰራተኛ፣ ወ/ሮ አልማዝ ኹበደ ዚባሕር ትራንዚትስራ አስኪያጅ፣ አቶ ዳዊት መኮንን ደላላ እና አቶ ዳዊት አብተው ሠራተኛ ናቾው። እነዚህ ግለሰቊቜ ዚተጠሚጠሩት ኚትራንዚትድርጅቶቜ ጋር በመመሳጠር እቃዎቜ ዚጉምሩክን ስርዓት ባልጠበቀ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ በማድሚግና ያልተገባሀብትን ማካበት በሚሉ ወንጀሎቜ ነው።¾áˆáŠ•áŒ­፡ ሰንደቅ ጋዜጣ ዚሚቡዕ ሚርይ 29 ዕትም አዲስ አበባ

ሰማያዊ ፓርቲ በመጪው እሁድ በሚጠራው ሰልፍ ላይ 100ሺህ ሰው ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል

በመስኚሚም አያሌው


ዚፊታቜን ግንቊት 25 ቀን 2005 ዓ.ም በሚካሄደው እና ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው
ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ኹ100 ሺህ በላይ ሰዎቜ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዚሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ለዝግጅት ክፍላቜን
እንደገለፁት፤ ፓርቲው ባለፈው ግንቊት 17 ቀን 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ህብሚት ጜ/
ቀት ፊት ለፊት ሊያካሂድ ዹነበሹውን ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያራዝም መንግስት
በጠዹቀው መሰሚት ዚፊታቜን እሁድ ያካሂዳል። መንግስት በፀጥታ እና ሰላም ማስኚበር
ሂደት ኹአቅም በላይ ዹሆነ ቜግር ሲያጋጥመው ሰልፉን ለሌላ ጊዜ እንዲዛወር መጠዹቅ
ይቜላል ዹሚል ህግ በመኖሩ ሰልፉ ኚአንድ ሳምንት በኋላ እንዲደሚግ መወሰኑን
ፕሬዝዳንቱ ገልጾዋል።
ሰላማዊ ሰልፉን በአፍሪካ ህብሚት በዓል ወቅት ማካሄድ ዹተፈለገው ኢትዮጵያ በአሉን
ስለምታዘጋጅ እና መንግስት ትኩሚት ሰጥቶ ዚሚሰራው ስራ በመሆኑ ዚኢትዮጵያ
ህዝብና ሚዲያው እንዲሁም አለም አቀፍ ሚዲያዎቜ ስለሚሰሙት ጥያቄው ኹፍ
ብሎ ይሰማል ኹሚል አስተሳሰብ መሆኑን ዚገለፁት ፕሬዝዳንቱ፤ ዹሰላማዊ ሰልፉ ቀን
መራዘም ምንም ዹተለዹ ነገር እንደማይፈጥር ገልፀዋል። “ዚቜግሩ ባለቀትም ሆነ
መፍትሔ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ነው። ዹሚጹቁነንም መንግስት እዚህ ነው ያለው” ያሉት
ፕሬዝዳንቱ፣ ሰልፉ በታሰበለት ቀን ቢካሄድ ጥሩ እንደነበር ገልፀው ቀኑ መቀዚሩም ያን
ያህል ለውጥ እንደሌለው ተናግሹዋል።
ዹሰላማዊ ሰልፉ በመራዘሙ በፊት ይሳተፋል ተብሎ ኚታሰበው በላይ ሰው ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል። ሰላማዊ ሰልፉን በህጉ
መሰሚት ማስፈቀዱ እና ህዝቡም ጊዜ ወስዶ እንዲወያይበት በመደሹጉ ኹ100ሺ በላይ ሰዎቜ በሰልፉ ላይ ይገኛሉ ተብሎ
ይጠበቃል። በሰልፉ ዚሚነሱት አራት ጥያቄዎቜ በመሆናቾው ህዝቡ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እና ዚተነሱ ጥያቄዎቜን
ዹተመለኹተ ብቻ እንዲሆንም ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል። በሰላማዊ ሰልፉ ወቅትም ዚታሰሩ ፖለቲኚኞቜ እና ጋዜጠኞቜ እንዲለቀቁ፣
ዚእስልምናን እምነት ነፃነት በመጠዹቃቾው ዚታሰሩት ዚሙስሊም ዚመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚ቎ አባላት እንዲፈቱ፣ ዹተፈናቀሉ ሰዎቜ
ወደሚኖሩበት አካባቢ በሰላም ተመልሰው ካሳ እና ድጎማ ተደርጎላቾው ህይወታ቞ውን እንዲቀጥሉ እንዲሁም ዚመልካም
አስተዳደር ቜግሮቜ እንዲፈቱ እና በስራ አጥነት እና በሙስና ላይ መንግስት አፋጣኝ መፍትሔ እንዲፈልግ ዹሚሉ ጥያቄዎቜን
አንግበው ሰላማዊ ሰልፉን እንደሚያካሂዱም ተገልጿል።
ኚጠዋቱ 4 ሰዓት ጀምሮ ሰላማዊ ሰልፉ መነሻውን ግንፍሌ አካባቢ ኹሚገኘው ዚፓርቲው ጜ/ቀት በማድሚግ በአራት ኪሎ፣ ፒያሳ
እና ቾርቾል ጎዳና አልፎ እስኚ ድላቜን አደባባይ ወይም ኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት አደባባይ ዹሚደሹግ ሲሆን፤ በእለቱም አጠቃላይ
ዚሀገሪቱን ሁኔታ ዹሚገልፁ ንግግሮቜ እና መፈክሮቜ ይደሹጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።¾
(ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ ዚሚቡዕ ሜይ 29 ዕትም)

EPRDF, no identity and no vision

FOR  IMMEDIATE  RELEASE
EPRDF, no identity and no vision
                                                                                                                March 28 2013
For the past twenty one years, the Tigray People Liberation Front (TPLF) that has no mandate to rule Ethiopia has actually ruled Ethiopia with iron fist dashing on the  Trojan horse,  the  EPRDF ( Ethiopian People Revolutionary Democratic Front).  The EPRDF, a political front; composed of a hodgepodge of ethnically assembled organizations, is a hollow group of ethnic demagogues created by its late leader to materialize his lifelong dream of dividing Ethiopia along ethnic lines. Ironically, the EPRDF that blatantly boasts to have averted the disintegration of Ethiopia, firmly stood up to the dreams of its creator and augmented the fragmentation of Ethiopia, the very country it calls home.
On Saturday March 23, 2013, the EPRDF started its 9th and possibly what could be its last congress with an embarrassing; and to the vast majority of Ethiopians with a pointless theme of – “The Thoughts of Meles”.  In fact, if there is one good cause served by the 9th EPRDF congress, it should be that, the Trojan horse EPRDF proved to the Ethiopian people that it is a party in existence with a borrowed identity that rules over a nation of ninety million people with a dead vision of a deceased man. The EPRDF is a party that lives in the past, failed to cease the moment and has no vision for the future.
The four-day congress that ended on Tuesday came to an end with exactly the same hollowness that it started. To the surprise of its own members and diehard supporters, the four -day congress looked like much of a eulogy of a man (dead for seven months) than an occasion to map a vision for Ethiopia’s future.  Despite all indications of the nation’s chronic problems of ethnic conflict, poverty, human rights abuse, deteriorating living conditions, and alarming outflow of skilled manpower, the EPRDF vowed to extend its grip on power and carry on the same old failed policies of the past. All in all, the handmade toy, the EPRDF, shamelessly told the Ethiopian people that it has no vision of its own and nothing new on its plate.
Ginbot 7, Movement for Justice, Freedom and Democracy not only invalidates the resolution of the 9th congress of the EPRDF, but it also extends its call to the Ethiopian people inside and outside Ethiopia to come together and fight in unison to stop the implementation of a policy that has a hard to reverse  detrimental effect on our nation. Ginbot 7 reiterates its perennial message to the Ethiopian people and to the international community at large that there are much better alternatives to the tested and failed policies of the EPRDF that benefit the interest of the Ethiopian people, the Horn of Africa and all other parties’ involved. The international community, donor nations and most importantly, the EU, United Kingdom and the United States must come to their senses and acknowledge that freedom; justice and democracy are God given human values that the people of Ethiopia thirst for just like the British and the American people.

May 28, 2013

ዚእንክርዳድ ውርስ ክፍል ፩ /The Inheritance of Chaffs/

Part-I/
በሚኚት ስምኊን “ዚሁለት ምርጫዎቜ ወግ“ ዹተሰኘ መፅሐፉን በሞራተን አዲስ ሲያስመርቅ ´´áŠ áˆ®áŒŒá‹‹ ኢትዮጵያ እዚፈራሚሰቜ በአዲሷ ኢትዮጵያ እዚተተካቜ…………´´ እያለ ተናግሮ ነበር።በእርግጥ በሌላ በኩል ´´áˆ€áŒˆáˆ­ ማለት ብሄር ብሄሚሰቊቜ እንጂ ወንዝና ተራራው አይደለም፥ዚግዛት አንድነት ጉዳይ ዚነፍጠኝነት ጉዳይ ነው´´ እያሉ ዚወያኔ ርዕሳን ሲናገሩ መስማቱንም ለምደነዋል።
እስኪ በቅርቡ በተዘጋው ዚወያኔ ዹ21 ዓመት ዚመጀመሪያ ምዕራፍ ´´áŒˆáŠá‰£áŠ“á‰µ´´ ያሏትን ኢትዮጵያ እና ለትውልድ ያስተላለፉትን ውርስ እንመልኚት።
ሀ. áˆ›áˆ…በራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውርሶቜ
1.    áˆ˜áˆ€á‹­áˆáŠá‰µ /Illiteracy/
በኢትዮጵያ ዚወታደራዊው አስተዳደር ሲወድቅ ኚመሀይምነት ዹተላቀቀው ዚህብሚተሰብ ክፍል 60% ሲሆን ይህም ኹነበሹው ሃምሳ ሁለት ሚሊዹን አጠቃላይ ህዝብ ውስጥ 31.2 ሚሊዹን ይደርስ ነበር።ኹ21 ዓመት ዚወያኔ አገዛዝ በኋላ ኚመሃይምነት ዹተላቀቀው ዚህብሚተሰብ ክፍል ዚቁልቁለት ጉዞውን ቀጥሎ 30% ብቻ ሲሆን ይህም ኹ80ሚሊዹን አጠቃላይ ህዝብ ውስጥ መፃፍና ማንበብ ዚሚቜለው 24 ሚሊዹን ሲሆን ኚዛሬ 21ዓመት በፊት ኹነበሹው በ7.2 ሚሊዹን ያንሳል።በተጚማሪም 35.2 ሚሊዹን አዳዲስ መሃይሞቜ ሲፈጠሩ በሀገሪቱም ያለው አጠቃላይ ዹመሃይም ቁጥር 56 ሚሊዹን ደርሷል።
መሀይምነት በራሱ ዹጹለማ ኑሮ ኹመሆኑ ባሻገር መሀይም ማህበሚሰብ ለኢኮኖሚው ኚሚያደርገው አስተዋፆ ይልቅ በሀገር ዕድገት ላይ ሾክም እና ጎታቜ መሆኑ በተለይ አሁን ካለው ዹአለማቀፍ ሁኔታ አንፃር ዚመሀይምነት ጠባሳ በሀገራቜን ላይ ዚሚያስኚትለውን ጫና በዚህ አጭር ፅሁፍ መዘርዘር ዚማይታሰብ ሲሆን አጠቃላይ ሂደቱ ግን በሻዕቢያ ተፀንሶ በወያኔ እዚተተገበሚ ያለው ‘‘ዚመቶ አመት ዚቀት ስራ‘‘ ውጀት ሊሆን እንደሚቜል ይገመታል።
ለመሆኑ ኹ20 በላይ ዩኒቚርሲቲዎቜንና በርካታ ትምህርትቀቶቜን ዚገነባው ዚወያኔ መንግስት ‘‘ቆመንልሃል“ ዹሚለውን ህዝብ እንዎት ኚመሃይምነት ዚቁልቁለት ጉዞ ሊታደገው አልቻለም?
1.1  á‹šá‰°áŒˆáŠá‰¡á‰µ ተቋማት አላማ ፖለቲካዊ አጀንዳ መያዛ቞ውእንደሚታወቀው ዚወያኔ መንግስት በዹክልሉ ብሎም በዞን ኚተሞቜ ‘‘ዩኒቚርሲቲ“ እያለ በርካታ ተቋማትን ዹኹፈተ ሲሆን በተጚማሪም በዚወሚዳውና በዹቀበሌው ‘‘ትምህርት ቀት“ መክፈቱ ይታወሳል።ይሁን እንጂ ይህ ሁኔታ ኹላይ ሲታይ /From surface value/ በጎ ዚልማት ጅማሬ ቢመስልም ወደውስጥ ዘልቀን ስናዚው ግን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚያስቜል ሁኔታ ፖለቲካዊ አጀንዳ ዚያዘና በአካባቢው ላይ ዚወያኔን ተቀባይነት ለማስገኘት ዹሚደሹግ ሩጫ ነው።ለምሳሌ ወያኔ በምርጫ -97 በጉራጌ ዞን መሾነፉን ተኚትሎ ‘‘ጉራጌው ኹነፍጠኛው ጋር ወግኗል“ በሚል በዞኑ ኹፍተኛ ቅስቀሳ ዹተደሹገ ሲሆን እንደ አርቲስት መሐሙድ አህመድ አይነት ስመጥር ዚአካባቢው ተወላጆቜ በተገኙበት ኢ.ህ.አ.ዮ.ግ. ለጉራጌ ህዝብ መብት ´´áˆ˜áŠšá‰ áˆ­´´ ያደሚገው አስተዋጜኊ በሰፊው ኹተነገሹ በኋላ መለስ ዜናዊ በወልቂጀ ኹተማ በመገኘት ዚወልቂጀ ዩኒቚርሲቲን ዚመሰሚት ድንጋይ አኑሯል።ይህም በዋናነት ዚጉራጌ ህዝብ በወያኔ ላይ ያለውን ቅሬታ ለማለዘብ ተብሎ ዹተደሹገ ዚፖለቲካ ስራ ነበር።ዚእነዚህና መሰል ተቋማት ዚመጀመሪያ አላማ ፖለቲካዊ ተቀባይነትን ለማግኘት ብቻ ዚተመሰሚቱ በመሆኑ ዚወያኔ መንግስት ህዝቡን በጅምላ ለትምህርት ማንቀሳቀስ /Mass Mobilization/ ተስኖታል።
በቂ ዚትምህርት ተቋማት ባልተሟላበት ዚወታደራዊው መንግስት ዘመን ሰዎቜ ዛፍ ስር ሳይቀር እንዲማሩ ህዝብን ማንቀሳቀስ በመቻሉ ቢያንስ 60% ዚሀገሪቱ ህዝብ ኚመሀይምነት መላቀቅ ሲቜል በወያኔ ዹአገዛዝ ዘመን ግን ዚተሻለ ቁጥር ያላ቞ው ትምህርትቀቶቜና ዹኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማት በተገነቡበት ሁኔታ ዚመሀይምነት አኃዙ ወደላይ ማሻቀቡ በእርግጥ ኹወንዝና ተራራ በላይ ህዝቊቜን ዚመውደድ ኢህአዎጋዊ ፍቅር ውጀት ይሆን?´´á‰ áŠ–áˆ« ዹተለሰነ መቃብር ´´ እንዲል መጜሐፍ።ወትሮስ መቃብር ዚቱን ያህል ቢያስውቡት አጜም እንጂ ህያው አይኖርበት።
1.2 á‰µáˆáˆ…ርትን ለማስፋፋት በሚል ሜፋን ቀጣይነት ያለው እርዳታ ለማግኘት á‰ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« ታሪክ እንደወያኔ መንግስት ኚለጋሜ ሀገራት ዹውጭ እርዳታ ያገኘ መንግስት ዹለም።ይህም ሊሆን ኚቻለባ቞ው ምክንያቶቜ አንዱ ወያኔ በኢትዮጵያ ትምህርትን አስፋፋለው ዹሚለው ፕሮፖጋንዳ ሲሆን ለጋሜ ሀገራትንም ለማማለል በዚአካባቢው ዚሚገነቡ ተማሪ አልባ ትምህርት ቀቶቜ በዋናነት ዚሚጠቀሱ ናቾው።ለጋሜ ሀገራትም ስለተገነቡት ትምህርት ቀቶቜ እንጂ በውስጡ ስለሚማሩት ተማሪዎቜ አሀዝ ትኩሚት ስለማይሰጡ በትምህርት ማዳሚስ ሜፋን ስም ወያኔ ለሚያካሂደው ንግድ አመቺ ሁኔታን ሲፈጥር በኢትዮጵያ ውስጥም መሀይምነት እጅግ እንዲስፋፋ አድርጓል።
2. á‹šáŠšá‹á‹µáˆ…áŠá‰µáŠ¥áŠ“áŠ¢-ፍትሀዊዚሀብትክፍፍል /Abject Poverty and Unfair Wealth Distribution/
ወጣቱ ደራሲና ጋዜጠኛ መሐመድ ሰልማን ´´á’ያሳ መሐሙድ ጋ ጠብቂኝ´´ በተሰኘው መጜሐፉ ሁለት ኢትዮጵያዎቜ እንዳሉ ይነግሹናል።ዚኢቲቪዋ ኢትዮጵያና በገሃዱ አለም ዚምናውቃት ኢትዮጵያ።
ሚሊዹነር ገበሬዎቜ እንደአሞን ዚፈሉባት፣ዚኢኮኖሚ ዕድገቷ ዚምዕራቡን አለም እጅግ በማሳሰቡ ኒዎ ሊበራሎቜ ዕድገታቜሁን ካላቆማቜሁ እያሉ ባለስልጣኖቿን ዚሚወተውቱባት፣አንድ ስማ቞ው እንዳይጠቀስ ዹፈለጉ ዹውጭ ሀገር ዲፕሎማት ሌሎቜ ዚአፍሪካ ሀገራት ኚሷ ብዙ ሊማሩ እንደሚገባ቞ው ዚመሰኚሩላትን ዚኢቲቪዋን ኢትዮጵያ ለወያኔና ሆድ አደር ጋዜጠኞቹ እንተወውና በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ዚድህነት መጠንና አይነተኛ መገለጫዎቹ እንዲሁም ስላለው ኢ-ፍትሀዊ ዚሀብት ክፍፍል እንመልኚት።
2.1 áŠ¥áŒ…áŒ ዹኹፋ ድህነት /Abject Poverty/:- á‰ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« ያለውን ዚድህነት መጠን በቁጥር ኹመግለፅ ይልቅ ዋና ዋና መገለጫዎቹን ማዚቱ ዹበለጠ ግንዛቀ ይፈጥርልናል።ይህም ማለት ትርፍራፊ ምግቊቜ እንደ ምግብ መሞጣ቞ውን እና አብዛኛው ህዝብ ኚቻለ በቀን ሁለቮ አልያም በቀን አንድ ጊዜ መብላቱን እንደዋና ዚድህነት መገለጫ ሳናነሳ ማለት ነው።
2.1.ሀ. á‹šáŒ…ምላ ስደት/Mass Migration/  á‰ áŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« ቅድመ ወያኔ ታሪክ ዚኢትዮጵያ ወጣት በብዛት ዚተሰደደበት ወቅት ቢኖር ዹቀይ ሜብር ዘመን ሲሆን ይህም በወቅቱ በነበሹው ዚፖለቲካ አፈና እንጂ እጅግ ስር በሰደደ ድህነት ምክንያት አልነበሹም።ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት አብዛኛው ዚኢትዮጵያ ወጣት በጅምላ እዚተሰደደ ሲሆን በሀገር ቀት ያለውም ቀዳሚ ምርጫው ስደት እንደሆነ በቅርብ ዚወጣውን ዹአለማቀፉ ዚቀውስ አጥኚ ቡድንን /International Crisis Group/ ጥናት ማዚት ብቻ በቂ ነው።
አብዛኛው ስደተኛም ዚኢኮኖሚና ዚፖለቲካ ስደተኛ ሲሆን ኚዕድሜ አንፃር በሁሉም ዚዕድሜ ክልል፣ኚፆታ አንፃር ሁለቱም ፆታዎቜ፣ኚትምህርት ደሹጃ አንፃር ዚተማሩትም ያልተማሩትም ዚተካተቱ ሲሆን ህይወታ቞ው አደጋ ላይ ሊወድቅ እንደሚቜል እያወቁ እንኳን ስደትን መምሚጣ቞ው ዜጎቻቜን በሀገራ቞ው መሰሚታዊውን ነገር እንኳን ማግኘት እንዳልቻሉ ኚማሳዚቱም ባሻገር ዚድህነቱም መጠን ምን ያህል ስር እንደሰደደ ያሳዚናል።
ሀገራቜን ተማሪዎቿን እስኚ ኹፍተኛ ተቋማት ለማድሚስ ዋጋ ያልኚፈለቜበት ያህል ዛሬ በህሊና ብስለት፣በዕውቀትና በዕድሜ አፍላ ዹሆኑ ወጣቶቻቜንን በዚስደተኛ ጣቢያው ተጥለው ስናይ ድህነት ኹጊዜ ወደ ጊዜ ዚግዛት አድማሱን እያሰፋ ኚገዢዎቻቜን እና በዙሪያ቞ው ካሉት ሰዎቜ ውጪ ያለውን ሰፊውን ዚህብሚተሰብ ክፍል እጅ ተወርቜ ጠርንፎ እንደያዘው ፍንትው አድርጎ ያሳዚናል።
2.1.ለ. áŠšá‹µáˆ…áŠá‰µ ጋር ግንኙነት ያላ቞ው በሜታዎቜ ሥርጭት /Poverty Related Diseases/  áŠšá‹µáˆ…áŠá‰µ ጋር ቀጥታ ግንኙነት ካላ቞ው በሜታዎቜ በዋናነት ኀቜ አይ ቪ ኀድስ፣ዚሳምባ ነቀርሳ፣ወባ፣ዚልጅነት ልምሻ ዚመሳሰሉት ሲሆኑ ያለምንም ማጋነን ኹላይ በተዘሚዘሩት ዚበሜታ አይነቶቜ ዹተጠቁ እና እዚተጠቁ ያሉ በርካታ ዜጎቜ ኚሚገኙባ቞ው ሀገሮቜ መካኚል ኢትዮጵያ አንዷ ስትሆን በተለይ ዚኀቜ አይ ቪ ኀድስ ስርጭት እዚህ ደሹጃ ዹደሹሰው በወያኔ ዘመን ነው።ለዚህም እንደማስሚጃ ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ በአንድ ወቅት ሲናገሩ ደርግ ወድቆ ኚአሜሪካ ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ በዚሆ቎ሎቜ እንግዳ መቀበያ ላይ /Reception/ ኮንዶም ይቀመጥ ዹነበሹ ሲሆን ወያኔ አዲስ አበባ ኚገባ ኚጥቂት ወራት በኋላ ግን ይህ ልምድ ዹተቋሹጠ ሲሆን ቢያንስ ኹ1983-1988 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በወያኔ መንግስት በኩል ግንዛቀን በህብሚተሰቡ ውስጥ ለመፍጠር ዚተሰራ ነገር ባለመኖሩ በርካታ ህዝብ በዚህ በሜታ ሊጠቃ ቜሏል።በሌላ በኩል ኀቜ አይ ቪ ኀድስም ሆኑ ሌሎቜ በሜታዎቜ ለወያኔ ዹውጭ እርዳታ መለመኛ መንገድ መሆናቾውን ልብ ልንለው ዚሚገባ ጉዳይ ነው።
2.1.ሐ. á‹šáŒŽá‹³áŠ“ ተዳዳሪነት /Street Life and Loitering/መጠኑ ይለያይ እንጂ ዚጎዳና ተዳዳሪነት በአብዛኛው አለም ዹተለመደ ሲሆን ለምሳሌ በጀርመን፣በኢንግላንድና በስካንዲኔቪያን ሀገሮቜ ሁሉም ዜጋ ዚመኖሪያ ቀት ዹሚሰጠው ሲሆን በነዚህ ሀገራት ዹሚገኙ ዚጎዳና ተዳዳሪዎቜ ይህን ህይወት በፈቃዳ቞ው ፈልገው ዚሚያደርጉት ነው።
ወደ ኢትዮጵያ ሁኔታ ስንመለስ ግን በቅርቡ ዚወጡ መሚጃዎቜ እንደሚያመለክቱት ድህነት ገፍቶ ወደ ጎዳና ዚጣላ቞ው ሰዎቜ ሁለተኛ ዲግሪ ያላ቞ው ምሁራን፣ቁጥራ቞ው በርካታ ዹሆኑ ዚመጀመሪያ ዲግሪ ያላ቞ው ምሩቃን፣በተለያዩ መስሪያ ቀቶቜ በተለያዚ ሙያ ያገለግሉ ዚነበሩ ዜጎቜ ሲገኙበት ለዚህም እንደመንስኀ ዚሚነሳው ዜጎቻቜን ዚወያኔ አባል ካልሆኑ አልያም ፖለቲካዊ አቋማቾው ወያኔን ዹሚጋፋ ኹሆነ በሰፊው ዚድህነት ባህር ውስጥ እንዲደፈቁና ለጎዳና ህይወት እንዲዳሚጉ ይገደዳሉ።
ኹዚህም ባሻገር በገጠር አካባቢ መሬት ዚፖለቲካ መሳሪያ ኹመሆኑ በተጚማሪ ገበሬው በማዳበሪያ ዕዳ ኑሮው ስለሚናጋ በርካታ ህዝብ ወደኹተማ እንዲፈልስ በዚያም በጎዳና ላይ ኑሮውን እንዲገፋ ይደሹጋል።
2.2 áŠ¢-ፍትሀዊ ዚሀብት ክፍፍል /Unfair Wealth Distribution/:-ሀገራቜን ኢትዮጵያ ኹዕዝ ኢኮኖሚ ተላቃ ገበያ መር ኢኮኖሚ እዚተኚተለቜ ነው ኚተባለ ኚሁለት አስርት ዓመታት በላይ ቢሆንም በማህበሚሰቡ ውስጥ እዚታዚ ያለው ዚሃብት ክፍፍል ግን ፍጹም ገበያ መር ኢኮኖሚ ኚሚያስኚትለው ተጜዕኖ ተመጣጣኝ ካለመሆኑ ባሻገር በሃገሪቱ ውስጥም እዚታዚ ነው ዚሚባለው “ዕድገት“ ዚጥቂት ቡድኖቜ ዕድገት ሆኖ እናገኘዋለን።
በመሆኑም በሃገሪቱ ውስጥ ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚኚፋ ለመጣው ድህነትና ኢ-ፍትሐዊ ዚሀብት ክፍፍል ዐይነተኛ ሚና እዚተጫወቱ ዚሚገኙትን ጉዳዮቜ እንመልኚት።
2.2.ሀ. á‹šá–ለቲካ ተቋማት አወቃቀር /The Nature of Political Institutions/በግልፅ እንደሚታዚው ዚወያኔ መንግስት ዚሃገሪቷን ዚፖለቲካ ተቋማት ያዋቀሚበት መንገድ ሁሉን አሳታፊ /All-inclusive/ ያልሆነ ይልቁንም ጥቂት ዚአንድ አካባቢ ተወላጅ ኅሩያን /Elites/ በዋናነት ዚሚያሜኚሚክሩት መዝባሪ ተፈጥሮ /Extractive Nature/ ያለው ሆኖ እናገኘዋለን።ይህ አይነቱ ዚፖለቲካ ተቋማት አደሚጃጀት በባህሪው እውነተኛ መድብለ ፓርቲ /Bona fide Pluralism/ እንዳይፈጠር በግልጜም ይሁን በህቡዕ /Overtly or Covertly/ ስለሚኚላኚል ተጠያቂነት ዚሌለበት ገደብ አልባ ሥልጣን /Unconstrained Power/ በጥቂት ኅሩያን እጅ በህግ ላልተገደበ ጊዜ እንዲቆይ ያደርገዋል።ይህም መዝባሪ ዚፖለቲካ ተቋም ለሀገር እና ለህዝብ ዘለቄታዊ ጥቅም ኚመስራት ይልቅ ዚጥቂት ቡድኖቜን ሥልጣን ለማጠናኚሪያነት ዚሚሚዱ አቻ መዝባሪ ዚኢኮኖሚ ተቋማትን /Extractive Economic Institutions/ በመገንባት ላይ ይወሰናል።ኹዚህም ባሻገር ዚስርዐቱ ዋነኛ አጀንዳ ዚፖለቲካ ሥልጣኑን ማስጠበቅ በመሆኑ ዚሀገሪቱን አብዛኛ መዋዕለ ነዋይ ህዝብን ለማፈን ዹተጋነነ ዚፖሊስ ኃይልን እና ዚደህንነት ተቋማትን በመገንባት፣በካድሬ ምልመላ እና ስልጠና እንዲሁም በድርጅታዊ ተግባራት ላይ ስለሚያውለው በስርዐቱ ዙሪያ ካሉ ጥቂቶቜ ውጪ ያለው ሰፊው ዚህብሚተሰብ ክፍል ለገዥዎቹ ዚሀብት ምንጭ ኹመሆን በዘለለ ዚሃገሪቱ ዚሀብት ተካፋይ ሊሆን አይቜልም።በተጚማሪም በዚህ ዓይነት ዚፖለቲካ ስርዐት ውስጥ በሙስና ላይ ዹሚኖሹው ተጠያቂነት ለዘብተኛ በመሆኑ ኚግለሰብ ጀምሮ እስኚተደራጀ ዚሙስና ወንጀል መመልኚት ዹተለመደ ተግባር ይሆናል።ለዚህም ነው በኢትዮጵያ ዹሚገኙ ዚፖለቲካ እና ዹጩር ሹመኞቜ ዚሀገሪቱን ሀብት በመዝሹፍ እና በማሞሜ ተግባር ዚተጠመዱት።
2.2.ለ. á‹šáŠ¢áŠ®áŠ–áˆš ተቋማት አወቃቀር /The Nature of Economic  Institutions/በኢትዮጵያ ያለው ዚኢኮኖሚ ተቋማት አወቃቀር በዋናነት በሥልጣን ላይ ላለው ቡድን ተጚማሪ ኃይልን በሚፈጥር መልኩ መዝባሪ ባህርይ /Extractive Nature/ ያለው ሲሆን ዚሀገሪቱ ዚተፈጥሮ ሃብትም ኹሞላ ጎደል በዚህ ቡድንና በሥልጣኑ ዙሪያ ባሉ ዚጥቅም ተሳሳሪዎቜ /Cronies/ እጅ ይገኛል። በአሁኑ ጊዜም ኹፍተኛ ብዥታ እዚፈጠሚ ያለው ዚእዚህ አናሳ ቡድንና በሥልጣኑ ዙሪያ ያሉ ጥቅመኞቜን ዚሀብት ዕድገት ዹመላው ህብሚተሰብ እና ዚሀገሪቱ ዕድገት አስመስሎ ዚማቅሚቡ ጉዳይ ነው።
በመሰሚቱ መዝባሪ ዚፖለቲካ እና ዚኢኮኖሚ ተቋማት እርስ በእርሳ቞ው ተመጋጋቢ ሲሆኑ እንዲህ አይነቱ ዚፖለቲካ ተቋም ሥልጣንን ያለገደብ በጥቂቶቜ እጅ በማድሚግ አቻ ዹሆኑ ዚኢኮኖሚ ተቋማትን ለመፍጠር፣ዚኢኮኖሚ ተቋማቱን በተለዹ ሁኔታ ተጠቃሚ ዚሚያደርጉ ህጎቜንና አዋጆቜን ለማፅደቅ፣በገበያው ላይ ተጜዕኖ ለመፍጠር፣ነጻ ፉክክር እንዳይኖር እንቅፋቶቜን ለመፍጠር /To erect entry barriers/ ሲሚዳ በምላሹ እነዚህ መዝባሪ ዚኢኮኖሚ ተቋማት ዚሀገሪቱን ሀብት ኚአብዛኛው ህዝብ በመዝሹፍ በሥልጣን ላይ ያለውን ቡድን በሀብት እና ኃይል ይበልጥ እንዲጠናኚር ያደርጉታል።
ለዚህም አይነተኛ ማሳያ ዹሚሆነን ዚህወሃት ቡድን ዚፖለቲካ ሥልጣኑን ያለገደብ ሲቆጣጠር “ኀፈርት“ ዚሚባል መዝባሪ ግዙፍ ዚንግድ ኢምፓዚር ዚገነባ ሲሆን ኚኀፈርት ዹተሹፈውን ክፍተት ዚፖለቲካ እና ዹጩር ባለስልጣናት እንዲሁም በሥርዓቱ ዙሪያ ዚሰፈሩት ጥቅመኞቜ በግላቾው እና በዘመዶቻ቞ው ስም ባስመዘገቧ቞ው ዚንግድ ተቋማት ስልጣንን ተገን ያደሚገ ካፒታሊዝም /Crony Capitalism/ መመስሚት ቜለዋል።በመሆኑም ዚወያኔ መንግስት በዹጊዜው ዚሚያወጣ቞ው ባለሁለት አሃዝ “ዕድገት“ በእርግጥም ዚኢትዮጵያ ዕድገት ሳይሆን ዚእነዚህ ጥቂት ቡድኖቜ ግዙፍ ዚንግድ ተቋማት እድገት ሆኖ እናገኘዋለን።
 3. áˆ™áˆµáŠ“ /Corruption/
´´áˆáˆ­áŠ® ፈጠነ፥ብዝበዛ ቞ኮለ´´
በአንድ ወቅት በኢትዮጵያን ሪቪው /ethiopianreview.com/ ድሚ-ገጜ ላይ ´´áŠ áˆµáˆ«áŠ áŠ•á‹°áŠ›á‹ ትዕዛዝ´´ /The Eleventh Commandment/ ዹተሰኘ ጜሑፍ ጜፌ ነበር።በእርግጥ አስራአንደኛው ትዕዛዝ ማለት ´´á‰ á–ለቲካቜን እስካልመጣህ፥ዹምንልህንም እስካደሚግህ ድሚስ ብትሰርቅም፣ብትዘርፍም ምንም አይደል´´ ዚምትለዋ ዚወያኔ ያልተፃፈቜ ህግ ናት።
ለዚህም ነው አንድ ዚወያኔ ባለስልጣን ለገጣፎ አካባቢ በስሙና በቀተሰቊቹ ስም 60 /ስልሣ/ ዚመሬት ይዞታዎቜን ዚያዘ፣ለዚህም ነው በሲፒኀ ስኬል መሠሚት ደሞዛቾው ኹ5000.00 /አምስት ሺህ/ ብር ዚማይበልጥ ጄነራሎቜ ኹ10,000.00 /አስር ሺህ/ ዶላር በላይ ዚሚኚራዩ ቀቶቜን ዚገነቡት፣ለዚህ ነው ዚሚንስትሮቻቜን ሚስቶቜ ኚቻይና አዲስ አበባ እንዲሁም ኚዱባይ አዲስ አበባ ዚሚመላለሱ ሲራራ ነጋዮ ዚሆኑት፣ለዚህም ነው ዚቀድሞዋ ቀዳማዊ እመቀት አዜብ መስፍን በአንድ ቀን ዚአልባሳትና ጌጣጌጥ ግብይት 1.2 ሚሊዹን ዩሮ ወይም በአማካይ 26.4 ሚሊዹን ብር ማውጣታ቞ውን ኚስፔን ጋዜጊቜ ያነበብነው።
እንዲሁ ለማሳያ ያህል ጠቀስኩት እንጂ ኹግልገል ካድሬዎቜ ጀምሮ እስኚሚንስትሮቻቜን እና ዹጩር ሹመኞቜ ድሚስ ዚመግባቢያ ቋንቋቾው ሁሉ ´´á‰ á‹‹áˆŒá‰µáˆ… አስብ፥በእጅህ ተናገር´´ ኹሆነ ዘመናት አልፈዋል።ዛሬ ኚጥንት ጀምሮ በሙስና ኚሚታወቁት ናይጄሪያን ኚመሳሰሉ ሀገራት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀን በሙሰኛ ሀገራት ዹደሹጃ ሠንጠሚዥ ዚመጀመሪያው ሚድፍ ላይ እንገኛለን።
በሌላ በኩል በ1993 ዓ.ም. ዹተቋቋመው ´´á€áˆš-ሙስና ኮሚሜን´´ በመባል ዚሚታወቀው መስሪያ ቀት ልክ እንደ ፍርድ ቀቶቜ ሁሉ ዚህዝብ አመኔታ ዹሌለው ተቋም ሲሆን ቀዳሚ አላማውም አስራአንደኛውን ትዕዛዝ ዹሚተላለፉ ዚወያኔ ባለስልጣናትን ለመቅጣት እንጂ በርግጥም እንደስያሜው ሙስናን ለመዋጋት ዹቆመ አይደለም።
» » » »(ክፍል ፪ ይቀጥላል)« « «
» » » »(Part II to be continued)« « «

(በዳዊት ፋንታ)
(By: Dawit Fanta)

“አባይ ይገደብ፤ ኢህአዎግም ይገደብ፤ አባይ ይቀዚስ ኢህአዎግም ይቀዚስ!” – ኚአቀ ቶኪቻው


                                                                አቶ በሚኚት

“ዚዘመናት ብሶት ዹወለደው ጀግናው ዚኢህአዎግ ሰራዊት ኹዚህ በፊት ደርግ ሲጠቀምበት ዹነበሹውን ዚሬድዮ ጣቢያ ለሰፊው ህዝብ áŒ¥á‰…ም ተቆጣጥሮታል፡፡ ጉንቊት ሃያ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ መህሚት!” አለ ታጋዩ…“ዚዘመናት ብሶት ዹወለደው ጀግናው ዚኢህአዎግ ሰራዊት ኹዚህ በፊት ደርግ ሲጠቀምበት ዹነበሹውን ዚሬድዮ ጣቢያ አሁን ደግሞ áˆˆáˆ«áˆ± ጥቅም ተቆጣጥሮታል፡፡ ቆጣጥሮታልም፤ ግንቊት ሃያ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ መህሚት!” አልኩ እኔ…“ኢህአዎግ ደርግን ደመሰሰ እና ሌላ ቀዳበት” አለ ልጅ ያሬድ! ”ኢህአዎግ ደርግን ደምስሶ በደርግ ዜማ ሌላ ቀዳበት” አልኩ እኔ á‹›áˆ¬ ግንቊት ሃያ ነው፡፡ áŠ áŠá‹› ፀጉራ቞ውን አሳድገው አዲሳባ ዚገቡ ሰዎቜ ዲሞክራሲን እና መልካም አስተዳደር ያሳድጉልናል… ብሎ ተስፋ ዚጣለባ቞ው áˆáˆ‰ በ቎ስታ ብለው ኚጣሉት እነሆ ሃያ ሁለት አመት እንደዋዛ ሆናቾው፡፡መልካም አስተዳደሯንም ለራሳ቞ው እያደሯት፤ ዎሞክራሲዋንም ራሳ቞ው እዚኮመኮሟት ህብሚተሰቡን እንቁልጭልጭ አሉት፡፡ዛሬ ዚግንቊት ሃያ በዓል ሲኚበር ዚአባይ ወንዝን ዚማስቀዚስ ስራ ይሰራል ተብሏል፡፡ ወንዙ ተቀይሶ ምን ላይ ሊሆን ነው… እንዎትነው ነገሩ በሳፋ ነው እንዎ ግድቡ ዚሚሰራው… ብዬ ልጠይቅ ወይስ አልጠይቅ…!አስታውሳለሁ፤ “አባይ ይገደብ በቃ” ብለው ጠቅላዩ ዚወሰኑት ኚሁለት አመት በፊት “በቃ” በሚል ሀይለ ቃል …ኢህአዎግይበቃዋል ግንቊት ሃያን ዘንድሮ ለመጚሚሻ ጊዜ እናኚብራለን ኹዛም ለድጋፍ ሰልፍ ወጥተን በዛው እንቀራለን፡፡ ኢህአዎግእስካልወሚደ ድሚስም እቀታቜን አንገባም…. ዹሚል እንቅስቃሎ በፌስ ቡክ በኩል ተጀምሮ ዹነበሹ ጊዜ ነው፡፡በዚህ በ”በቃ” ጊስ እነ ርዮት አለሙ እነ ውብሞት ታዬ እነ አቶ ዘሪሁን ገብሚ እግዚአብሄር እነ ሂሩት ክፍሌ ወድያው ለእስርሲዳሚጉ ቀስ በቀስ ደግሞ ሌሎቜም ለቃሊቲ እና ለቂሊጩ ተዳርገዋል፡፡ (በተለይ ዹነዚህ ወዳጆቌን ፍርድ ሂደት ስኚታተል ነበር እናአጋነንክ ቢሉኝም ባይሉኝም ዚአቃቀ ህግ ማስሚጃ “በቃ ዹሚለውን ዚፌስ ቡክ እና ዚአደባባይ እንቅስቃሎ ትኩር ብላቜሁአይታቜኋል” ዹሚል ነበር)እንቅስቃሎው በፌስ ቡክ ተጀምሮ በዚአደባባዩም “በቃ” ዹሚል ሃይለቃል በመፃፍ ተሟሙቆ ዹቀጠለ ነበር፡፡ በርካቶቜም ግንቊትሃያ መስቀል አደባባይ ዹሚፈጠሹውን ተዓምር እያሰቡ አንድም ደስታ አንድም ፍርሃት ሲፈራሚቅባ቞ው አንደነበር ትዝ ይለኛል፡፡ይሄኔ አቶ መለስ ፈርሾው ዘዚዱ፤ (ሁል ጊዜ ቁጭ ብለው አሰቡ… እያልንኮ ፍራሜ ዹሌላቾው አስመሰልና቞ው… “ፈርቾው” ማለትፍራሜ ዘርግተው እጅግ በተመስጊ ማሰብ ማለት ነው…) አስበው አስበውም፤ “ለምን አባይን አንገድበውም…” አሉ እርሳ቞ውብለው እምቢ… እንዎት… ለምን… በምን… አይባልምና እሺ እሺ ተብሎ ተጀመሹ፡፡ ዹዛን ጊዜውን ግንቊት ሃያም መንግስታቜንለአባይ ግድብ ድጋፍ ሰልፍ ውጡልኝ፡፡ አለ… በዛውም ዚህዝቡ ዹተቃውሞ ሃሳብ ተገደበ፡፡ዚአቶ መለስን ብልጠት በመኮሚጅ ፈተናዎቜ ይታለፋሉ ብለው ዚሚያምኑት አቶ በሚኚት ደግሞ ዛሬ እነሆ በግንቊት ሃያው አባይወንዝን ዚማስቀዚስ ስራ እነደሚሰራ በ቎ሌቪዥና቞ው ብቅ ብለው ነገሩን፡፡ጥሩ ኮርጀዋል…! አኮራሚጃ቞ው ስም ሁሉ ሳይቀር እንደሚቀዳ አይነት ኮራጅ ነው፡፡ህዝቡ ይህንን ዜና ሲሰማ ምን አላቾው… ዹሚለውን ቀት ለቀት ሄደን መጠዹቅ ብንቜል ጥሩ ነበር፡፡ መጠዹቅ ባንቜል ግንመጠርጠር እንቜላለን እና አንዲህ እንጠሚጥራለን፤“አባይ ይገደብ፤ ኢህአዎግም ይገደብ፤ አባይ ይቀዚስ ኢህአዎግም ይቀዚስ!” ሳይላ቞ው አይቀርም፡፡

ወያኔ እና እኛ ሙስና ስንል

በቅርቡ በሀገር ውስጥ ገቢና በጉሙሩክ አገልግሎት መስሪያ ቀት ዚሚሰሩ ጥቂት ባለስልጣኖቜና ተባባሪ ዚተባሉ ግለሰብ ነጋዎዎቜ፣ በሙስና ተወንጅለው ወህኒ መውሚዳ቞ውን ተኚትሎ ወያኔ ፀሹ-ሙስና ድርጅት ለመምሰል ኚተግባሩ ዹበለጠ ዚኚበሮ ድምጜ እያሰማን ይገኛል። አንዳንድ ዹዋህም ይህን ኚበሮ በመስማት ሙስናን ለማጥፋት ዘመቻ ዹተጀመሹ መስሏ቞ው ተስፋ ሲያደርጉ ይታያል።
በመሰሚቱ ሙስና በወያኔ ስርአት ውስጥ ዚስርአቱ መቆሚያ ምሰሶ ኹሆነ ውሎ አድሯል። በሀገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ተቋማት እዚተመናመኑ በሄዱበት ፍጥነት ነው ሙስና እዚደራ ዹሄደው። ኹላይ እስኚታቜ በተዘሹጋው ዚወያኔ ስርአት ውስጥ ኚቁንጮ ባለስልጣናት እስኚታቜኛው አገልጋይ ድሚስ በሙስና ያልተዘፈቀ ዚስርአቱ አገልጋይ መፈለግ ኚዝንጀሮ ቆንጆ ዚመምሚጥ ያህል ኚባድ ሆኗል።
ዚወያኔ ትላልቅ ሙሰኞቜ ለምልክት ትንንሜ ሙሰኞቜን አልፎ አልፎ በማሰር ፀሹ ሙሰኛ መስለው ሊያሞኙን ቢሞክሩ ዛሬ ዚመጀመሪያ቞ው አይደለም። ወያኔ ሙስናን ክስ ዚሚጠቀምበት አንድም በውስጡ ካፈነገጡ ሃይሎቜ ጋር ዚፖለቲካ ልዩነትን ለማወራሚጃ ወይም ለውጭ ለጋሟቜ ሙስናን ዹሚጠላ መስሎ ለመታዚት ሲፈልግ ብቻ መሆኑን ኚልምድ እና ኚተግባሩ ህዝቡ ያውቀዋል።
ዚወያኔ መንግስት ሀገሪቱን ወደ ድህነት ማቅ ቁልቁል እያስገባና ሀገሪቱ በእዳ እያስያዘ፣ በአንጻሩ ግን ዚስርአቱ ቁንጮ ባለስልጣናት በሙስና ተዘፍቀው፣ በልፅገውና ኚብሚው፤ ራሳ቞ውን ኚሙስና ነጻ ሆኖ ለመታዚት ሲያሻ቞ው ግልገሎቹን በማሰር እና በራሳ቞ው ሚዲያ አስሚሜ ምቜው ይጚፍራሉ።
በእኛ እይታ ወያኔ ራሱ ቆሞ ዚሚሄድ ሙስና ነው። ወያኔና ሙስናን፣ ሙስናንና ወያኔን መለያዚት አስ቞ጋሪም ነው። ዚወያኔ አባልና ደጋፊ ዹሚሰበሰበው፣ ዹሚመለመለው በመንግስት ሀብትና ንበሚት ሰዎቜን በማባበል ነው። ይህም ሙስና ነው።
ወያኔ ለዚእለቱ ዚፖለቲካ ድርጅታዊ ስራውና በምርጫ ጊዜ በገፍ ካለ አቀት ባይ ዹሚጠቀመው ዚመንግስት ገንዝብ፣ ተሜኚርካሪ፣ ነዳጅ፣ ቢሮ፣ ዹሚኹፈለው ዚመንግስት ውሎ አበል፣ ዚሚገለገልበት ዚህዝብ ቎ሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ጋዜጣ ወዘተ ዚሙሰኝነት ስርአታዊነቱ መገለጫ ነው። ዚመንግስት ስራ እድልን ኚተማሩ ዜጎቜ ሳይቀር እዚነጠቀ በዘርና በወያኔ አባልነት መለኪያ ለተመለመሉ አባሎቜ ዹሚሰጠው ስጊታ ዘግናኝ ሙስና ነው።
ኀፈርት ዚተባለው ዚወያኔ ኩባንያ ኚህዝብና ኚመንግስት በተዘሹፈ ሀብት መመስሚቱን እንደማያውቅ ትተን ትላንት ኚባንክ ካለተኚራካሪ እዚተበደሚ ዚሚነግድብን ንግድ፣ ሲኚስር ብድሩና ወለዱን መክፈል ሲያቅተው ወያኔ ሙስና ብለን ይህን እንድንጠራው አይፈልግም።
ግንቊት 7 ዚፍትህ፣ ዚነጻነትና ዚዲሞክራሲ ንቅናቄ ወያኔ ተገዶ ወይም ተወግዶ በሀገራቜን በህግና ህግ ብቻ ዚሚሰራ መንግስት መመስሚትን እንደ ግብ ዚምንቆጥሚው ለዚህ ነው። ግንቊት 7 በሀገራቜን ሙስና ላይ ዹአመሹሹ ትግል ማድሚግና ሙሰኞቜን ማጥፋት ዚሚቻለው ወያኔን ያስወገድን እለት ብቻ ነው። ስለዚህም ዚሀገራቜን ህዝብ ሆይ ይህን ተሚድተህ ትግሉን በአስ቞ኳይ ትቀላቀል ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

May 27, 2013

Meles Zenawi Net Worth


Net Worth: 3 milliarder dollarStats

  • Source of Wealthpolitikk
  • Meles Zenawi Age58years gammel
  • Meles Zenawi Birth PlaceAdwa, Etiopia
  • Meles Zenawi Sivil statusGift (Azeb Mesfin)
Meles Zenawi nettoformue: Meles Zenawi Asres var tidligere statsminister i Etiopia som ledet landet fra 1995 til sin dÞd i 2012. Han var ogsÃ¥ president i Etiopia 1991-1995. Han var en av de siste literate og fremtidsrettede ledere i Afrika. Zenawi hadde en MBA fra Storbritannia, og en mastergrad i Þkonomi fra Nederland. Hans formue er i dag pÃ¥ 3 milliarder dollar.
Han sluttet seg til Tigrayan Folkets Liberation Front (TPLF) som medlem i 1975. Til slutt ble han valgt som leder for TPLF og EPRDF. Ledet av ham og andre ledere, var TPLF i stand til Ã¥ overta makten i landet i 1991 som borgerkrigen tok slutt. Ved Ã¥ bli statsminister, introduserte han en multi-party politisk system og tillot private pressen i landet. Han gikk med pÃ¥ Ã¥ samarbeide med USA mot grupper og organisasjoner som Al Qaida opererer ut av landet.

Han ble tildelt Rwanda 'National Liberation Medal og ogsÃ¥ "World Peace Prize" for sitt bidrag til global fred. Zenawi ogsÃ¥ fikk "Yara"-prisen for Ã¥ gjennomfÞre en grÞnn revolusjon i landet.Noen andre priser han hadde fÃ¥tt inkluderte Afrika Politisk Leadership Award i 2008, og Good Governance award.
Han giftet seg med Azev Mesfin, som er i dag medlem av den etiopiske parlamentet. Meles Zenawi dÞde i en alder av 57 Ã¥r den 20. august 2012. Han dÞde av en infeksjon etter Ã¥ ha en operasjon pÃ¥ grunn av en hjernesvulst.

ዚኢህአዎግና ዚሻዕቢያ ድርድር ተበጠሰ

ኳታር በተናጠል ዚጀመሚቜው ኢትዮጵያንና ኀርትራን ዹማሾማገል ሂደት መበጠሱ ተሰምቷል። ኚሜምግልናው ዙሪያ ዚግብጜ ሚና ስለመኖሩ አመላካቜ ጉዳዮቜ አሉ እዚተባለ ነው። በድርድሩ ኢህአዎግ በዋናነት እንደ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠው ዚትግራይ ህዝባዊ ዎሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደሚት/ ጉዳይ እንደሆነም ለማወቅ ተቜሏል።
አቶ መለስ ዚኢትዮጵያን ወደብ እንደተራ ጉዳይ አሳልፈው በመስጠት ኀርትራን እንደ አገር እውቅና በሰጡበት ወቅት ድጋፍ ለማሰማት ቀዳሚ ዚነሚቜው ኳታር ኹበሹሃው ትግል ጀምሮ ዚሻዕቢያ ወዳጅ አገር እንደሆነቜ ይታወቃል።
haile and esayasኹዚሁ ዹኹሹመ ወዳጅነት በመነሳት ኳታር በ2008 ኚኢህአዎግ ጋር ተፈጥሮ ዹነበሹውን ዚጞብ ግድግዳ አፍርሳ ወደ ኢትዮጵያ ዚመጣቜው በዋናነት ሁለቱን አገሮቜ መልሶ ለማስታሚቅ በተያዘ እቅድ ስለመሆኑ ለጉዳዩ ቅርብ ዹሆኑ ይናገራሉ። በተለይም አሁን ያለው ዚኀርትራ አስተዳደር እጣ ፈንታ አብዝቶ ያስጚነቃት ኳታር በኀርትራ ወደብ ሊዝ በማድሚግ፣ ኢንቚስትመንት ላይ በመሳተፍና ልዩ ድጎማ በማድሚግ ቀዳሚውን ስፍራ ስለምትይዝ ቜግር ኚመፈጠሩ በፊት ላይ ታቜ ማለቷ እንደማይደንቅ ስምምነት አለ።
ዹጎልጉል áˆáŠ•áŒ­ ዹሆኑ ዲፕሎማት እንዳሉት ኳታር አሁን እርቁን ዚፈለገቜው በኀርትራ መሚጋጋት እንዲፈጠርና ዚኀርትራ ኢኮኖሚ አንዲያገግም ለማድሚግ በሚል ነው። በሌላ በኩል ህወሃት ዚዘወትር ስጋቱ ዹሆነውን ሻዕቢያን ለማስወገድ ሌት ኹቀን እንደሚሰራና ይህም በድርጅት ደሹጃ አቋም ዚተያዘበት ጉዳይ በመሆኑ ዚኀርትራ መንግስት መሰሚታዊ ዹአቋም ለውጥ ሳያደርግ ኚኢህአዎግ ጋር ዚድርድር ስምምነት ላይ መድሚስ አስ቞ጋሪ እንደሚሆን ሁሉም ወገኖቜ ዚሚሚዱት ጉዳይ ነው።
ኚውስጥም ኚውጪም ፖለቲኚኞቜ ትኩሚት ሰጥተው እዚተኚታተሉት ያለው ዚሁለቱ አገሮቜ  ዹሰላም ድርድር ዲፕሎማቱ እንዳሉት ሁለት አብይ ጉዳዮቜ አሉበት። ሁለቱ አብይ ጉዳዮቜ ደግሞ ሊነጣጠሉ አይቜሉም። በኀርትራ እለት እለት እዚሰለለ ዹሄደው ዚአገሪቱ ኢኮኖሚና ዚኑሮ ውድነቱ ዚኢሳያስን አስተዳደር አናግቶታል። በተጚማሪ ሆን ተብሎ ይሁን በሌላ ምክንያት ኚሃያላኑ አገራት ጋር ዚገጠሙት ዚሚዥም ጊዜ ፍትጊያ ዚኢሣያስን ትኚሻ አዝሎታል። ኹዚህም በላይ እድሜ ለመለስ ዹፍቅር ጊዜያ቞ው ሲሻግት “አሞባሪ” አድርገዋ቞ው።
ኹዓለምና ኹአህጉር መድሚኮቜ ሙሉ በሙሉ ተገልሎ ዹኹሹመው ዚኢሳያስ አስተዳደር በተለያዩ ደሚጃዎቜ ዚደሚሰበትን እግድና ቅጣት ለመቋቋም ዚዲፕሎማሲ ዘመቻ ዹጀመሹው ኚውጪ ያለውን ቜግር ተኚትሎ በአገር ውስጥ ዹገጠመውን ፈተና ለመቋቋም እንደሆነ ተንታኞቜ ያስታውሳሉ። በውስጥ ዚፖለቲካና ዚኢኮኖሚ አጣብቂኝ ውስጥ ያለው ሻዕቢያ ወንበሩ እዚወላለቀ ስለሆነ ኚቀድሞው ወዳጁ ህወሓት ጋር ለመወዳጀት ይፈልጋል።
ኀርትራ ኢኮኖሚዋ እንዲነቃቃ ኢትዮጵያን ዚንግድ ሞሪኳ ማድሚግ ዚመጀመሪያው ስራ ነው።  ያለ ስራ “ሙት” ሆኖ ዹተቀመጠውን ዚአሰብን ወደብ ኢትዮጵያ ኚጅቡቲ ባነሰ ዋጋ እንድትጠቀምበት ማድሚግና ወደቡ ላይ ህይወት መዝራት ዛሬ ላይ ግድ እዚሆነ ዚመጣ ጉዳይ ነው። በተለይም ኢትዮጵያ ጅቡቲ ላይ ዚራስዋን ወደብ ለመገንባት ዚጀመሚቜው እንቅስቃሎና ለጅቡቲ ዚወደብ ኪራይ ዚምትገፈግፈው እጅግ ኹፍተኛ ወጪ ግማሹ እንኳን ኀርትራ ቋት ውስጥ ቢገባ አሁን ዹተፈጠሹውን ዚኑሮ ግለት ጋብ እንደሚያደርገው በርካቶቜ ይስማሙበታል።
በዚሁ መነሻ ዚኢሳያስ መንግሰት ኚገባበት ዹመኖርና አለመኖር ስጋት ለመገላገል እቅድ ተነድፎለት ዹተጀመሹውን ድርድር ኢህአዎግ ዹህልውና ጥያቄ በመጠዹቁ ሳቢያ ብዙም ሳይራመድ በእንጭጩ ተኮላሜቷል። ኢህአዎግ በድርድሩ መሰሚታዊ ሃሳብም ሆነ በሌሎቜ ዝርዝር ዚኢኮኖሚ ነጥቊቜ ዹተፈለገው ርቀት ድሚስ ለመጓዝ ፈቃደኝነቱን ለመግለጜ ጊዜ አልወሰደም ነበር። ዚለበጣም ቢመስልም አቶ ሃይለማርያም አስመራ ድሚስ ለመሄድ ዝግጁ መሆኑንን ማስታወቃ቞ው አይዘነጋም።
ዹሆነ ሆኖ ኢሳያስ አሁን ባላ቞ው ዚፖለቲካ አቋም ኚሳ቞ው ጋር መነገድ ዹዛለውን ክንዳ቞ውን ማፈርጠም በመሆኑ ኢህአዎግ እንዳልተዋጠለት ዚሚጠቁሙት ዲፕሎማቱ “ፖለቲካዊ ይዘቱ ኢኮኖሚያዊ ሜርክናውን ዋጋ ቢስ አድርጎታል” በማለት ስለማይነጣጠሉት ሁለት ተያያዥ ጉዳዮቜ አስሚድተዋል።
ኳታር ሶማሊያ ላይ በነበራት አቋምና ዚገንዘብ ተሳትፎ ኚኢትዮጵያ ጋር ዚነበራት ዚዲፕሎማሲ መስመር ኚመቋሚጡም በላይ “ለሶማሊያ ጉዳይ አባቱ ነኝ” ይሉ በነበሩት አቶ መለስ ክፉኛ ተዘልዝላ ነበር። ያ ሁሉ አልፎ ዛሬ በኢንቚስትመንት ስም እርቅ አውርዳ ዚገባ቞ው ኳታር በጀመሚቜው ድርድር ኢህአዎግ ያነሳው መሰሚታዊ ዹህልውና ጥያቄ አላላውስ ብሏታል።
ተቀማጭነታ቞ው ሎንደን ዹሆነ ዹጎልጉል áˆáŠ•áŒ­ እንዳሉት ዚኢህአዎግ ለመደራደሪያ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠው አጀንዳ ኀርትራ ውስጥ ዚሚንቀሳቀሰውን ዚትግራይ ህዝባዊ ዎሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደሚት/ ታጣቂ ሃይሎቜ ተላልፈው እንዲሰጡት ወይም ወደ ትግራይ ድንበር እንዲገፉለት ነው።
ቀደም ሲል ዚትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት ህወሃት አካል ዚነበሩት እነዚህ ክፍሎቜ “ኀርትራ ውስጥ ታግተው ዚተቀመጡ”  ሃይሎቜ ስለመሆና቞ውና ኹ30 እስኚ 40 ሺህ ዚሚደርስ ወታደር እንዳላ቞ው ለህወሃት ቅርበት ባላ቞ው ዚተለያዩ መገናኛዎቜ መዘገቡ ይታወሳል። በገለልተኛነታ቞ው ዚሚታወቁ መገኛዎቜም ቢሆኑ ዚደሚት ሃይል ኚአርበኞቜ፣ ኚቀንሻንጉል፣ ኚጋምቀላ፣ ኚአማራ፣ ወዘተ ብሚት አንጋቢዎቜ ጋር በጥምሚት ለመሥራት መዘጋጀቱንና ይህም ሁኔታ ለህወሃት ስጋት እንደሚሆን አመልኹተው ነበር።
ኚኢህአዎግ ዚሚወጡ ዚምርመራ መሚጃዎቜ እንደሚያሳዩት ህወሃት ደሚትን እዚፈራ ነው። ደሚት “በኀርትራ ዚታገተ ሃይል ነው” በማለት ዚድርጅቱን ሃይል ለማጣጣል ቢሞኚርም፣ ዚደሚት ሃይል እንደሚባለው አለመሆኑንን ዚሚያሚጋግጡ መሚጃዎቜ አቶ መለስ በህይወት እያሉ ቀርቩላቾዋል። ኚዚያ በኋላ ነበር ደሚት ጥንካሬው እንዳይጎለብት ህወሃቶቜ መስራት ዚጀመሩት።
በወቅቱ ኚኢህአዎግ ጓዳ ያፈተለኩ መሚጃዎቜ እንደሚጠቁሙት ኢትዮጵያ አሰብን ለመጠቀም ዚሚያስቜላት ድርድር ተጀምሮ ነበር። በስዊድን ዚሚኖሩ ዹጎልጉል ምንጭ ዹሆኑ ዚኀርትራ ተወላጅ ኚዓመት ኚስድስት ወር በፊት ዚአሰብ ወደብ እንዲታደስና ስራ እንዲጀምር ተወስኖ እንደነበርና ስራው ሲጀመር ስራ አቁመው ዚነበሩ ሰራተኞቜና አገልግሎት አቋርጠው ዚነበሩ ድርጅቶቜ ስራ቞ውን እንዲጀምሩ መመሪያ ተሰጥቶ እንደነበር ያስታውሳሉ። ስራው አሁን በምን ደሹጃ እንደሚገኝ ለጊዜው መሹጃ እንደሌላ቞ው ተናግሹዋል።
በተለያዚ ወቅት አቶ መለስን ኚቀድሞው ወዳጃ቞ው አቶ ኢሳያስ ጋር መልሶ ለማሻሚክ ግብጜን ጚምሮ ዚተለያዩ አገሮቜ እንደተሳተፉ ዚሚገልጹ አሉ። ዚግብጜን ዚሞምጋይነት ሚና ጥርጥር ውስጥ በማስገባት አስተያዚት ዚሚሰጡት ዲፕሎማት አሁን ኳታር ኚጀመሚቜው ድርድር ጋርም ግብጜን ያያይዛሉ። ኚኳታር ካዝና በሚወጣ ገንዘብ ሻዕቢያ ዚኢትዮጵያን ተቃዋሚዎቜ እንዲያደራጅ አጥብቃ ዚምትሰራውና ዚምትደጉመው ግብጜ አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያና ኀርትራ አስተማማኝ ሰላም አውርደው በሰላም በጉርብትና እንዲኖሩ አትመኝም።
ኳታር ግን በቀድሞው አቋም መቀጠሉ አግባብ እንዳልሆነና በ2008 ኚኢትዮጵያ ላይ እጇን እንድታነሳ ተጠይቃ ባለመቀበሏ ዹተሰበሹው ዚዲፕሎማሲ ግንኙነት ለማቃናት መስራት ዚጀመሚቜው ኚሊቢያው መሪ ጋዳፊ ሞት በኋላ እንደሆነ ዚሚገልጹ ክፍሎቜ ኳታር አሁን በጀመሚቜው “ዚትልቅ አገር ነኝ” ስሜትና በአፍሪካ ቀንድ ጂኩ ፖለቲካ ላይ ያላት ሚና መጎልበት ኢትዮጵያን መወዳጀት ብ቞ኛው አማራጯ እንደሆነ ይናገራሉ።
ሻዕቢያ እዚኚሰመ ሲሄድ ኢህአዎግ በሌላ በኩል በአፍሪካም ሆነ በዓለም ደሹጃ ማደጉ ለንግድና ለፖለቲካ ዝናዋ ኢህአዎግን መወዳጀት አማራጭ ዹሌለው ጉዳይ ዚሆነባት ኳታር ሩጫዋ በጊዜ ዚተኮላሞው ኚኢህአዎግ ወገን በተነሳ “ዚማይታሰብ” በተባለ ጥያቄ ነው። ዚደሚት ዹጩር ሃይል ተላልፎ እንዲሰጠው ወይም ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እንዲገፋለት ዹተዹቀው ኢህአዎግ ይህ እስካልሆነ ድሚስ ኚሻዕቢያ ጋር አንድ መቀመጫ ላይ ተቀምጩ ለመነጋገር አለመቻሉ ለኳታር ሜምግልና ዚመጀመሪያውና ሊመለስ ያልቻለ ፈተና ሆኗል።
ኚድሮ ጀምሮ አድብታ ዚኢትዮጵያን ተቃዋሚዎቜ በመርዳት ዚምትታወቀው ግብጜ ኢህአዎግ በፈለገው መልኩ ድርድሩ ሊካሄድ እንደማይቜል አቋም ይዛ እዚሰራቜ እንደሆነ፣ ለዚህም ሲባል ኚአንዳንድ ዹተቃዋሚ ሃይሎቜ ጋር ለመነጋገርና በሻዕቢያ አማካይነት ድጋፍ ለመስጠት ፍላጎት ማሳዚቷን ዹጎልጉል áˆáŠ•áŒ­ ዚሆኑት ዲፕሎማት አስሚድተዋል። ዲፕሎማቱ በደፈናው ኹመናገር ውጪ ግብጜን ያነጋገሚቻ቞ውን ዹተቃዋሚ ሃይሎቜ አልዘሚዘሩም።
ኳታር ዚምጜዋን ወደብ በሊዝ ኚመያዟ በተጚማሪ ለአሰብ ወደብ ዚነዳጅ ማጣሪያ ማደሻና ለወደቡ ስራ ማስቀጠያ ድጋፍ ማድሚጓ አይዘነጋም። ያለ ስራ ተቀምጩ ዹነበሹው ወደብ ለስራ እንዲዘጋጅ ዚታሰበው ለማን ተብሎና ማን እንዲጠቀምበት ታስቊ ነው ሚለው ጉዳይ ፖለቲካዊ ውሳኔ ዹሚጠይቅ አብይ ጉዳይ ኹሆነ ዓመት ኚስድስት ወር አስቆጥሯል። ኢህአዎግ ዹሚደጉመው ዚኀርትራ ዚሜግግር መንግስት አዲስ አበባ መቋቃሙም ዚሚታወስ ነው።

May 26, 2013

በሚኒሶታ ለቀተክርቲያን ሰላምና አንድነት ኹቆሙ ምእመናን ዹተላለፈ ጥሪ

በስመ አብ ወወለወድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ፤ አሜን!
ግንቊት ፳፻፭ ዓ.ም

                               á‰£áˆˆá‰á‰µ ፳ ዓመታት በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ላይ ዚደሚሱ
                                ጥፋቶቜና በደሎቜ ባጭሩ እና ዚምንገኝባትን ቀተክርሰቲያን አንድነትና ሰላም
                                                               áŠ áŒœáŠ•á‰°áŠ• ስለመጠበቅ።
                                  ለቀተክርቲያን ሰላምና አንድነት ኹቆሙ ምእመናን áˆšáŠ”áˆ¶á‰³

 á‹šáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ በሥርዓትና በምልዐት ዚተሟሙትን ፓትርያርክ ኚመንበራ቞ው

በማውሚድና በማባሚር
 á‹ˆá‹«áŠ” ዚራሱን ጉዳይ አስፈጻሚ ጳጳስ በመንበሩ በመሟሙ ምክንያት ዚቀተክርስቲያኗ አባቶቜና ምእመናን በታሪክ ባልታዚ ሁኔታ
እንዲኚፋፈሉ ተደርጓል
 á‹šáŠ¢á‰µá‹®áŒµá‹« ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ለኢትዮጵያ ዳር ድንበር መኹበር ለታሪክና ለቅርስ መጠበቅ ያበሚኚተቜው

አስዋጜኊ በግንባር ቀደምትነት ዚሚጠቀስ ነበር። ነበር መባሉ ግን
እጅግ አሳዛኙ በዘመናቜን በምሬት ዹምንቀበለው እውነታ ሆኗል።  á‹šá‹ˆá‹«áŠ” ባለስልጣናት በተደጋጋሚ በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋህዶ ቀተክርስቲያን ላይ ዚጜርፈት ነገር ሲያስተጋቡ ቀተክርስቲያኗን ይመሩና መንጋዋን ይጠብቁ ዘንድ ዚተሟሙ አባቶቜ ድርጊቱን ሳይገስጹና ሳያወግዙ በዝምታ አልፈውታል።  áŠ á‰¶ ተፈራ ዋልዋ፣ አቶ ስብሐት ነጋ፣ አቶ አባይ ጞሐዬና ሌሎቜም ባለሥልጣናት በግልጜ ዚቀተክርስትያኗን ህልውና ሲያንቋሜሹና ሲያዋርዱ ተሰምተዋል። ለምሳሌም ያህል ኊርቶዶክስ ዹነፍጠኛ ዋሻ ነቜ፣ መነኮሳትን ዹተለዹ ዚፓለቲካ አጀንዳ ያላ቞ው ናቾው፤መለኪያው ኊሮቶዶክስና አማራ ዹነበሹውን ሥርዓት ሰብሚነዋል ወዘተ ዹሚሉ ዚድፍሚትና ዚማዋሚድ ቃላት
ሲነገሩ መስማቱ እንግዳ አይደለም።
 á‰ áŠ á‰£á‰¶á‰œ መካኚል ዹተፈጠሹውን መለያዚትና መወጋገዝ በመፍታት ሰላምና እርቅን ለማምጣት ግድ ያላ቞ው ውድ
ዚቀተክርስቲያን ልጆቜ ጥሚት በኚንቱ ሲመክን ዚአባቶቜ ዝምታ እና ዹዚሁ ሰላምንና አንድነትን ዚማፍሚስ ዚአመጞኝነት ተግባር አካል
መሆን እጅጉን አሳፋሪና አስነዋሪ ክርስቲያናዊ ያልሆነ ተግባር ነው። ይህንን ዚብዙዎቜን ተስፋ ያጚለመ ድርጊት አስመልክቶ
በሁለቱም ወገኖቜ ይሁንታን ካገኘ በኋላ ዚማደራደር/ዚማስታሚቅ/ወንጌላዊ ተግባር ሲያኚናውን ዹነበሹው ዚኢትዮጵያ ኩ/ተ/ቀ/ክ
ዹሰላምና አንድነት ጉባዔ ለዓመታት ዚተለፋበት ዹሰላምና እርቅ ሂደት አስመልኚቶ ዚካቲት 12/2005ዓ.ም ባወጣው መግለጫ
ዚእርቅና ዹሰለም ሂደቱ እንዳይሳካ ያደሚጉትን ዋና ዋና ምክንያቶቜን ሲገልጜ፦
 1.‘‘በኢትዮጵያ ያሉ አንዳንድ አባቶቜ ኚቀተክርስቲያን ሰላምና አንድነት ይልቅ ለሢመተ ፓትርያርክ ቅድሚያ
በመስጠታ቞ውና ዚላኳ቞ውን ልዑካን ሪፖርት ሳይሰሙ አስመራጭ ኮሚ቎ መሰዹማቾው፤
 2.ዚኢ/ኩ/ተ/ቀ/ክ ዹሰላምና አንድነት ጉባዔ አባላት በልዑካኑ ዚስምምነት ውሳኔ መሰሚት ወደ አዲስ አበባ ቅዱስ ሲኖዶስ
ተሰይመው ኚሔዱ በኋላ ዚተላኩበትን ዓቢይ ዚቀተክርስቲያን ጉዳይ ለቅዱስ ሲኖዶስ እንዳያቀርቡ እስካሁን ድሚስ እንኳን
ማንነታ቞ው ባልታወቁና ባልተሚጋገጠ ግለሰቊቜ ተላለፈ በተባለ ሕገ ወጥ ትእዛዝ ወደ መንበሹ ፓትርያርኩ ቅጜሚ ግቢ እንዳይገቡ
በጥበቃ ሰራተኞቜ መኹልኹላቾው፤
 3.ኹዚህም በላይ እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ አንደኛውን ልዑክ ካለአንዳቜ ምክንያት በግዳጅ ኹሀገር እንዲወጡ መደሹጉ
ሁለተኛውንም ልዑክ በማጉላላትና ወደ ቀተክህነት ግቢ እንዳይገቡ በማገድ በቀጠሮ እንኳን ለሚጠብቃ቞ው ዚቅዱስ ሲኖዶስ
ጉባዔ ኹላይ ዹዘሹዘርናቾውን ዚመፍትሔ ሃሳቊቜ ዚያዘውን ዹሰላምና አንድነት ጉባዔ ደብዳቀ አቅርበው እንዳያስሚዱና ቅዱስ
ሲኖዶስ በጉዳዩ እንዳይመክርበት መደሹጉ
 4.ገና ኚጅምሩ ጀምሩ እርቀ ሰላሙን ዹማይፈልጉና በግልጜ ይቃወሙ ዚነበሩ አንዳንድ አባቶቜ ፈጜሞ ዚተዛባና ኚእውነት ዚራቀ
መሠሚተቢስ መሹጃ ለመንግስት ባለሥልጣናትም ሆነ ለኅብሚተሰቡ መስጠታ቞ው
 5.በሐዋሪያዊት ቀተክርስቲያናቜን ፍጹም ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ለማድሚግ ላለፉት ሊስት አመታት ሲካሔድ ዹቆዹው
ዚእርቀ ሰላም ጥሚት ኚዳር እንዳይደርስ በሚፈልጉ ጥቂት ዚቅዱስ ሲኖዶስ አባላት አማካይነት ቅዱስ ሲኖዶስ እንደ አንድ ልብ
መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆኖ ዹተጀመሹው ዚእርቀ ሰላም ውይይት ለውጀት እንዲበቃ ባለማድሚጉ ምክንያት መንግስት
በቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ሥልጣን ላይ ግልጜ ተጜእኖና ጫና በማድሚጉ
 6.በመጚሚሻም ጥር 8/2005ዓ.ም በአዲስ አበባ ዹሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ ስድስተኛ ፓትርያርክ ለመሟም በቜኮላ መወሰኑ
ዹሰላሙን በር ኚመዝጋቱም በላይ ዚእርቀ ሰላሙን ውጀት በጞሎትና በታላቅ ተስፋ ሲጠባበቅ ለቆዹው መላው ሕዝበ ክርስቲያን
ታላቅ መርዶ ሆኗል።’’በማለት በዝርዝር አስሚድቷል። ኹዚህም ሌላ በቅርቡ በቀተክርሰተያኗ ላይ እዚደሚሰ ያለውን በደል
ብንመለኚት
 á‹šá‰³áˆ‹á‰ ሰማዕት ዚአቡነ ጎጥሮስ ሐውልት ኚስፍራው ሲነሳ ዚአባቶቜ ዝምታ ወይንም ዚድርጊቱ ተባባሪ መሆን፣
 á‹šá‰…ድስት ሥላሎ መንፈሳዊ ተቋም በአንድም በሌላም ምክንያት ሲዘጋ ዚአባቶቜ ዝምታ ወይም ዚድርጊቱ ተባባሪ መሆን
 áŠšáˆáˆ‰áˆ በላይ ደግሞ አሁን በቅርቡ ለዘመናት በኢትዮጵያ ሕገ-መንግስትና በፍታብሔር ሕግ ውስጥ እውቅናና ሕጋዊ ሰውነት
ዚተሰጣትን ቀተክርስቲያን ሕጋዊ መብቷን ለመግፈፍና ለማፍሚስ እንደ ማንኛውም በኃይማኖት ስም እንደተራጁ ድርጅቶቜ እንደ
አዲስ ተመዝግባ ፈቃድ በማውጣትና በማሳደስ ብቻ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባት ዚሚገልጜ ሹቂቅ አዋጅ ወጥቶ ቀርቧል።
ይህም ቀተክርስቲያንን ዚማዳኚሙና ዚማፍሚሱ ታላቁ ሀራ አንዱና ትልቁ እቅድ መሆኑ አያጠራጥርም። ይህ ሁሉ ሲደሚግም
ዚቀተክርስቲያናቜን አባቶቜ ዝምታ እጁጉን ዚሚያስደምም ሆኗል።
 á‹ˆá‹«áŠ” በያዘው ዹጾሹ-አማራነትና ጾሹ-ኊርቶዶክስ ፖሊሲ በአርሲ፣በጅማ፣በደቡብ ህዝቊቜ፣ በጎንደር፣በደሮ፣ በአሰቊት፣በዝቋላ፣በ
ዋልድባ ገዳማት፣ቀተክርስቲያናት፣ካህናትና ምእመናን ላይ ሞት፣መቃጠል፣ዝርፊያና ውድመት ሲደርስ ዚቀተክርስቲያኗን መብትና
ዚምእመናንን ደህንነት ለመጠበቅ ዚተሟሙ አባቶቜ በማወቅም ሆነ በ቞ልተኝነት ዝም ብለው በማዚት ዹዚህ ሁሉ በደል ፈጻሚዎቜና
አስፈጻሚዎቜ ደጋፊ እና ተባባሪ ሆነው መገኘታ቞ው በጣም አሳዛኝና ሐዋርያዊ ተልዕኮን መዘንጋት ነው።
 á‹šá‹‹áˆá‹µá‰£ ገዳም ወደስኳር ፋብሪካት እዚተቀዚሚ ነው። ዚአባቶቜ ዝምታ ወይም በድርጊቱ ተባባሪ መሆን ፣
 á‹œáŒŽá‰œ በተለይም ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን አባላት ያለምንም ወንወጀል ኚቀት ንብሚታ቞ው
ሲፈናቀሉ፣ለስደትና ለእንግልት ሲዳሚጉ ዚሚያጜናና቞ው አባት አጥተው ምስካዬ ኅዙናን ዚተባለቜ ቀተክርስቲያንን መጠጊያና
መሞሻ ለማድሚግ ሲሞክሩ ኚቀተክርስቲያን ቅጜር እንዲባሚሩ መደሹጉ በዘመናቜን ያሉ ‘ብጹአን አባቶቜ’ታሚክ መሆኑ እጅግ
ኚማሳዘን አልፎ በርግጥም መጜሐፍት እንደሚነግሩን ዚተመሚጡን እስኚሚያስት ድሚስ ተዐምራትን ያደርጋል ዚተባለለት
ዚመጚሚሻው ዘመን መንፈስ በግልጥ እዚሰራ ያለበትን ዘመን መሆኑን ዚሚያሳስብ ነው።ይህም ለእውነትና
ለኃይማኖት፣ለቀተክርስቲያንና ለመንጎቿ ዹሚገደው አባት ፈጜሞ ዚጠፋበት ጊዜ ላይ መድሚሳቜንን ዚሚያስዳ ነው።
 áŠ¥áŠ•áŒá‹²áˆ… በዚህ ሁኔታ ነው በቀተክርስቲያን ላይ ጥቃትና ደባ ኚሚፈጜምና ኚሚያስፈጜም መንግስት ተብዬ ጎን እንቁም፤
እርሱን ኹሚደግፉና ዚጉዳዩ አስፈጻሚ ኹሆኑ አባቶቜ ጋር አብሚን እንሰለፍ እዚተባለ ዹሚሰበኹውና ዹሚነገሹው???!!!

በውጪ አገራት ያሉ ቀተክርስቲያናትን አስተዳደርና አመሰራሚት በተመለኹተ
 á‰ á‹áŒª አገራት ያሉ ቀተክርስቲያናት ዚሚቋቋሙበት ሕግና ሥርዐት በሚገኙበት አገር ዚቀተክርስቲያናትና ሌሎቜ ኚታክስ ነጻ
ለመሆን ዚሚመሰሚቱበት ሕግና ደንብን ተኚትሎ መሆኑን ባለመሚዳት በቀተክርስቲያናት መካኚል ልዩነት ያለ ይመስል እኛ
ኚቀተክርስቲያን ተገልለናል እነዚያ በዚህኛው እነዚያ በዛኛው ሲኖዶስ ሥር ናቾው ሲባል ይሰማል።
 áŠáŒˆáˆ­ ግን ሁሉም ቀተክርስቲያናት ዚሚተዳደሩት ባሉበት አገር ህግና ተቀባይነት ባለው መተዳደሪያ ደንብ ወይንም ባይ ሎው
መሰሚት በቊርድ አመራር ሰጪነት ኚቀሚጥ ነጻ ዚሚያደርጋ቞ውን ሕግ ዚሚያኚብሩ ሲሆኑ ነው። ቀተክርስቲያናቱም ያለልዩነት
በቊርድ ኩፍ ትሚስቲስ ነጻ አገልጋዮቜ ብቻ ዚሚመሩና በዚአመቱ ኚቀሚጥ ነጻ ዚሚያደርጋ቞ውን ቅጜ እዚሞሉ ዚእድሳት ፈቃድ
እያወጡ አገልግሎት ዚሚሰጡ ናቾው። አሁን ያለውን ዚኢትዮጵያ ቀተክርስቲያን ቃለ-አዋዲ ዚውጪ አገር መንግስታትና
ሕጎቻ቞ው ዚማያውቁትና በውጪ አገር ሊሰራበት ዚማይቜል ነው። ስለሆነም ወደ እናት ቀተክርስቲያን ይሁን በስደት ባለው
ሲኖዶስ ሥር እንሁን ዹሚለው አካሔድ ኚምኞት ዚማያልፍ ነባራዊ ሁኔታን ያለመሚዳት ነው። ምክንያቱም ሁሉም በአንድ አይነት
ሕግ ብቻ ዚሚመሰሚቱና ዚሚተዳደሩ በመሆናቾው።
ስለሆነም ልዩነት ያለው ወገንተኝነትን ኚመግለጜ አኳያ ብቻ ነው። ይህም ኚመንበራ቞ው ዚተባሚሩትን ወይም በወያኔ ዚተሟሙትን
ፓትሪያርኮቜ ስም በመጥራትና ባለመጥራት ዚሚገለጜ ነው። ይህን ለማድሚግ ደግሞ ጉዳዩን በመሹጃ በተደገፈ ማጣራት ዚጉዳዩን
ወይም ዚልዩነቱን መንስዔ በትክክል አውቆ ለመወሰን አስ቞ጋሪ ሁኔታ በመፈጠሩ ምክንያት ሁለቱ ወገኞቜ በሰላምና በእርቅ ሂደት
ወደ አንድነት እስካልመጡ ድሚስ እንደ ክርስቲያን ዚቜግሩን ውል በሚገባ ሳያውቁ ለዚህኛው ወይንም ለዛኛው ወገን ወግኖ
መገኘት ኢክርስቲያናዊ በመሆኑ ዚሁለቱንም ወገኖቜ/ፓትርያርኮቜ ስም ኚመጥራት በመቆጠብ ወደ ሰላምና አንድነት
ዚሚመጡበትን መንገድ መደገፉ ትክኚለኛ አማራጭ መሆኑ ዚታመነ ነው።
 á‰ á‹šá‹°á‰¥áˆšáˆ°áˆ‹áˆ መድኃኔዓለም ቀተክርስቲያን ሁሉም ወገኖቜ ዚቀተክርስቲያኑን አቋም እስካኚበሩ ድሚስ መጥተው መባሚክ፣
ማስተማርና መቀደስ አልተኹለኹሉም።
 á‰ á‹šáˆ…ም መሰሚት በኢትዮጵያ ሲኖዶስ ስር ያሉም ሆኑ በውጪው ያሉ እንዲሁም ኚሁለቱም ወገን ያልሁ አባቶቜ በተለያዚ ጊዜ
መጥተው ቀድሰዋል፣ አስተምሚዋል ፣ቡራኬ ሰጥተዋል።
 áŠšáˆ‹á‹­ እንደተጠቀሰው መለያዚቱ ያሳሰባ቞ው ውድ ዚቀተክርስቲያኗ ልጆቜ በኹፍተኛ ጥሚት ዹሰላምና እርቅ ኮሚ቎ አቋቁመው
ለሊስት ዙር ያህል ጥሚት አድርገው ውጀቱም በግልጜ በዚሁ ኮሚ቎ እንደተገለጞው ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ አንዳንድ ለስልጣን
በቋመጡ አባቶቜና አይዟቜሁ ባዩ መንግስት ተብዬ እንዲጚናገፍ ሆኗል። በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆሚጥምና አሁንም ቢሆን
ወደዚሁ ዚእርቅና ሰላም ሒደት እንደሚመለሱ ተስፋ እናደርጋለን።
 á‹­áˆ…ም በእግዚአብሔር ፈቃድ እስኪፈጞም ድሚስ ወገንተኝነትን ለቀተክርስቲያን ብቻ በማድሚግ በእውነትና በእምነት መጜናት
አማራጭ ዹሌለው መንገድ ነው። በጭፍን ኹዚህኛው ወይንም ኚዚያኛው ወገን መወገን ግን ለሥርዓተ ቀተክርስቲያን
መጣስ፣ዚእርቅና ሰላም ሒደት እንዳኖር፣ ለሕሊናና ለእግዚአብሔር ሳይሆን ለጥቅምና ለወገኔ ይድላው በማለት ኚኃይማኖት
መውጣት ነው።
 áˆµáˆˆá‹šáˆ… ዚምንገኝበትን ቀተክርስቲያን ሰላምና አንድነት አጜንተን በመጠበቅ በተስፋ እዚኖርን ለእግዚአብሔር መንግስት
ለመብቃት እንዘጋጅ።
ዹሰላም አምላክ ሰላምን ያድለን
አንድነታቜንን ይጠብቅልን አሜን!

May 25, 2013

"ዚህዳሎው ግድብ" ኚግማሜ በላይ ዚኢትዮጵያ አይደለም

ትልቁን ድርሻ ኀፈርት ይዟል

hidassie dam"በራሳቜን መሐንዲስ, በራሳቜን ገንዘብ, በራሳቜን ዚተባበሚ ክንድ እንገነባዋለን" በማለት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመስቀል አደባባይ ታላቅ ህዝባዊ ድጋፍና "መዓበላዊ መነቃቃት" ፈጠሩበት ዚተባለለት ዹ "ህዳሎው" ግድብ 51 በመቶ ድርሻ ዚኢትዮጵያ እንዳልሆነ ነዋሪነታ቞ው በአውሮፓ ዹሆነ ዲፕሎማት በተለይ ለጎልጉል ገለጹ.
ስማ቞ው ምስጢር እንዲሆን ዚጠዚቁት ዲፕሎማት እንዳሉት 51 በመቶ ባለድርሻ ዚሆነቜው አገር አውሮፓ ዚምትገኝ ዚኢትዮጵያ አጋር አገር ናት ለጊዜው ዚባለድርሻዋን አገር ስም መግለጜና ዹውሉን ዝርዝር ይፋ ማድሚግ ያልፈለጉት ዲፕሎማት ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ ዚፈለገቜውን ውሳኔ በራስዋ ለማስተላለፍ እንደማትቜል;. ያላት ድርሻ 49 በመቶ ብቻ በመሆኑ ድምጜን በድምጜ በሚሜሚው በአብላጫ ድምጜ ህግ መሰሚት በግድቡ ላይ ዹሚወሰነው ውሳኔ 51 በመቶ ባለድርሻ በሆነቜው አውሮፓዊቷ አገር መሆኑን አብራርተዋል.
49 በመቶ ተብሎ ዹተገለጾው ዚድርሻ መጠን ጅቡቲን ጚምሮ ዚተለያዩ አገሮቜ ዚተቀራመቱት መሆኑን ያመለኚቱት ዹመሹጃው ባለቀት, አገር ውስጥ ካሉት ዚንግድ ተቋማት መካኚል ኀፈርት ትልቁን ድርሻ መውሰዱን እንደሚያውቁ ተናግሹዋል.
ዚመንግስት መስሪያ ቀቶቜ, ዹግል ባለሃብቶቜ, ማህበራት, ባንኮቜና ዚተለያዩ ግለሰቊቜ በትዕዛዝ አክሲዮን መግዛታ቞ውን ያስታወሱት እኚሁ ዲፕሎማት "በግድቡ ዙሪያ ኚሚፈራው ዚጞጥታ ቜግር በላይ አስጊው ጉዳይ ዚባለድርሻዎቜ ምስጢር መሆን ነው" ሲሉ ስጋታ቞ውን ገልጾዋል.
መንግስት ለግንባታው ዹሚሆን ኹፍተኛ ገንዘብ ኚአውሮፓዊቷ አገር ማግኘቱን ያመለኚቱት ዹጎልጉል ምንጭ, "ኹአገር ውስጥ በአክሲዮን ስም ዹሚሰበሰበው ገንዘብ ለአገር ውስጥ በጀት ማሟያና ለመንግስት ዚስራ ማኹናወኛ ዹሚውል ነው" ብለዋል.
መንግስት በተለያዚ መድሚክ በተደጋጋሚ ፕሮጀክቱ "በአገር ውስጥ ባለሙያ, በአገር ውስጥ ሃብት, ዹሚኹናወን ዚህዳሎ መገለጫ ነው" በሚል ብሄራዊ መነቃቃት ዚተፈጠሚበት ዚአቶ መለስ ማስታወሻ እንደሆነ ኚመግለጜ ውጪ ስለ አክሲዮን ድርሻና አክሲዮን ስለገዙ አገራት እስካሁን ዹተናገሹው ዹለም.
ግድቡ በመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 5 ቢሊዮን ዶላር እንደሚፈጅ መገለጹ ይታወሳል. ዚአባይ ግድብ ኚሱዳን ድንበር 10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ቀኒሻንጉል ክልል እንደሚገኝ መንግስት ዚግድቡን ሥራ ይፋ ሲያደርግ ማስታወቁ አይዘነጋም.
ይህ በእንዲህ እያለ ፋና በዛሬው እለት ባሰራጚው ዜና "ዹወንዙን ​​ተፈጥሯዊ ዚፍሰት አቅጣጫ ዚማስቀዚሩ ስራ እዚተሰራ" መሆኑን ዹገለጾ ሲሆን:. "ወንዙ ይሄድበት ዹነበሹውን ቊታ 1780 ሜትር ኚፍታ ያለው ግድብ ዚመካኚለኛው ክፍል ዚሚያርፍበት እንደሚሆንም" ዚፕሮጀክቱ ሥራአስኪያጅ ኢንጅነር ስመኘው መናገራ቞ውን ጠቅሷል "አቅጣጫውን ዚማስቀዚሩ ስራ ኹመጭው ክሚምት በፊት "ለማጠናቀቅ ርብርብ እዚተደሚገ መሆኑን መሃንዲሱ ጠቅሰው: በቅርቡም ዕውን ይሆናል ብለዋል ግድቡ ግንባታው ዚተጀመሚበት en ኛ ዓመት በዓልም ኚመጪው ሚቡዕ ጀምሮ በአዲስ አበባ:. እንዲሁም መጋቢት 24 ፕሮጀክቱ በሚገኝበት ስፍራ በተለያዩ ስነ ጥበባዊ ዝግጅቶቜና 'መለስ ቃልህ ይኚበራል; ታላቁ ዚህዳሎ ግድብም በህዝባቜን ተሳትፎ እውን ይሆናል' በሚል መሪ ቃል ይኚበራል "በማለት ዹዜናው ዘገባ ገልጟዋል.

May 24, 2013

ዜና በጚዋታ አይነት ነገር፤ ሰማያዊዎቜ አምርሹዋል፤ አምሹዋልም!

253297_418646384899981_1037053069_nዚሰማያዊ ፓርቲ አመራር ግንቊት 14 ለአዲሳባ ስብስባ እና ሰላማዊ ሰልፍ “አዋቂ” ጜ/ቀት (ሙሉ ስሙን ሚስቌዋለሁ… በህገ መንግስቱ መሰሚት ሰላማዊ ሰልፍ ፈቃድ አይጠዹቅም እወቁልን ነው ዚሚባለው… ስለዚህ ስሙን ኚተሳሳትኩ እንኳ እንዲህ ነው መሆን ያለበት ዹሚል መኚራኚሪያ ላነሳ ፈልጌ ነው ማለት ነው…) ብቻ ለማሳወቅ ደብዳቀ ይዘው ቢሄዱ ዚጜ/ቀቱ ሃላፊዎቜ ደብዳቀውን አንቀበልም ብለው… “ገግመው” ነበር፡፡ “ገገመ” ቃሏ ኚአራዳ ስትሆን እምቢ ማለት ሳይገባው እምቢ አለ… ለማለት ታገለግላለቜ፡፡
ዚጜ/ቀቱ ሃላፊዎቜ ለምን ደብዳቀውን አንቀበልም እንዳሉ እንጃላ቞ው… ምናልባት እነርሱም በመንግስታ቞ው ዚተኚፉበት ጉዳ ይኖራል፡፡ (ይቺ ዚግዳጅ ቊንድ ግዢ እኮ ሰራተኞቜ ዚስራ ተነሳሜነት ላይ ኚባድ ዹሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ነው ያላት….) ዚምሬን ነውኮ… እነዚህ ሃላፊዎቜ በመንግስታ቞ው ላይ ቅሬታ ባይኖራ቞ው ኖሮ ደብዳቀውን ተቀብለው …
ለሰማያዊ ፓርቲ ባሉበት፤
ደብዳቀያቜሁን በጥሞና ተመልክተነዋል፡፡ ጥያቄያቜሁ ህገ መንግስታዊ እና ተገቢም ነው፡፡ ዚስብሰባ እና ሰላማዊ ሰልፍ “አዋቂ” ጜ/ቀትም ይህንን አይነት ጥያቄዎቜን ያበሚታታል፡፡ ነገር ግን በዕለቱ እንግዶቜ ስለሚበዙ እና ዚጥበቃ ሃይላቜንም ስራ ስለሚበዛበት መልካም ፈቃዳቜሁ ሆኖ ሰላማዊ ሰልፋቜሁን ለሌላ ግዜ ብታዘዋውሩት ደስታቜን ወደር ዹለውም፡፡
ኚሰላምታ ጋር!
አባይ ይገደባል ሰልፍም ይፈቀዳል፡፡
ዚማይታይ ማህተም እና ፊርማ፡፡
አድርጎ በጹዋ ደንብ መሞኘት ይቻል ነበር፡፡ ነገር ግንብዙዎቹ ዚመንግስት ሰራተኞቜ በተለይ ኹዚህ ዚግዳጅ ለአምስት መሚባዊ አደሚጃጀት እና ዚግዳጅ አባይ መዋጮ በኋላ አድማ ላይ ናቾው እና ደብዳቀ አንቀበልም ይላሉ፡፡ ይሄ ኚስራ ማቆም አድማ ተለይቶ አይታይም፡፡ ይሄ ፈቃድ ካልተጠዚቀበት ተቃውሞ ካለይቶ አይታይም፡፡
ዹሆነ ሆኖ አሁን ሰማያዊ ፓርቲ ደብዳቀውን በእማኞቜ ፊት ጠሚቀዛ ላይ አስቀምጊ ወጥቷል፡፡ በህጉ መሰሚት ሰልፉን ኚማድሚግ ምንም ዚሚያግደው ነገር ዹለም ማለት ነው… ትላንት ዚሰማያዊ ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎቜ ጥቁር ለብሰው ውለዋል፡፡ ዛሬም፡፡ ነገ ደግሞ ዹሚጠበቀውን ሰልፍ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ስለዚህም ሰማያዊዎቜ አምርሹዋል… አምሹዋልም!

May 23, 2013

ሰበር ዜና፣ ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፉን በታቀደው ቊታና ስዓት እንደሚያካሂድ አስታወቀ


ሰማያዊ ፓርቲ ዹተሰጠ ማብራሪያ
ሕገ ወጥነት ኚዓላማቜን አይገታንም!!!
ሕግ ምን ይላል?
አዋጅ ቁጥር ፫/፲፱፻፹፫ ዓ.ም 
ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት ዚወጣ አዋጅ፤ ሰላማዊ ሰልፍ ዚጠራው አካል ስላለበት ግዎታ በአንቀጜ ፬ ላይ እንዲህ ይላል  አንቀጜ ፬፤ ዚማሳወቅ ግዎታ፤
፩/ ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ህዝባዊ ዚፖለቲካ ስብሰባ ዚሚያዘጋጀው ማንኛውም ግለሰብ፣ ቡድን ወይም ድርጅት ዚታሰበው ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ ዚፖለቲካ ስብሰባ ኚሚካሄድበት ጊዜ ቢያንስ ኹ፵፰ ሰዓታት በፊት በጜሑፍ ዚማሳወቅ ግዎታ አለበት፡፡
፪/ ዚማሳወቂያው ጜሑፍ ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ ዚፖለቲካ ስብሰባ በኹተማ ኹሆነ ዹሚደሹገው ለኹተማው አስተዳደር ጜ/ቀት፤ ኹኹተማ ውጭ ኹሆነ ለአውራጃው አስተዳደር ጜ/ቀት ይሆናል፡፡
መልስ ሰጪው አካል ዹኹተማ ወይም ዚአውራጃው አስተዳደር ጜ/ቀት ያለበትን ግዎታና ኃላፊነት አንቀጜ ፮ ላይ እንዲህ ብሎ ደነግጋል፡፡
አንቀጜ ፮፤ ዹኹተማው ወይም አውራጃው አስተዳደር ጜ/ቀት ኃላፊነት፣
፩/ ኹተማው ወይም ዚአውራጃው አስተዳደር ጜ/ቀት ዹሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ ዚፖለቲካ ስብሰባ ጥያቄ በጜሑፍ ሲቀርብለት ሰላምን ኚማስፈን ጞጥታን ኚማስጠበቅና ዚሕዝቡን ዕለታዊ ኑሮ እንዳይሰናኚል ኚማድሚግ አንጻር አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ ዚማድሚግ ኃላፊነት አለበት፡፡
፪/ ኹተማው ወይም ዚአውራጃው አስተዳደር ጜ/ቀት በዚህ አዋጅ አንቀጜ ፮ ንዑስ አንቀጜ ፩ ዚተመለኚቱትን ሁኔታዎቜ በማገናዘብ ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ ዚፖለቲካ ስብሰባ በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ሥፍራ ቢደሚግ ይሻላል ዹሚል አስተያዚት ካለው ምክንያቱን በመግለጜ ይህንኑ ጥያቄው በደሹሰው በ፲፪ ሰዓት ውስጥ በጜሑፍ ለአዘጋጁ ማሳወቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ ሆኖም ዹኹተማው ወይም አውራጃው አስተዳደር ጜ/ቀት ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ ዚፖለቲካ ስብሰባው ምን ጊዜም በዚትኛውም ቊታ ሊካሄድ አይቜልም ማለት አይቜልም፡፡
ምን ተደሹገ?
ሰማያዊ ፓርቲ ዚጠራውን ዹተቃውሞ ሰልፍ ማወቅ ዚሚገባው በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቀት ዹሰላማዊ ሰልፍና ዚህዝባዊ ስብሰባ ማሰወቂያ ቢሮ እንዲያውቅ ዚሚያደርግበትን ደብዳቀ ግንቊት 14 ቀን 2005 ዓ.ም ኚጧቱ 4፡00 ሰዓት ዹተጠቀሰው ቢሮ ድሚስ አቅርቧል፡፡ ዚቢሮው ኃላፊ ደብባቀ አልቀበልም በማለታ቞ው ኚሰዓት በኋላም ኹቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ደብዳቀውን እንደገና አቅርቩ አሁንም አልቀበልም በማለታ቞ው ጉዳዩ ይመለኚታ቞ዋል ዚተባሉ ዚተለያዩ አካላት እስኚ ኚንቲባው ፅ/ቀት ኃላፊና ዚካቢኔ ጉጋዮቜ ምክትል ኃላፊ ድሚስ በመሄድ ደብዳቀውን እንዲቀበሉ ቢጠዚቁም “ደብዳቀ እንዳንቀበል ኹበላይ ታዘናል” በማለት በቃል ተመሳሳይ ዹአንቀበልም መልስ ሰጥተዋል፡፡ ኚብዙ ጥሚት በኋላ ኚፓርቲው በኩል ሊስት ሰዎቜ ኹማዘጋጃ ቀቱ ደግሞ ሊስት ሰዎቜ ዹአይን ምስክርነት ባሉበት በሰላማዊ ሰልፍና ዚህዝባዊ ስብሰባ ማሰወቂያ ቢሮ ኃላፊ ጠሹጮዛ ላይ አስቀምጠው ወጥተዋል፡፡ ኹዚህም በጠጚማሪ ደብዳቀው በፖስታ ቀት በኩል በሪኮመንዎ እንዲደርስ ተልኳል፡፡
ምን ይደሹጋል?
ሰማያዊ ፓርቲ በሕግ ዹተቋቋመ ህግ ዚሚያኚብር ፓርቲ ነው፡፡ ፓርቲው ዹሚገዛው ለህግ እንጅ ለውንብድና ባለመሆኑ ሰልፉን በዚህ መልኩ ለማሰናኹል ዚማይቻል መሆኑን ዚሚመለኚታ቞ው አካላት ሁሉ እንዲያውቁት ማሳሰብ ይፈልጋል፡፡ ሰልፉን ለማድሚግ እስኚ አሁኗ ሰዓት ድሚስ በህግ በኩል ዹጎደለ አንድም ቅንጣት ነገር ባለመኖሩ ሰልፉ በታቀደው ቊታና ስዓት ዚሚካሔድ መሆኑን ያሳውቃል፡፡
ግንቊት 15 ቀን 2005 ዓ.ም
አዲስ አበባ

Total Pageviews

Translate