Pages

Jan 14, 2013


ምርጫ ቊርድ 33ቱን ፓርቲዎቜ ጚምሮ ምልክት ያልወሰዱ በምርጫው እንደማይሳተፉ ገለጾ

ኢሳት ዜና:-ምርጫ ቊርድ እስካለፈው ሳምንት መጚሚሻ ቀርበው ዚምርጫ ምልክቶቻ቞ውን ያልወሰዱ ፓርቲዎቜ በሚያዝያው ምርጫ መሳተፍ እንደማይቜሉ በይፋ አስታወቀ፡፡ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኹ33ቱ ፓርቲዎቜ መካኚል ዚአንዱ  á‹šáŠ áˆ˜áˆ«áˆ­ አባል ዚምርጫ ቊርድ እርምጃ 33ቱ ፓርቲዎቜ ኚምርጫው ወጥተናል ኚማለታ቞ው በፊት “አባሚና቞ዋል” ለማለት ዹተወሰደ ስልታዊ እርምጃ ነው በሚል አጣጥለውታል፡፡
ቊርዱ ባወጣው ፕሮግራም መሰሚት ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ በማዕኹል በቊርዱ ጜ/ቀት ተገኝተው ዚመወዳደሪያ ምልክቶቻ቞ውን ዚሚወስዱበት ጊዜ ህዳር 14 ቀን 2005 ዓ.ም ዹነበሹ ቢሆንም  ፣ ዚፓርቲዎቜን ተሳትፎ ለማበሚታታት ሲባል ይኾው ጊዜ በተደጋጋሚ እንዲራዘም መደሹጉን ጠቅሶ ባለፈው ሳምንት መጚሚሻ ጊዜው መጠናቀቁን ይፋ አድርጓል፡፡
ኚቊርዱ ጜ/ቀት በተገኘው መሹጃ መሰሚት በጊዜ ገደባ቞ው ቀርበው ዚመወዳደሪያ ምልክቶቻ቞ውን ዚወሰዱ ፓርቲዎቜ ካሉት 75 ፓርቲዎቜ መካኚል 28 ያህሉ ብቻ ናቾው፡፡
ዹ33ቱ ፓርቲዎቜን ኹሚወክሉ ፓርቲዎቜ ዚአንዱ ዚአመራር አባል ዹሆኑ ስለጉዳዩ ተጠይቀው ነገሩ ቊርዱ ጩኞታቜንን ለመቀማት እሜቅድድም ውስጥ ዚገባ ያስመስለዋል ብለዋል፡፡
“33ቱ ፓርቲዎቜ ሕጋዊ በሆነ መንገድ ኚምርጫው በፊት ኚምርጫ ጋር በተያያዘ ባሉ ቜግሮቜ ላይ ተወያይተን እንድንፈታ ዕድል ስጠን በሚል ጥያቄዎቻቜንን በዝርዝር አቅርበናል፡፡ ቊርዱ ለጥያቄዎቻቜን መልስ ሳይሰጥ ኚአንድ ወር በላይ ኹቆዹ በኋላ ልክ ዚኢህአዎግ ባለስልጣናት በዚመድሚኩ ዚሚሉትን በመድገም “ቜግሮቜ አሉ ለተባለው ዹቀሹበ ማስሚጃ ዹለም፣ያሉትም ተፈትተዋል” በሚል በወጉ እንኳን ሳያነጋግሚን ጥያቄያቜን ውድቅ አድርጓል፡፡ይህ ሁኔታ ፓርቲዎቹን ብቻ ሳይሆን ዚሚወክሉትን ህዝብ መናቅ መሆኑን በመገንዘብ በምርጫው አጃቢ ሆኖ ላለመቅሚብ ዚጋራ ስምምነት እንደነበሚ እና ይህንንም አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን በመዘገባ቞ው በይፋ “ኚምርጫው ወጥተናል” ብለን መግለጫ ኚመስጠታቜን በፊት ቊርዱ ተሞቀዳድሞ “ምልክት ባለመውሰዳ቞ው ተባሚዋል” ለማለት ዹዘዹደው ዚሕጻን ጚዋታ ነው ሲሉ አጣጥለውታል፡፡
ያለፓርቲዎቜ ስምምነት እዚተጓዘ ያለው ዚዘንድሮ ምርጫ ሚያዝያ 6 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስአበባ፣በድሬዳዋ ፣በደቡብ ብሔር ብሔሚሰቊቜና ሕዝቊቜ ክልል ለኹተማ አስተዳደር፣ለወሚዳና ዹቀበሌ ም/ቀቶቜ ምርጫ እንደሚካሄድ ቊርዱ ያወጣው መርሃግብር ያሳያል፡፡

4 አመት ዚተፈሚደባ቞ው ዹሜጋው ባለስልጣን በሳምንቱ ኚእስር ተፈቱ


4 አመት ዚተፈሚደባ቞ው ዹሜጋው ባለስልጣን በሳምንቱ ኚእስር ተፈቱ

ኢሳት ዜና:-ዚኢትዮጵያ ገቢዎቜና ጉምሩክ ባለስልጣን በሜጋ ኪነጥበባት ኀ/ዹተ/ግ/ማ እና በቀድሞ ስራአስኪያጁ አቶ ዕቁባይ á‰ áˆ­áˆ„ ላይ በመሰሹተው ክስ መሰሚት አቶ ዕቁባይ አራት ዓመት ኚአምስት ወራት ቅጣት ኚተላለፈባ቞ው በኋላ ቅጣቱ á‰ áŒˆá‹°á‰¥ ተደርጎላቾው ተለቀዋል።ጥር ፫ (ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ዚባለስልጣኑ መለቀቅ ዚፍትህ ሥርዓቱ አድሎአዊነት በግልጜ ዚሚያሳይ መሆኑን አንድ ዹሕግ ባለሙያ áŒˆáˆˆáŒžá‹‹áˆ፡፡
ዚባለስልጣኑ ዓቃቀ ሕግ ባቀሚበው ክስ መሰሚት ዚፌዎራሉ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀት አስሚኛ ወንጀል ቜሎት ጉዳዩን áˆ²áˆ˜áˆˆáŠšá‰µ ቆይቶ ተጠርጣሪዎቹ በሁሉም ክሶቜ ጥፋተኛ ናቾው ያላ቞ው ሲሆን ድርጅቱም ሆነ ግለሰቡ ጥፋተኛ ዚተባሉበት áŠ áŠ•á‰€áŒŸá‰œ ዹ15 ዓመት ጜኑ እስራትና ዹ50 ሺ ብር መቀጫን ዚሚያስኚትሉ ቢሆንም ባልተለመደ መልኩ አቶ ዕቁባይ 12 እርኚን ዝቅ ያለ ቅጣት ማለትም አራት ዓመት ኚአምስት ወራት ፍ/ቀቱ ኚማስተላለፉም በተጚማሪ ቅጣቱም በገደብ áŠ¥áŠ•á‹²á‹«á‹áˆ‹á‰žá‹ ትላንትና ዹሰጠው ውሳኔ ዚፍትህ ስርዓቱን ጥያቄ ውስጥ ዚሚጥል አሳዛኝ ውሳኔ ነው ሲሉ ባለሙያው áŒ á‰áˆ˜á‹‹áˆ፡፡
ዚገቢዎቜና ጉምሩክ ባለስልጣን ኹዚህ በፊት ኚሰሳ቞ው ሰዎቜ መካኚል አይኀምአፍ በመባል ዚሚታወቁት አራጣ አበዳሪ áŠ á‰¶ አዹለ ደበላ ኹፍተኛ ተደራራቢ ሕመም እንዳለባ቞ው በቅጣት ማቅለያነት አቅርበው እንደነበር ባለሙያው አስታውሶ áŠáŒˆáˆ­ ግን እሳ቞ው በዚህ ምክንያት ቅጣቱ በ12 እርኚን ቀርቶ በስድስትም ዝቅ ሊልላቾው አልቻለም፡፡
አቶ ዕቁባይ ግን ዚሥርዓቱ ቁንጮዎቜ አንዱ በመሆናቾው፤ ዚሳንባ ሕመምተኛ መሆናቾው ተሹጋግጧል በሚል እንደትልቅ ዚቅጣት áˆ›á‰…ለያ ፍ/ቀቱ መያዙ ዹፍ/ቀቶቜ ነጻነት ዚይስሙላ መሆኑን ኚማሳዚት ባለፈ በዜጎቜ መካካል አድልኊ መፍጠሩ እጅግ áŠ¥áŠ•á‹°áˆšá‹«áˆ³á‹áŠ• ተናግሹዋል፡፡
ዚኢትዮጵያ ህግ ለዳኞቜ ሕሊና ዹሚተወው ነገር መኖሩን ዚጠቀሱት ባለሙያው እንደአገር ግን አንዱን 15 እና 20 á‹“መት እዚቀጡ ሌላውን በአራት ዓመትና በገደብ መልቀቅ ለፍትህ ሥርዓቱ ትልቅ ኪሳራ ነው ብለዋል፡፡
ዹሜጋ ኪነጥበባት ኹ1997-2000 ዓ.ም ድሚስ ገቢን አሳውቆ ግብርን ባለመክፈልና አትራፊ ድርጅት ሆኖ ሳለ áŠ¥áŠ•á‹°áŠšáˆ°áˆš በማስመሰል ዚንግድ ትርፍ ግብር ባለማስታቅና ዹተጭበሹበሹ መሹጃ በማቅሚብ ወንጀል መኚሰሱ ዚሚታወስ áŠá‹፡፡
አቶ ዕቁባይ ግብርና ታክስ በዚህ መልኩ ሲያጭበሚብሩ ዚቅርብ አለቃቾው ዚሜጋኔት ኮርፖሬሜን ዋና ስራ አስኪያጇ á‹šáŠ á‰¶ መለስ ባለቀት ወ/ሮ አዜብ መስፍን እንደነበሩም ይታወቃል፡፡
ወ/ሮ አዜብ ግን በዚሁ ጉዳይ ላይ ተጠያቂ አልሆኑም ነበር።

“ዚመለስን ሌጋሲ ማስቀጠል ዚማንቜል ኹሆነ ህዝቡ እሳት ሆኖ እንዳያቃጥለን እንሰጋለን” ሲሉ ዚኢህአዎግ አባላት ተናገሩ


“ዚመለስን ሌጋሲ ማስቀጠል ዚማንቜል ኹሆነ ህዝቡ እሳት ሆኖ እንዳያቃጥለን እንሰጋለን” ሲሉ ዚኢህአዎግ አባላት ተናገሩ

ኢሳት ዜና:-በሚስጥር ዹደሹሰን በአዲስ አበባ  ዚኢህአዎግ ድርጅት ጜህፈት ቀት ያዘጋጀው ሚስጢራዊ ሪፖርት እንደሚያመለክተው  á‹šáŠ¢áˆ…áŠ á‹ŽáŒ አባላት ኚመለስ ሌጋሲ እና ኚልማት ጋር ዚተያያዙ በርካታ ጥያቄዎቜን ማንሳታ቞ው ተመልክቷል።ጥር ፬ (አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ዚኢህአዎግ አባላት  ካነሱዋ቞ው ሀሳቊቜ መካኚል “  መስመሩን ያላወቁ አባላት ባለበት እንዎት ሌጋሲውን ማስቀጠል ይቻላል? አባሎቜ ራሳ቞ው ጀርባ቞ው መጠናት አለበት፣ ንፋስ ወደ ነፈሰበት ዚሚነፍሱ ቁጥራ቞ው እዚበዛ ነው፣ ዚመለስ ሌጋሲ ሊኖር ዚሚቜለው ስርአቱ እስካለ ድሚስ ነው፣ ዚሚስጥር ጠባቂነት ቜግር በአመራሩ ኹላይ እስኚታቜ አለ፣ አመራሩ ኪራይ ሰብሳቢነትን አምርሮ አይታገልም፣ህወሀት ሀይለማርያምን ማስቀጠል ዚለበትም ምክንያቱም ታግሎ ዚመጣ ሰው ነው መምራት ያለበት”   ዚሚሉት ይገኙበታል።
በጥሩ ጎን ተብለው ኚተጠቀሱት ሀሳቊቜ መካኚል ” ዚመለስን ሌጋሲ ለማስቀጠል ዹማይፈልግ ዚሰማዕታትን አደራ ለመቀበል ዝግጁ ያልሆነ ሰው ነው፤ ዚመለስን ሌጋሲ ለማስቀጠል አመራር መሆን አያስፈልግም ፣ መለስ ትክክለኛ ሃገር ወዳድ ነው፣ ደፋር መሪ ነው፡፡ በሌሎቜ መሪዎቜ ያልተደፈሩ ተግባራትን ዹደፈሹ ነው፡፡”  á‹šáˆšáˆ‰á‰µ ተዘርዝሹዋል።

ዚኢህአዎግ ዚሰራተኛ አባል መድሚክ ዚአቶ መለስን ሌጋሲ ኚማስቀጠል አንጻር ካነሱዋ቞ው ጥያቄዎቜ መካኚል ደግሞ ዚሚኚተሉት ተጠቅሰዋል ”  áˆµáˆˆ መለስ ብቻ ይወራል መለስን ዹፈጠሹው ኢህአዎግ ስለሆነ ዚኢህአዎግን ሙሉነት ብናወራ አይሻልም ወይ፣ ኚመለስ ብዙ እንማራለን በርካታ ጠንካራ ጎኖቜ አሉት፣ እኛ ዚሱን ሌጋሲ ለማስቀጠል ዚህብሚተሰቡን ቜግር ለመቅሹፍ ምን ያህል ዝግጁ ነን፣ስለሌጋሲ እያወያያቜሁን ነው፣ እናንተ እራሳቜሁ ቁርጠኝነታቜሁ እስኚምን ድሚስ ነው፣ ራስን ኚማብቃት አንጻር ኚመለስ ሌጋሲ ዹምንማሹው አለ ሆኖም አመራሩም ሆነ አባሉ ቜግር አለበት ማስተካኚል አለብን” ዚሚሉት ተጠቅሰዋል።

ዚኑሮ ውድነቱን በተመለኹተ አባሎቜ ካነሱዋ቞ው ነጥቊቜ መካኚል ደግሞ ” በኑሮ ውድነቱ ዚመንግስት ሰራተኛው እዚተጎዳ በመሆኑ ዚህዳሎ ጉዞአቜንን ኚማሳካት አንጻር አንዱን ሀይል እንዳናጣው እንሰጋለን፣ ያለፈው አመት ቜግር በታዚበት ዹአሁኑ እቅድ ኚስፋት አንጻር ለማሳካት ይኚብዳል” ዚሚሉት ይገኙበታል።

ዚኢህአዎግ ሰራተኛ አባላት በመለስ ሌጋሲ ላይ ካነሱዋ቞ው ጥያቄዎቜ መካኚል ደግሞ ” ስለመለስ ሌጋሲ እናውራ ስንል በሙት መንፈስ መመራት አያስምስልም ወይ? ዚመለስ ሌጋሲ እያልን ዚምናወራው ሁሌ ጠንካራ ጎኑን ነው፣ ደካማ ጎን ዹለውም ወይ? ጠናካራ ዹሆኑ ዹተቃዋሚ ፓርቲ ፓርላማ እንዲገቡ ልምን አላዳሚገም።” ዚሚሉት ተነስተዋል።
ዚአባላት መድሚክ ካነሱዋ቞ው ነጥቊቜ ውስጥ ደግሞ  ”
- ዚመለስ ሌጋሲ ማስቀጠል ማንቜል ኹሆነ ህዝቡ  እሳት ሆኖ እንዳያቃጥለን እንሰጋለን ስለዚህ ሌጋሲውን ኚማስቀጠል ውጭ ሌላ አማራጭ ሊኖር አይቜልም
- ሌጋሲውን ለማስቀጠል አቅም ክፍተት አለብን
- ዚመለስ ሌጋሲን መውሚስ ሲባል እሱን መሆን ሳይሆን ባለንበትና በተሰማራንበት ዚህዝብ አገልጋይነት ስሜት መፍጠር መላበስ ነው፣ ኚመለስ ሌጋሲ አባሉ ሲመዘን እና ዚሰአት መስዋት መክፈል አንፈልግም እሱ ግን ዚህይወት መስዋትነት ኹፍሎ አሳይቶናል” ዚሚሉት ይገኙበታል።
ግንባሩን በተመለኹተም ” ዚአባላት ዚተሳትፎ ቜግር አለ፣ ዚውስጥ ድርጅት ስራቜን በጣም ተዳክሞአል፣ ድጋፍና ክትትል አካባቢ ያለው ስራም አናሳ ነው፣ አመራሩ ዹሚፈልገን ለዘመቻ ስራ እንጅ በቋሚነት ዹመደገፍ ቜግር አለበት ፡” ዚሚሉት ተጠቅሰዋል።
በህዝብ መድሚክ ኚተነሱት ጥያቄዎቜ መካኚል ደግሞ “ተማሪዎቜ በአጥር እዚዘለሉ ጫትና ሺሻ ቀት እዚገቡ ተቾግሹናል፣ ሺሻ ቀት ኹቀን ወደ ቀን ሲበራኚት ለምን እርምጃ አትወስዱም ፣ ሺሻ ቀቶቜ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ሲታሰብ ሚስጢሮቜ ኚፖሊስና ኚአስፈጻሚ በኩል ይወጣሉ፣ ኚፖሊስ ሲጠሩ በወቅቱ አይመጡም፣ ዚጞጥታ ኮሚ቎ ተብለው ዚተመደቡት እራሳ቞ው ቜግር አለባ቞ው፣   á‹šáˆšáˆ‰á‰µ ይገኙበታል።

ይድሚስ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ… ኹዛም እኔም ደስ ይበለኝ


ወዳጄ እንዎት ሰነበቱልኝ፤ ዛሬ አስ቞ኳይ ጉዳይ ገጠመኝና ዚደቡብ ልጆቜ በኬኒያ ዹሚለውን ጚዋታ ሳልቀጥልልዎ ልቀር ነው። በምትኩ ዚቀድሞው ዚደቡብ ክልል ፕሚዘዳንት ዹአሁኑ ዚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ለሆኑት አቶ ሃይለማሪያም አንድ ደብዳቀ አዘጋጅቻለሁ… እማኝ ይሆኑኛል አብሚዋ቞ው ያንብቡልኝ!
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፤ ሃይለማሪያም ደሳለኝ፤
በመጀመሪያ ሰላም ልበልዎ መሰለኝ፤ እንዎት አሉልኝ! ቀጥሎም ልጠይቅዎ መሰለኝ፤ ያንን ሃይማኖተኝነትዎን ተዉት ወይስ እንዳለ ነው? ባለፈው ግዜ በፓርላማው “እግዜር ኢትዮጵያን ይባርክ” ሲባል ኹፓርላማ አባላቱ ጋር ሆነው ኚት ብለው ሲስቁ አይቌዎታለሁ…? ወይስ አላዚዎትም? ዹሆነው ይሁንና፤ ቢያንስ ግን ዹፓርላማ አባላቱን በምግባራ቞ው ሲገስፁ ባለማዚ቎ ነው ሃይማኖተኝነቱን ትተውት ይሆን…? ብዬ መጠራጠሬ፤ ግድዚለም አለተዉትም በሚለው ታሳቢ አድርጌ ልቀጥል፤
እንኳን ለጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚልደት በዓል አደሚስዎ! እንዲሁም በዚሱስ ስም ቀልብዎን አሰባስበው ያንቡብልኝ፤
ያኔ ዚስልጣኑ በር ላይ ቆመው ዚሀገሪቱ ጠቅላይ ዹመሆን አለመሆንዎ ነገር እንደ አጓጊ ትያትር ልብ ሰቀላ ላይ ሳለ፤ ኚተለያዩ ቊታዎቜ እርስዎ ቀጣዩ ጠቅላይ ዹመሆን እድል እንዳልዎት ፍንጭ በሰማን ቁጥር፤ ነግሰው በፍንጭትዎ ፈገግ ሲሉልን እዚታዚን “ወፌ ቆመቜ ባልወደቀቜ…” እያልን ደጋፊዎ ሆነን ዹቆዹን እጅግ በርካቶቜ ነን።
ለዚህ በርካታ ምክንያቶቜ አሉን፤ ኚምክንያቶቻቜን ውስጥም፤ ታጋዮቹ ደማቾው ቶሎ ቶሎ ግንፍል እያለ ፓርላማ ውስጥ ቁጣ቞ው አሰልቜቶን ነበርና ቢያንስ እኒህ ዚሀይማኖት ሰው ሰኹን ብለው ሲናገሩ እንሰማ቞ው ይሆናል። ዹሚለው አንዱ ነበር። ሌለውስ…? ሌላው ደግሞ አሁንም ኚዕምነትዎ አንፃር መዋሞት እንደነውር ይቆጠራልና እንደቀድሞዎቹ… ዹምናውቀውን ሀቅ ሲዋሹን አናይም ኹሚል ተስፋም ነበር። ሌላስ…? ሌላማ እንግዲህ እርስዎም እንደቀድሞዎቹ “ፈሪሳውያን” በርባን ይፈታ ክርስቶስ ይሰቀል ዹሚሉ አይደሉምና ንፁሀንን ለሞትና ለእስር አይንዎ እያዚ አሳልፈው አይሰጡም በሚል ተስፋም ነበር።
ኹነበር በኋላ፤
በዛንም ቀን አነሆ እርስዎ ዚተኚበሩት፤ አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ በተቀበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ምትክ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሟሙ። መጀመሪያ ደስ አለን ቀጥሎም ደስታቜን ኹምን ዚተነሳ ነበር…? ብለን ጠዹቅን።
ቆይማ ደሹቅ አደሚኩብዎ መሰል… ትንሜ ዋዛ እንጚምርበት፤ ለመሳቅ ይዘጋጁ በእርስዎ ላይ ዚተቀለደቜ አንዲት ቀልድ ናት፤ አዲስ መስመር ይውሚዱና ያገኟታል። (በቅንፍም አይዝዎት አዲስ መስመር ይውሚዱ ነው ያልኩዎ ኚስልጣንዎ ይውሚዱ አላልኩም።)
በአንዱ ቀን አሉ ኚሶስቱ ልጆቜዎ አንዷ ኩርፍ ብላ ሳሎን ተቀምጣ አገኟት፤ ታድያ እርሶ ሆዬ በአባት አይንዎ እያዩ እና አናቷን ዳበስ ዳበስ እያደሚጉ “ምን ሆነሻል ልጄ!?” ሲሉ ጠዚቋት። እርሷም ለንቊጯን ጣል አድርጋ ዹፈተና ውጀቷ ጥሩ እንዳልሆነ ነገሚቜዎ፤ ይሄኔ እርስዎ ሆዬ “አይዞሜ ያገኘሜው ዚስራሜን ውጀት ስለሆነ አትኚፊ” አሏት፤ እርሷ ግን “ዚሚያናድደውኮ እሱ ነው!” አለቜዎ። ለካስ ልጅዎ ፈተናዋን ዚወደቀቜው ኹሰው ኮርጃ ሰርታ ኖሯል። ይሄኔ እርስዎ ሆዬ ሊመክሩ… መቌም ምክር ቀላል ነውና፤ “ልጄ ዹሰው ነገርማ መኮሚጅ አይገባም…” ብለው ገና  ሲጀምሩላት ኚኢትዮጵያ ቎ሌቪዥን ዚእርስዎ ንግግር ሲጀምር እኩል ሆነ፤ “መሹጃ አለን ማስሚጃ ግን ዹለንም…” ብለው ልክ እንደ ሟቹ ሲናገሩ ተሰማ፤ ይቺን ንግግር አቶ መለስ ፈጠሯት፤ ኹዛ ሰው ለሰው ድራማ ኮሚጃት፤ ኹዛ ደግሞ እርስዎ ኮሚጇት… ልጅዎ ይሄንን ሁሉ አዚቜ ሳቀቜም። ኹዛ ስለኩሚጃ አስኚፊነት እንዎት ይምኚሯት…!
ቀልዷ አላሳቀቜዎትም መሰል። አዎ ዋናው ቁምነገሯ ማሳቁ ላይ ሳይሆን በኩሚጃዎ ቀተሰብዎም መሳቀቁን ለመጠቆም ነው።
እናልዎ ስንት ተስፋ ያደሚግንብዎ ሰውዬ ኹውሃ አጠጣጥዎ ጀምሮ እስኚ ኩስትሪያዎ እና ቁጣዎ ድሚስ ቁርጥ ያለፉትን ሆነው ቁጭ! እኛም፤ ለመሆኑ ቪዲዮውን ስንት ግዜ ቢያዩት ነው!? ብለን ተደነቅን፤ ተደንቀንም ፃፍን፤
በነገራቜን ላይ በዚህ ዹፓርላማ ውሎዎ ላይ ኚብ቞ኛው ተቃዋሚ ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉ ስለ ማተሚያ ቀት ተጠይቀው ዚመለሱት መልስ አስደምሞኛል። እዝቜው ላይ ነገርን ነገር ያንሳውና “በሀገሪቱ ውስጥ ያሉት ማተሚያ ቀቶቜ 34 ይመስሉኝ ነበር ለካስ ኚሁለት መቶ በላይ ማተሚያ ቀቶቜ አሉ…” ብለው ገና መልስዎ ሲጀምሩ ድሮውንም ስለሚመሯት ሀገር ያልዎት ዕውቀት አናሳ መሆኑን “አስፎገሩ” ለዚህም ነው ይህንን ንግግርዎን ኢቲቪ ማታ ድጋሚ ሲያቀርበው በሳንሱር መቀሱ ቆርጩ ያወጣው።
ለነገሩ እርስዎ ስለሀገርዎ ጉዳይ ባዳ እንደሆኑ ካወቅን ቆዹን፤ ምነው እንኳ ባለፈው ጊዜ ኚአልጀዚራ ቎ሌቪዥን ጋር ቃለ ምልልስ ሲያደርጉ “ኀርትራ ዚሚወስደኝ ባገኝ ሄጄ ኚአቶ ኢሳያስ ጋር እታሚቅ ነበር” ብለው ሲሉ፣ ጋዜጠኛይቱ፤ “ታድያ ዹዚህ ዹዚህ እግር ኳስ ቡድናቜሁ ሰሞኑን ኀርትራ ሄዶ እንዳይጫወት ለምን ኚለኚላቜሁ?” ብላ ብትጠይቅዎ “ይሄንን ገና ካንቺ ሰማሁ” ብለው ብንሰማ እኛ ለርስዎ ተሾማቀን፣ ተሾማቀን ሾማቂ መሆን አልነበር እንዎ ዹተመኘነው…!?
ዹኔ ነገር፤ ዚጀመርኩትን ወሬ ሳልቋጭ ሌላ ጚዋታ ውስጥ ዶልኩዎ አይደል፤ ይቅርታ ያድርጉልኝ፤ እኔስ ኚአንዱ ጚዋታ ወደሌላ ጚዋታ ነው ዚዶልኩዎ አንዳንዶቜ አሉ ኚቜግር ወደ ቜግር ዚሚዶሉ፤ እነርሱን ነው መገሰፅ! ታድያ ስም አልጠቀስኩም…
እናልዎ ታድያ “ማተሚያ ቀቶቜን ዚኢህአዎግ ካድሬ ደውሎ በፍፁም አያስፈራራም” ብለው አፍዎን ሞልተው ሲናገሩ ብሰማ እኔ አፍሬ አፌን ያዝኩልዎ…
ይሄ መልስዎ ኹምን ጋር ይመሳሰላል መሰልዎ አንዳንድ እናቶቜ አሉ ልጆቻ቞ውን ዚተንኚባኚቡ መስሏ቞ው ለባሰ ጥፋት ዚሚያጋልጧ቞ው። እንዲህ አይነት እናቶቜ ስለ ልጃቾው ጥፋት ስሞታ ቢመጣላ቞ውም “ዹኔ ልጅ በፍፁም እንዲህ አያደርግም” ይላሉ። ይሄ አይነቱ ምላሜ ልጆቹን ዚባሰ አጥፊ እነዲሆኑ ነው ዚሚያደርጋ቞ው። እንዲህ አይነት እናትና ልጆቜ በዚሰፈሩ አሉ፤ እርስዎም ሰፈር አይጠፉም። (ዚድሮ ሰፈርዎ ማለቮ ነው)
ታድያ እርስዎም እዲህ እንዳሉት እናቶቜ “ዹኔ ካድሬ በፍፁም እንዲህ አያደርግም ይሉልኛል” እኔ አለሁ አይደል እንዎ ያልሞትኩ እማኝ፤
በአንድ ወቅት አንድ መፅሀፍ ላሳትም ፈልጌ ላንቻ አካባቢ ያለ አንድ ማተሚያ ቀት ሄጄ ነበር። ቀብድ ኚኚፈልኩት በኋላ መፅሐፌን ማተም ሊጀምር ሲል ሜፋኑን ተመለኹተው። በሜፋኑ ላይ ዚአራት ሰዎቜ ፎቶግራፍ ይታያል። ዚዳኛ ብርቱካን ሚዎቅሳ፣ ዚዶክተር ብርሃኑ ነጋ፣ ዹጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እና ዹምንም አቶ ልደቱ አያሌው ፎቶግራፍ ነበሚበት።
እና አታሚዬ እነዚህን ፎቶግራፎቜ ብቻ ተመልክቶ ዚሰጠሁትን አስራ ምናምን ሺህ ብር ቀብድ መለሰልኝ፤ ኹዛም፤ “እኔ በእሳት አልጫወትም ሰዎቹ አስጠንቅቀውኛል ውሰድልኝ” አለኝ። “በእሳት አልጫወትም” ያለው እናንተን መሆኑ ነው። በወቅቱ መንግስታቜን ፀሐይ እንጂ እሳት እንዎት ይባላል ብዬ ቅር ብሎኝ ነበር። አሁን ግን እርስዎም ደጋግመው ሲናገሩ እንደሰማሁት፤ ማንኛውም ሰዉ መንግስትን አንድ ጥያቄ ሲጠይቅ “ይሄ በእሳት መጫወት ነው” ሲሉ ብሰማ እውነትም መንግስ቎ እሳት ነውና እውነትም ይፋጃልና! ስል ዕውቀቮን አዳብሬያለሁ።
ዹሆነው ሆኖ አቶ ሃይለማሪያም ተስፋ ዚጣልንብዎትን ያህል ተስፋ እያስቆሚጡን ነው።
ዛሬ ይሄንን ደብዳቀ እንድፅፍልዎ ያስገደደኝ ዋናው ምክንያት፤ ሰሞኑን በፌስ ቡክ ላይ አጭር መልዕክት ሰድጄልዎ ምንም ምላሜ በማጣ቎ እስቲ ደግሞ ዘርዘር አድርጌ ልንገራ቞ው ብዬ ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስ቎ር፤
አሁን በቅርቡ ሁለት ህፃናት ልጆቜ በታጠቁ ዚፖሊስ ሀይሎቜ ተገድለዋል። ይሄ ዚምነግርዎት ታሪክ ጋዛ ውስጥ በሮኬት ጥቃት ዹሆነውን አይደለም። እኛው ሀገር ኢትዮጵያቜን ውስጥ ነው። ሮኬት በሆኑ ፖሊሶቜዎ ዹተደሹገ እንጂ፤
አንዷ ጡት ጠብታ ያልጚተሚሰቜ ህፃን በእናቷ ጀርባ እንደታዘለቜ አዲሳባ ውስጥ “ቀታቜን ፈሹሰ” ብለው ለመንግስት አቀት ሲሉ በፖሊስ ዱላ ተመታ መገደሏን ሰምተን ሀዘኑ ኚልባቜን ሳይወጣ፤ ሌላው ዚሰባት አመት ህፃን ደግሞ በሀሹር ኹተማ ያለምንም ሰሚ አንድ አመቱን ዹደፈነው ዚሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ላይ በአጋጣሚ በመገኘቱ ተገደለ። ምናልባት ይህንን አልሰሙ ይሆናል።
በሀገሪቱ ውስጥ ስንት ማተሚያ ቀት እንዳለ ዚማያውቁ ሰውዬ፣ ዹሀገርዎ ብሄራዊ ቡድን ኀርትራ ሄዶ እንዳይጫወት መኹልኹሉን ኚውጪ ጋዜጠኛ ዹሚሰሙ ሰውዬ፣ ይሄንን ጉዳይ እስካሁን አልሰማሁም ነበር፤ ቢሉኝ አይገርመኝም። አሁን ግን ይስሙኝ…
ባለፈው ግዜ በፌስ ቡክ ገፄ ላይ እንዳልኩዎ ይህ አይነቱ ጭካኔ ዚሄሮዶስ ወታደሮቜ ብቻ ናቾው ያደሚጉት።
ወቅቱ ኢዚሱስ ክርስቶስ ይወለዳል እርሱም ዹአለም ሁሉ ንጉስ ይሆናል ተብሎ ትንቢት ዚተነገሚበት ወቅት ነበር። ታድያ ሄሮዶስ በዚቜ ምድር ላይማ እኔ እያለሁ ማንም አይነግሳትም ብሎ በዛን ወቅት ዚተወለዱ ህፃናትን በሙሉ አስጚፈጚፈ። ቁጥራ቞ውም ሶስት ሺህ ይደርስ ነበር።
በነገራቜን ላይ በሀሹር ኹተማ ለተገደለው ህፃን አስኚሬን ለመውሰድ እናቲቱ ሶስት ሺህ ብር ክፈይ ተብላለቜ አሉ።
እናም ራሄል ስለ ልጆቿ አለቀሰቜ ልቅሶዋም በሰማይ ተሰማ!
ይላል እያነበቡ ያደጉት መፅሐፍ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሆይ በዚሱስ ስም፤ ዛሬ ነገ ሳይሉ ይህ አይነቱን ጥቃት ያስቁሙ። እንዲሁም ይህንን ዹፈፀሙ ሰዎቜ ቅጣታ቞ው ሲፈፀም ያሳዩን ይህንን ማስፈፀም ኚተሳንዎ ፍፃሜዎ ቢሆን ይሻልዎታል።
አክባሪዎ!

ቻይና በኢትዮጵያዊያን ላይ ዚምታደርሰው ሰቆቃ

Jan 11, 2013


ኹ33 ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ ዹተሰጠ መግለጫ

ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቊርድ ዚምርጫውን ሂደት እዚገፋ ያለው ለገዢው ፓርቲ ብቻ በተመቻ቞ ሜዳ ነው!

ኹ33ቱ ዚአዳማ ፔ቎ሜን ፈራሚ ፓርቲዎቜ ዹተሰጠ መግለጫ

በምርጫ አስፈፃሚው፣ ኚምርጫ አስተዳደርና በምርጫው ሂደት ላይ ዚሚታዩ መሠሚታዊ ቜግሮቜን በማንሣት ቜግሮቹ ስለሚፈቱበት መንገድ ዚውይይት /ምክክር/ መድሚክ እንዲመቻቜ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቊርድና ለመንግሥት አካላት ጥያቄአቜንን ማቅሚባቜን ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቊርድ ዚማያሣምኑ ምክንያቶቜ በመስጠት ጥያቄዎቻቜንን ሙሉ በሙሉ ውድቅ ማድሚጉን በቃል ዹገለፀልን ሲሆን ለመንግሥት ላቀሚብነው ጥያቄ ምላሹን እዚተጠባበቅን ነው፡፡
ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ዚምርጫ ቊርድ ዚተጣለበትን ዹአገርና ዚሕዝብ ኃላፊነት ወደጐን በመግፋት ምርጫውን ሠላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ለማድሚግ ዚመወዳደሪያ ሜዳውን ኚማስተካኚል ይልቅ ዚገዢው ፓርቲ ወገንተኝነቱንና ጉዳይ ፈፃሚነቱን ባሚጋገጠበት አቋሙ በመግፋት ወደ ምርጫ እንቅስቃሎ መግባቱን በይፋ አውጇል፡፡
እኛ በያዝነው ሠላማዊ ዚትግል መሥመር በምርጫ ዚመሣተፍ /አለመሳተፍ ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ ዚሚገባ ያለመሆኑንና ዚሕዝብ ዘርፈ ብዙ ውስብስብ ጥያቄዎቜ ምላሜ ዚምንሰጥበት ብ቞ኛው ዚመንግሥት ሥልጣን መያዣ መሣሪያቜን መሆኑን በተደጋጋሚ በግልጜ አስቀምጠናል፡፡ ዚአካባቢ ምርጫ ወደ ሕዝቡ ዘልቆ ለመድሚስ ዚሚያስቜል እንደመሆኑ ኹአገር አቀፍ ምርጫ ያነሰ ትኩሚትና ቊታ ዹምንሰጠው አይደለም፡፡ ይልቁንም ለምንፈልገው ዚሥርዓት ለውጥና ዚዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መሠሚቱ ዚሚጣለው በሕዝቡ ውስጥ ስለሆነ ለዚህ ምርጫ ተገቢውን ትኩሚት ሰጥተን ጠንክሹን ለመንቀሳቀስ ዝግጅታቜንን በተባበሚና በተቀናጀ መንገድ ለማድሚግ እዚተንቀሳቀስን ባለንበት ነው ዚጋራ ጥያቄዎቻቜንን ያቀሚብነው፡፡ ይሁን እንጂ ምርጫ ቊርድ በኢህአዎግ እዚተመራና እዚታገዘ ኹጊዜ ሰሌዳ በፊት በመሠሚታዊ ጉዳዮቜ ላይ መወያዚት ይቅደም በማለት 41 ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ በአዳማው ስብሰባ ላይ ላቀሚብነው ዚቊርዱ ሰብሣቢ “ዚውይይት መድሚክ ይዘጋጃል” በማለት ዚመለሱትን፣ እንዲሁም 33 በሕጋዊና ሠላማዊ መንገድ ዚምንታገል ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ፔቲሜን ፈርመን ላቀሚብነው ዚቊርዱ ጜ/ቀት ኃላፊ “ባትጠይቁንም ማድሚግ ያለብን ነው” “. . . ጉዳዩን ሣታጮሁት በትዕግሥት ጠብቁ” ማለታ቞ውን ክደው ኚአዳማ በተመለሱ በ4ኛው ቀን አፀደቅን ባሉት ዹጊዜ ሰሌዳ ገፍተውበታል፡፡ በዚህ መሠሚት ቊርዱ መዝግቀ ዚምሥክር ወሚቀት ሰጠሁ ብሎ ኚሚዘሚዝራ቞ው 75 ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ውስጥ 28ቱ ብቻ ዚምርጫ ምልክት በወሰዱት፣ ዚምልክት መምሚጫ ጊዜ አልፏል /ተጠናቃል/፣ ኚማለት አልፎ ዚሕዝብ ታዛቢዎ አስመርጬ ዚመራጮቜ ምዝገባ ጀምሬአለሁ፣ በቀጣይም በጊዜ ሰሌዳዬ መሠሚት እቀጥላለሁ ዹሚል ዘመቻውን ተያይዞታል፡፡ በምርጫ ህጉ መሠሚት በምርጫ ዘመን በፓርቲዎቜ ዹሚደሹገው ቅስቀሳና በፓርቲዎቜ መካኚል በመገናኛ ብዙኃን ዚሚካሄደውን ዚፖሊሲዎቜ አማራጭ አቀራሚብ ቊርዱ በፍትሃዊነት ዹአዹር ጊዜ ደልድሎ መምራት ሲገባው ራሱ አፀደቅሁ ካለው ዹጊዜ ሰሌዳ ውጪ በኢህአዎግና መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዚምርጫ ውድድር እንቅስቃሎ /ክርክር/ ሲያደርጉ ማስቆም አልፈለገም፣ አልቻለም፡፡
በዚህ ተጚባጭ እውነታ ውስጥ ነው ጥያቄዎቻቜሁ ዚተመለሱ ናቾው . . .በማለት ወደ ምርጫ ማስፈጞም ዚገባው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ዚምርጫ መወዳደሪያው ሜዳ ተስተካክሏልና ያለአንዳቜ ጥያቄ በምርጫው ተሣትፋ ካልፈለጋቜሁ ተውት ዹሚል ዚማንአለብኝነት ግልጜ መልዕክት ነው፡፡ ስለሆነም ለጉዳዩ ዋነኛና ቀዳሚ ባለቀት ለሆነው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ እና ምርጫውን ለምትደግፉና ለምትኚታተሉ ዹዓለም ማኅበሚሰብ አባላት በድጋሚ ዚምናስተላልፈው ጥሪ ምርጫ ቊርድ በኢህአዎግ አይዞህ ባይነት በያዘው “ካፈርኩ አይመልሰኝ” አቋም መግፋቱ በጥያቄአቜን መሠሚት ዚምርጫ መወዳደሪያ ሜዳውን ዚሚያስተካክል ስላልሆነ በቀጣይ ተወያይተን ዚምናሳውቃቜሁን ዚጋራ አቋም በንቃት እንድትጠብቁና ሂደቱን በትኩሚት እንድትኚታተሉ ነው፡፡
ቊርዱ 28 ፓርቲዎቜ ብቻ በተመዘገቡበትና ለጥያቄዎቻቜን (ጥያቄዎቹ ዹ41 ፓርቲዎቜ መሆናቾውን በማጀን) መልስ ባልተሰጠበት ይልቁንም ቜግሮቹ እዚተባባሱ በመጡበት በምርጫው እቀጥልበታለሁ ዹሚለው አቋም ምርጫውን ተአማኒ አሣታፊ እና ተቀባይነት ያለው አያደርገውምና ውሣኔውን እንደገና በመመርመር ለአገራቜን ዚዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስተዋጜኊ ለማድሚግ አሁንም ጊዜው ያልመሞበት መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ሌሎቜ አሁን በተያዘው ዚምርጫ ሂደት ውስጥ ዚገባቜሁ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ያቀሚብና቞ው ጥያቄዎቜና ቜግሮቹ ዹሃገርና ዚጋራ መሆናቾውን ተሚድታቜሁ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ዚበኩላቜሁን አስተዋጜኊ እንድታደርጉ ዳግም አገራዊ ጥሪያቜንን እናቀርብላቜኋለን፡፡
በተባበሚ ትግላቜን ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንገነባለን!
ታህሳስ 25/2005፣ አዲስ አበባ
በአንድነት ፓርቲ ዚህዝብ ግንኙነት ዚተሰራጚ

ጉዕሜ አበራ ማነዉ?

ጉዕሜ ኣበራ ቆላ ተንቀን በሚባለዉ በተንቀን ኣዉራጃ ተወልዶ ያደገ እና ለሆዳ቞ዉ ኚሚያድሩ አደርባዮቜ እና ህዝባ቞ዉ ኚሚያስጚፍጭፉ አንዱ ሲሆን በት/ቱ ሰነፍ እና ኣቃጣሪ ዹሆነ ግለGuesh Abera TPLF spy áˆ°á‰¥ ነዉ፡፡
ጉዕሜ በቅርቡ በተንቀን በኣሉላ ኣባ ነጋ ስም ሲጠራ ዹነበሹዉ ት/ቀት በመለሰ በመቀዚሩ ኚተደሰቱት ሰዎቜ አንዱ ሲሆን ተንቀን ምን ታመጣላቹ? ተንቀኖቜ ስታለቅሱ ትኖራላቹ እያለ በተንቀን ተወላዶቜ ሜብር ሲፈጥር ዹነበሹ እና ኣሁንም በተንቀን ተወላጆቜ ክፍፍል ለመፍጠር ዚቀት ስራ ተሰጥቶት እዚሰራ ያለ ሰዉ ነዉ፡፡ጉዕሜ አበራ ዚኣሉላ ት/ቀት ተቀይሮ መለስ ተብሎ እንዲጠራ ካደሚጉት ካድሬዎቜ አንዱ ሲሆን ዹኹተማዉ ስም ተንቀን ቀርቶ መለስ ዜናዊ ተብሎ ኹተማዉ ራሱ እንዲጠራ እናደርጋለን እያለም ሲናገር ዚሚደመጥ ሰብእናዉ ሜጊ ለሆዱ ያደሚ ዚሰዎቜ መጠቀሚያ ዹሆነ አሳፋሪ ሰዉ ነዉ፡፡
ጉዕሜ በብዛት ዓጋመ፣ ተምቀን፡ እንደርታ እና ራያ ዚሚያንቆሞሹ ፅሕፎቜ በፌስ ቡክ እና በሌሎቜ ዚህዝብ መገናኛ ብዙሃን ዚሚለጥፍ ሰዉ ሲሆን በአሁኑ ሰአት በተንቀን ተወላጆቜ እንደ ወንጀለኛ እና ኚዳተኛ ዹሚቆጠር ሰዉ ነዉ፡፡ ጉዕሜ ንፁሃን ዚትግራይ ልጆቜ ለማስወንጀል እና ለማሾበር ስም ዚሚቀያይርና ለትግራይ ተወላጆቜም አገራቹ አትገቡም፡ ፎታቹ ኀርፖርት ገብቶዋል እያለ በህዝብና መንግስት ክፍተት እዚፈጠሚ ዹሚገኝ በተፈጥሮ ዹዋህ ግን ለሰዎቜ መጠቀሚያ በጣም ምቹ ዹሆነ ሰዉ ነዉ፡፡
ኹዚህ በተጚማሪ ጉዕሜ ዚትግራይ በተለይም ዚተንቀን ተወላጆቜ እንዲገደሉ እና እንድታሰሩ ስም ዝርዝር ኣሳልፎ ዚሚሰጥ ሲሆን ለዚህም በ ዚተንቀን እና በሌሎቜ ዚትግራይ ተወላጆቜ ጥርስ ዚገባ ሰዉ ነዉ፡፡ ጉዕሜ ኣበራ ወደ ኣሜሪካ ኚመጣ 3ት ዓመት ያደሚገ ሲሆን በኣሜሪካ ቀት ተሰጥቶት ዹሚኖር እና በተንቀንም በነፃ መሬት ተሰጥቶት በህዝብ ገንዘብ ቀት ዚገነባ ሰዉ ነዉ፡፡ ጉዕሜ በተደጋጋሚ ኣሉላ ኣባነጋ ፡ ሃፄ ዮሃንስ ፡ ሓዹሎም ኣሚአያን እና ሌሎቜ ጀግኖቜ ዚሚያጥላሉ ፅሕፎቜ ዚሚለጥፍ እና በቅርቡም እኔ እኮ ዚተንቀን ልጅ ኣይደለሁም ስለሆነም ዚተንቀን ጉዳይ ዠብ ይብላዉ ብሎ ይናገር እንደነበር አሱ በቅርበት ዚሚያዉቁ ይናገራሉ፡፡ ጉዕሜ በአሁኑ ሰኣት ዉጪ በሚኖሩ ዚተንቀን ተወላጆቜ ሙሉ በሙሉ ዹተገለለ እና በዚማንነት ዚቀዉስ ዉስጥ ዹሚገኝ ሰዉ ነዉ፡፡
እ/ሔር አገራቜን ይጠብቅልን

ኢትዮ቎ሌኮም ዚወያኔ ዘሚኝነት ፖሊሰ መንጞባሚቂያ መሆኑን ዚግንቊት ሰባት ዹአገር ዉስጥ ኢንተሊጀንስ አጋለጠ

ዹመሹጃ ቮክኖሎጂ መሠሚት ዹሆነዉ ዚ቎ሌኮሚኒኬሺን ዘርፍ አፍሪካ፤ ላቲን አሜሪካና ኢሲያ ዉስጥ ዹሚገኙ በእደገት ወደ ኋላ ዚቀሩ አገሮቜን ለዘመናት ኚተዘፈቁበት ዹኋለ ቀርነት ማጥ ዉስጥ ጎትቶ አዉጥቶ ወደ ፈጣን ዚእድገት ጎዳና ይወስዳ቞ዋል ተበሎ ዚታመነበትና በአንዳንድ አገሮቜ ዉስጥ ይህ ለእድገት አመቺነቱ በተግባር ዚተመሰኚሚለት ዘርፍ ነዉ። ይህ ዘርፍ ገበሬዉ፤ ሰራተኛዉ፤ ተማሪዉ፤ ወታደሩና ለሌላም በማንኛዉም ዚስራ ዘርፍ ለተሰማራ ዚህብሚተሰብ ክፍል ዚእዉቀት ምንጭ በመሆን ዚስራ ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ዹሚሹደና በህብሚተሰብ መካኚል ፈጣን ዹሆነ ዹመሹጃ ልዉዉጥ አንዲኖር ዚሚያደርግ ዘርፍ ነዉ። በእድገት ወደ ኋላ ለቀሚቜዉ አገራቜን ኢትዮጵያም ይሀ ዘርፍ እጅግ በጣም አስፈላጊ ዹሆነ ዘርፍ ነዉ። ነገር ግን በአፍሪካ ዉስጥ አገራቜን ኢትዮጵያ እጅግ በጣም ወደኋላ ኚቀርቜባ቞ዉና ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ ዘሹኛና አምባገነን አገዛዝ ሆን ብሎ እድገታ቞ዉ እንዲገታ ካደሚጋ቞ዉ ኋላ ቀር ዘርፎቜ ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ይሄዉ ዚ቎ሌኮሚኒኬሺን ዘርፍ ነዉ።
እራሱን “ልማታዊ መንግስት” ብሎ ዚሚጠራዉ ዚወያኔ አገዛዝ ስልጣን ኚያዘባ቞ዉ ዚመጀመሪያዎቹ አመታት ጀምሮ አስኚ ቅርብ ግዜ ድሚስ እንደ ቀት ዉስጥ ዕቃዉ ኚተቆጣጠራ቞ዉና ዚኢትዮጵያን ህዝብ በሚጠቅም መልኩ እንዳያድጉ ካደሚጋ቞ዉ ቁልፍ መስሪያ ቀቶቜ ዉስጥ አንዱ ኢትዮ቎ሌኮም ነዉ። ወያኔ ኢትዮ቎ሌኮምን ያላደሚገዉ ነገር ዹለም። ዘሚኝነትን በሚጠቅም መልኩ አደራጅቶታል፤ ዚራሱን ሰዎቜ ጠቅጥቆበታል፤ ቻይናዎቜን አምጥቶ ዚስለላ ተቋም አድርጎታል፤ ዹሚገርመዉ ዛሬ ኢትዮ቎ሌኮም ዚተራቀቀዉ በስልክ፤ በኢንተርኔትና በሌሎቜም ዹመገናና አገልግሎቶቜ ሳይሆን ዜጎቜን በመሰለልና ዹመሹጃ ጹለማ በመፍጠር ርካሜና ጎታቜ ስራዎቜ ነዉ። ይህንን ርካሜ ስራ ደግሞ በቅርቡ ዹአገዛዙ ዚኢንፎርሜሺን ደህንነት ኀጀንሲ ሹም ብ/ጄኔራል ተክለብርሃን ወልደአሹጋይ “ዚኢትዮጜያ ቎ሌኮምኒኬሜን” ዚኀብሚተሰቡን ሰላም ዚሚያጠፉ ዌብሳይቶቜን ዚመቆጣጠርና ዚኢንተርኔት ድሚገጟቜና ብሎጎቜን ዚማገድ አቅም ሊኖሹው ይገባል፡፡መርሁም ይህ ነዉ በማለት በአዳባባይ አሹጋግጧል።
ዚግንቊት ሰባት ዚፍትህ፤ ዚነፃነትና ዚዲሞክራሲ ንቅናቄ ዹአገር ዉስጥ ኢንተሊጀንስ ዘርፍ በላፉት አስራ ሁለት ወራት ይህንኑ ኢትዮ቎ሌኮም በሚል መጠሪያ ዹሚተወቀዉንና በስለላ ስራ ላይ ዚተሰማራዉን ዚሲቪል መስሪያ ቀት አደሚጃጀት፤ አወቃቀርና ዹሰዉ ኃይል አመዳደብ በቅርብ ተኚታትሎ ኹዚህ ቀትሎ ዚሚታዚዉን መሹጃ አጠናቅሯል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሚገባ እንደሚያዉቀዉ ዘሹኛዉ ዚወያኔ አገዛዝ ዚኢትዮጵያን ቎ሌኮሚኒኬሺን ተቋም ኹኋላ ቅርነት ለማላቀቅ በሚል ሰበብ ዚኮርፖሬሺኑን ዚማኔጅመንት ዘርፍ ለፈሚንሳይ ኩባኒያ መስጠቱ ዚሚታወስ ነዉ። ወያኔ እንደሚለዉ ዚኢትዮ቎ሌኮም ማነጅመንት ለፈሚንሳዩ ኩባኒያ ዹተሰጠዉ ዚኮርፖሬ ኑን አቅም ለማሳደግ ቢሆን ኖሮ መልካም ነበር፤ ነገር ግን ወያኔ ዹሚናገሹዉና ዚሚሰራዉ ስራ ዚተለያዚ በመሆኑ ዛሬ ወያኔ ኢትዮ቎ሌኮም በዹዘርፉ ዹሹጂም ግዜ ልምድ ያላ቞ዉን ባለሙያዎቜ አባርሮ ታማኝ ዚህወሀት ታጋዮቜን በመተካት ኮርፖሬሺኑን ዚለዚለት ዚስለላ ተቋም አድርጎታል። ስለሆነም ዛሬ ብዙ ዚአፍርካ አገሮቜ ትልቅ ግስጋሎ ያደሚጉበትና ዚዜጎቻ቞ዉን ህይወት ዚለወጡበት ዘርፍ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዜጎቜን እዚሰለለ አገሹን ዹመሹጃ ጹለማ ዉስጥ ዹኹተተ ተቋም ሆኗል።
ባላፉት ሁለት አመታት ዚኢትዮ቎ሌኮም ማነጅመንት ኀን አንድና ኀን ሁለት በሚባሉ ሁለት ኹፍተኛ ዚአስተዳደር እርኚኖቜ ተኹፍሎ በሁለቱም ኹፍተኛ ዚአመራር እርኚኖቜ ዉስጥ ዹሰዉ ኃይል ተመድቧል። ይህ በኹፍተኛ ማነጅመንት ደሹጃ ዹተመደበዉ ዹሰዉ ኃይል ኢትዮጵያዉያንንና ዚፈሚንሳይ ዜጎቜን ዚሚያጠቃልል ነዉ። በኀን አንድና በኀን ሁለት ዚማነጅመንት ደሹጃ ዚስራ ድርሻ ዚተሰጣ቞ዉ ኢትዮኊጵያዉያን በቁጥር 54 ሲሆኑ ኹዚህ ዉስጥ 46.3 በመቶ ወይም ሃያ አምስቱ ዚትግራይ ተወላጆቜ ናቾዉ። በዚህ ኹፍተኛ ዚማነጅመንት እርኚን ዉስጥ ዚኊሮሞ፤ ዚአማራና ዚተቀሩት ስድሰት ክልሎቜ ድርሻ በቅደም ተኹተል 18. 5 በመቶ፤ 29.6 በመቶና 5.6 በመቶ ብቻ ነዉ። ኚሁለቱ ዚማነጅመንት እርኚኖቜ ዉስጥ ኀን አንድ ዚሚባለዉ ኹፍተኛዉ ሲሆን በዚህ እርክን ዉስጥ ሰምንት ዚትግራይ ተወላጆቜ ሲኖሩ ዚአማራና ዚኊሮሞ ተወላጆቜ እያንዳንዳ቞ዉ ሁለት ቊታ ዚያዙ ሲሆን በዚህ ኹፍተኛ ዚአመራር እርኚን ዉስጥ ኚተቀሩት ስድስት ክልሎቜ ዹተመደበ አንድም ሰዉ ዹለም።
ጠቅለል ባለ መልኩ ሲታይ ኚእያንዳንዱ 3.3 ሚሊዮን ዚኊሮሞ ተወላጅ ዉስጥ በኢትዮ ቎ሌኮም ኹፍተኛ አመራር ቊታ ዹተሰጠዉ አንድ ዚኊሮሞ ተወላጅ ብቻ ሲሆን ትግራይን ስንመለኚት ግን ኚእያንዳንዱ 194 ሺ ዚትግራይ ተወላጅ ዉስጥ ቢያንስ አንድ ሰዉ በኢትዮ ቎ሌኮም ኹፍተኛ አመራር ቊታ ላይ ተቀምጧል። ይህ ዚስራ አመዳደብ ዚትምህርት ቜሎታንና ልምድን ተኚትሎ ዚተሰራ ነዉ ቢባል እንኳን ዹላቀ ዚትምህርት ደሹጃና ዚስራ ልምድ ያለ቞ዉ ዚኊሮሞ ተወላጆቜ ቁጥር ተመሳሳይ ዚትምህርት ደሹጃና ዚስራ ልምድ ካላ቞ዉ ዚትግራይ ተወላጆቜ ቁጥር በአስር እጥፍ መብለጡ ምንም ጥርጥር ዹለዉም። ሌላም መራራ ሀቅ አለ። 66 ነጥብ 2 በመቶ ዹሚሆነዉን ዚኢትዮጵያ ህዝብ ኚሚያቅፉት ኚኊሮሚያና ኚአማራ ክልል N1 በሚባለዉ ኹፍተኛ ዚአመራር አርኹን ዉስጥ በአመራር ቊታ ዚተቀመጡ ዜጎቜ ብዛት አራት ብቻ ነዉ (ሁለት ኚኊሮሚያ ሁለት ኚአማራ)። ኹጠቅላላዉ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዉስጥ 5.4 በመቶዉ ብቻ ኚሚኖርበት ኚትግራይ ክልል ግን ስምንት ሰዎቜ ኀን አንድ በሚባለዉ ኹፍተኛ ዚአመራር ቊታ ላይ ተቀምጠዋል።
በኢትዮ ቎ሌኮም ኹፍተኛ አመራር ቊታ ላይ ኚተቀሩት ስድስት ዚአገሪቱ ክልሎቜ ዚመጡትን ሰዎቾ ስንመለኚት ዚሚታዚዉ ስዕል እጅግ በጣም ዚሚያሳዝንና ወያኔ ዚብሔር ብሔሚሰቊቜ እኩልነት እያለ ኚሚሰብኚዉ ስብኚት ጋሹ ዹሚጋጭ ነዉ። በ2012 ኚኊሮሚያ፤ ኚአማራና ኚትግራይ ክልል ዉጭ በተቀሩት ስድስት ክልሎቜ ዉስጥ ዹሚኖሹዉ ህዝብ 25,627,349 እንደሚሆን ይገመታል። ኹዚህ ህዝብ ዉስጥ በኢትዮ ቎ሌኮም ኹፍተኛ አመራር ቊታ ላይ ዚመቀመጥ እድል ያገኙት 0.000012 በመቶ ብቻ ወይም ኚእያንዳንዱ 8.5 ሚሊዮን ህዝብ አንዱ ብቻ ነዉ። እንግዲህ ይህንን ነዉ ወያኔ ዚኢትዮጵያ ብሔር ብሔሚሰቊቜ እኩልነታ቞ዉን ተጎናጜፈዋል እያለ ዹሚናገሹዉ።
ዚግንቊት ሰባት ዚፍትህ፤ ዚነፃነትና ዚዲሞክራሲ ንቅናቄ ኹዚህ ቀደም ወያኔ “ዚኢትዮጵያ መኚላኚያ” ጩር እያለ ዚሚጠራዉን ሠራዊት ምን ያክል ዹኔ በሚላቾዉ ዚህወሀት ሰዎቜ ብቻ እንደሚቀጣጠር ዚሚያሳይ መግለጫ በመሹጃ አስደግፎ ለህዝብ ማቅሚቡ ዚሚታወስ ነዉ። አሁንም ወያኔ ኢትዮ቎ሌኮምን ምን ያክል ዚራሱ ዚቀት ዉስጥ እቃዉ እንዳደሚገዉ ዚሚያሳዚዉን በጜሁፍና በአኀዝ ዹተፈገፈ መሹጃ በዛሬዉ እለት ለህዝብ ይፋ ዚሚያደርግ መሆኑን እዚገለጞ ኹአሁን በኋላም ዚወያኔን ዘሚኝነትና ህግወጥነት ዚሚያጋልጡ ስራዎቜን በተኚታታይ እዚሰራ ለህዝብ ዚሚያቀርብ መሆኑን ይገልጻል።

ዚጥናቱ እጠቃላይ ውጀት

ማስታወሻ: ኹላይ በስዕሉ ዚሚታዚው እንደተጠበቀ ሆኖ በኢትዮ-቎ሌኮም ቁልፍ ዚሃላፊነት ቊታወቜ ውስጥ ቢያንስ ቢያንስ ወደ 50% ዹሚሆነው ቊታ ዚተያዘው በትግራይ ተወላጆቜ ነው።
ይንንም ለማብራራት ያህል በአሁኑ ሰአት ካለው ጠቅላላ ዚሃፊነት ቀልፍ ቊታወቜ 14ቱ በፈሚንሳውያን ዚተያዙ ቢሆንም ኹ14 ዚፈሚንሳይ ባለሙያወቜ ኚያዟ቞ው ቀልፍ ቊታወቜ ውስጥ 7ቱ በትግራ ተወላጆቜ እንደሚያዙ ይጠበቃል። ይህም ማለት በትግራይ ተወላጆቜ ዚተያዙትን እና ዚሚያዙትን ቁልፍ ዚኢትዮ-቎ሌኮም ቊታወቜ ኹተጠቅላለው 64ቱ ዚሃላፊነት ቊታ቞ው ውስጥ 32ቱ በትግራይ ተወላጆቜ ዚተያዙ ይሆናሉ። ይህም ማለት ኹጠቅላላወ ዚኢትዮ-቎ሌኮም ቁልፍ ዚሃልፊነት ቊታ቞ው ውስጥ ግማሹ ማለትም 47% ዚሚሆኑትን በትግራይ ተወላጆቜ ዚተያዙ መሆናቾው ያሳያል።

ዚጥናቱ ዝርዘር ማብራያ

በዚህ ሰነድ ላይ ዚተጠቃለሉት ስሞቜ በኢትዮ ቎ሌኮም ዋና መስሪያ ቀት ዉስጥ በሁለት ኹፍተኛ (N1 & N2) ዚአመራር እርኚኖቜ ዉሰጥ ዚተመደቡ ሰዎቜ ስምና ዚመጡበት ብሔር ስብጥር ነዉ። ባጠቃላይ በሁለቱ ዚአመራር እርኚኖቜ ዉስጥ 68 ሰዎቜ ዹሚገኙ ሲሆን ኹዚህ ዉስጥ አስራ ሰባቱ (N1 ዉስጥ 8 N2 ዉስጥ 9) ዚፈሚንሳይ ተወላጆቜ ነበሩ። ሆኖም ቀስ በቀስ በተደሹገዉ መሾጋሾግ ዚፈሚንሳይ ዜጎቜ ዚለቀቁት ቊታ እዚተመሚጠ ለትግራይ ተወላጆቜ ብቻ በመሰጠቱ አሁን በN1 ዉስጥ 5 N2 ዉስጥ 9 ባጠቃላይ 14 ዚፈሚንሳይ ዜጎቜ አሉ ፤ በቅርቡ አንድ ሌላ ዚፈሚንሳይ ዜጋ በኢትዮጵያዊ ዚተተካ ቢሆንም ይህ ሠኢድ አራጋዉ ዚተባለ ግልሰብ አማራ ይሁን ትግሬ ለግዜዉ በዉል ለይቶ ማወቅ አልተቻለም። በእርኚን አንድ ዉስጥ ስምንት ዚትግራይ፤ ሁለት ዚአማራና ሁለት ዚኊሮሞ ተወላጆቜ ሲኖሩበት ኚሌሎቹ ሰባት ክልሎቜ ዚመጣ አንድም ሰዉ በዚህ N1 በሚባለዉ ዚአመራር አርኹን ላይ አልተመደበም። በአጠቃላይ በ N1 ዚአመራር አርኹን ዉስጥ 17 ሰዎቜ ሲኖሩ አስራ ሁለቱ ኢትዮጵያዉያን አምስቱ ደግሞ ዚፈሚንሳይ ተወላጆቜ ናቾዉ። ኚአስራ ሁለቱ ኢትዮጵያዉያን ዉስጥ ሰባቱ ዚትግራይ ተወላጆቜ ናቾዉ። N2 በሚባለዉ ዚአመራር አርኹን ዉስጥ ደግሞ 51 ግለሰባኊቜ በአመራር ቊታ ላይ ዚተመደቡ ሲሆን 42 ኢትዮጵያዉያን 9ኙ ፈሚንሳዉያን ናቾዉ። ኚአርባ ሁለቱ ኢትዮጵያዉያን ዉስጥ አስራ ሰባቱ ዚትግራይ ተወላጆቜ ናቾዉ።
ይህ በኹዚህ ቀጠሎ ዹተቀመጠዉ ግራፍ እና ሰነተሚዥ ዚሚያሳዚዉ በኢትዮ ቎ሌኮም ኹፍተኛ አመራር ቊታ ላይ ዚተቀመጡትን ሰዎቜ ዚብሔር ስብጥር ነዉ። ግራፉ ዚሚያሳዚዉ ሊስቱን ማለትም ኚኊሮሚያ፤ ኚአማራና ኚትግራይ ክልል ዚተመሚጡ ሰዎቜን ለዚብቻ቞ዉ ሲሆን ኚተቀሩት ሰባቱ ክልሎቜ ዚመጡት ሰዎቜ ግን ተጹፍለቀዉ አንድ ላይ ነዉ ዚቀሚቡት።
ማስታወሻ: ኹላይ በሰንጠሚዡ ዹጠቀሰው ዚህዝብ ብዛት እኀአ በ2007 CSO ያወጣዉን ዚህዝብ ብዛት መግለጫ ተንተርስሶ በ2012 ዚኢትዪጵያ ህዝብ ብዛት 90,076, 661 ይሆናል በሚል ግምት ዹተቀመሹ ነዉ።
በኢትዮ ቎ሌኮም ኹፍተኛ አመራር ቊታ ላይ ዚተቀመጡት ሰዎቜ ዚብሔር ስብጥር
ኹላይ በተቀመጠዉ ዚህዝብ ብዛት መሠሚት በ N-1 እና በ N-2 ዚአመራር እርኚን ኢትዮ ቎ኊኮም ኚተመደቡ ሰራተኞቜ ዉስጥ ዹሚኹተለዉን ገሀድ እዉነት መመልኚት ይቻላል።
ኚእያንዳንዱ 3.3 ሚሊዮን ዚኊሮሞ ተወላጅ ዉስጥ በኢትዮ ቎ሌኮም ኹፍተኛ አመራር ቊታ ዹተሰጠዉ አንድ ዚኊሮሞ ተወላጅ ብቻ ሲሆን ትግራይን ስንመለኚት ግን ኚእያንዳንዱ 193.9 ሺ ዚትግራይ ተወላጅ ዉስጥ ቢያንስ አንድ ሰዉ በኢትዮ ቎ሌኮም ኹፍተኛ አመራር ቊታ ላይ ተቀምጧል። ይህ ዚስራ አመዳደብ ዚትምህርት ቜሎታንና ልምድን ተኚትሎ ዚተሰራ ነዉ ቢባል እንኳን ዹላቀ ዚትምህርት ደሹጃና ዚስራ ልምድ ያለ቞ዉ ዚኊሮሞ ተወላጆቜ ቁጥር ተመሳሳይ ዚትምህርት ደሹጃና ዚስራ ልምድ ካላ቞ዉ ዚትግራይ ተወላጆቜ ቁጥር በአስር እጥፍ መብለጡ ምንም ጥርጥር ዹለዉም። ሌላም መራራ ሀቅ አለ። 66.2 በመቶ ዹሚሆነዉን ዚኢትዮጵያ ህዝብ ኚሚያቅፉት ኚኊሮሚያና ኚአማራ ክልል N1 በሚባለዉ ኹፍተኛ ዚአመራር አርኹን ዉስጥ በአመራር ቊታ ዚተቀመጡ ዜጎቜ ብዛት 4 ብቻ ነዉ (2 ኚኊሮሚያ 2 ኚአማራ)። ኹጠቅላላዉ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዉስጥ 5.4 በመቶዉ ብቻ ኚሚኖርበት ኚትግራይ ክልል ግን 7 ሰዎቜ N1 በሚባለዉ ኹፍተኛ ዚአመራር ቊታ ላይ ተቀምጠዋል።
ኹዚህ በታቜ ያለው ሠንጠሚዥ ዚሚያሳዚዉ ኢትዮ-቎ሌኮም ዉስጥ N-1 በመባል በሚታወቀዉ ኹፍተኛ ዚአመራር እርኚን ላይ ዚተቀመጡትን ባለሙያዎቜ ዚብሔር ስብጥር ነዉ፤ በዚህ ስብጥር ዉስጥ ዚፈሚንሳይ ዜጎቜም አሉበት። በ N-1 አመራር እርኚን ዉስጥ ኚትግራይ፤ ኚኊሮሚያና ኚአማራ ብሔሚሰቊቜ ዉጭ ኚሌሎቹ ዚተካተተ ማንም ዹለም።
ኢትዮ-቎ሌኮም ዉስጥ N-1 በመባል በሚታወቀዉ ኹፍተኛ ዚአመራር እርኚን ላይ ዚተቀመጡትን ባለሙያዎቜ ዚብሔር ስብጥር
ኹላይ ካለው ሰንጠሚዥ ላይ እንደምንመለኚተዉ በ N-1 ዚአመራር እርኚን ደሹጃ ላይ ዚተቀመጡ ኢትዮጵያዉያን ብዛት አስራ አንድ ሲሆን ሰባቱ ዚትግራይ ተወላጆቜ ናቾዉ። ዚእነዚህን 7 ሰዎቜ ዚስልጣን ቊታ ስንመለኚት ደግሞ ሁሉም ዚያዙት ቊታ ቁልፍ ቁልፋዩን ቊታ ነዉ። ለምሳሌ ዚፕሮግራም ማነጀር፤ ፕሮግራም ዳይሚክተርና ዚቺፍ ፋይናንሻል ኊፊሰርነቱን ቊታ ዚያዙት ዚትግራይ ተወላጆቜ ሲሆኑ ዚኊሮሞዉና ዚአማራዉ ተወላጆቜ በቅደም ተኹተል ዹህግ አማካሪነቱንና ዚኢዲተርነቱን ቊታ ነዉ ዚያዙት።
ኹዚህ በታቜ ያለው ሠንጠሚዥ ዚሚያሳዚዉ ኢትዮ-቎ሌኮም ዉስጥ N-2 በመባል በሚታወቀዉ ኹፍተኛ ዚአመራር እርኚን ላይ ዚተቀመጡትን ባለሙያዎቜ ዚብሔር ስብጥር ነዉ። በ N-2 ኹፍተኛ ዚአመራር እርክን ዉስጥ ዘጠኝ ዚፈሚንሳይ ዜጎቜ ዹሚገኙ ቢሆንም በሰንጠሚዡ ዉስጥ ዚፈሚንሳይ ዜጎቜ ቁጥር አልተካተተም (N-2 ኹ N-1 ያነሰ ደሹጃ ነዉ)።
ኢትዮ-቎ሌኮም ዉስጥ N-2 በመባል በሚታወቀዉ ኹፍተኛ ዚአመራር እርኚን ላይ ዚተቀመጡትን ባለሙያዎቜ ዚብሔር ስብጥር
ኢትዮጵያ ዉስጥ በህዝብ ብዛትም ሆነ በተማሹ ሰዉ ሀይል ብዛት ኹፍተኛዉን ቊታ ዚያዘዉ ዚኊሮሚያ ክልል ነዉ። በህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀትም ኹፍተኛዉን ዚመቀመጫ ቁጥር ዚያዙት ዚኊሮሚያ ክልል ተወካዮቜ ናቾዉ። ሆኖም በሰንጠሚዡ ላይ እንደምንመለኚተዉ ኢትዮ቎ሌኮም ዉስጥ በN-1ም ሆነ በN-2 ደሹጃ በአመራር ላይ ኚተቀመጡት መሪዎቜ ዉስጥ ዚኊሮሚያ ድርሻ ኹክልሉ ትልቅነት ጋር ሲነፃፀር አነስተኛ ነዉ ወይም ኚትንሿ ትግራይ ጋር ሲወዳደር ቁጥሩ እጅግ በጣም አነስተኛ ነዉ።
በፖለቲካ ሀይል መስክም ቢሆን እንደዚሁ ነዉ። ህወሀት በህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ዉስጥ ያለዉ መቀመጫ ብዛት 8 ብቻ ነዉ። ሆኖም ዚፖለቲካዉ ጡንቻዉ 178 መቀመጫ ካለዉ ኊህዎድ ጋር ሲወዳደር ሰማይና ምድር ነዉ። ህወሀት ዚአገሪቱን ጩር ሀይል፤ ፖሊሰ ሰራዊት፤ ዚደህንነት ተቋምና ዚኀኮኖሚ መዋቅሮቜ ይቆጣጠራል። ኊህዎድ ግን ኹሰሞኑ እንደማስተዛዘኛ ኚተወሚወሚለት ዚይስሙላ ምክትል ጠ/ሚኒስትርነት ዉጭ ይህ ነዉ ዚሚባል ዚፖለቲካ ጡንቻ ዹለዉም áŠšáˆŠáˆµá‰± ክልሎቜ ማለትም ኚአማራ፤ ኚኊሚሚያና ኚትግራይ ክልሎቜ ዉጭ በሌሎቹ ስድስት ክልሎቜ ዉስጥ 25,627,349 ያክል ህዝብ እንደሚኖር ይታመናል። ኢትዮ቎ሌኮም ዉስጥ በ N- 1 ኹፍተኛ ዚአመራር ቊታ ላይ ዚእነዚህ ሰባት ክልሎቜ ድርሻ ሊስት ብቻ ነዉ። እንግዲህ ዜጎቜ በሞያ቞ዉ በሚሰሩት ስራ፤ በፖለቲካ ህይል አሰላለፍና በኀኮኖሚዉ ዘርፍ ዉስጥ በሚጫወቱት ሚና እንዲዚህ አይነት አይን ያወጣ አድሎ ዚሚደሚግባ቞ዉ ኹሆነ ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፈጠርኩት ዹሚለዉ እኩልነት ምኑ ላይ ነዉ? ዚባህል ዘፈን መዝፈን ኹሆነ እንደዛሬዉ በ቎ሉቪዥን አይታይም እንጂ ድሮም እንዘፍናለን።



Ethiopia, the same regime another Genocide?

G7 Press Release – January 10, 2013
On December 13, 2003, members of the special unit of the Ethiopian military entered the town of Gambella in south western Ethiopia, and over the course of the next three days, the special force unit tortured and killed 424 ethnic Anuaks and burned their houses to ashes. The Ethiopian Human Rights Council and Dr. Gregory H. Stanton, founder and President of Genocide Watch, alerted the international community about the Gambella genocide. The world gave a deaf ear to the horror in Gambella, and as a result, the Ethiopian military continued its crime against humanity killing more than 2000 ethnic Anuaks and causing over 50,000 to flee their ancestral home land.
On December 10, 2013, exactly 10 years after the Gambella genocide, the Ethiopian military strikes again, this time in Southern Ethiopia killing more than 150 men, women, and children. According to an eye witness account, the Ethiopian army surrounded the village of ethnic Suris in South Ethiopia, tied the villagers into a group of two, and massacred them execution style. Ginbot 7, Movement for Justice, Freedom and Democracy strongly condemns the barbaric action of the TPLF security forces against the Suri community and calls on all civilized nations of the world to hold the Ethiopian regime accountable for its actions and bring the perpetrators of this heinous crime to justice.
The continued silence of the international community, especially donor nations such as the U.S, U.K., and members of the European Union has emboldened the Ethiopian regime to continue committing crimes against defenseless people in different parts of the country.
Ginbot 7 is deeply disturbed by the acquiescence of the international community and the quiet support provided to a rogue regime that repeatedly commits crimes against humanity.
Ginbot 7 urges the international community to reconsider its hypocritical policy and use its leverage to rein the TPLF regime to stop the mass killing in Ethiopia.
Ginbot 7 and the Ethiopian people understand the importance of the global war on terror. However, membership in the international military campaign against terror must not allow the criminal regime in Ethiopia to terrorize its own people. The US, the UK and the EU cannot fight terrorism in Somalia while enabling a terrorist regime to commit genocide in Ethiopia. This misguided foreign policy is morally reprehensible and a danger to the long term stability of Ethiopia.

ዹጀርመን አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎቜ ካህናት፣ ዲያቆናትና ምእመናን ዚተማኅጜኖ ደብዳቀ አቀሚቡ

በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ዹጀርመን አጥቢያ አብያተ
ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎቜ ካህናት፣ ዲያቆናትና ምእመናን ዚተማኅጜኖ
ደብዳቀ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለዉ «áŠšáˆáˆ‰áˆ ግን ፍቅር ይበልጣል።»
ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን በውስጧ ብቻ ሳይሆን ኚሌሎቜ ቀተ
እምነቶቜ ጋር እንኳ ፍቅርን በማስቀደም በመፈቃቀርና በመኚባበር በክርስቶስ ራስነት፣
በሐዋርያት አስተምህሮና እምነት መሠሚት ላይ ሐዋርያዊ ተልእኮዋን ስታፋጥን
ዘመናትን አስቆጥራ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት እኛ ካለንበት ዘመን ደርሳለቜ። ዚቀተ
ክርስቲያኗ ሐዋርያዊ ጉዞ በርግጥ ጥንትም ቀላል አልነበሹም። ሆኖም በተለያዩ ጊዜያት
ዚገጠሟት ፈተናዎቜ በአመዛኙ ኹዉጭ ዚመጡ እንደመሆና቞ው ዚቀተ ክርስቲያኒቱ
ዚእምነት አባቶቜ በጜናትና በሃይማኖት ተጋድሎ አልፈውት ዛሬ ታሪክ ሆኗል። ዚዛሬዋ
ቀተ ክርስቲያናቜንም ኹመንጋዉ እሚኛ ስያሜ ጋር በተገናኘ በተለይም ላለፉት ሃያ አንድ
ዓመታት እጅግ አሳዛኝ ሂደትን አሳልፋለቜ። ዛሬም ዹሚሰማዉ ሁሉ ፆሩ እንዳልበሚደ
ያመለክታል። ይህ ዹዉጭ ተፅዕኖ ብቻ ነዉ ለማለት እንዲኚብድ ዚሚያደርገዉ ደግሞ
አሁንም ኹዚሁ ዹፈተና አዙሪት መዉጣት እንዳትቜል ዹተደነቀሹው ውስጣዊ መሰናክል
መኖሩ ነዉ።
በፓትርያርክ ስያሜ መግባባት ጠፍቶ ዹሀገር ውስጥና ስደተኛ ሲኖዶስ በሚል
አባቶቻቜን መለያዚታ቞ዉና ይልቁንም እስኚመወጋገዝ መድሚሳ቞ው ኅሊናቜንን
ሲፈታተነው ቆይቷል። ይህን ዚመለያዚት መንፈስ ይሰብራል ዚተባለ ዚእርቅ ሰላሙ
ውይይት በዳላስ መጀመሩን ሰምተን መንፈሳቜን ነቅቶ ፈጣሪያቜን ፍሬዉን እንዲያሳዚን
ስንማፀንም ሰነበትን። ዚእርቀ ሰላሙ ዉይይት በይደር ተቀጥሮ ሳለ ውጀቱ ሳይታይ
በሀገር ቀት ለፓትርያርክ ስያሜ እጩ መሚጣ ብሎም ዝግጅት መኖሩን መስማት፤
ዚዚህቜ ቀተ ክርስቲያን ልጅ ነኝ ብሎ በጜናት ለሚቆም ኊርቶዶክሳዊ ሁሉ ምን ያህል
አስደንጋጭና አንገት አስደፊ እንደሆነ ማብራሪያ ዚሚያስፈልገው አይደለም።
ምክንያቱም በአሁኑ ሰዓት ካህናትም ሆኑ ምእመናን ዚቀተ ክርስቲያናቜን አንድነት
ተጠብቆ ማዚት ዋና ምኞታ቞ው ብሎም እፎይታ ስለሆነ ነው። ይህ ሳይሆን ቢቀር ግን
በቀጣይም አዳዲስ ገለልተኞቜ አብያተ ክርስቲያናትና መንፈሳዉያን ማኅበራት
እንዳይፈጠሩም ስጋት አሳድሯል።
ዘንድሮ ሰላሳኛ ዓመቷን ዚምታኚብሚዉ፤ በዘመነ ስደት (ደርግ) በዓለም ዙሪያ
ለተቋቋሙት አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ቀዳማዊት ፋናወጊ ዚሆነቜው በጀርመን
ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክስቲያን ባለፉት ሃያ አንድ ዓመታት ትኩሚቷን
በኊርቶዶክሳውያን አንድነት ላይ ብቻ በማድሚግ በዚህ ሀገር ዚሚኖሩ ምእመናንን
አሰባስባ ቆይታለቜ፤ አሁንም በእምነት ጜናት ስለ አባቶቜ ኅብሚትና ስለ ቀተ ክርስቲያን
አንድነት ትሰብካለቜ። ለዚህም ነው ኚስድስተኛዉ ፓትርያርክ ምርጫ አስቀድሞ
ሊታሰብበት ዚሚገባው በአባቶቜ መካኚል ዚዶግማ ልዩነት ስለሌለ እርቀ ሰላም
ይዉሚድ፧ አንድነት ይቅደም ዹሚል ጥሪዋን ደግማ ደጋግማ ዚምታስተላልፈው።
«áŠ¥áˆ­áˆµ በእርሱ ዹሚቃወም መንግሥት አይጾናም» እንዳለ ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ፤
ፍቅርና ትኅትናን ብሎም አንድነትን ለእኛ ለልጆቻ቞ዉ ዚሚሰብኩ አባቶቻቜን
እንደመሪያ቞ዉና እነሱም በሐዋርያነት እንደሚኚተሉት ፈጣሪያ቞ዉ ቃልን በተግባር
ዚሚገልጹ መምህራን እንዲሆኑላትም ትሻለቜ። ኹፍቅር ዚሚበልጥ አንዳቜ ነገር ዹለምና፤
ሥልጣንም ሆነ ፓርትርያርክነት። እኛ እንደ ቀተ ክርስቲያን ልጅነታቜን በሙሉ ልብ
አባት ዹምንለው፤ እርሱም በእኩል ዓይን ልጆቌ ዹሚለን ዹመንጋ መሪ እንፈልጋለን።
በዚብዙኃን መገናኛውና ማኅበራዊ መድሚኮቜ ዚሚጥላላ፤ በዚሄደበት በዚህቜዉ ቀተ ክርስቲያን ምእመናን ዓይንህ ላፈር እዚተባለ ዚሚዘበትበት፣ ዹዓለም መሳቂያና መሳለቂያ ዹሆነ አባት
እንዲኖሚንም አንመኝም። ለዚህም ነዉ በአባቶቜ መካኚል እርቅ ወርዶ እኔ ዚአጵሎስ፣ እኔ ዚጳውሎስ፤ እኔ ዚኬፋ በሚል ዚተበታተኑት ዚአንዲት እናት ቀተ ክርስቲያን ምእመናንን ጌታቜን
«áŠ¥áˆšáŠ›á‹áˆ አንድ መንጋውም አንድ» እንዳለ በአንድ ጥላ ሥር አሰባስቡ ዹሚል ጥሪያቜንን ዚምናስተላልፈው።
ብፁዓን አባቶቻቜን፤ ዛሬ ዚቀተ ክርስቲያኒቱ ዚወደፊት እጣ ፈንታ ውሳኔ በእናንተ እጅ ላይ ይገኛል። በኢጣልያ ወሚራ ጊዜ በጀኔቫው ዓለም አቀፍ ጉባኀ ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለ ሥላሎ ዚተናገሩትን
እኛም እንድገመውና ስለ እውነት ፍርድ ካልተሰጠ « እግዚአብሔር እና ታሪክ ይፈርዳሉ። » ለውድቀቷም ሆነ ለልማቷ ኚእናንተ በፊት ዚሚወቀስም ሆነ ዚሚወደስ አይኖርም። በቀተ
ክርስቲያኒቱ አንድነት ብሎም በምእመናን ኅብሚት ኚእናንተ በላይ ዹሚጠቀምና ዹሚኹበር አይገኝም። ስለዚህም አሁንም ጥሪያቜን ኚእናንተ ላይ አትኩሯል። ዚተሞኚማቜሁት ኃላፊነት
ዚምትገኙበትንም መስቀለኛ መንገድ ኚእኛ ኚትናንሟቹ ልጆቻቜሁ በተሻለ መንፈሳዊ ዓይን እናንተ ታዩታላቜሁ ብለንም እናምናለን። ቀደምት ዚሃይማኖት አባቶቻቜሁ አባቶቻቜን እንኳን
ዚፓትርያርክነት ሥልጣን ቀርቶ ዚአንድ ገዳም አለያም ማኅበሹ መነኮሳት አበምኔትነት ላለመቀበል ያደርጉት ዹነበርነዉን ሜሜት ኚእኛ በላይ እናንተ ታዉቁታላቜሁ። ስለ ትኅትናም ይሁን
ኃላፊነቱን በመፍራት እምቢታ቞ዉ ጠንቶ ሲያስ቞ግሩም በግንድ እስኚመታሰር እንደሚደርሱም ይዘነጋል ብለን አናስብም።
በጥቅምቱ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኀ ውሳኔ መሠሚት ዹተጀመሹዉ ዹሕገ ቀተ ክርስቲያን ዝግጅት ኚፍጻሜ ሳይደርስ፤ ባለፉት ፓትርያርክ ዘመነ ፕትርክና ተጀምሮ ዹነበሹውና አሁንም በሂደት ላይ
ያለው ዚእርቀሰላም ጉዳይ እልባት ሳያገኝ ዚሚደሚገውስ ዚፓርትርያርክ ምርጫ ጥቅሙ ለማን ነዉ? ተሰያሚዉ ፓትርያርክ እኮ በሙሉ ልቡ ዚሚቀበሉት ምእመናን ያስፈልጉታል። ለዚህም ነዉ
ለአባቶቻቜን ስጋታቜንን እንድናሰማ ዚተገደድነዉ፤
ዘወትር ዚምናኚብራቜሁ ብፁዓን አባቶቻቜን፣
ጭንቀታቜን ሁሉ ዚቀተ ክርስቲያናቜን አንድነት ጞንቶ እንዲኖር ነውና ይህንኑ ጭንቀታቜንን በሚኚተሉት ነጥቊቜ ስናጠቃልል ብፁዓን አባቶቻቜንም ለዚህ ጭንቀታቜን ኹፍተኛ ትኩሚት
እንደምትሰጡት ሙሉ ተስፋ በማድሚግ ነው።
ነ ጥ ቩ ቹ ም፦
1ኛ፤ ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት በመኹፋፈል ምክንያት በቀተ ክርስቲያናቜን ላይ ዹደሹሰዉ ዚጉዳት ጠባሳ እንዲሜር አባታዊ ብሎም መንፈሳዊ ኃላፊነታቜሁን ለመወጣት ኹሁሉም በላይ ዚቀተ
ክርስቲያናቜንን አንድነት እንድታስጠብቁልን እንጠይቃለን፤
2ኛ፤ ኹምንም በላይ ዚተሰጣቜሁን ሃይማኖታዊ ግዎታ በማስተዋል እርቀሰላሙ ሳይቋጭና ዚቀተ ክርስቲያን አንድነት ሳይመለስ ወደ ፓትርያርክ ምርጫ ዹሚደሹገዉን ዝግጅት እንድትገቱ
በትኅትና እንጠይቃለን፤
3ኛ፤ ዚመንፈሳዊ መሪ አባት ምርጫ ጉዳይ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ዚሃይማኖት አባቶቜና እንዲሁም ዚምእመናን ጉዳይ መሆኑን ኚእኛ በላይ እናንተ ታዉቁታላቜሁ። ስለሆነም ኚቀተ
ክርስቲያኒቱ ቀኖና ውጭ ዹሚደሹግ ጫና ካለ ይህን ዹመቋቋም መንፈሳዊ ጜናት እንድታሳዩ እንጠይቃለን፤
4ኛ፤ ኹዓለም ዙሪያ ዹሚቀርበው ዚካህናትና ዚምእመናን ተማኅፅኖ ሰሚ አጥቶ ሢመተ ፓትርያርክ ዹሚፈጾም ኹሆነ እንደ ደንቀዙ፣ እንደ ደብሚ ታቊሩና እንደ ቊሩ ሜዳ በጉባኀ ለሊቃውንቱ
ዚመኚራኚሪያ ዕድል ተሰጥቶ ዚመጚሚሻ ውሣኔ ያገኝ ዘንድ እናሳስባለን።
5ኛ፤ ለእኛ ለልጆቻቜሁ ያልታዚ፥ ለእናንተ ለአባቶቻቜን ብቻ ዚታዬ ካለ፥ ኚሢመተ ፓትርያርክ አስቀድሞ በዓለም ዙሪያ ተበትና ለምትገኘው ቀተ ክርስቲያን ሁኔታውን ዚሚያስሚዳ ግብሚ ኃይል
ኹመንበሹ ፓትርያርክ ቢልካልን።

ዹጀርመን አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎቜ ካህናት፣ ዲያቆናትና ምእመናን ዚተማኅጜኖ ደብዳቀ አቀሚቡ |
6ኛ፤ በተራ ቁጥር አምስት ዹተጠቀሰውን ለማድሚግ ኹወጭ አንጻር ዚማይቻል ሆኖ ኹተገኘ በውጭ ዹምንገኝ ሊቃውንት፣ካህናትና ዲያቆናት በያለንበት ሀገሹ ስብኚት ባሉት ብፁዓን አባቶቻቜን
መሪነት ጉባኀ እንድናካሂድ ዕድሉ ቢሰጠን።
አንዲት ሐዋርያዊት ቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን በተመሠሚተቜበት ዚክርስቶስ ደም ጞንታ እንደምንትኖር እናምናለን።
ልዑል እግዚአብሔር አባቶቜን ኹፈተና፣ ቀተ ክርስቲያንን ኹመኹፋፈልና ምእመናንንም ኚመበታተን ይሰውርልን።
«áŠ¥áˆšáŠ›á‹áˆ አንድ መንጋውም አንድ» ይሁንበኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን
ዹጀርመን ሀገሹ ስብኚት ካህናት እና ምእመናን

በአላማጣ ወሚዳ ዚተነሳውን ተቃውሞ ተኚትሎ በርካታ ሰዎቜ ታሰሩ

ኢሳት ዜና:- ነዋሪዎቹ ለኢሳት እንደገለጹት ኹተማዋን ዚወሚሩዋት ዚፌደራል ፖሊሶቜ ተቃውሞውን አስነስተዋል በማለት ዚጠሚጠሩዋ቞ውን ሰዎቜ ይዘው በማሰር ላይ ናቾው። ወጣቶቜን ጚምሮ በኹተማዋ እና በዙሪያ ባሉ ዹገጠር ቀበሌዎቜ ዚሚታወቁ ዹአገር ሜማግሌዎቜ ታስሚዋል።ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ወሚዳው ባለስልጣናትን ህዝቡን ለማነጋገር ስብሰባ መጥራታ቞ውም ታውቋል። ነዋሪዎቹ እንደሚሉት በነገው እለት መንግስት ዚሚያቀርበውን አማራጭ በመስማት ምናልባትም ተመሳሳይ ተቃውሞ ሊካሄድ ይቜላል።
ተማሪዎቜ ዛሬ ትምህርት አለመጀመራ቞ውን ለማወቅ ተቜሎአል።

ልጃቾው በፖሊስ ኮማንደር ዚተገደለባ቞ው አባት ኚሆስፒታል ወጥተው በወቅቱ ስለተፈጠሚው ድሚጊት ተናገሩ

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- ታህሳስ  ፳፮(ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ልጃቾው  በፖሊስ ኮማንደር ዚተገደለባ቞ው አባት ኚሆስፒታል ወጥተው በወቅቱ ስለተፈጠሚው ድሚጊት ተናገሩ
በጌዲዮ ዞን በዲላ ኹተማ ኮማንደር ግርማ በዹነ ዚተባለ ዹዞኑ ዚፖሊስ ዹሰው ሀብት ማደራጃ መምሪያ ሃላፊ ኹ10 ቀናት በፊት አንድ ዹ14 አመት ታዳጊን ወጣት በሜጉጥ ገድሎ አባቱን  ደግሞ ማቁሰሉን መዘገባቜን ይታወሳል።
ዚማቹ አባት አንገታ቞ው አካባቢ በመመታታ቞ው ወደ አዋሳ ሪቚራል ሆስፒታል ተወስደው ዹነበሹ ሲሆን፣ ምንም እንኳ ጥይቱ ባይወጣላ቞ውም መጠነኛ መሻሻል አድርገው ወደ ቀታ቞ው ተመልሰዋል።
አቶ ሚፍታህ ሙሀመድ ለኢሳት እንደገለጹት ኮማንደሩ ልጃቾውን ዚገደለባ቞ው ያለምንም ምክንያት ሲሆን፣ ልጃቾው መሞቱን እንዳዩ ኮማንደሩን “ልጄን ገድለህ አትሄድም ” በማለታ቞ው እሳ቞ውንም እንደመታ቞ው፣ እንዳጋጣሚ ሆኖ ጥይቱ አንገታ቞ውን ሾርፎ በመሄዱ መትሚፋ቞ውን ተናግሹዋል፡፡ ደማቾው እዚፈሰሰ ኚኮማንደሩ ጋር ግብግብ ተያይዘው አብሚው መውደቃቾውን፣ ጩሀት በማሰማታ቞ው አንድ ዚፖሊስ አዛዥ መድሚሱንና ግለሰቡ መያዙን እርሳ቞ውም ብዙ ደም ፈሷ቞ው ስለነበር መዘሚራ቞ውን ተናግሹዋል::
ኚባለስልጣኑ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንዳልነበራ቞ው ዚተናገሩት አቶ ሚፍታህ ባለስልጣኑ በማን አለብኝነት ተነሳስቶ ያደሚገው ሊሆን ይቜላል ብለዋል።
ጉዳዩ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እዚተካሄደበት መሆኑን ዚተናገሩት አቶ ሚፍታህ ፣ መጚሚሻውን ፈጣሪ ብቻ ነው ዚሚያውቀው ብለዋል።
ዚዲላ ነዋሪዎቜ ወታቱ በተገደለ ማግስት ኹፍተኛ ተቃውሞ በመሰማት ገዳዩ ለፍርድ እንዲቀርብ ጠይቀው እንደነበር መዘገባቜን ይታወሳል። አንዳንድ ስማ቞ው እንዳይገለጥ ዹፈለጉ ሰዎቜ እንደሚሉት በአካባቢው ተወላጅ በሆኑትና ባልሆኑት ላይ ኹፍተኛ አድልዎ ይታያል።

በጋዜጠኛ አበበ ገላው ላይ ታቅዶ ዹነበሹውን ዚግድያ ሎራ በኖርዌይ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አወገዙ

ኢሳት ዜና:- በጋዜጠኛና አክቲቪስት አበበ ገላው ላይ ሊቃጣ ዹነበሹውን ዚግድያ ወንጀል ተኚትሎ  በኖርዌይ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በኖርዌይ ጥገኝነት ጠይቀው  ዚሚኖሩ ዚመንግስት ሰላዮቜን ለማጋለጥ ኚመቌውም ጊዜ በላይ  á‰†áˆ­áŒ á‹ መነሳታ቞ውን ለኢሳት በላኩት መግለጫ አስታውቃል።ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
“በአበበ ገላው ላይ ሊሰነዘር ዹነበሹው ዚግድያ ወንጀል በኀፍቢአይ መርማሪዎቜ መክሾፉ ቢያስደስተንም፣ በስደት፣ ዲሞክራሲና ነፃነት በሰፈነበት አገር ወያኔዎቜ እንዲህ አይነት አስኚፊ ወንጀል ለመፈፀም ማሰባ቞ው እጅግ አስቆጥቶናል፤በጣምም አበሳጭቶናል” በማለት ኢትዮጵያኑ ስሜታ቞ውን ገልጾዋል።
በኖርዌይ በተለያዩ አጋጣሚዎቜ ዚመንግስት ሰዎቜ  ለነፃነት፣ለዲሞክራሲና ለፍትህ በሚታገሉና በኖርዌይ በሚገኙ ወገኖቜ ላይ በአካል፣ በስልክ፣በኢ-ሜይልና በሌሎቜ መንገዶቜ ዛቻና ማስፈራሪያ ማድሚጋ቞ውን ያስታወሱት ኢትዮጵያኑ፣  áˆˆá‹ˆá‹°áŠá‰± እንዲህ አይነት ሁኔታ እንዳይኚሰት  ፀሹ ዲሞክራሲና ኢሰብአዊ ድርጊት ፈፃሚዎቜን አጋልጠው በማውጣት ህጋዊ ምርመራ እንዲደሚግባ቞ው እንደሚያደርጉ ገልጾዋል።
ኹዚህ በፊት በተለያዩ ዹዜና አውታሮቜ እንደተዘገበው ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ዚማይቜሉና ዚጥገኝነት ጥያቄያ቞ው ውድቅ ተደርጎባ቞ው  በኹፍተኛ ቜግር ውስጥ ዹሚገኙ ኢትዮጵያውያን በኖርዌይ መኖራ቞ው ይታወቃል፡፡

Jan 9, 2013

ዹኑ እና እዩኝ” ኑዛዚያዊ ዚወያኔ ጥሪ


ዚህዝብ ድጋፍ ዹሌለው  ዚመኚላኚያ ሠራዊት በዚትኛውም አለም ቢሆን ለድል ዚበቃበት ጊዜ አናሳ ነው። ወያኔዎቜ ሰሞኑን ኚእዚአቅጣጫው ዚተፈጠሚባ቞ውን ውጥሚት ለማላላትና ለማስተንፈስ ይሚዱኛል ያሏ቞ውን ዚህብሚተሰብ ክፍሎቜ “ዹኑ እና እዩኝ ኑዛዚያዊ ጥሪ” እያቀሚቡ ነው።
እርግጥ ነው ሰራዊቱ በቡሬ ግንባር በመሪዎቹ አድሎአዊ ዘሹኛ አስተዳደር ተማሮ እርስ በእርሱ በመታኮስ፤ ዚበርካታ ዚሰራዊት አባላት ሂዎት ሲቀጠፍ አይተናል፣ ሰምተናልም፤ ምንአልባት ዚእነ በሚኚት ዚ቎ሌቪዝን ካሜራ ይኌኛውን አላዹው ይሆናል።
ሰራዊቱ ዛሬ በዘር መድሎ እዚታሞ፣ ዘሚኝነት ለስራ እድገትና ሹመት መመዘኛ በሆነበት፣ ስብእናው፣ ማንነቱ በህወሃት ካድሬዎቜ ተደፍሮ፣ ሙያው ተዋርዶ እና እርስበርስ ተኹፋፍሎ ቀንን እዚቆጠሚ ባለበት ጊዜ፤ ይህንን ሰራዊት ኢትዮጵያዊ ውክልና ያለው አስመስለው፤ በክፉ ቀን ደራሜ አድሚገው መቁጠራ቞ው ሞኝነት ነው።
ወያኔዎቜ መራራውን እውነት መራራም ቢሆን፤ በግልጜ ዚሚታይን፣  ያለውን እውነትና ነባራዊ ሁኔታ እስኚመቌ በመካድ ራሳ቞ውን ሲያታልሉ ይኖራሉ? ሰራዊቱ በአሁኑ ሰአት በዚግንባሩ እዚኚዳ ወደጎሚቀት ሀገሮቜ በመሰደድ ዹተቃዋሚ ሃይሎቜን እዚተቀላቀለ ነው። ይህን ዹመኹፋፈልና ዚመፍሚስ ሃቅ ለመደበቅ ዚተቀነባበሚ ትርኢት እናሳያቜሁ ሲሉ ራሳ቞ውን ያታልላሉ።
በመኚላኚያ ሰራዊቱ ውስጥ ለዘሹኛ መሪዎቜ ዚሀብት ማካበቻና ዚስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ውድ ህይወቱን እንደ አልባሌ ነገር በሶማሊያ አደባባዮቜ እንደተፈጞመበት ሎራ ህይወቱን ዚሚገብርበት ቅንጣት ያህል ስሜት፣ ሁኔታ አሁን አይኖርም። በተለይም አበው ዚሰጡንን ዚታሪክ ማንነታቜንንና ሃውልቶቻቜንን በማፍሚስ፣ አንድነታቜንን በማናጋት ለበታተነን እና ዚአንድን ዘር ዚበላይነት መሰሚት ላደሹገ ስርአት፤ ሰራዊቱ ኚቶ ክቡር  á‹šáˆ†áА ህይወቱን  አይለግስም።
ሰራዊቱ ኚህዝብ አብራክ ዚወጣ ለህዝብ  በህዝብ ዹሆነ እንጅ በአሁኑ  ዘመን በገዛ ወገኑ ላይ ጥይት ዚሚያርኚፈክፍበት ጊዜ ያለፈበት ለመሆኑ ኚአሚቡ አለም ዹጾደይ አቢዮት በተለይም ኚግብጹ ህዝባዊ አቢዮት ዚህዝብ አሞናፊነት፣ ኚመኚላኚያው ጠባቂነት ብዙ ትምህርት ዹቀሰመ ሠራዊት ነዉ።
እንግዲህ ይህን በዘርና በማንነቱ ኹፋፍለው ዚያዙትን ሰራዊት፣ ዚእነሱን ዹኹፋፍለህ ግዛ ጥቅም ያስኚብርላ቞ው ዘንድ እዚተመኙ ነገርግን ለፍርሃታ቞ው መደበቂያ አርቲስት ተብዪዎቹን በመጥራት “ኑ ጉልበታቜንን እዩና ለህዝብ ንገሩ እኛ ብንናገር ዹሚሰማን ዹለም” ሲሉ መማጾናቾውን በቲቪ መስኮታ቞ው አይተናል። በርግጥ ነው አርቲስቶቜ ዹተኹበሹ ሙያ቞ውን ለዘር ዚፖለቲካ ስርአት፣ ህዝባዊ ውክልና ለሌለው አምባገነናዊ አገዛዝ መጠቀሚያ ማድሚጋ቞ው በታሪክ ተጠያቂ ያስደርጋ቞ዋል።
ሰራዊቱ ሁሉም ዜጎቜ በእኩልነት ዚሚኖሩባት፣ አንድነቷ ዚተኚበሚባት፣ እውነተኛ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመመስሚት በሚደሹገው ማናቾውም ዚህዝብ ትግል ኚህዝብ ጎን በመቆም ዹአበውን ዚጀግንነት አርአያ በመኹተል ለአምባገነኖቜ ዚስልጣን እድሜ ማራዘሚያና በደሙ ውስኪ ኚሚራጩበት ለወያኔ አዛዊቜ መጠቀሚያ ኹመሆን እምቢ ሊል ዚግድ ይላል። ኚህዝብ አብራክ ዚወጣ ዹሀገር ልጅ ለሀገር አንድነት ህልውና፣ ለነጻነት ጮራ ትግል እንቅፋት መሆን ዚለበትም።
ሁሌም ህዝብ አሾናፊ ነው፤ ሙባሚክ በአለም አለ ዚሚባል ዹጩር ሰራዊትና ዹቮክኖሎጅ ብዛት ዹነበሹው አምባገነን መሪ ነበር፤ ጋዳፊ ዚመኚላኚያ ጡንቻ቞ውን በ቎ሌቪዥን መስኮቱ ደጋግመው ለአለም ሲያሳዩ ሲኮፈሱ ነበር፤ ኚቶ ዚአንዱም ዚሰራዊት ሃይል ዚህዝብ ቁጣ ማእበልን ሊገታው፣ ሊያቆመው አልተቻላ቞ውም። ታዲያ ዚኛዎቹ ትንሜዪ አምባገነን ዘሹኛ መሪዎቜ ምን ሞቷ቞ው ይሆን ዚሰራዊት ህብሚ-ትርኢት ማሳዚት ዚጀመሩት?
ህወሃት ሁሉን እንደሚያውቅ እና ጥንካሬውን በአዋጅ እንዲናገሩለት በመሚጣ቞ው እንደራሎዎቜ ሲያስነግር፣ ነገርግን በአንጻሩ ባዶነቱንና ዚድንጋጀው መጠኑ ማዹሉን ለህዝብ እያሳዚ መሆኑን ልብ ያለው አልመሰለንም፤ ታዲያ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ኚፍርሃት አሹንቋ በመውጣት ዚአዚሩ ትርኢት ሳያስደነግጠው ትንሜም ትልቅም ቢሆን በራስ አነሳሜነት በዚአካባቢው ተደራጅቶ ትግሉን በማገዝ ወያኔን በማስገደድ ወይም ዚማስወገድና ዹማፋፋም ሚና መጫዎት ይኖርብናል።
ሰራዊቱ ዚህዝብ ነጻነትና መብት ሲጠበቅ፤ ዚእርሱም ዚነጻነትና ዲሞክራሲያዊ እኩልነቱ እንደሚጠበቅ ተሚድቶ ህዝባዊ ዚነጻነት ትግል ጎራን መቀላቀል ብልህነት ነው።

Civil Society Crackdown in Ethiopia – Human Right Watch

By:Laetitia Bader, January 4, 2013,
On 1 January 2013, Ethiopia took up its seat on the United Nations Human rights Council. The uncontested election – Africa put forward five countries for five seats – has raised some eyebrows, given the country’s own poor rights record. Elected member countries are obliged to ‘uphold the highest standards in the promotion and protection of human rights’. Yet, in Ethiopia, hundreds of political prisoners languish in jails where torture is common and a crackdown on the media and civil society is in full swing.
The blogger Eskinder Nega exemplifies the fate of those who dare to speak out. Eskinder was arbitrarily arrested and jailed following the controversial 2005 elections. After his release from prison two years later, he was placed under ongoing surveillance and banned from publishing. Then, in 2011, he was rearrested, convicted in an unfair trial under Ethiopia’s broad terrorism law, and sentenced to 18 years in prison.
Since the 2005 elections, the human rights situation in Ethiopia has progressively deteriorated: the government has shut down legitimate political avenues for peaceful protest; and opposition leaders, civil society activists and independent journalists have been jailed or forced to flee. Furthermore, state-driven development policies, including large-scale agricultural development and ‘villagization’ programmes, have seen communities forcibly relocated from their traditional lands, without adequate consultation or compensation, to villages that lack basic services
The ruling party has passed a host of laws attacking the media and civil society, including the Charities and Societies Proclamation that has made independent human rights work in the country almost impossible. The state has frozen the assets of the last two remaining groups – the leading women’s rights organization, the Ethiopian Women Lawyers Association EWLA) – which has provided free legal aid to over 17,000 women – and the Human Rights Council (HRCO).
Ethiopia’s security forces have in recent years been implicated in crimes against humanity and war crimes in the Somali and Gambella regions. But Ethiopia has not only succeeded in stemming criticism at the national level but also internationally. And the worsening human rights situation has not dampened donors’ enthusiasm, even when their assistance has harmed democratic institutions or minority populations. Ethiopia’s friends and partners in the region should use its three-year term on the Council to put its rights abuses under the international spotlight. They should use debates to urge the Ethiopian government to release all political prisoners, lift unlawful restrictions on civil society and the media, and stop blocking visit requests byUNhuman rights experts.

Can Ethiopia became an African Economic Miracle?

Posted by  | | 
Eric Schmidt, Google Chairman’s travel to North Korea to prod the regime about the importance of Internet access and technology is commendable; however Ethiopia, a U.S. ally has avoided such criticism and scrutiny despite subjecting its citizens to similar situation.
Ethiopia’s Internet access like North Korea’s is limited, strictly regulated, and allowed only with government approval. The Ethiopian government controls major resources, including land, banking, telecommunication, and keeps a record number of journalist, human rights activists, and opposition leaders in prison.
Both Ethiopia and North Korea suffer perennial famine and remain one of the poorest nations in their respective continents. Ethiopia’s per capita according to 2011 World Bank data is $374, while North Korea is $1200. Recently, the blocking of Skype by the Ethiopian government created uproar by the International community, but fizzled out without causing any major changes in government policy. Blocking access to technology puts Nations like Ethiopia and North Korea at Risk.
In 1996 at the dawn of the Internet, the U.S. government gave a grant through the Mickey Leland Foundation to wire all Ethiopian universities and high schools with broadband Internet services. The grant was in an effort to leapfrog Ethiopia’s access to technology in order to bring about economic growth at rates enjoyed by East Asian countries and help end its food dependency and perennial famine. The late congressman Mickey Leland died in Ethiopia in 1989 as he was trying to stave off hunger and famine in western Ethiopia. This grant was seen as the best chance to end Ethiopia’s perennial famine and backwardness and to transform it into an economically viable nation similar to other countries that improved their economy by leveraging technology
Prime Minister Meles Zenawi blocked the grant because it stipulated open access and competitive bidding for the installation of the network. The regime was afraid that the citizens of Ethiopia would use the power of the Internet to organize against the status quo that has been highly detested by the majority of Ethiopians primarily for the lack of democracy and government control on land and other resources.
During the 1996 project, Mr. David Shinn, the former U.S. Ambassador to Ethiopia, did everything he could to convince Meles to accept the grant and allow broadband access in order to end Ethiopia’s economic backwardness and perennial famine. Similar efforts by many other groups were aborted because of the regime’s fear of technology as well as lack of interest in leveraging technology for development in most parts of Ethiopia except in the province of Tigre, where Meles was from. In Tigre, the establishment of the Mekele Institute of Technology (MIT) was a break through. Unfortunately, the graduates from MIT are primarily deployed in cyber spying, blocking websites, and filtering email and phone conversations against the opposition.
According to the International Telecommunication Union (ITU), Ethiopia ranks at the bottom of nations in accessing and leveraging technology (see graph below). Even war torn Somalia has better Internet and mobile services than Ethiopia.
Many countries have been able to propel their economy and living standards by leveraging technology. Five years ago, an initiative to upgrade information technology was undertaken in the southwestern Shoa province in Ethiopia. This initiative was led by Ethiopian expatriates, David Levine and Phillip LeBel, two former Peace Corps volunteer teachers who had taught in Ethiopia in the 1960s, and Appropriate Technology Group where I served as director. The project focused on creating a technology corridor to make Ethiopia the outsourcing center of Africa in 10-20 years and to give alternative development to this highly densely populated and poor region stretching from Gibe River to Awassa.
The plan was to start by equipping 15 high schools in the area with computers and Internet access as part of a technology corridor with the elite of the students going to planned post-secondary institutions to form a core of technological innovation center that could help transform the region into a high-technology hub. The initial shipment was sent on July, 2009 to Djibouti with brand new servers, hubs, and various educational software on a container ship. However, when it reached Djibouti, the Ethiopian government refused to grant a permit to move the equipment into Ethiopia. They demanded an exorbitant tariff, though the organization had an approval from the Ethiopian Embassy and other concerned agencies in Ethiopia to donate the equipment to the schools through a nonprofit agency in Ethiopia. . The group was forced to abandon the project after several months of delays and failed negotiations inspite of U.
S. support for the initiative. .
Technology has become an important tool in increasing GDP and standard of living for many nations including China, India, and others. In Ethiopia, out of 85 million people, less than 700,000 or less than 1% of the population have limited Internet access. Besides deliberately limiting access, the cost to use the Internet is exorbitant. Most Internet access is extremely slow. Instead of broadband access, the country uses primarily dialup internet connection that costs more than high speed service. In addition, to establish a traditional dialup service often takes over six months. Part of the delay is due to a rigorous application process and in an effort to use censorship that is supervised by the national security agency. The agency keep records, blocks websites, radios, TVs, and maintains a total monopoly on all forms of information technology in use in the country.
Denial of access to technology to people and economy can cause incalculable harm. Meles took over Ethiopia in 1991 and a year later the Internet was born. Marc Andreesen from the University of Illinois, my alma Mater, unveiled the Internet browser- Mosaic in 1992 and Netscape in 1994. Since then companies like Amazon, Yahoo, AOL, eBay, Google, Facebook and more, were created and their total revenue alone is over a trillion dollars compared to Ethiopia’s $5.7 billion annual budget for 2011. Out of Ethiopia’s $5.7 billion, 42% or $2.4 billion comes from foreign aids and loans. Incidentally, the city of Houston, with a population 2.2 million has a budget of approximately $4.3 billion vs. $3.3 billion for Ethiopia with 85 million people.
Again according to the Word Bank, Ethiopians survive on a dollar a day as measured by their per capita income of $374 compared to $48,000 per capita income for the U.S.A. Ethiopia is also miserably poor compared with other African countries.
Despite these shocking poverty statistics, the Ethiopian regime like North Korea denies private ownership of Land, Telephone, Internet and other major industries, as well as makes it difficult to obtain education or government jobs unless one is a card carrying members of the ruling party.
One might ask why focus on access to technology or information technology. The answer is that many countries have been able to improve their economy and living standard by leveraging technology as witnessed by many successful economies such as those in East Asia. Overall, Information technology reduces transactions costs and it brings major increase in productivity and enables countries leveraging technology to better compete in the global economy. Despite these factual evidences, Ethiopians have been denied the opportunity to take advantages of this important tool for their economic development.
Many economists believe that there are two main factors that enable a country to enjoy rapid economic growth: discovery of natural resources  or leveraging technology or both. Ethiopia, despite its prime location, so far has not discovered any gas or oil, but it failed to take advantage of one factor that was readily available, leveraging technology, despite many opportunities to do so.
In its continuing effort to impose censorship by limiting access to Internet and technology, the regime is condemning entire generations of Ethiopians to ongoing poverty that could have been redressed by more open and forward-looking choices.
Like North Korea, Ethiopia has a new ruler, Hailemariam Desalegn. Can Eric Schmidt or President Obama pay a visit to Ethiopia to prod this Luddite regime to finally grant unfettered Internet and technology access to create a sustained and rapid economic growth in Ethiopia similar to the Asian Miracle.
Dula Abdu, is a former banker and professor of economics and has been promoting Internet access in the USA and in Africa. He can be reached at dula06@gmail.com.

ታማኝ በዹነ



                      ታማኝ በዹነ
                      ባመነበት á‹šá‹ˆáˆ°áА
                      ወስኖ ዚሚሰራ
                      ለሚሰራው á‹šáˆ›á‹­áˆáˆ«
ዘልቆ ገደብ áˆˆá‰‹áˆ ዹፍቅር áŒ¥áˆá‰€á‰±
ኚኖሚበት áˆá‹µáˆ­ ደምና áŠ¥á‰µá‰¥á‰±
አገር ቀትም áˆ†áА ኚባህር á‰£áˆ»áŒˆáˆ­
ዚትም ዚትም á‰¢áˆ†áŠ• ዚትም áˆ€áŒˆáˆ­ ቢኖር
ዚኢትዮጵያን á‰œáŒáˆ­ ሲሰማ áˆ²áŠ“áŒˆáˆ­
ዚነጻነት ፍትህ áˆáˆ°áˆ¶áŠ“ ማገር

ምሳሌ አታገኙም መሬትን ብትዞሩ
እንደታማኝ ያለ ለህዝብ ለአገሩ
አይፈራም ማንንም ይመስክር ስሙ
ታማኝ በዹነ ነው ፀንቶ በአቋሙ
                               áˆŒáˆ‹á‹áˆ› ሌላውማ
                                       áŠ¥áˆ›áˆ›
እኔ ምን አገባኝ ዚሚሏትን ወግ
እሱ ነው ያሚዳት ኢትዮጵያን እንደ በግ
አዳሪ ለሆዱ ክብሩን አስነጣቂ
ሲጣልበት ውሻ ዚእጅ እባሜ ናፋቂ
ዚሚታመን ጠፋ ለእውነት ያደሚ
ውሜት ገኖ ናኝ በቀይሜ ኹበሹ
ሊወርድ ዘብጥያ እውነትም ታሰሚ
ታሪክ ተሚት ተሚት ብስራት ተበሰሹ
                                ሆኖም ግን ሆኖም ግን
                                        እማማ

ኹአቅም በላይ ሆኖ ህዝብ ቢ቞ገርም
ታማኝ ደርሶልሻል አይዞሜ በዛው አይቀርም
እስኚ ግዜው ድሚስ ያቆዚው በጀና
ለአገሩ ያብቃው ጥሩ ሰው ነውና
                                                                                             
                                                                                        ያሬድ ኀልያስ        áŠ–áˆ­á‹Œá‹­ ቮሌማርክ


ዹጋዜጠኛ ርእዮት አለሙ ይግባኝ ውድቅ ተደሹገ


ኢሳት ዜና:-ርእዮት ዛሬ ሰበር ሰሚ ቜሎት ባትቀርብም ጠበቃዋ፣ አባቷ እና ሌሎቜ ዚስራ ባልደሚቊቿና ጓደኞቿ በቜሎቱ ተገኝተው ውሳኔውን ሰምተዋል።ታህሳስ  ፴(ሰላሳ ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ሰበር ሰሚ ቜሎቱ በርእዮት ዹቀሹበው አቀቱታ ዹህግ ክፍተት ዚለበትም ሲል ውሳኔ አሳልፎአል።
ጋዜጠኛና መምህርት ርእዮት ጥር 17 ቀን 2004 ዓም በፌደራሉ ኹፍተኛው ፍርድ ቀት 3ኛ ወንጀል ቜሎት ዹ14 አመት ጜኑ እስራትና ዹ33 ሺ ብር ቅጣት እንደተወሰነባት ይታወሳል።
ዚርእዮት ጠበቃ ኹፍተኛው ፍርድ ቀት ያስተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም ይግባኝ ያሉ ሲሆን፣ ዚፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀትም ውሳኔውን ኹ15 አመት ወደ 5 አመት ዝቅ አድርጎት እንደነበር ይታወሳል።
በሰበር ሰሚ ቜሎቱ ዛሬ ዹሰጠው ብይን ትክክል አለመሆኑን ዹህግ ባለሙያ ዚሆኑት ርእዮት አባት አቶ አለሙ ደምቊባ ገልጾዋል

Total Pageviews

Translate